የሕግ ቤት
7.53K subscribers
688 photos
5 videos
1.23K files
562 links
የሕግቤት Access legal information from Law center, The House of Law.
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
Download Telegram
የፌዴራል_የዳኝነት_አስተዳደር_ዓዋጅ_ቁጥር_1233_2013.pdf
2.1 MB
Federal Judicial Administration Proclamation 1233/2021 - የፌዴራል የዳኝነት አስተዳደር ዓዋጅ ቁጥር 1233/2013
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለ ሕግ
የኢትዮጵያ ሕግ ትምሕርት ቤቶች ማሕበር ተመሰረተ።
=================================‼️‼️‼️‼️‼️
ማኀበሩ ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር፣
በሕግ ትምህርት ቤቶች መካከል ትብብር እንዲኖር ማበረታታት እና የሕግ ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተ የልምድ ልውውጥ እንዲሁም በተለያዩ ሐሳቦች ላይ ውይይት የሚደረግበት ነጻ መድረክ ሆኖ ማገልገልና
ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር እና የመሳሰሉት ዓላማዎቹን ይዞ የኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶች ማኀበር ዛሬ ሐምሌ 03/2013 ዓ/ም አባል ትምህርት ቤቶችና የፍትህ ዘርፉ ባለድሻ አካላት በተገኙበት በሂልተን ሆቴል ተመስርቷል።
አቶ መስፍን....
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from አለ ሕግ
Equality before the law⁉️
The case of Jacob-Zuma‼️

Supporters of the former president of the Republic of South Africa are demonstrating against the decision of the court. Do they understand that they are protesting to the rule of law? Contempt of court is a crime. Zuma was jailed under court decision, not a political one. If you reject the court, you are rejecting law. People should demonstrate when the law is violated, not when respected. Everyone is equal before the law. If you believe that your leader is above the law, then you are against the rule of law. Everyone is equal before the law. That must be the core principle Africans should stand for.
Kassahun Yibeltal‼️‼️
Senior Lawyer
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል

በ:- ወንድዬ ብርሃኑ

የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

መልካመ ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1994-offences-relating-to-invoices
👍1
የብድር ውል ‼️
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡

አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡

የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡

የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡

የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........
.......................ተበዳሪውም በአበዳሪው ሳይጠየቅ መክፈል ቢፈልግ ለመክፈል ያለውን ሀሳብ ከአንድ ወር በፊት ካስታወቀ በኋላ ዕዳውን መመለስ እንደሚችል እንዲሁ ተደንግጓል፡፡

በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡

የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም፡፡
federal attorney general
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
👍1
charge case.docx
11.4 KB
የወንጀል ክስ ፎርም English version Hypothetical case.
@EthiopianLawStudentsUnion
via about law
Forwarded from TeleBirr Bot
🎈Welcome to Tele Birr Bot
➣ ቴሌ ብር Botን ሲጠቀሙ

📋 ሲመዘገቡ 15.00 ብር Bonus

🎁 በየ 48:00 ሰሀት(2 ቀን) 3.00 ብር ጉርሻ

🔗 ጓደኛ በመጋበዝ 5.00 ብር ያገኛሉ።

TeleBirr Botን ይቀላቀሉ

🔗 https://t.me/TeleBirrProBot?start=Bot6408842
ከጤና ሙያ ጋር የተያያዙ ጥፋቶች የአስተዳደርና የፍትሐብሔር ኃላፊነት
---------------------------

1. የሕክምና የሙያ ስህተት / Medical Malprctice /
የህክምና የሙያ ስህተት የሚለዉ ፅንሰ ሀሳብ ወጥ የሆነ የሕግ ትርጉም አልተሰጠዉም፡፡ ነገር ግን በጥቅሉ የህክምና ስህተት ማለት አንድን የህክምና ባለሙያ ባለዉ አቅምና ችሎታ የህክምና ሥራዉን በሚያከናዉንበት ጊዜ ለሚሰራዉ ሥራ ጥንቃቄ በጎደለዉ መልኩ ወይም ጥንቃቄ መዉሰድ ሲገባዉ ሊመጣ የሚችለዉን ጉዳት እያወቀ ወይም ማወቅ ሲኖርበት በታካሚዉ ላይ ጉዳት ማድረስ ነዉ፡፡ ታካሚዉና የህክምና ጤና ተቋሙ የህክምና ዉል በመፈጸም ግዴታ ሲያቋቁሙ ታካሚዎች በሚታከሙበት ጊዜ በታካሚዉ ላይ ሊመጣ የሚችለዉ ጉዳትና አዳጋ በመገንዘብ አካሚዉ ጥንቃቄ በጎደለዉ መልኩ ከተከናወነ ለሚደርሰዉ ጉዳት እንደዉሉ ያልተፈፀመ በመሆኑ ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ1962 የወጣዉ የፍትሐብሔር ሕግ የጤና ባለሙያዉ የማዳን ዋስትና የለዉም እንደሚል በመጥቀስም የጤና ባለሙያ ለማዳን ዋስትና እንዲሰጥ እንደማይገደድ ተደንግጓል፡፡ ለዚህም ነዉ አንድ ታካሚ የሚጠበቀዉን የሕክምና ዉጤት አላገኘሁም በማለት የሕክምና ባለሙያን ለመክሰስ የማይችለዉ፡፡ የሕክምና ስህተት ሕግ ሀኪሞች ወይም ሌላ የሕክምና አገልግሎት ሰጪ አካላት የሕክምና አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት በታማሚው ላይ በቸልተኝነት ለሚያደርሱት ጉዳት ያለባቸውን ተጠያቂነት የሚገዛ ሕግ ነው፡፡ ቸልተኝነት ከደረጃዉ ዉጪ ሕክምና መስጠት ወይም የታወቀ የሕክምና ሥነ-ሥርዓትን በጤና ባለሙያዎች የተለመደ አሰራር መሰረት አለመከተል ነዉ፡፡ አንድ የሕክምና ባለሙያ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ በተመሳሳይ ጉዳይ ሌሎች የሕክማና ባለሙያዎች ሊያከብሯቸው ወይም ሊፈጽሟቸው የሚገባውን መደበኛ ጥንቃቄ (“standard of care”) ሊያከናውን ወይም ሊከተል ባለመቻሉ ምክንያት በታማሚው ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ የሕክምና ባለሙያው ለጥፋቱ ተጠያቂ የሚሆንበት አሠራር የሕክምና ስህተት ሕግ ይባላል፡፡

1.1 የህክምና ስህተት ተፈጽሟል የሚባለዉ ምን ምን ሲሟላ ነዉ?

