Forwarded from አለ ሕግ
የጥብቅና ፈቃድ የተሰጣቸው ጠበቆችና ድርጅቶች በተለያየ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ሊደረጉ ነው
13 June 2021
ታምሩ ጽጌ
ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የጥብቅና ፈቃድ የሰጣቸውን ጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች ለሕዝብ ተደራሽ እንዲሆኑ በተለያየ መንገድ ይፋ እንዲያደርግ የሚፈቅድ አዋጅ ፀደቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በሙሉ ድምፅ ባፀደቀው፣ የፌዴራል የጥብቅና አገልግሎት ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ እንዳብራራው፣ ተገልጋዩ ማኅበረሰብ ጠበቆችን በቀላሉ ማግኘት እንዲችል፣ የጠበቆችን ዝርዝር መረጃ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በረቂቅ አዋጁ ለውይይት ያልቀረበ ቢሆንም፣ በአዋጁ አንቀጽ 17(4) አዲስ ንዑስ አንቀጽ ተደርጎ መካተቱን የሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ አስታውቋል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ቀርበው የነበሩና በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ውይይት የተደረገባቸው በርካታ አንቀጾች ላይ ማሻሻያ ተደርጎ ፀድቋል፡፡ አዋጁ የፀደቀው ቋሚ ኮሚቴው በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉ ዝርዝር ውይይቶችን በአስረጂነት ከቀረቡ ከፍተኛ የሕግ ባለሙያዎች ከተረዳና ጭብጦችን በመያዝ ከመረመረ በኋላ መሆኑንም በውሳኔው ገልጿል፡፡
ባደረገውም ምርመራ፣ ‹‹ጠበቃ›› በአገር ውስጥ ፈቃድ የተሰጠው ብቻ ሳይሆን በውጭ አገር ሕግ መሠረት የጥብቅና ፈቃድ የተሰጣቸውንም እንደሚያካትት፣ ጥብቅና ‹‹ሙያ›› በመሆኑ በረቂቁ ‹‹የጥብቅና ድርጅት›› የተባለው ‹‹የጥብቅና ሙያ አገልግሎት ድርጅት›› ተብሎ መስተካከሉን ቋሚ ኮሚቴው ያሳለፈው ውሳኔ ያስረዳል፡፡
የጥብቅና አገልግሎት የሚለውም በተመሳሳይ ‹‹የጥብቅና ሙያ አገልግሎት›› በሚል ተስተካክሏል፡፡ ደላላ የሚለው ቃል ሕጋዊ ቃል ሆኖ በንግድ ሕጉ በመደንገጉ፣ በዚህ አዋጅ ‹‹አገናኝ›› በሚል እንዲተካ መደረጉንም አክሏል፡፡
ጠበቆች የጥብቅና ፈቃዳቸውን ለማሳደስ ‹‹የፀና የመድን ዋስትና›› አንዱ መሥፈርት ሆኖ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ የነበረ ቢሆንም፣ አገሪቱም የፀና ዋስትና አሠራር ስለሌላት፣ አስገዳጅ መሥፈርት መሆኑ እንዲቀር ተደርጓል፡፡ ጠበቃው የጥብቅና ፈቃዱን ለሰጪው አካል መልሶ፣ ከሕግ ሥራ ውጪ ከሁለት ዓመት በላይ ከቆየ፣ ፈቃዱን ለማግኘት እንደ አዲስ ፈተና መውሰድ እንዳለበት፣ የቆየው ግን በሕግና ተያያዥ ሥራዎች ላይ ከሆነ ያለፈተና እንደሚወሰድ በአዋጁ ተካቷል፡፡ አዋጁ ለኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር መመርያ የማውጣት ሥልጣን ስለሰጠው፣ የአፈጻጸም ዝርዝር እንደሚያወጣም የቋሚ ኮሚቴው የውሳኔ ሐሳብ ያብራራል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ላይ ያልነበረና በአንቀጽ 23(4) ሥር የጥብቅና ፈቃድ ሰጪው የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ‹‹ቢሮ ማሟላት››ን እንደመሥፈርት ሊጠይቅ እንደማይችል በአዋጁ ተካቷል፡፡
