Nessim Mahaba 📚 نسيم المحؚة 🛖
4.94K subscribers
778 photos
282 videos
671 files
742 links
╱◥██████◣
│∩│🪟▀│🪟│
▓▆▇█▓🚪▓█▇
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበሚካትሁ
ዹ ቻናላቜን ተኚታታዬቜ በዚህ ቻናል
➀ ኢስላማዊ ባህሎቜን
➀ ዚሀገራቜን ዓሊሞቜ ስራዎቜን
➀ ልዩልዩ መጜሐፍ pdf
➀ ዳእዋ መንዙማ ታሪኮቜንና ዚተለያዩ ስራዎቜ እናቀርባለን
╱◥██████◣
│∩│🪟▀│🇪🇹 @nessim_muhaba
ዓላማቜን ኢስላማዊ ባህላቜንን ማስፋፋት ነው♥
Download Telegram
አላህ ሆይ!
በንግግርና በጠባይ፣ በእውቀትና በስራ፣ በዱንያም ሆነ በአኺራ ዚነብይህ አሜኚር አድርገን። ኚነብይህ በሚካም ድርሻቜንን አግዝፈው!
አሚን
❀13🥰9
‹‹ዚዳናው ፀሐይ›› ☀

​ሞይኜ አሕመድ ኣደም (1821 - 1893) — ዚመጀመሪያው ዚዳና ሞይኜ (1870 - 1893)

​"ፀሐይ በምድር ላይ ሲጓዝ አዹን!"
❀4🔥1
‹‹ዚዳናው ፀሐይ›› ☀

​ሞይኜ አሕመድ ኣደም (1821 - 1893) — ዚመጀመሪያው ዚዳና ሞይኜ (1870 - 1893)

​"ፀሐይ በምድር ላይ ሲጓዝ አዹን!"

​ይህን ድንቅ ቃል ዚተናገሩት አሕመድ ሞላ ነበሩ። አሕመድ ሞላ በዚያ ዘመን በዹጁ አካባቢ ዚነበሩ አስፈሪ ሜፍታ ነበሩ። ነገር ግን ዚዳናውን ሞይኜ ካገኙ በኋላ ሕይወታ቞ው ሙሉ በሙሉ ተቀዚሚ። ሞይኹ በሕይወታ቞ው ላይ ትልቅ ተፅዕኖ አሳደሩፀ በንስሐ ተመልሰው ሕይወታ቞ው እንዲሰካ፣ እንዲያበራና እምነታ቞ው እንዲጠነክር ምክንያት ሆኑላ቞ው።
​አሕመድ ሞላ ስለ ሞይኜ አሕመድ ዚሰጡት ምስክርነት ኚልብ ዹመነጹና እውነተኛ ነበር። ሞይኹን በጥቂት ቃላት ‹‹ፀሐይ በምድር ላይ ሲጓዝ አዚን›› በማለት ገለጻ቞ው። ኚእርሱ በኋላ ዚመጡ ታላላቅ ሊቃውንት እንኳ ለዚህ አገላለጜ ዚሚተካ ሌላ ዚተሻለ ቃል ሊያገኙለት አልቻሉም።

​ዹግርማ ሞገሳ቞ው ኚፍታ
​ሞይኜ አሕመድ ኣደም ስማ቞ው ብቻ ሳይሆን ተግባራ቞ውም ታላቅ ነበር። ኚእርሳ቞ው ጋር ኹ40 ዓመታት በላይ አብሚዋ቞ው ዚኖሩትና ሁለተኛው ዚዳና ሞይኜ ዚሆኑት ምሁር (1893 - 1914) ስለ እርሳ቞ው ሲናገሩፊ

• ​"አንድም ቀን ፊታ቞ውን ቀና ብዬ አይቌው አላውቅም" በማለት ዚነበራ቞ውን ታላቅ ግርማ ሞገስ ገልጞውታል።

​ፈጣሪ ዚለገሳ቞ው ክብርና ደሹጃ በጣም ኹፍ ያለ ነበር። እርሳ቞ውን ማክበር ብቻ ሳይሆን፣ ማንነታ቞ውን በሚገባ ማወቅ ራሱ ትልቅ መታደልን ይጠይቃል።