1. ሐኪሙ ለታካሚዉ ሕክምና የመስጠት ግዴታ አለመወጣቱ፤
አንድ የህክምና ባለሙያ ለአንድ ታካሚ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ግዴታ ያለበት መሆኑን ወይም ሕክምናዉን የሰጠዉ እርሱ መሆኑን በማረጋገጥ የህክምና ስህተት ተፈጥሯል የሚለዉን ጉዳይ ለመወሰን ከሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች አንዱ ነዉ፡፡ ይህ የሚሆነዉ የአካሚና ታካሚ ሕጋዊ ግንኙነት መኖሩ ሲረጋገጥ ነዉ፡፡
አንድ የህክምና ባለሙያ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እስከተሰማራና የህክምና ተግባራትን የሚያከናውን እስከሆነ ድረስ የሚያከናውናቸውን ተግባራት እና በዘርፉ ያሉትን የህክምና አሰራሮች ላይ እውቀትና ክህሎቱን በየጊዜው መገንባት አለበት፡፡ ለዚህም ነው ከሐኪም ቀዳሚ ግዴታዎች መካከል ዋነኛዉ በሚያከናዉነዉ ተግባር ብቁ ባለሙያ ሆኖ መገኘት ነዉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ለተገልጋይ የሚሰጠዉ አገልግሎትና እንክብካቤ የዘር፣ የጾታ፣ የሃይማኖት ወዘተ… መድልኦ የሌለበትና ተመሳሳይነት ሊኖረዉ ይገባል፡፡

አንድ ሐኪም ተገቢዉን የሙያ ትጋትና ጥረት በማድረግ ጥንቃቄ የተሞላበት የህክምና አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ በዚህ መሰረት ሐኪሙ በህክምና ሙያዉ ጥበብ ወይም አሰራር መሰረት ማድረግ የሚጠበቅበትን እንዲሁም ከታካሚዉ ጋር በገባዉ የዉል ስምምነት ወይም በሕግ መሰረት የተጣለበትን ግዴታ ሳይወጣ ቀርቶ በታካሚዉ ላይ ጉዳት ካደረሰ እና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ የሕክምና ስህተት ፈጽሟል ለማለት ይቻላል፡፡ አንድ ሐኪም ከህክምና ሙያዉ አሰራርና ጥበብ ዉጭ የሕክምና አገልግሎት መስጠት አለመስጠቱ የሚረጋገጠዉ በተመሳሳይ ሙያ ላይ በተሰማሩ የሕክምና ባለሙያዎች ነዉ፡፡ ስለሆነም አንድ ሐኪም ግዴታዉን አልተወጣም ሊባል የሚችለዉ ከሕክምናዉ አሰራር ጥበብ ዉጭ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት በታካሚዉ ላይ ጉዳት ካደረሰ ነዉ፡፡

2. የመንስኤ (ምክንያት) እና የዉጤት ግንኙነት፤

አንድ የህክምና ባለሙያ የህክምና ስህተት ፈጽሟል ለማለት እና በህግ ተጠያቂ ለማድረግ በታካሚዉ ላይ የደረሰዉ የአካል ወይም የህይወት አደጋ የተፈጠረዉ በሐኪሙ ስህተት መሆን ይኖርበታል፡፡ በምክንያቱና በወጤቱ መካከል ግንኙነት አለ የሚባለዉ በነገሮች የታወቀ ወይም የተለመደ ሂደት የሀኪሙ ድርጊት ወጤቱን ለማስገኘት የሚችል ሆኖ ሲገኝ ነዉ፡፡ ይህ አይነቱ መርህ ወንጀልን ለማቋቋም እንደ አንድ መስፈርት የተቀመጠ ሲሆን በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 24 ንዑስ አንቀጽ 1 ስር በግልጽ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ የህግ ስርአት የቅርብ ምክንያትን እንጂ የሩቅ ምክንያትን አይቀበልም፡፡ በሌላ በኩል ጉዳት ባይደርስም ነገር ግን የህክምና ባለሙያው መከተል ያለበትን የተለመደ ሥርዓት ባለመከተል የፈፀመው ተግባር ካለ የህክምና ስህተት የለም ማለት አለመሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡

3. ጉዳት መድረስ፤

ጉዳት ደረሰ የሚባለዉ የህክምና ባለሙያዉ በቸልተኝነት ጉዳቱን ያደረሰ ስለመሆኑ ሲረጋገጥ ሲሆን አንድ ሀኪም ለታካሚዉ የሕክምና አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት ወይም ከዚያ በኋላ በታካሚዉ ላይ ጉዳት አድርሶ እንደሆነ ነዉ፡፡ ጉዳት ማለት ከቀላል የአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ የሚችል እና በሀኪሙ ስህተት ምክንያት የተፈፀመ ማለት ነዉ፡፡ ለምሳሌ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት አንድ ሐኪም ከህክምናዉ አሰራር ዉጭ ሕክምና በማድረግ በታካሚዉ ላይ የሚያደርሰዉን ጉዳት መጥቀስ ይቻላል፡፡