ማንኛውም ጠበቃ በዓመት ከ24 እስከ 30 ሰዓታት የሚደርስ የሕግ ሥልጠና መውሰድ እንዳለበት፣ ጠበቃው ከጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሳይመደብለት ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት መስጠት እንደሚችልና ትክክለኛነቱና እውነት መሆኑ ተረጋግጦ እውቅና እንደሚሰጠውም በአዋጁ አካቷል፡፡ ጠበቃው የዲሲፕሊን ጥፋት ማለትም ለፍርድ ቤት ወይም ለሚመለከተው አካል ፈቃዱን እንዲያሳይ ሲጠየቅ ፈቃደኛ ካልሆነ፣ የያዘው ጉዳይ የት እንደደረሰ በደንበኛው ሲጠየቅ በአግባቡ ካላሳወቀ ካመናጨቀና ክብሩን ከነካ፣ ያለአሳማኝ ምክንያት በቀጠሮ ቀን ከፍርድ ቤት ከቀረ ወይም ከዘገየ፣ ለማኅበሩ መክፈል የሚጠበቅበትን ክፍያ በወቅቱ ካልከፈለና ፈቃዱን በወቅቱ ካላሳደሰ ከ5000 ብር እስከ 7000 ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚጣልበት በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ አዋጁ በርካታ ድንጋጌዎች ተካተው በሙሉ ድምፅ ፀድቋል፡፡
https://t.me/lawsocieties
@lawsocieties
@lawsocieties https://t.me/lawsocieties
13 June 2021
ታምሩ ጽጌ
ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የጥብቅና ፈቃድ የሰጣቸውን ጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች ለሕዝብ ተደራሽ እንዲሆኑ በተለያየ መንገድ ይፋ እንዲያደርግ የሚፈቅድ አዋጅ ፀደቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በሙሉ ድምፅ ባፀደቀው፣ የፌዴራል የጥብቅና አገልግሎት ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ እንዳብራራው፣ ተገልጋዩ ማኅበረሰብ ጠበቆችን በቀላሉ ማግኘት እንዲችል፣ የጠበቆችን ዝርዝር መረጃ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በረቂቅ አዋጁ ለውይይት ያልቀረበ ቢሆንም፣ በአዋጁ አንቀጽ 17(4) አዲስ ንዑስ አንቀጽ ተደርጎ መካተቱን የሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ አስታውቋል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ቀርበው የነበሩና በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ውይይት የተደረገባቸው በርካታ አንቀጾች ላይ ማሻሻያ ተደርጎ ፀድቋል፡፡ አዋጁ የፀደቀው ቋሚ ኮሚቴው በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉ ዝርዝር ውይይቶችን በአስረጂነት ከቀረቡ ከፍተኛ የሕግ ባለሙያዎች ከተረዳና ጭብጦችን በመያዝ ከመረመረ በኋላ መሆኑንም በውሳኔው ገልጿል፡፡