​ዚዳናን ምድር ዹማዘመን ጉዞ
​ዚዳናው ሞይኜ አሕመድ ኣደም (ዳንይ አወል) ዚዳናን መካነ-ዕውቀት (ማዕኹል) ለተኚታታይ 22 ዓመታት በዕውቀት እና በደግነት መርተዋል፣ አዘምነዋልም።

​ፈጣሪ መልካም ስራ቞ውን ይውደድላ቞ውፀ በሚኚታ቞ውም በሁላቜን ላይ ይደር! 🀲✚

ምስል ፊዚታላቁ ዚዳና ሐሪማ መስጂድ እና ሞይኜ ሙሀመድ-ዘይን ዳንዩሳሊስ ፣ ሞይኜ አህመድ-ኑር አራተኛው ኾሊፋ ዚነበሩት።

✍ ያሞሐበ ዳኒ
❀11
ኚሙጊራ አቡሚዚንን ዋቢ በማድሚግ እንደተዘገበው ዚነቢዩ [ï·º] አጎት ዐባስ [ሚዲዚላሁ ዐንሁ]: ‐ «አንተ ታላቅ ነህ ወይስ ነቢዩ [ï·º]?» በማለት ተጠዚቁ።
እርሳ቞ውም እንዲህ በማለት መለሱ: ‐ «እርሳ቞ው ታላቅ ና቞ው። እኔ ቀድሜያ቞ው ተወልጃለሁ!»
📚 ሲዚሩ አዕላሚ‐ኑበላእ
:
ዘውቅ ተመልኚት! አደብ ተመልኚት! አንዳንዎ ትክክል መሆን ብቻ አይበቃም! ኚቃላትህ ስር አገላለፅህ ብዙ ዹሚነግሹው ነገር አለ!

❀15
ዚነቢዩን ï·º ሐዲስ ስለማክበር አስደናቂ ምሳሌ: ‐
ኢማም አል-ሶጋኒ [ሹሒመሁላህ] ዚሶሒሕ አል-ቡኻሪ ቅጂን በሚገለብጡበት ጊዜ በራሳ቞ው ላይ ያስቀመጡት መስፈርት ዹሚደንቅ ነው።
ኢማሙ በቅጂያ቞ው ላይ ስለራሳ቞ው እንዲህ ብለዋልፊ
“ይህንን ዚሚጜፈው ሰው አላህ ኚአሳማሚ ቅጣቱና ኚኚባድ ቁጣው ይጠብቀውፀ ይህን መጜሐፍ ሲጜፍ ሁሌም በጟም ላይ ሆኖ፣ በውዱእ ሁኔታ ላይ እንዲሆን በራሱ ላይ ግዎታ አድርጓል።
ኚነቢዩ ï·º ዹተዘገበ እያንዳንዱን ሐዲስ ኹጹሹሰ በኋላ ለአላህ ምስጋና ሁለት ሹኹዓ ሶላት ይሰግዳል።
ኚዚያም አንድ ሱጁድ በማድሚግ ዚዲንና ዚዱንያ ፍላጎቱን ኹአላህ ይለምናል።
ኚሱጁዱ ቀና ካለ በኋላ ኚቁርኣን ውስጥ ዐስር አንቀጟቜ ወይም ኚዚያ በላይ ያነባል።
ኚዚያም በነቢዩ ï·º ላይ ዐስር ጊዜ ወይም ኚዚያ በላይ ሰለዋት ያወርዳል።
ኚዚያ በኋላ ዚሚቀጥለውን ሐዲስ መጻፍ ይጀምራል። 
እንዲሁም ተለይተው በሚቀመጡ ብዕሮቜ ብቻ ይጜፋልፀ እነዚያንም ብዕሮቜ ለዚህ መጜሐፍ ብቻ ይጠቀማል።
በጥንቃቄም ይጠብቃ቞ዋልፀ ኹሞተም በኋላ አስኚሬኑን ለማጠብ ዚሚያገለግለው ውሃ በእነዚያ ብዕሮቜ እንዲሞቅ ይናዘዛል።”
አላህ እነዚህን ዚመሰሉትን ታላላቅ ሰዎቜ በሰፊ ምሕሚቱ ይቃኛቾው!
ይህ ሁሉ ሐዲስን እንደ ተራ ጜሑፍ ሳይሆን ዚነቢዩ ï·º ቅርስ፣ ዚዲን ብርሃን እና ዚቀልብ ሕይወት እንደሆነ በአንክሮ ዚተሚዱ ሰዎቜ መሆናቾውን ያሳያል።