4. በታካሚው ላይ የደረሰው ጉዳት ወደ ሚታወቅ ሌላ ጉዳት ያጋለጠው መሆንን ማረጋገጥ፣

ምንም እንኳን የሕክምና ባለሙያው የሕክምና ስህተት ቢፈጽምም ወይም የፈጸመው ድርጊት በተመሳሳይ የሕክምና ባለሙያ መስፈርት ከደረጃ በታች ቢሆንም ስህተት የተፈጸመበት ታማሚ ጉዳት እንደደረሰበት እስካላረጋገጠ ድረስ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ይዞ ለመሔድ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው መፍትሄ በአንድ አጥፊ ምክንያት ጉዳት መድረሱን ማረጋገጥና የደረሰውን ጉዳት የሚክስ ውሳኔ የመስጠት ተግባር በመሆኑ ነው፡፡ ሆኖም በአስተዳደራዊ ጥፋት ረገድ በዲስፕሊን የህክምና ባለሙያውን ሊጠይቅ ይችላል፡፡
ምን ዓይነት ስህተቶች ናቸው የሕክምና ስህተት የሚባሉት ለሚለዉ ስህተቶች የሕክምና ስህተት የሚባሉት በተለያዩ ዘርፍ ውስጥ ሊወድቁ ይችላሉ፡፡

ከእነዚህም መካከል፡-•

 በምርምራ ወቅት ታማሚውን በተገቢዉ ሁኔታ አለመመርመር ወይም የታማሚውን ሁኔታ ለመመርመር መዘግየት፣
 የምርመራ ውጤቶችን በተሳሳተ መንገድ መረዳት ለምሳሌ የኤክስሬይ ዉጤቶችን አሳስቶ ማንበብ ወይም መረዳት፣
 መድኃኒት ከመስጠት ጋር በተያያዘ ለምሳሌ ትክክል ያልሆነ፣ የተሳሳተ ወይም የሚጋጭ የመድኃኒት ትዕዛዝ መስጠት፣
 አንድ የሕክምና ሥነ ሥርዓት ያለውን ጉዳት ወይም ሥጋት ለታማሚው አለመንገር፣ አለማስረዳት ወይም አለማስጠንቀቅ፣
 ታማሚው ወይም የቅርብ ቤተሰቡ በግልጽ ፈቃዱን ሳይሰጥ በታማሚው ላይ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን መፈጸም፣
 የህክምና ስነ-ስርዓት ወቅት ስህተት መፈፀም ለምሳሌ በቀዶ ጥገና ወቅት ወይም ልጅ በማዋለድ ጊዜ ስህተት መፈፀም እና ሌሎችን ያካትታል፡፡
2. ሕክምና ተቋማት እና የጤና ባለሙያዎች የአስተዳደርና የፍትሐብሔር ኃላፊነት፤

2.1 አስተዳደራዊ እርምጃዎች፤

አስተዳደራዊ እርምጃ ማለት አንድ ሠራተኛ በሚሰራዉ ጥፋት መሰረት በዲስፕሊን የሚጠየቅበት ሥርዓት ማለት ነዉ፡፡ የአስተዳደራዊ እርምጃ ዓላማ ሠራተኛዉ ከፈጸመዉ ጥፋት እንዲታረምና ብቁ ሠራተኛ እንዲሆን ለማስቻል ወይም የማይታረም ሆኖ ሲገኝ ከስራዉ በማሰናበት የሚወሰድ የመፍትሔ እርምጃ ነዉ፡፡ የዲሰፕሊን ጉድለት የፈፀመ ሠራተኛ እንደጥፋቱ ክብደት የቃል ማስጠንቀቂያ፣ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ ከስራ ደረጃና ደመወዝ ዝቅ ማድረግ እንዲሁም ከስራ ማሰናበትን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመለከት መንግስት ደረጃዉን ባልጠበቀ የጤና አገልግሎት እንዲሁም ብቃትና የሙያ ሥነ-ምግባር በጎደለዉ የጤና ባለሙያ ምክንያት በዜጎች ላይ ሊደርስ የሚችለዉን የጤና ችግር ለመከላከል ይቻል ዘንድ የጤና አገልግሎቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የተለያዩ ሕጎችን በማዉጣትና በተግባር ላይ በማዋል የቁጥጥር ሥርዓት ዘርግቷል፡፡ አዋጅ ቁጥር 1112/2011 በአንቀጽ 48 አግባብ ባለዉ አካል የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ወይም የህክምና ሙያ ሥራ ፈቃድ የተሰጠዉ ማንኛዉንም ሰዉ ጤናን በተመለከተ አዋጆችን፣ ደንቦችን ወይም መመሪያዎችን በመተላለፍ ሲሰራ የተገኘ እንደሆነ የተሰጠዉ የህክምና ምስክር ወረቀት ወይም ፈቃድ ሊታገድ ወይም ሊሰረዝ እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 41 እና 90 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

አንድ የጤና ባለሙያ የጤና አገልግሎት ለመስጠት አስቀድሞ በሙያው እውቅና ካለው ተቋም የሰለጠነ መሆኑ ተረጋግጦ እና ቃለ መሀላ እንዲፈፅም ይደረጋል፡፡ ይህን ተላልፎ የአሰራር ስርዓቱን ወይም የሥነ-ምግባር መመሪያዎችን ሲጥስ እርምጃ የሚወሰደዉ የጤና ስነ-ምግባር ኮሚቴ ለኢትዮጵያ የምግብና የመድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በሚያቀርበዉ የዉሰኔ ሀሳብ አማካኝነት ነዉ፡፡

የምግብ የመድሀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 299/2006 አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የጤና ስነ-ምግባር ኮሚቴ የሚቋቋመዉ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አማካኝነት ሲሆን የስራ ድርሻዉም የሚቀርቡለትን ጉዳዮች አጣርቶ ጥፋት በፈፀሙ የጤና ባለሙያዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለባለስልጣኑ መስሪያ ቤት የዉሰኔ ሀሳብ የሚያቀርብ ነዉ፡፡