ባደረገውም ምርመራ፣ ‹‹ጠበቃ›› በአገር ውስጥ ፈቃድ የተሰጠው ብቻ ሳይሆን በውጭ አገር ሕግ መሠረት የጥብቅና ፈቃድ የተሰጣቸውንም እንደሚያካትት፣ ጥብቅና ‹‹ሙያ›› በመሆኑ በረቂቁ ‹‹የጥብቅና ድርጅት›› የተባለው ‹‹የጥብቅና ሙያ አገልግሎት ድርጅት›› ተብሎ መስተካከሉን ቋሚ ኮሚቴው ያሳለፈው ውሳኔ ያስረዳል፡፡
የጥብቅና አገልግሎት የሚለውም በተመሳሳይ ‹‹የጥብቅና ሙያ አገልግሎት›› በሚል ተስተካክሏል፡፡ ደላላ የሚለው ቃል ሕጋዊ ቃል ሆኖ በንግድ ሕጉ በመደንገጉ፣ በዚህ አዋጅ ‹‹አገናኝ›› በሚል እንዲተካ መደረጉንም አክሏል፡፡
ጠበቆች የጥብቅና ፈቃዳቸውን ለማሳደስ ‹‹የፀና የመድን ዋስትና›› አንዱ መሥፈርት ሆኖ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ የነበረ ቢሆንም፣ አገሪቱም የፀና ዋስትና አሠራር ስለሌላት፣ አስገዳጅ መሥፈርት መሆኑ እንዲቀር ተደርጓል፡፡ ጠበቃው የጥብቅና ፈቃዱን ለሰጪው አካል መልሶ፣ ከሕግ ሥራ ውጪ ከሁለት ዓመት በላይ ከቆየ፣ ፈቃዱን ለማግኘት እንደ አዲስ ፈተና መውሰድ እንዳለበት፣ የቆየው ግን በሕግና ተያያዥ ሥራዎች ላይ ከሆነ ያለፈተና እንደሚወሰድ በአዋጁ ተካቷል፡፡ አዋጁ ለኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር መመርያ የማውጣት ሥልጣን ስለሰጠው፣ የአፈጻጸም ዝርዝር እንደሚያወጣም የቋሚ ኮሚቴው የውሳኔ ሐሳብ ያብራራል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ላይ ያልነበረና በአንቀጽ 23(4) ሥር የጥብቅና ፈቃድ ሰጪው የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ‹‹ቢሮ ማሟላት››ን እንደመሥፈርት ሊጠይቅ እንደማይችል በአዋጁ ተካቷል፡፡
ማንኛውም ጠበቃ በዓመት ከ24 እስከ 30 ሰዓታት የሚደርስ የሕግ ሥልጠና መውሰድ እንዳለበት፣ ጠበቃው ከጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሳይመደብለት ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት መስጠት እንደሚችልና ትክክለኛነቱና እውነት መሆኑ ተረጋግጦ እውቅና እንደሚሰጠውም በአዋጁ አካቷል፡፡ ጠበቃው የዲሲፕሊን ጥፋት ማለትም ለፍርድ ቤት ወይም ለሚመለከተው አካል ፈቃዱን እንዲያሳይ ሲጠየቅ ፈቃደኛ ካልሆነ፣ የያዘው ጉዳይ የት እንደደረሰ በደንበኛው ሲጠየቅ በአግባቡ ካላሳወቀ ካመናጨቀና ክብሩን ከነካ፣ ያለአሳማኝ ምክንያት በቀጠሮ ቀን ከፍርድ ቤት ከቀረ ወይም ከዘገየ፣ ለማኅበሩ መክፈል የሚጠበቅበትን ክፍያ በወቅቱ ካልከፈለና ፈቃዱን በወቅቱ ካላሳደሰ ከ5000 ብር እስከ 7000 ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚጣልበት በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ አዋጁ በርካታ ድንጋጌዎች ተካተው በሙሉ ድምፅ ፀድቋል፡፡
https://t.me/lawsocieties
@lawsocieties
@lawsocieties https://t.me/lawsocieties
Telegram
የሕግ ቤት
የሕግቤት Access legal information from Law center, The House of Law.
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
የፌዴራል_ጥብቅና_አገልግሎት_ፍቃድ_አሰጣጥ_እና_አስተዳደር_አዋጅ.doc
259 KB
የፌዴራል_የዳኝነት_አስተዳደር_ዓዋጅ_ቁጥር_1233_2013.pdf
2.1 MB
Federal Judicial Administration Proclamation 1233/2021 - የፌዴራል የዳኝነት አስተዳደር ዓዋጅ ቁጥር 1233/2013
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለ ሕግ
የኢትዮጵያ ሕግ ትምሕርት ቤቶች ማሕበር ተመሰረተ።
=================================‼️‼️‼️‼️‼️
ማኀበሩ ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር፣
በሕግ ትምህርት ቤቶች መካከል ትብብር እንዲኖር ማበረታታት እና የሕግ ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተ የልምድ ልውውጥ እንዲሁም በተለያዩ ሐሳቦች ላይ ውይይት የሚደረግበት ነጻ መድረክ ሆኖ ማገልገልና
ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር እና የመሳሰሉት ዓላማዎቹን ይዞ የኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶች ማኀበር ዛሬ ሐምሌ 03/2013 ዓ/ም አባል ትምህርት ቤቶችና የፍትህ ዘርፉ ባለድሻ አካላት በተገኙበት በሂልተን ሆቴል ተመስርቷል።
አቶ መስፍን....
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
=================================‼️‼️‼️‼️‼️
ማኀበሩ ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር፣
በሕግ ትምህርት ቤቶች መካከል ትብብር እንዲኖር ማበረታታት እና የሕግ ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተ የልምድ ልውውጥ እንዲሁም በተለያዩ ሐሳቦች ላይ ውይይት የሚደረግበት ነጻ መድረክ ሆኖ ማገልገልና
ሕግ በአገር እድገት ላይ የሚኖረውን ሚና በሕግ ትምህርት አማካኝነት ማሳደግና ማጠናከር እና የመሳሰሉት ዓላማዎቹን ይዞ የኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶች ማኀበር ዛሬ ሐምሌ 03/2013 ዓ/ም አባል ትምህርት ቤቶችና የፍትህ ዘርፉ ባለድሻ አካላት በተገኙበት በሂልተን ሆቴል ተመስርቷል።
አቶ መስፍን....
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Telegram
የሕግ ቤት
የሕግቤት Access legal information from Law center, The House of Law.
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
Forwarded from አለ ሕግ
Equality before the law⁉️
The case of Jacob-Zuma‼️
Supporters of the former president of the Republic of South Africa are demonstrating against the decision of the court. Do they understand that they are protesting to the rule of law? Contempt of court is a crime. Zuma was jailed under court decision, not a political one. If you reject the court, you are rejecting law. People should demonstrate when the law is violated, not when respected. Everyone is equal before the law. If you believe that your leader is above the law, then you are against the rule of law. Everyone is equal before the law. That must be the core principle Africans should stand for.
Kassahun Yibeltal‼️‼️
Senior Lawyer
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
The case of Jacob-Zuma‼️
Supporters of the former president of the Republic of South Africa are demonstrating against the decision of the court. Do they understand that they are protesting to the rule of law? Contempt of court is a crime. Zuma was jailed under court decision, not a political one. If you reject the court, you are rejecting law. People should demonstrate when the law is violated, not when respected. Everyone is equal before the law. If you believe that your leader is above the law, then you are against the rule of law. Everyone is equal before the law. That must be the core principle Africans should stand for.
Kassahun Yibeltal‼️‼️
Senior Lawyer
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Telegram
የሕግ ቤት
የሕግቤት Access legal information from Law center, The House of Law.
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል
በ:- ወንድዬ ብርሃኑ
የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡
መልካመ ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1994-offences-relating-to-invoices
በ:- ወንድዬ ብርሃኑ
የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡
መልካመ ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1994-offences-relating-to-invoices
👍1
የብድር ውል ‼️
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡
አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡
የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡
የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡
የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡
አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡
የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡
የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡
የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........
.......................ተበዳሪውም በአበዳሪው ሳይጠየቅ መክፈል ቢፈልግ ለመክፈል ያለውን ሀሳብ ከአንድ ወር በፊት ካስታወቀ በኋላ ዕዳውን መመለስ እንደሚችል እንዲሁ ተደንግጓል፡፡
በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡
የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም፡፡
federal attorney general
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡
የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም፡፡
federal attorney general
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Telegram
የሕግ ቤት
የሕግቤት Access legal information from Law center, The House of Law.
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
https://www.facebook.com/lawsocieties
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
👍1