እኛም ቢያንስ ሱናን በመማር፣ በመኹተል እና በማክበር በፈለጋቾው ላይ እንራመድ። አላህ ይርዳን!
❀7
🊅“ካልታገላቜሁ አሾናፊ ትሆናላቜሁ!”

ኚአዕዋፋት መካኚል ንስር አሞራን ዚሚፈታተነው ቁራ ብቻ ነው፡፡ በንስር ጀርባ ላይ ይወጣና በእግሮቹ ቆንጥጊ፣ በመንቆሩ ዚንስርን አንገት መንኚስ ይወዳል፡፡ ነገር ግን ንስር ኚቁራ ጋር በመጣላት ቁራን ለማጥፋት በማሰብ ጊዜውን አያባክንም ፀ ኹፍ ብሎ ይበራል እንጂ፡፡ ፍጥነቱን እዚጚመሚ ኹፍ ብሎ መብሚር ሲጀምር ቁራ አዹር ያጥሚውና ኚንስር ጀርባ ላይ ለመውሚድ ይገደዳል፡፡
 
ቁራ ጥበብንና ተንኮልን አስተባብሚው ኚያዙት በራሪ እንስሳት መካኚል አንዱ ስለመሆኑ ይነገርለታል። ዹሞተ እንስሳን ዘንጥሎ ለመብላት አቅሙ ባይፈቅድለት እንኳን ለውጥ አልባ ትግልን ኚማድሚግ ይልቅ እነ ጥንብ አንሣዎቜ እስኚሚዘነጥሉለት ይታገሣል። ኚሌሎቹ ጋር ተጋፍቶ በሜሚያ ለመብላት አቅሙ ባይፈቅድለትም አንዱን ጆፌ ኹኋላው ነክሶ እርስ በእርሳ቞ው ካጣላ቞ው በኋላ ፀ በጠባ቞ው ሰዓት ዚድርሻውን ይመገባል። ቂመኛ ስለመሆኑም ይነገርለታል። ይህ ሁሉ ክህሎት ቢኖሚውም ቅሉ ኚንስር አሞራ ጋር ግን ዚሚወዳደር አይደለም። ይህንን ዚተሚዳ ዚሚመስለው ንስር ጊዜና ጉልበቱን ኚቁራ ጋር በመጣላት ማሳለፍን አይፈልግም። ኹፍ ብሎ በመብሚር ኚቁራ ጋር ያለውን ዹመገኛ ልዩነት ያሰፋል። ዹሰው ልጅም ልክ እንደንስሩ ዚመብሚር ጥበብ እና አቅም ተሰጥቶታል። ዋናው ቁም ነገር ዹተሰጠውን ጥበብ እና አቅም መጠቀሙ ላይ ነው። 

