Natinael Mekonnen
7.82K subscribers
16.3K photos
1.09K videos
20 files
2.52K links
ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21
Telegram https://t.me/NatinaelMekonnen21
Download Telegram
የፌዴራል ቤቶች ኮፖሬሽን የጽዱ ኢትዮጵያን ንቅናቄን በመቀላቀል የ 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

ኮርፖሬሽኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ለሆነው የ“ጽዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” ንቅናቄ የ5 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ውብና ዘመናዊ ከተማ ለመፍጠር የሚደረገውን አገራዊ ጥረት የሚያግዙ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነም ነው ፡፡

በሚገነባቸው ዘመናዊ ሕንጻዎችና የመኖሪያ መንደሮች ውበትን ፣ጥራትንና እና ዘመናዊነት ታሳቢ ያደረጉ ግንባታዎች እንዲሆኑ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ ለጽዱ ኢትዮጵያ ንቅንናቄ መሰል ድጋፎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ታሳቢ በማድረግ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድጓል፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠሚ አቢይ አህመድ ዛሬ ወለጋ ነቀምት ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2016 ዓ.ም አጠቃላይ ክልላዊ የፖሊስ አመራርና አባላት የፍትህ ማሻሻያ (ትራንስፎርሜሽን) ግምገማ ተካሄደ።

በአጠቃላይ የግምገማው አፈፃፀም በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ የተከናወነ ሲሆን 12700 የሚሆን አመራር እና አባላት በግምገማው ሂደት አልፈዋል።

በዚህም በግምገማው 291 የሚሆኑ አመራሮች በከባድ ማስጠንቀቂያ ያለፉ ሲሆን 41 አመራር እና አባላት ላይ በብልሹ አሰራር በተጨማሪም ህዝብን የሚያማርር ተግባር በመፈፀማቸው በህግ እንዲጠየቁ እና ከስራ በማገድ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

የክልሉ ሰላምና  ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ  አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ  እንደገለፁት የፖሊስን ተቋም ለማዘመን በሚደረገው ርብርብ አባሉ በተሰማራበት የስራ ዘርፍ ቁርጠኛ ሆኖ ለማሳካት ርብርብ ሲያደርግ ጥቂት አመራርና አባላት እየተከናወነ ያለውን ስራ የሚያደናቅፉ የስነ-ምግባር ችግር የሚስተዋልባቸው  በመኖራቸው በየጊዜው በመከታተል  የእርምት እርምጃ በመውሰድ ማስተካከሉ ለተቋማዊ ለውጡ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ሀላፊው አክለውም ፖሊስ ውድ የሆነውን ህይወቱን ሳይሳሳ ለሀገርና ህዝብ የሚሰጥ ይህ ሀይል በጥቂት አባላትና አመራር የሙያ ስነ-ምግባር ችግር ሊወቀስ ስለማይገባ በየጊዜው አባላቱ ያለበትን ቁመና በመገምገምና በመከታተል የዘመነና ብቃት ያለው አባልን ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ በበኩላቸው የቱሪስት መስህብ የሆነው ክልሉ ላስመዘገበው አስተማማኝ ሰላም ህብረተሰቡና የፀጥታ ተቋሙ እያከናወነ ያለው ቅንጅታዊ ስራ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ይህንን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራርና አባላቱ የተሰጣቸውን ሀላፊነት በብቃት መወጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

ከምን ግዜውም በተሻለ ህብረተሰቡ ለፖሊስ አለኝታነቱን በተግባር እያሳየ ባለበት በዚህ ጊዜ አንዳንድ አመራርና አባላት ከሙያዊ ስነ-ምግባር ባፈነገጠ የተቋሙን ስም የሚያጠለሹ መኖራቸው በግምገማው የተለየ በመሆኑ እነዚህን አመራርና አባላት አስተማሪ እርምጃ በመውሰድ ለተቋማዊ  ስኬት ይሰራል ብለዋል።
የቱሪዝም ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡት የ9ወራት አፈፃፀም ሪፓርት ላይ ያነሷቸው ነጥቦች

•የቱሪዝም መረጃ አያያዝን ለማዘመን የሚያስችል tourism satellite account(TSA) ስርአትን ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው::

•የኮንሶ አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ የ8 ቅርሶች ጥገና ስራ እየተከናወነ ነው::

•ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የጌዲኦ መልካምድር እና የባሌ ተራሮችን በሚዳሰስ ቅርስነት በሀረሪ ክልል የሚከበረውን ሸዋል ኢድ ደግሞ በማይዳሰስ ወካይ ቅርስነት ከ 40 አመት በህላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ሶስት ቅርሶቿን ማስመዝገብ የቻለችበት አመት መሆኑን::

•የሚንስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ አካባቢ ምቹ በማድረግ እና የሰው ሀብት ልማት ላይ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል::