የጤና ሙያ ሰነ-ምግባር ኮሚቴ አንድ የጤና ባለሙያ ከሕክምና ስነ-ምግባር ዉጪ በመስራት በተገልጋዩ ላይ ጉዳት ያደረሰ ከሆነ ወይም ጉዳት ባያደርስም የስነ ምግባር መርሆችን ተላልፎ ከተገኘ ጉዳዩን አስመልክቶ ተገቢዉን ማጣራት በማድረግ በባለሙያዉ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋል፡፡ ከእነዚህ ዉስጥም የሙያ ፈቃድ ማገድ ወይም እንደ ጥፈቱ ክብደት የሙያ ፈቃድ መሰረዝ፣ የገንዘብ ቅጣት መጣል፣ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ፣ የቃል ወይም የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ የደመወዝ ቅጣት መጣል እንዲሁም ሌሎች እርምጃዎችን ሊያካትት ይችላል፡፡

2.2 የጤና ባለሙያዎች የፍትሐብሔር ኃላፊነት፣

ማንኛዉም የጤና ባለሙያ ከምንም ነገር በላይ ለታካሚዉ ጤንነት ቅድሚያ ሊሰጥ ይገባዋል፡፡ የጤና ባለሙያዉ በሚሰጠዉ አገልግሎትም ሆነ በሚወስነዉ ወሳኔ ምክንያት ለሚከሰት ስህተት ወይም ጉዳት በሕግ አግባብ ተጠያቂነት አለበት፡፡ አንድ የጤና ባለሙያ የህክምና ሙያዉ በሚፈቅደዉ መልኩ ታካሚዉን ማገልገል ይጠበቅበታል፡፡

የፍትሐብሔር ኃላፊነት ሲባል አንድ የጤና ባለሙያ ከተገልጋዩ ወይም ከታካሚው ጋር በሚያደርገዉ የዉል ስምምነት የሚፈጠር ወይም ከዉል ዉጪ በሆነ እና በሕግ በተደነገገ ጊዜ የሚመነጪ ኃላፊነት ነዉ፡፡ ይህ ዓይነት ኃላፊነት አጥፊዉ በገንዘብ ወይም ዋጋ ባለዉ ዕቃ ወይም ንብረት የሚቀጣበት ሥርዓት ነዉ፡፡ አንድ ሐኪም የሕክምናዉ ጥበብ ከሚፈቅደዉ ዉጪ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት በተገልጋይ ላይ ጉዳት ካደረሰ እንደነገሩ ሁኔታ ማለትም ከዉል ዉጪ ወይም ከዉል በሚመነጭ ኃላፊነት ጉዳት የደረሰበትን ተገልጋይ የመካስ ነዉ፡፡

3.3 የሕክምና ተቋማት የፍትሐብሔር ኃላፊነት፤

የሕክምና ተቋማት ባለሙያዎቻቸዉ ለታካሚዎች የሕክምና አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት በታከሚዉ ላይ አካላዊ ብሎም ለሞት የሚዳርግ ጉዳት ሊያደርሱ ይቻላሉ፡፡ በዚህ ወቅት የሕክምና ተቋማት ለሚደርሰዉ ጉዳት ከህክምና በለሙያው ጋር በአንድነት በፍትሐብሔር ተጠያቂ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከላይ እንዳየነዉ የፍትሐብሔር ኃላፊነት ስንል አንድ ሰዉ በዉል ወይም ከዉል ዉጪ ከሚመነጭ የሚኖርበት ኃላፊነትን የሚመለከት ሲሆን የሕክምና ተቋማትም ከታካሚዎቻቸዉ ጋር በሚያደርጉት የዉል ስምምነት ወይም ከዉል ዉጪ በሚያደርሱት ጉዳት የፍትሐብሔር ኃላፊነት ይኖርባቸዋል፡፡

3.3.1 የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ኃላፊነት፣

የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ሠራተኞቻቸዉ በተቋሙ ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት በሚያገኙ ታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት ከዉል ወጪ ኃላፊነት አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2126 መሰረት የመንግስት ሹም ወይም ሠራተኛ በራሱ ጥፋት በሌላ ሰዉ ላይ ጉዳት የደረሰ እንደሆነ በማናቸዉም ምክንያት ቢሆን ኪሳራዉን ለመክፈል ይገደዳል፡፡ ነገር ግን የተደረገዉ ጥፋት የመንግስቱን ስራ ሲሰራ የደረሰ የስራ ጥፋት የሆነ እንደሆነ የተጎዳዉ ሰዉ ኪሳራ ከመንግስት ላይ ለመጠየቅ ይችላል፡፡ ሠራተኛዉ ያደረገዉ ጥፋት የግል ጥፋቱ የሆነ እንደሆነ ግን መንግስት ኃላፊነት አይኖርበትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2127 የሥራ ጥፋት ምን ማለት እንደሆነ ያስቀመጠ ሲሆን ጥፋቱ እንደ ሥራ ጥፋት ሆኖ የሚቆጠረዉ ጥፋት አድራጊዉ በዚሁ ጥፋት ላይ የወደቀዉ በቅን ልቦና በስልጣኑና በሥራዉ ክፍል መልካም ያደረገ መስሎት የፈፀመ ሲሆን ነዉ፡፡ በቅን ልቦና ያልተሰራ ለመሆኑ ተቃራኒ ማስረጃ ያልቀረበ እንደሆነ የሹሙ ወይም የሰራዉ አሰራር በቅን ልቦና እንደተሰራ ይገመታል በማለት አስቀምጧል፡፡ በአንድ የመንግስት የጤና የሕክምና ተቋም ተቀጥሮ የሚሰራ የሕክምና ባለሙያ በተቋሙ ዉስጥ ሆኖ ታካሚዎችን በሚያክምበት ወቅት ጥፋት ከፈፀመ ኃላፊ ሊሆን የሚገባዉ የህክምና ተቋሙ ነዉ፡፡