ኹ"ዹጠፋውን መንገድ ፍለጋ" መጜሐፉ ዚውስጥ ገጜ ዹተወሰደ

📌አሁኑኑ ይ🀄ላ🀄ሉን
@MuhammedNessim
❀12
«በግፈኞቜ ሚዳቶቜና በተኚታዮቻ቞ው ላይ ዓይናቜሁን በመደነቅና በመደሰት አታተኩሩፀ ካያቜኋ቞ውም በልባቜሁ ውስጥ እነሱን መቃወምና መጥላት ይኑርፀ ያለዚያ ሥራቜሁ ይበላሻልና።"
ታቢዒዩ ታላቅ ዓሊም ሰዒድ ኢብኑል‐ሙሰዪብ [ሹሒመሁላህ] 
:
ግፍንና ጚቋኝነትን ዚሚያግዙ ሰዎቜን በመደነቅ ወይም በመኹተል በደስታ መመልኚት ዹወንጀላቾው ተካፋይ ያደርጋል። ቢያንስ በቀልብ መጥላት ቅንጣት ታክል ኢማን ካለው ሰው ዹሚጠበቅ አነስተኛው ደሹጃ ነው። አላህ እንዲህ ይላል: ‐
{وَلا تَركَنوا إِلَى الَّذينَ ؞َلَموا فَتَمَسَّكُمُ النّارُ وَما لَكُم مِن دونِ اللَّهِ مِن أَولِياءَ ثُمَّ لا تُنصَرونَ}
«ወደእነዚያም ወደ በደሉት አትጠጉ፡፡ እሳት ትነካቜኋለቜና፡፡ ኹአላህም ሌላ ጠባቂዎቜ ዚሏቜሁም፡፡ ኚዚያም አትሚድዱም፡፡»
❀5
«ኚግፈኞቜ ሚዳቶቜና በተኚታዮቻ቞ው ላይ ዓይናቜሁን በመደነቅና በመደሰት አታተኩሩፀ ካያቜኋ቞ውም በልባቜሁ ውስጥ እነሱን መቃወምና መጥላት ይኑርፀ ያለዚያ ሥራቜሁ ይበላሻልና።"
ታቢዒዩ ታላቅ ዓሊም ሰዒድ ኢብኑል‐ሙሰዪብ [ሹሒመሁላህ]
:
ግፍንና ጚቋኝነትን ዚሚያግዙ ሰዎቜን በመደነቅ ወይም በመኹተል በደስታ መመልኚት ዹወንጀላቾው ተካፋይ ያደርጋል። ቢያንስ በቀልብ መጥላት ቅንጣት ታክል ኢማን ካለው ሰው ዹሚጠበቅ አነስተኛው ደሹጃ ነው። አላህ እንዲህ ይላል: ‐
{وَلا تَركَنوا إِلَى الَّذينَ ؞َلَموا فَتَمَسَّكُمُ النّارُ وَما لَكُم مِن دونِ اللَّهِ مِن أَولِياءَ ثُمَّ لا تُنصَرونَ}
❀7
ይህንን ቆንጆ ታሪክ አንብበው ይተኙ።
**

ሜፋኑን ብቻ አይቶ አለመጣል
****
አነስ ኢብኑ ዓሚር ዚሚባል አንድ ሰው ቆንጆ ሎት ዚማግባት ምኞት ነበሚው፡፡ ዹሆነ ጊዜ በኒቃብ ዚተሞፈነቜ አንዲት ሎት አገባ፡፡ መልኳን አላዹም ነበር፡፡ በጫጉላው ምሜት ወደ መኝታው ገብቶ ፊቷን ስትገለጥ ለዐይን ዚማትስብ መልኹ ጥፉ ሆነቜበት፡፡ አብሯት አላደሚም፡፡ ቜላ አላት፡፡
እሷም በሁኔታው ተሰማት፡፡ መራራቁ ለቀናት ቀጠለ፡፡ አላስቜል ሲላት ሄዳ ጠዚቀቜው፡፡ ብልህ ሎት ነበሚቜና 

‹አነስ ሆይ! ኾይር ነገር እኮ መጥፎ ብለን ባሰብነው ነገር ተሾፍኖ ሊመጣ ይቜላል፡፡› አለቜው፡፡
በዚህ ቀን አብሯት አደሚ፡፡ ጋብቻውም ዹሚሰምር መሰለ፡፡
ሆኖምግን ቀልቡ ብዙም አልኚጀላትም፡፡ አሁንም ተመልሶ ራቃት፡፡ ያኔ ተለያት፡፡
ኚዚያን ጊዜ ጀምሮ ለድፍን ሀያ ዓመታት አላገኛትም ነበር፡፡ ሲለያዩም ስለመፀነሷ ያወቀው ነገር አልነበሚም፡፡ ኚሀያ አመት በኋላ ወደ ሀገሩ መዲና ተመለሰ፡፡ ለመስገድ አስቊም መጀመሪያ መስጂድ ገባ፡፡