•የድሬ ሼክ ሁሴን መካነ ቅርስ ዙሪያ የሚስተዋሉ መሰረታዊ የቱሪስት አገልግሎቶች ጉድለቶችን ለመሙላት ፕሮጀክት ተቀርፆ ለትግበራ ዝግጁ ተደርጓል።

•በነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ የኬብል ካር እና ቱሪስት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ፕሮጀክት ጥናት፣ የዲዛይን ስራ ማጠናቀቅ ተችላል፡፡

•የጂማ አባጂፋር ቤተመንግስት እድሳት ተጠናቆ በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋል::

•ከፈረንሳይ መንግስት ጋር በመተባበር በላሊበላ ከተማ በዋናነት ቱሪስቶች በከተማዉና አካባቢዉ የሚገኙ ቅርሶችን ከመጎብኘት ባሻገር ያለዉን ዕምቅ የባህል ሀብት በአንድ ስፍራ መጎብኘት የሚችሉበት ደረጃዉን የጠበቀ የባህል/ቱሪዝም ማዕከል ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነዉ፡፡

•በአፋር ክልል በኤርታኢሌ የእሳተ ጎመራ ድንቅ የተፈጥሮ ትዕይንት መመልከቻ ቦታ ላይ ለጎብኝዎች መወጣጫ የሚሆን ደረጃዎች ግንባታ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናዎን ላይ ናቸዉ፡፡

•በተለያዩ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዘርፎች 75 የሀገር ውስጥ እና 16 የውጭ ባለሃብቶች ሴክተሩን ተቀላቅለዋል፡፡

•ከዘርፉ በ9ወራት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ ገቢ3.5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ 3.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡

•በዘርፉ ባለፉት 9ወራት 81,673 የስራ እድሎች ተፈጥረዋል፡፡ ከዚህ መካከል 30,968 ቋሚ የስራ እድሎች ሲሆኑ 50,705 ደግሞ ግዚያዊ ናቸው::
በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሀሞሮ ወረዳ ላይ ለበርካታ ዓመታት የህዝብን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ የሽኔ አባላት ለምዕራብ ዕዝ ክፍለጦር እጅ መስጠታቸው ተገለፀ።

በጃን ኢፓ ሲመራ የነበረውና ሰላሳ አምስት የሰው ሀይል ያለው ቡድን ሙሉ ለሙሉ ከሰላሳ አራት የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ጋር እራሱ አመራሩን ጃን ኢፓን ጨምሮ በቀጠናው ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊት እጅ ሠጥተዋል።

የክፍለጦሩ ምክትል አዛዥ ሻለቃ ወልዳይ አስፋው በአካባቢው ለብዙ ዓመታት ከህዝቡ ጋርና ከሽብር ቡድኑ ጋር ባደረግነው ውይይት ከጦርነት ይልቅ ሰላምን አማራጭ አድርገው በፈቃደኝነት ከፍተኛ አመራሩን ጃል ኢፓን ጨምሮ ሰላሳ አምስት ታጣቂዎች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጅ እንዲሠጡ አድርገናል ብለዋል።

በጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም ያሉት ሻለቃ ወልዳይ አስፋው ቀጣይም በድርድርና በሰላማዊ ውይይት የሚያምኑትን ታጣቂዎች እየመከርን ወደ ሰላም እንዲመጡ የማድረግ ስራዎችን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን አጠናክረን እንቀጥልበታለን ብለዋል።

የሀሞሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቀጤሳ ሽፈራው መከላከያ ሰራዊቱ በየጊዜው በሽብር ቡድኑ ላይ በሚወስደው እርምጃ ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረው ዛሬም አብዛኛው የሽብር ቡድኑ የሰላምን አማራጭ እንዲጠቀም ያደረገው ሠራዊቱ በመሆኑ ትልቅ ክብር ይገበዋል ሲሉ ተናግረዋል።

የሽብር ቡድኑ ከፍተኛ አመራር ጃን ኢፖ አሁን እያደረግን ባለው የትግል አቅጣጫ ለኦሮሞ ህዝብም ሆነ ለኢትዮጵያ የማይጠቅምና እርስ በእርስ ደም የሚያፋስስ በመሆኑ የእስካሁኑ ይበቃል በማለትና በተሰጠን የሰላም አማራጭ መጠቀምን በመምረጥ በእኔ የሚመራውን ሙሉ ቡድን ይዤ ለመከላከያ ሰራዊቱ እጅ ሰጥቻለው ሲል አስረድቷል።
„በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማስቀረት እንደ ሰጎን አንገትን በአሸዋ ስውጥ መደበቅ ሳይሆን፤ የችግሩን መንስኤ መጋፈጥና በሰከነ መንገድ መፍታት ይገባል“

አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) በታሪካዊው ራስ መኮንን አዳራሽ በተካሄደው 4ኛው ልዩ ሴሚናር ላይ ከተናገሩት የተወሰደ፡፡