ይኸዉም ጥፋቱ የተፈፀመዉ ከላይ በተገለፀዉ መሰረት በቅን ልቦና በስልጣኑና ለስራዉ ክፍል መልካም ያደረገ መስሎት የተፈፀመ ሲሆን ነዉ፡፡ የሕክምና ጥፋት ተፈጽሟል አልተፈጸመም የሚለዉን ጉዳይ አጣርቶ ትክክለኛ መረጃ ለፍርድ ቤት ወይም አግባብ ላለዉ አካል ሊሰጥ የሚችለዉ በሙያዉ በቂ ዕዉቀት፣ልምድ እና ክህሎት ያለዉ ባለሙያ መሆን ይገባዋል፡፡ በሌላ በኩል ግን ጥፋቱ የሐኪሙ ወይም የሰራተኛዉ ከሆነ የጤና የሕክምና ተቋሙ ኃላፊነት አይኖርበትም፡፡ ታካሚዉ ከተቋሙ የጉዳት ካሳ ተቀብሎ ከከሆነም መንግስት ጥፋት ከፈፀመዉ ሐኪም ወይም ሠራተኛ ላይ ለመጠየቅ መብት ይኖረዋል (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2126(2)፡፡የመንግስት የሕክምና ተቋማት ስለ ሠራተኞቻቸዉ ያለባቸዉ ኃላፊነት የሚመሰረተዉ ተቋሙ ከሠራተኛዉ ጋር የሥራ ቅጥር ዉል ስምምነት ፈጽሞ ከሆነብቻ መሆኑን
👍1
ከላይ የተጠቀሱት የሕግ ድንጋጌዎች ያስረዳሉ፡፡ ነገርግን በሕክምና ተቋሙ የሥራ ቅጥር ዉል ሳይፈጽሙ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሠራተኞች የሚኖሩበት አጋጣሚ ስለሚኖር እነዚህ ሠራተኞች ( የሕክምና ባለሙያዎች) በታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት እራሳቸዉ ተጠያቂ ናቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2134 መሰረት አንድ ሰዉ የተጠየቀዉን ሥራ በሚሰራበት ጊዜ ለሥራዉ ጥፋት ጥፋተኛዉ በሥራ ሰጪዉ ሥልጣን ስር ያልሆነ እንደሆነ ነፃነቱንም እንደያዘ መሆኑ ከታወቀ አሰሪዉ በኃላፊነት እንደማይጠየቅ አስቀምጧል፡፡ ስለሆነም በዚህ ወቅት ለሚደርሰዉ ጉዳት ኃላፊነት የሚወስደዉ በራሱ ሥልጣን የሚሰራዉ ሠራተኛ / Indepenent Contactor / ይሆናል፡፡ በራሱ ስልጣን የሚሰራዉ ሠራተኛ በታካሚዉ ላይ ለሚያደርሰዉ ጉዳት የሚጠየቀዉ በራስ ጥፋት በሌላሰዉ መብትና ጥቅም ላይ የሚደርስ ጉዳት (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2027(1) እና 2031 (1) በሚለዉ ሕግ ነዉ፡፡