መስጅዱ ጥግ ላይ በዕድሜ ወጣት ዚሆኑት ዚመስጅዱ ኢማም ትምህርት ይሰጣሉ፡፡ በዕውቀታ቞ውና በአንደበተ ርቱእነታ቞ው ተገሹመና ስለማንነታ቞ው መጠዹቅ ጀመር፡፡

‹ኢማም ማሊክ ይባላል፡፡ አባቱ ኚሀያ አመት በፊት ነበር መዲናን ለቆ ዚወጣው፡፡ አነስ ይባላል፡፡› አሉት፡፡

አነስ ወደ ኢማሙ ተጠጉና አወሯ቞ው፡፡
‹‹ወደ ቀትዎ አብሚን እንሄዳለን፡፡ ነገርግን እኔ አልገባም፡፡ ለእናትዎም ‹በር ላይ ያለው ሰውዬ ኾይር ነገር እኮ መጥፎ ብለን ባሰብነው ነገር ተሾፍኖ ሊመጣ ይቜላል፡፡›› ይሏታል፡፡ አሏ቞ው፡፡

ኢማሙም ዚተባሉትን ነገር ለእናታ቞ው ተናገሩ፡፡ እሷም ነገሩ ወዲያው ገባት፡፡
‹በል ፍጠን.. ዹጠፋው አባትህ ነው ዚመጣው!፡፡› አለቻ቞ው፡፡

ዚምትገርም እናት ናት፡፡ ይህን ሁሉ ዓመት ሲርቃት ጥሎን ጠፋ፣ ጠላን፣ ጣለን 
 ብላ አላማሚሚቜም፡፡
በመጥፎ ነገርም አልጠሚጠሚቜም፡፡ በርግጥም ዚኢማም ማሊክ ኢብኑ አነስ እናት ዚሆነቜው ያለምክንያት አይደለም፡፡ ትምህርቷ፣ ንቃቷና ለአላህ ያላት ፍራቻ ኹፍ ያለ ቢሆን እንጂ፡፡ ትልቅነት ኚቀት ይጀምራል 
 

ኢማም ማሊክ ኚአራቱ ዚዓለማቜን ታላላቅ ዚመዝሀብ ኢማሞቜ አንዱ ና቞ው። ኢማሙ ዳሩል ሂጅራ በመባል ይታወቃሉ።
❀18🥰5
በቀን ውስጥ ደጋግመን ዚምንፈጜመው ሶላት ውስጥ እንኳን ዹመልክተኛው [ï·º] ድርሻ ሰፊ ነው: ‐
⚀ በእያንዳንዱ እንቅስቃሎ ውስጥ ፈለጋቾውን መኚተልፀ
⚁ ለርሳ቞ው ሰላምታ ማድሚስፀ
⚂ ሞሀዳ ማድሚግፀ ለርሳ቞ው መልክተኝነት ምስክርነት መስጠትፀ
⚃ በርሳ቞ው፣ በቀተሰቊቻ቞ው እና በባልደሚቊቻ቞ው ላይ ሶለዋት ማድሚግ።
🔞 አላህ ለመልክተኛው [ï·º] ዹሰጠው ደሹጃ ዹሚደንቅ ነው!
በቅጥራ቞ው ውስጥ ያኑሚንና!
❀15
በሐሰን ደሹጃ በተዘገበ ሰነድ ተወዳጃቜን ï·º እንዲህ ብለዋልፊ
«በቂያማ ቀን ኚሰዎቜ ሁሉ ኚእኔ ይበልጥ ቅርብ ዚሚሆኑት በእኔ ላይ ሰላዋትን በብዛት ዚሚያወርዱ ና቞ው።»


በነቢዩ ï·º ላይ ሰላዋትን በብዛት ዚሚያወርድ ሰው በቂያማ ቀን ኚእርሳ቞ው ቅርብ ዚሚሆነው፣ በእርግጥም ይህ ተግባር ወደ እርሳ቞ው ስለሚያቀርበው ነው። በተጚማሪም ሰላዋትን በብዛት ማውሚድ ለነቢዩ ï·º ያለውን ጥልቅ ፍቅር ያሳያልፀ ምክንያቱም አንድ ሰው ዹሚወደውን ነገር ብዙ ጊዜ ያወሳል፣ ደጋግሞ ይዘክራል። በስተመጚሚሻም ሰው ኹሚወደው ጋር ይሆናል። 

በሌላ በኩልም ዚነቢይ ï·º ወዳጅ ዹሆነ ሰው ለነቢዩ ï·º ያለው ጠንካራ ፍቅር ሱና቞ውን በጥንቃቄ በመኹተልም ይገለፃል።

"አንድን አካል ዚሚወድ ሰው ለሚወደው ታዛዥ ይሆናል።"


እንዲህ ያለ ሰው፣ ሰላዋትን በብዛት በማውሚዱ፣ በፍቅሩና ሱና቞ውን በመኚተሉ፣ መንፈሱ ወደ ነቢዩ ï·º መንፈስ ይቀርባል። በእርሱና በወደዳ቞ው ነቢይ መካኚልም መተዋወቅ፣ መግባባት፣ መተሳሰርና መመሳሰል ይፈጠራል። ስለዚህም በቂያማ ቀን ኚነቢዩ ï·º ቅርብ ይሆናል። በተለይም ዹሰውዹው ኑር (ብርሃን) ኚነቢዩ ï·º ብርሃን ዚተቀዳ ስለሆነ፣ ዚፍቅራ቞ው ዓርማም በእርሱ ላይ ስለታተመ በቂያማ ቀን ዐጃቢያ቞ው ይሆናል።

አቡ ዐብዱላህ አስ-ሳሂሊ እንዲህ ብለዋልፊ «በነቢዩ ï·º ላይ ሰለዋትን በማዘውተር ኹሚገኙ ጥቅሞቜ አንዱ፣ ዹተኹበሹው ዚነቢዩ ï·º ምስል በቀልብ ውስጥ በድምቀት መታተሙ ነው። ይህም ሰላዋትን በቀጣይነት፣ በቅን ኒያ፣ በተገቢው አደብ እና ትርጉሙን በማሰላሰል ሲደጋገም ዹሚገኝ ይሆናል።

በዚህ ልማድ ዚነቢዩ ï·º ፍቅር በልብ ውስጥ በጥልቀት ይሰርፃል። ዚዛኪሩን ሩሕ ኚነቢዩ ï·º ሩሕ ጋር ያስተሳስራል። ይህም እንደ ፍቅሩ ጥንካሬ መጠን ዹበለጠ እያደገ ይሄዳል።
ሰው ኹሚወደው ጋር ነውፀ ፍቅር ደግሞ መኹተልን ያስገድዳልፀ መኹተልም ወደ መድሚስና ወደ መቀራሚብ ያመራል።»
አላህ እንዲህ ይላል፩

«አላህንና መልእክተኛውን ዚሚታዘዝ ሰው፣ ኚእነዚያ አላህ ጾጋውን ኚሰጣ቞ው ነቢያት፣ እውነተኞቜ፣ ሞሂዶቜና መልካም ሰዎቜ ጋር ይሆናልፀ እነርሱም እጅግ መልካም ጓደኞቜ ና቞ው።» (አን-ኒሳእ፡ 69)
ዹአላህ ነቢይም ï·º እንዲህ ይላሉ: ‐

«ሩሖቜ (ነፍሶቜ) እንደተደራጁ ሠራዊቶቜ ና቞ውፀ [በሩሕ ዓለም] ዚተዋወቁት ይጣመራሉ፣ ያልተዋወቁት ይለያያሉ።»
📚 መጧሊዑል‐መሰራት