3.3.2 የግል የሕክምና ተቋማት ኃላፊነት፣

የሕግ ሰዉነት የተሰጣቸዉ የግል የጤና የሕክምና ተቋማት ሠራተኞች በታካሚ ላይ በሚያደርሱት ጉዳት ልክ እንደ መንግስት የጤና የሕክምና ተቋማት ሁሉ በፍትሐብሔር ተጠያቂ ናቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2129 መሰረት የሰዉነት መብት የተሰጣቸዉ ድርጅቶች ሠራተኞቻቸዉ፣እንደራሴዎች፣ ወኪሎች ወ.ዘ.ተ የተሰጣቸዉን ስራ በሚያከናዉኑበት ጊዜ ኃላፊነትን የሚያስከትል ስራ የፈፀሙ እንደሆነ የፍትሐብሔር ኃላፊነት ያለባቸዉ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ አንድ የሕክምና ሠራተኛ ስራዉን በሚሰራበት ጊዜ ኃላፊነትን የሚያስከትል ጥፋት የሰራ እንደሆነ በፍትሐብሔር በኃላፊነት የሚጠየቀዉ አሰሪዉ ሲሆን ይህም የሚሆነዉ ጥፋቱ የደረሰዉ በመስራት ወይም ባለመስራት ሆኖ ስራን በመስራት ተፈፅሞ የሆነ እንደሆነ ነዉ፡፡ በመስራት ወይም ባለመስራት የደረሰዉ ጥፋት ሥልጣን በመተላለፍ ሆኖ ሰሪዉ እንዳይሰራ በግልጽ ተከልክሎ ቢገኝ እንኳ ጉዳት የደረሰበት ሰዉ ምክንያቱን ካላወቀ ወይም ሊዉቀዉ ይገባዉ ነበር የሚል ካልሆነ በስተቀር በፍትሐብሔር ኃላፊነት የሚጠየቀዉን ክልከላዉ ምክንያት ሆኖ ከኃላፊነት አያድነዉም (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2131 (1) እና (2) ይመለከቷል፡፡ ስለሆነም የግል የጤና የሕክምና ተቋማት ከላይ በተገለጸዉ አግባብ ሠራተኞቻቸዉ በታካሚዎች ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት ከዉል ወጪ ኃላፊ ይሆናሉ ማለት ነዉ፡፡ የተቋሙ የቅጥር ሠራተኞች ያልሆኑ ብዙ የጤና ባለሙያዎች በአንድ የጤና ተቋም ዉስጥ በተለይ ደግሞ በግል የጤና ተቋማት ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ለትርፍ ተቋቋሙ የግል የጤና ተቋማት አንዳንድ የሕክምና አገልግሎቶችን ለተገልጋዩ ኅብረተሰብ የሚሰጡት በራሱ ስልጣን በሚሰራ ሠራተኛ አማካኝነት ነዉ፡፡ በዚህ መንገድ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶች በቂ የሕክምና ባለሙያና የሕክምና መሣሪያ በሀገሪቱ ዉስጥ በሌለባቸዉ ሲሆን ለአብነት ያህልም የፊዚዮትራፒስት፣ የራዲዮሎጂስት እና የኒሮሎጂስት ባለሙያዎች የሚሰጧቸዉን የሕክምና አገልግሎቶች መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዚህ ወቅት በግላቸዉ የሕክምና አገልግሎት በተቋሙ የሚሰጡ ሠራተኞች በታካሚዉ ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት የጤና ተቋሙ የፍትሐብሔር ኃላፊነት የለበትም፡፡ ምክንያቱም በሠራተኛዉ እና በጤና ተቋሙ መካከል የስራ ዉል ወይም የቅጥር ዉል ስምምነት የሌለ በመሆኑ ነዉ፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2134 መሰረት አንደሰዉ የተጠቀሰዉን ሥራ በሚሰራበት ጊዜ ለሰራዉ ጥፋት ጥፋተኛዉ በስራ ሰጪዉ ሥልጣን ስር ያልሆነ እንደሆነ ነፃነቱንም እንደያዘ መሆኑ ከታወቀ አሠሪዉ በኃላፊነት አይጠየቅም በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ አንቀጽ የሚደነግገዉ ስለ / Indepenent Contactors / በራሱ ሥልጣን ስለሚሰራ ሠራተኛ ሲሆን የጤና ተቋማት በዚሁ ሠራተኛ ጥፋት ምክንያት በተቋሙ ዉስጥ የሕክምና አገልግሎት በሚያገኙ ተገልጋዮች ላይ ለሚደርስ ጉዳት ኃላፊነት አይኖርባቸዉም ፡፡ የጤና ተቋማት በራሱ ሥልጣን በሚሰራ ሠራተኛ በጤና ተቋሙ ተገልጋዮች ላይ ለሚደርስ ጉዳት የጤና ተቋማት ከዉል ዉጪ ኃላፊነት የለባቸዉም ሲባል ጉዳት የደረሰባቸዉ ተገልጋዮች የሕግ መፍትሔ የላቸዉም ማለት እንዳል ሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡.ምክንያቱም ጉዳቱ የደረሰባቸዉ የሕክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጉዳቱ የደረሰባቸዉ በራሱ ስልጣን በሚሰራ ሠራተኛ ከሆነ የጤና ተቋማቱን መጠየቅ የማይችሉ ቢሆንም አገልግሎቱን የሰጠዉን ሠራተኛ ግን በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ከመጠየቅ የሚከለክል ሕግ የሌለ በመሆኑ ነዉ፡፡ ይኸዉም በራሱ ሥልጣን በሚሰራ የሕክምና ባለሙያ በታካሚዉ ላይ ለሚደርሰዉ ጉዳት ከታካሚዉ ጋር የዉል ስምምነት ያለዉ ከሆነ በዉሉ መሰረት ተጠያቂ የሚሆን ሲሆን በሁለቱ መካከል የዉል ስምምነት ከሌለ ደግሞ ከዉል ዉጪ ኃላፊነት በራስ ጥፋት በሌላ ሰዉ መብትና ጥቅም ላይ የሚደርስ ጉዳት በሚለዉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2031(1) መሰረት ኃላፊ ይሆናል፡፡
ኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ
#Join #Join #Share
@EthiopianLawStudentsUnion
@EthiopianLawStudentsUnion
@EthiopianLawStudentsUnion
https://t.me/EthiopianLawStudentsUnion
👍1
📌 #የውርስ_ጉዳይን_የተመለከቱ_የይርጋ_ገደቦች ‼️⤵️

✍️ 1) ኑዛዜን ለመቃወም የተቀመጠ ጊዜ ገደብ

ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ በተመለከተ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቁጥር 973 ላይ የተመለከተው ተፈጻሚ ሚሆነው ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚለውን ክስ ኑዛዜው ሲነገር በነበሩ ሰዎች የቀረበ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973/1/ ላይ እንደተገለጸው “ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይም የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው አይጸናም ወይም አንዱ በኑዛዜው የተነገረው ቃል አይጸናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸውን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለ ክፍያው በሂሳብ አጣሪው የቀረበውን የድልድል አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜው ከተነበበት አንስቶ በሚቆጠር የአስራ አምስት ቀን ጊዜ አላቸው”፡፡

በሌላ መልኩ ደግሞ ኑዛዜው ሲነበብ ያልነበሩ ሰዎች መቃወሚያቸውን መቼ ሊቀርቡ ይችላሉ ለሚለው በፍ/ሕ/ቁ 974/1/ እና 2 ላይ የተገለጸ ሲሆን በዚህም መሰረት “ በኑዛዜ ንባብ ሥነ-ሥርዓት ላልነበሩ ወይም በኑዛዜው ንባብ ሥነ-ሥርዓት በወኪልነት ላልሰሙ ሰዎች እንዲሁም ኑዛዜው በሌሉበት የተነበበ እንደሆነ ከዚህ በላይ የተገለጸው የጊዜ ገደብ ለመቁጠር መነሻ የሚሆነው ሥለ ክፍያው ድልድልና አመዳደብ ሀሳቡን ከተነገራቸው ቀን አንስቶ ነው”፡፡

በፍ/በ/ህ/ቁ 973/2/ ላይ በተገለጸው መሰረት ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከአምስት ዓመት በኋላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ሟች ከሞተ ከአምስት ዓመት በኋላ ስለ ኑዛዜው መጽናትና ስለክፍያው አመዳደብ አጣሪው ያቀረበውን የድልድል ሀሳብ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን መቃወሚያ ሊቀርብበት አይችልም፡፡