اللهم صل وسلم وؚارك على سيدنا محمد، وعلى آله وصحؚه أجمعين.💚💚💚
❀13
ኚነቢዩ ï·º ቃላት መካኚል ልቊናዬ አብዝቶ ዚሚወደው፣ በጥማት ዹተንገበገበ ሰው ውሃ ሲያገኝ በስስት እንደሚጚልጠው መንፈሮን ዚሚያሚካው፣ ዹዓይኔ እንባ ቢደርቅ እንኳ ዚእንባ ዶፍ ዚሚያራጚኝ፣ ነፍሮ በፍጹም ጥበቃ ውስጥ እንዳለቜ እንዲሰማኝ ዚሚያደርገኝ፣ እምነት቎ እንዳይናድ ዚሚያጠናክርልኝ፣ ዚማይሞሜ መኚታ እንዳለኝ እንዲሰማኝ ዚምታደርገኝ አንዲት ቃል አለቜ። 
:
እርሱም ተወዳጁ ï·º ለእመቀታቜን አስማእ ቢንት ዑመይስ [ሚድዚላሁ ዐንሃ] ዚተናገሩት ቃል ነው።
ባለቀቷ ሰይዲና ጃዕፈር ኢብን አቢ ጧሊብ [ሚድዚላሁ ዐንሁ] ኹተሰዉ በኋላ ልጆቿ በድህነትና በቜግር ውስጥ እንዳይወድቁ ስትፈራ፣ ነቢዩ ï·º እንዲህ አሏትፊ

«በእነርሱ ላይ ድህነትን ትፈሪያለሜ? እኔ በዱንያም በአኺራም ጠባቂያ቞ው (ወልያ቞ው) ነኝ።» አሏት።

ላ ኢላሃ ኢለላህ!

ልብ ያለው ሰው ሁሉ በዚህ ቃል ንዝሚት ይንቀጠቀጣል።
በዚህ ንግግር ውስጥ ታላቁ ሰው ï·º በጌታ቞ው ዘንድ ያላ቞ው ኹፍተኛ ደሹጃና ክብር ፍንትው ብሎ ይታያል። እንደውም ደሹጃቾውን አሟልቶ ዚሚያውቀው ኹፍ ያለው አላህ ብቻ እንደሆነ ይሳበቃል። 

እስኪ አስቡት 
«እኔ በዱንያም በአኺራም ጠባቂያ቞ው ነኝ!»
በዱንያ... እና
በአኺራም...
ሱብሓነላህ!
❀13🥰10👍4
አልላሁምመ ሶልሊ ወሰልሊም ወባሪክ ዐለይሂ

... وأُصَلِّيْ وَأُسَلِّمُ عَلَى النُّوْرِ الْمَوْصُوْفِ ؚِالتَّقَدُّمِ وَالْأَوَّلِيَّةِ، اَلْمُنْتَقِلِ فِي الْغُرَرِ الْكَرِيْمَةِ وَالْجَِؚاهِ ۞ وَأَسْتَمْنِحُ اللهَ تَعَالـٰى رِضْوَانًا يَخُصُّ الْعِتْرَةَ الطَّاهِرَةَ النَّـَؚوِيَّةَ ۞ وَيَعُمُّ الصَّحَاَؚةَ وَالْأَتَؚْاعَ وَمَنْ وَالَاهُ ۞ وَأَسْتَجْدِيْهِ هِدَايَةً لِسُلُوْكِ السُّـُؚلِ الْوَاضِحَةِ الْجَلِيَّةِ ۞ وَحِفْ؞ًا مِنَ الْغَوَايَةِ فِي خِطَطِ الْخَطَأِ وَخُطَاهُ ۞ وأَنْ؎ُرُ مِنْ قِصَّةِ الْمَوْلِدِ النََؚّوِيِّ ُؚرُوْدًا حِسَانًا عَؚْقَرِيَّةً ۞ نَا؞ِمًا مِنَ النَّسَؚِ ال؎َّرِيْفِ عِقْدًا تُحَلَّى الْمَسَامِعُ ؚِحُلَاهُ ۞ وأَسْتَعِيْنُ ؚِحَوْلِ اللهِ وَقُوَّتِهِ الْقَوِيَّةِ؛ فَإِنَّهُ لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا ؚِالله.

عَطِّرِ اللّٰهُمَّ قَؚْرَهُ الْكَرِيْمَ
ؚِعَرْفٍ ؎َذِيٍّ مِنْ صَلَاةٍ وَتَسْلِيْمٍ
(اَللّٰهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وََؚارِكْ عَلَيْهِ)

አልላሁምመ ሶልሊ ወሰልሊም ወባሪክ ዐለይሂ
❀15🥰7
ዹአላህ መልክተኛን [ï·º] ማወቅ ማለት አፍ ኹተናገሹው በላይ እንደሆኑ መሚዳት ማለት ነው።

እርሳ቞ውን ዹማወቅ ቁልፍ ምልእ ደሹጃቾውን ማወቅ አልቜልም ብሎ እጅ መስጠት እና ጥልቅ እውቀቱን ለአላህ መተው ነው!


اللهم صل وسلم وؚارك على سيدنا ومولانا محمد وعلى آل سيدنا ومولانا محمد

አልላሁምመ ሶልሊ ወሰልሊም ወባሪክ ዐላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመዲን ወዐላ ኣሊ ዐላ ሰይዲና ወመላና ሙሐመዲን፡፡
❀18
ሙፍቲ ሀጅ ዓሊ ጉራ

ሙፍቲ ሀጅ ዓሊ ኢልማ቞ው በህር ዹነበሹና በ*ኚሜፍ*ዚተንቆጠቆጡ ዹአሏህ ባሪያ ነበሩ።ሀጅ ዓሊ በሀበሻ ኚሚታወቁ ታላላቅ ኡለማኊቜ ኢልምን በሚገባ ኹቀሰሙ ቡሀላ በተለያዩ ዚሀገራቜን ክፍሎቜ እዚተዘዋወሩ ኢልማ቞ውን አካፍለዋል።ሀጅ ዓሊ ኹሌላው ልዩ ዚሚያደርጋ቞ው በሁሉም ዚትምህርት አይነት ልዩ ቜሎታ ዚነበራ቞ው መሆኑ ነው።አብዘሀኛው አሊም በአንድ ወይም በሁለት ዚኢልም ዘርፍ እውቅና ያለው ቢሆንም ሀጅ ዓሊ ግን በሁሉም *ፈን* ነበር ታዋቂነታ቞ው።
ዚሙፍቲ ሀጅ ዓሊን ዚኢልም ስፋት ዳንዩ ሳሊስ፣ዳንዩ ራቢዕ፣ ዳንዩ ኻሚስ፣ሜይኜ ሙሀመድ በድሩ (በድሬ)፣ ሀጅ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ፣ሀጅ ሙሀመድ ራፊዕ፣ ሜይኜ ሙሀመድ አወል ((ዞብል) እና በሀገራቜን ዕውቅናን ዹተጎናፀፉ ኡለማኊቜ ዚኢልማ቞ውን ስፋት መስክሚውላ቞ዋል።
ሀጅ ዓሊ በዳንዩ ሳሊስ ዚኢልም ስፋት እና ሁለገብነት፣ በዳንዩ ራቢዕ አሏህ ዹለገሰው ሚስጥር
መብዛት እጅግ በጣም ይገሹሙ ነበር።
ሀጅ ዓሊ በስኚመጚሚሻ ወደ አኜይራ እስኪሄዱ ድሚስ ወልዲያ ኹተማ ተቀምጠው ኢልማ቞ውን ሲለግሱ ነበር ዚኖሩት (አሏህ ይማራ቞ው፣ ይዘንላ቞ው፣እኛንም ዚኢልማ቞ውን በሚካ ያንቧቧብን)።
በፈንታ ሙሀመድ ዳና✍
❀22
ምሜቱ ጁምዓ ነው። ድምቀቱም በሰለዋት ነው።

ሰው ሁሉ በሀሳብና ጭንቀት ዚተዳኚመበት ዘመን ላይ ነው ያለነው ።
ትልቁ መድሃኒት ሰለዋት ማብዛት ነው።

አልሏሁምመ ሶልሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐለይሂ ።

اللهم صل وسلم على سيدنا ومولانا محمد وعلى آل سيدنا ومولانا محمد

https://t.me/MuhammedNessim
❀12
አደርን በሚሕመቱ
ሁሌም ሚሕመትህ አይለዹን ዹኔ ጌታ
ዹደኹማቾው ሁሉ ይሚፉ።

https://t.me/MuhammedNessim
🔥2❀1