ከዚህ በላይ ከተገለጹት የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በተያያዘ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 82585 በቅጽ 15 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በትርጓሜውም “በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ድንጋጌዎች አቤቱታ አቅርቢው ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ ወይም የተወከለ የመሆን አለመሆን መስፈርት መሰረት በማድረግ ይርጋው መቁጠር የሚጀምርበትን ጊዜ እና ፍጹም የሆነ የይርጋ ጊዜ በቁጥር 974/2/ ከመደንገጋቸው በስተቀር ሁለቱም ድንጋጌዎች ኑዛዜው ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን ስርዓት የሚደነግጉ በመሆቸው ተያያዥነት አላቸው በማለት ኑዛዜ መኖሩን ማወቅ እና የኑዛዜውን ሙሉ ይዘት ማወቅ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው ሲል በፍ/ብ/ህ/ቁ 973/1/ የተመለከተው የ15 ቀን ጊዜ ገደብ የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ሳይሆን የመግለጫ ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በመሆኑም ስለ ኑዛዜ መኖር እንጂ ስለድልድሉ የማያውቅ ወራሽ መግለጫ የማቅረብ ግዴታ ስለማይኖርበት ጊዜው መቁጠር የሚጀምረው በኑዛዜው የተደረገውን ድልድል ካወቁበት ቀን ጀምሮ ነው” በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

በሟች የተደረገ ኑዛዜ ከውርስ የነቀለኝ በመሆኑ ሊፍርስ ይገባል በማለት ኑዛዜው ሲነበብ በነበረ አመልካች የሚቀርብ የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 መሰረት በተገለጠው የጊዜ ገደብ ነው ወይስ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 በተገለጸው ጊዜ ውስጥ ነው? የሚለው አከራካሪ ጉዳይ በመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 152134 በቅጽ 23 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በውሳኔውም መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ስለ ኑዛዜ መነበብ እንዲሁም ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ኑዛዜው እንዲፈርስ አቤቱታ የሚያቀርቡበትን ሥርዓትና ጊዜውን በሚመለከት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል /ነቅሎናል/ በማለት ኑዛዜው እንዲፈርስ የሚቀርብን ወይም የቀረበ አቤቱታን የሚመለከት አይይለም፡፡ በመሆኑም ኑዛዜው ከውርስ የመንቀል ውጤት ያለው በመሆኑ እንዲፈርስ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄ ሊታይ የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነውእንጂ በአንቀጽ 973 መሰረት አይደለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው የሕግ ትርጓሜ መሰረት ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ አንድ ኑዛዜ ፈራሽ ነው በሚል ስለሚቀርብ መግለጫ እና እንዲሁም መግለጫው እና ክሱ ሊቀርብ ስለሚገባው የጊዜ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ተፈጻሚነት የሚኖረው ኑዛዜ ሲነበብ በነበሩ ወይም በተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ሲሆን በአንቀጽ 974 ድንጋጌ ደግሞ ተፈጻሚነቱ በኑዛዜ ሥነ-ሥርዓት ባልነበሩ ወይም ባልተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነው፡፡

✍️ 2) የወራሽነት ጥያቄ ለማቅረብ የተቀመጠ ጊዜ ገደብ

የወራሽነት ጥያቄን ለማቅረብ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000 ላይ የተመለከተ ሲሆን ወደዚህ ነጥብ ከመግባቴ በፊት ወራሽነት ጥያቄ ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እደሚከተለው ለመዳሰስ እሞክራለሁ÷
በፍ/ብ/ሕ/ቁ 996(1) ላይ በተገለጸው መሰረት ወራሽ የሆነ ሰው የሟቹ ወራሽ መሆኑንና ከውርሱ ላይ የሚያገኘውን ድርሻ የሚያመለክት የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል በማለት የተገለጸ ሲሆን ይህ ማለት ፍ/ቤቱ የወራሽነት ምስክር እንዲሰጠው ወራሹ ሲፈልግ የሚጠይቀው እንጂ ሟችን ለመውረስ የግድ ከፍ/ቤቱ የወራሽነት ማስረጃ ማምጣት እንዳለበት የሚያስገድድ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በተግባር እንደሚስተዋለው ስመ ንብረቱ ለማዛወር እና ከሌሎች የሟች መብቶች ለመጠቀምና ለመስራት በፍ/ቤቱ የተረጋገጠ የወራሽነት የምስክር ወረቀት መጠየቁ የተለመደ አሰራር ሆኗል፡፡

ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን መሰረት በማድረግ አንድ ሰው ዋጋ ያለው የወራሽነት ማስረጃ ሳይኖረው ውርሱን ወይም ከውርሱ አንዱን ክፍል በእጁ ያደረገ እንደሆነ እውነተኛው ወራሽ ወራሽነቱን እንዲታወቅለትና የተወሰዱበት የውርስ ንብረቶች እንዲመለሱለት በዚህ ሰው ላይ የወራሽነት ጥያቄ ክስ ሊያቀብበት ይችላል በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 999 ላይ ተደንግጓል፡፡ ስለዚህ ይህን መሰል የክስ አቤቱታ አቤቱታ መቼ ሊቀርብ ይገናል ለሚለው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ ላይ የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡

በዚሁ መሰረት ከሳሽ መብቱንና የውርሱን ንብረት በተከሳሽ መያዛቸውን ካወቅ ሶስት ዓመት ካለፈ በኋላ ስለ ወራሽነት ጥያቄ የሚቀርበው ክስ ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡ በሌላ መልኩ በአንቀጽ 1000(2) ላይ እንደተገለጸው “ሟቹ ከሞተበት ወይም ከሳሹ በመብቱ ለመስራት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት አመት ካለፈ በኋላ ከዘር የወረደ ርስት ካልሆነ በቀር የውርስ ጥያቄ ክስ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን ተቀባይነት አያገኝም የሚለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡
👍3
ከዚህ በላይ በአንቀጽ 1000(1) እና (2) ላይ የተመለከቱት የጊዜ ገደቦች ከሌሎች የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በተለይም 1ኛ) አንድ ወራሽ የሟች ኑዛዜ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ኑዛዜ በእጁ እንደሚገኝ ለውርስ አጣሪው አቅርቦ ውርስ አጣሪው ኑዛዜውን በሚነበብበት ሰዓት ራሱ ወይም ወኪሉ ካልነበረ ወራሹ ኑዛዜው ከፈሰሰበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት አመታት ውስጥ መቃወሚያ ካላቀረበ ከዚያ በኋላ ሊቀርብ እንደማይችል በፍ/ሕ/ቁ 974(2) የተመለከተው በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) ካለው የጊዜ ገደብ ጋር እንዴት ተጣጥሞ ተግባራዊ ይሆናሉ ከሚለው ጋር ጥያቄ የሚያስነሳ ሲሆን በሌላ መልኩ በፍ/ሕ/ቁ 1000(1) እና (2) አተረጓጎምና አፈጻጸም እንዴት መሆን አለበት በሚል አልፎ አልፎ ጥያቄ ሲያስነሳ ይስተዋላል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ የሕግ ማዕቀፎች ላይ የተጠቀሱት የጊዜ ገደቦች በተመለከተ መከተል የሚገባንን የሕግ ትርጓሜ እንደሚከተው ለማብራራት ተሞክሯል÷ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 974/2/ ተፈጻሚ የሚሆነው የሟች ውርስ የሚያጣራ ፤በሕግ በኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሾመ የውርስ አጣሪ ፤ሟች አድርጎታል የተባለው ኑዛዜ አግኝቶ የኑዛዜውን ፎርምን የኑዛዜውን ዋጋ መኖር ፤የሟች ያለኑዛዜ ወራሾች ወይም አራት አካለመጠን ያደረሱ ሰዎች ባሉበት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 በተመረመረበት ሁኔታ ነው፡፡ ሆኖም ግን ኑዛዜ ያለ መሆኑን ለውርስ አጣሪው ሳያሳውቅ ቀጥታ የኑዛዜ ወራሽ መሆኑ እንዲታወቅለት ለፍ/ቤት አመልክቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት በመውሰድ የሟች ንብረት በእጁ ያደረገ ሰው ወይም በሀሰት የሟች ያለኑዛዜ ወራሽ ነኝ ብሎ የሟችን ንብረት ከወሰደው ሰው ለማስመለስ አግባብ የሆነው የይርጋ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 968 የተጠቀሰው ሳይሆን በፍብ/ሕ/ቁ 1000/1/ የተመለከተው ተፈጻሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡

በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ እና 1000/2/ አስመልክቶ የተለያዩ አተረጓገሞች የሚስተዋሉ ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 30158 ፤26422 እና 34011 በቅጽ 7/6/6/ እንዲሁም በቅጽ 11 በሰ/መ/ቁ 52407 የሰጠውን አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ለመዳሰስ ሞክሬያለው፡፡ በዚሁ አግባብ በፍ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ ሟች ከሞተ አስራ አምስት አመት በላይ ወይም ተከሳሹ በመብቱ ሊሰራበት ከቻለበት ቀን አንስቶ አስራ አምስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ አስራ አምስት ዓመት ካለፈው በኋላ ክስ ሊያቀርብ የሚቻለው ከዘር የወረደ ርስት በሆነ ንብረት ላይ ነው፡፡

ርስት የሚለው ቃል በፍ/ሕ/ቁ 1130 እና ስለ ንብረቶች በሚናገረው የፍ/ብሔር የህጉ ክፍል መሬት የሚያመለክት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ በኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት ርዕስት የሚለው መሬትን የሚመለከት መሆኑን ጠቅሶ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚሁ አግባብ ከዘር የወረደ ርዕስት የሚለው ቤትን አያጠቃልልም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ በርዕስት የሚተላለፍ መሬት ብቻ ማለት ሰለሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ መሰረት ለተወላጆች የሚተላለፍ መሬት ብቻ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በኢፌድሪ ህገ መንግስት መሰረት መሬት የመንግስትና የህዝብ ሀብት በመሆኑ ከዘር የወረደ ርዕስት ካልሆነ በስተቀር በማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/2/ ላይ የተገለጸው የተሻረ እና ተፈጻሚነት የሌለው ነው በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ አፈጻጸምን በተመለከተ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 32407 በቅጽ 11 ላይ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በዚህም መሰረት በወራሾች መካከል የሚነሳ የውርስ ንብረት ክርክር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1000/1/ በተደነገገው አግባብ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ መቅረብ ያለበት ሲሆን ወራሽ በሆነ እና ወራሽ ባልሆነ ተከራካሪ ወገን መካከል የሚቀርበው የውርስ ንብረት ይገባኛል ጥያቄ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1677 እና 1845 መሰረት በአስር አመት ጊዜ ውስጥ ካልቀረበ መብቱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡

✍️ 3) የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ስለመሆኑ

ወራሾች ተለይተው የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየ የውርስ ሀብት ያለ እንደሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1062 በተገለጸው መሰረት እያንዳንዱ የጋራ ወራሾች ውርሱን እንከፋፈል በማለት በማንኛውም ጊዜ ለመጠየቅ የሚችሉ በመሆኑ የክፍፍል ጥያቄ በይርጋ የማይታገድ ይሆናል፡፡

ሳሙኤል ግርማ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ

Ethiopia Legal Service
Ethiopian Law Student's Union
የኢትዮጵያ የህግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት
Ethiopian law school students Union (ELSSU)
https://t.me/EthiopianLawStudentsUnion
Forwarded from አለ ሕግ
የፈተና ቦታ እና ጊዜ መግለፅን ይመለከታል🔴🔴
የኢፌደሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ‼️‼️‼️
https://t.me/lawsocieties
https://www.facebook.com/lawsocieties/
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties