Biblical Teachings
651 subscribers
132 photos
5 videos
4 files
34 links
አላማችን በእውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት የተሞላንና የክርስቶስን ኢየሱስን ዳግም ምፅአት በመናፈቅ የሚኖር ትውልድን ማፍራት ነው!!

ማራናታ!! ማራናታ!! ማራናታ!!
Download Telegram
Biblical Teachings pinned «🤔🤔    ቁምነገር እንቅሰም   🤔🤔 3 ዛፎች ነበሩ ። 2ቱ የቆሙ ሲሆኑ አንዱ ግን ወድቋል። ከእለታት አንድ ቀን እኚህ ዛፎች የህይወት ህልማቸውን ይነጋገሩ ጀመር ። አንደኛው ዛፍ " እኔ ሳጥን ሆኜ የአለም ውድ እቃዎች እንዲቀመጡብኝ ጥልቅ ምኞቴ ነው " አለ፣ ሁለተኛውም ቀበል አድርጎ " እኔ መርከብ ሆኜ የአለም ነገስታት እንዲጓጓዙብኝ እንዲፈንጩብኝ እፈልጋለው" አለ ፣ ሶስተኛው ደግሞ " እኔ መድሀኒት…»
🤔🤔    ቁምነገር እንቅሰም   🤔🤔

3 ዛፎች ነበሩ ። 2ቱ የቆሙ ሲሆኑ አንዱ ግን ወድቋል። ከእለታት አንድ ቀን እኚህ ዛፎች የህይወት ህልማቸውን ይነጋገሩ ጀመር ። አንደኛው ዛፍ " እኔ ሳጥን ሆኜ የአለም ውድ እቃዎች እንዲቀመጡብኝ ጥልቅ ምኞቴ ነው " አለ፣ ሁለተኛውም ቀበል አድርጎ " እኔ መርከብ ሆኜ
የአለም ነገስታት እንዲጓጓዙብኝ እንዲፈንጩብኝ እፈልጋለው" አለ ፣ ሶስተኛው ደግሞ " እኔ መድሀኒት ሆኜ ብዙዎችን ማዳን ከቻልኩ ከዛ በላይ
ምንም ኣልፈልግም" አለ ። ሶስቱም ህልማቸውን አውርተው ሲጨርሱ ዛፍ ቆራጮች መጡ፡ የወደቀውን ይዘውት ሄዱ ። እሱም ሳጥን መሆን የህይወት ፍላጎቱ ቢሆንም ጠርበው የከብቶች መመገቢያ አድርገው ሰሩት።
ሁለተኛውንም መጥተው ቆረጡት ለጀልባነትም አዋሉት፡ መርከብ የመሆን ምኞቱም ባክኖ ቀረ። ሁለቱም ዛፎች ተናደዱ ህልማቸው የተጨናገፈም
መሰላቸው። ሶስተኛው ዛፍም ለምንም አገልግሎት ባለመዋሉ እጅጉኑ አስከፋው። ከአመታት በኋላ ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ አለም መጣ። እነሆ በ ቤተልሄም ቦታ ስላልነበር በከብቶች በረት
ተወለደ። እናቱ ማርያምም በከብቶች መመገቢያ ውስጥ ጠቅልላ አስቀመጠችዉ። የአለም ውድ ነገሮች ማስቀመጫ መሆን የፈለገው ዛፍም የውዶች ውድ የእንቁዎች አንቁ የሆነው ክርስቶስ ተቀመጠበት።ጌታም ሊያስተምር ሲሄድ በታንኳ ተጓዘ ፡ ያም
ታንኳ ያ የአለም ነገስታት እንዲጓዝብኝ እፈልጋለው ያለው ነበር፡ የነገስታት ንጉስም ተጓጓዘበት። ጌታችን እንዲሰቀል ሲፈረድበት የቀረውን ዛፍ ቆርጠው አመጡ በሱም ሰቀሉት። ለብዙዎች
መድሀኒት መሆን የፈለገው ዛፍ መስቀል ሆኖ አለም ሁሉ ዳነበት። ሶስቱም ዛፎች ህልማቸው የተጨናገፈ ሲመስላቸው ፈጣሪ ግን ካሰቡት በላይ አደረገላቸው። ወዳጆቼ ለእኛም ከራሳችን በላይ የሚያስብልን አምላክ አለን። ስለዚህ ህልማችን የተጨናገፈ ቢመስለን አምላክ አብዝቶ ሊሰጠን ስለሆነ ሁሌም በ ትዕግስት እንጠብቀው።

" እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።" ሮሜ 8:28

😊  Biblical Teachings 😊

    ቢያንስ ለ10 ሰዉ share 🙏

= መልካም ምሽት =

Join Us 👇👇👇👇
@Hesedd  @Hesedd   @Hesedd
🙏🙏እውነተኛና አስተማሪ ታሪክ🙏🙏

ወንጌላዊው ጂሚ ስዋጋርት በአገልግሎቱ ውስጥ የክብር ጊዜያትን አሳልፏል፣ነገር ግን የውርደት ጊዜያትንም አሳልፏል።  ዲያቢሎስ የዚህን ቅቡዕ ሰው ጂሚ ስዋግጋርትን ከቤቱ ጀምሮ ህይወቱን አለመረጋጋት ፈጠረበት። ይህን ያስከተለውን ቅሌት ሲመለከት ማህበረሰቡ ከስራ አግዶታል። የሱ የቅርብ ሰዎች ሁሉ የውሸት ፓስተር ይሉታል። ከ 500,000 በላይ የሂስቲንግ ቸርች አባላቱ ትተውት ሄደዋል። የተረሳው እና የተተወው ጂሚ ስዋግጋርት ብቻውን ሆነ። ሁሉም ሚዲያ የሚያወራው ስለ ቅሌት እና ማውገዝ ብቻ ነበር። የእግዚአብሔር ሰዎች እንኳን ይህን አሳዛኝ ታሪክ የደስታቸው ማእከል አድርገውታል በመጨረሻም ተቀናቃኝ የምንለውን እና የጂሚ ስዋግጋርት ምትክ የምንቀበልበት ቀን ደረሰ። ሰዎች BILLY GRAHAM በተፈጠረው ነገር ደስተኛ እንደሚሆን አስበው ነበር። ምክንያቱም እሱ ሊያቀርባቸው ባለው ንግግሮች የጂሚ ተከታዮችን ወደ ሌላ አቅጣጫ የማስቀየር ችሎታ ነበረውና ነው። ጋዜጠኞቹ ስለ ሁኔታው ምን እንደሚያስቡ ጠየቁት። በአጠቃላይ የሚገርመው ነገር ቢሊ ግራሃም “ይህ ነገር በጂሚ ላይ የደረሰ ከሆነ በእኔም ላይ ሊደርስ ይችላል” ሲል መለሰ። "ይህ የእግዚአብሔር ቅዱስ ሰው ነው ለክርስቶስ በሺዎች የሚቆጠሩ ነፍሳትን አሸንፏል.. አሁን ቆስሏል አንጨምርበት , እንፈውሰውና ወታደራችንን እናነሳ."

ውድ ወንድም እና እህቶቼ  -በፍፁም በሌሎቹ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ውድቀት በፍፁም ደስተኛ አትሁን፣ ዲያብሎስ የመጋቢህን አገልግሎት እያጠፋው መሆኑን ስታይ። - ዲያብሎስ የመጋቢህን ጋብቻ ሲያፈርስ ስታይ በፍጹም ደስተኛ አትሁን። - ዲያቢሎስ ፓስተራችሁን ሊያቆሽሽ ሲዘምት በፍፁም ደስተኛ አይሁኑ።

ዲያቢሎስ የመጋቢህን ሚስት ተጠቅሞ አገልግሎቱን ሲያጠፋ ስታይ ፈጽሞ ደስተኛ አትሁን። አገልጋይ መሆን ቀላል አይደለም!!

      Join Us 👉👉 @Hesedd
👍42🤔1
👆👆👆👆👆👆👆👆

ሰብስክራብ በማድረግ ህይወትዎን የሚገነቡ መንፈሳዊ ትምህርቶች ያግኙ !!
"When Kathryn Kuhlman passed away in 1976 - all of the power went out in an 800 bed hospital.

Her heartbeat should have read as irregular - and then moved to flatline. Her heart had been fine, (although her other organs were failing) but she never went to an irregular heartbeat. Kathryn was gone in the blink of an eye.

15 minutes after she passed away the brand new nurse (her first day on the job)- who was an unbeliever- went in to take her pulse .

Kathryn wasn’t cold.

Kathryn wasn’t warm.

Kathryn was hot.

The air in her room was thick with the fragrance of roses.

Not a few roses.

Millions of roses.

The head nurse in charge - came on the unit to write up the time of death. The time was 1:13 am on February 20th.

She chastised the new nurse for allowing roses on the ICU floor. Flowers aren’t allowed in the ICU.

The scent of roses didn’t fill one room, or one floor...but 4 floors of the hospital were overtaken by the scent of roses. The scent then permeated across the under pass that was connected to the hospital and then across the street and into the adjoining hospital.

There were no roses on the floor or in Kathryn’s room....but that’s where the fragrance originated from.

The new nurse said that she and the other nurse could barely stand in the room because the presence of Holy Spirit was so overwhelming.

The weight of glory.

When they checked the notes from the previous nurse - she had scribbled Kathryn Kuhlman’s final words and her last request...

“I shall die on February 20th at 1:13 am. Please have only roses at my funeral”

The new - unbelieving nurse- dropped in a chair, weeping, having been touched by the presence of the Holy Spirit.

Oh, to leave this world in that kind of GLORY. To bring just one more into the kingdom at your death and to be greated with roses!

Kathryn was met with millions of roses and the voice of her First Love...

“Well, done! My good and faithful servant” 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹



" ካትሪን ኩልማን በ 1976 ህይወቷ ሲያልፍ - ሁሉም ሃይል በ 800 አልጋዎች ሆስፒታል ውስጥ ወጣ. የልብ ምቷ መደበኛ ባልሆነ መልኩ ማንበብ ነበረበት - ከዚያም ወደ ጠፍጣፋ መስመር ተዛወረች. ልቧ ጥሩ ነበር, (ሌሎች አካሎቿ እየሳኩ ቢሆንም) ግን ወደ መደበኛ ያልሆነ የልብ ምት አልሄደችም ። ካትሪን በአይን ጥቅሻ ውስጥ ጠፋች ። ከ 15 ደቂቃዎች በኋላ አዲሷ ነርስ (በሥራ ላይ የመጀመሪያ ቀን) ካለፈች በኋላ - ያላመነች - የልብ ምት ሊወስድ ገባች ። ካትሪን ቀዝቃዛ አልነበረም ካትሪን ሞቃት አልነበረችም ካትሪን ሞቃት ነበረች በክፍሏ ውስጥ ያለው አየር በጽጌረዳ መዓዛ ወፍራም ነበር.ጥቂት ጽጌረዳዎች አልነበሩም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጽጌረዳዎች. ኃላፊዋ ነርስ - ለመጻፍ ወደ ክፍሉ መጣ. የሞት ጊዜ፡ ሰዓቱ በየካቲት 20 ከጠዋቱ 1፡13 ነበር፡ አዲሷን ነርስ ጽጌረዳ በICU ወለል ላይ እንድትፈቅዳለች በማለት ተቀጣች። አበቦች በICU ውስጥ አይፈቀዱም የጽጌረዳ ጠረን አንድ ክፍል አልሞላም ወይም አንድ ፎቅ...ነገር ግን የሆስፒታሉ 4 ፎቆች በፅጌረዳ ጠረን አልፈው ወጡ።ከዚያም ሽቶው ከሆስፒታሉ ጋር በተገናኘው መተላለፊያ በኩል ከዚያም ከመንገዱ አልፎ ወደ አጎራባች ሆስፒታል ገባ። ወለሉ ላይም ሆነ በካትሪን ክፍል ውስጥ ምንም አይነት ጽጌረዳዎች አልነበሩም .... ነገር ግን መዓዛው የመጣው ከዚያ ነው. አዲሷ ነርስ እሷ እና ሌላዋ ነርስ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት በጣም ስለሚያስቸግር በክፍሉ ውስጥ መቆም እንደቻሉ ተናግራለች። የክብር ክብደት። የቀደመውን ነርስ ማስታወሻ ሲፈትሹ - የካትሪን ኩልማን የመጨረሻ ቃል እና የመጨረሻ ጥያቄዋን ገልጻለች… “የካቲት 20 ቀን ከጠዋቱ 1፡13 ላይ እሞታለሁ። እባካችሁ በቀብሬ ጊዜ ጽጌረዳ ብቻ ይኑርህ” አዲሷ - ያላመነች ነርስ - ወንበር ላይ ወደቀች፣ እያለቀሰች፣ በመንፈስ ቅዱስ መገኘት ተነካ። ኧረ ይቺን አለም በዚህ አይነት ክብር ልተወው። በሞትክ ጊዜ አንድ ተጨማሪ ወደ መንግስቱ ለማምጣት እና በጽጌረዳዎች ለመደሰት! ካትሪን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ጽጌረዳዎች እና የመጀመሪያ ፍቅሯ ድምፅ ተገናኘች… “ደህና ፣ ተከናውኗል! የኔ መልካም ታማኝ ባሪያ" 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹


Join Here 👉👉 @Hesedd
👍4🤔1
አይቀሬው ዘላለም 😳

  
⬇️ እስኪ ቀላል ግን ዘላለምህን የሚወስኑ ሁለት እውነቶችን አብረን እንመልከት !!


     👉 ኢየሱስን ባለማመንህ ነገ ቀን በጨለመ ጊዜ ፍርድ ሲሆን ይነገርህ የነበረው የወንጌል ቃል እውነትና ልክ እንደነበር አውቀህ ራስህን ትኮንናለህ ትንቃለህም እግዚአብሔርም ደግሞ ልጁን በልብህ ላይ አላነገስክምና ወደ እሳት ባህር ለዘላለም ይጥልሀል..

  👉 ኢየሱስን በማመንህና ቃሉን ዕለት ተዕለትም በመከተልህ ነገ ላይ የፅድቅ ፀሃይ 'ትወጣልሀለች' እውነትና ፍርድ በተገለጡ ጊዜም ያመንከው የወንጌል ቃል ትክክል እንደሆነ አስቀድመህ አውቀሀልና ሽልማትን ከእግዚአብሔር እጅ ትቀበላለህ ..

          የቱ ይሻላል ?

     ለበለጠ መንፈሳዊ ትምህርቶችና አጫጭር ፅሁፎች ከታች ባለው ሊንክ ይቀላቀሉን !!

        @Hesedd   @Hesedd

     #biblical teachings
▶️▶️▶️ የሀይል ቅባት  ◀️◀️◀️


                  ክፍል 1⃣

  
  በዚህ ሀሳብ ላይ ከመነጋገራችን ቀድሞ ሀይልና ቅባት የተሰኙ መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውነታዎች ላይ ተገቢውን ትርጎሜና ፍቺ መስጠት ያስፈልገናል !!
       

  I. ሀይል ምንድን ነው ?
         

ሀይል የቁሳዊው ሆነ የመንፈሳዊው አለም ቁልፍ ነገር ነው !! ይህም "ያለ ሀይል" አንዳች ሀሳብ ተግባር ስለማይሆን ነው !!

   1. ለቁሳዊው አለም 

            ሉቃ 14:31

  ፨ በቁሳዊው አለም ሀይል የትኩረት ማዕከል ነው !! 

ጦርነት ያለ ሀይል በሽንፈት ይጠናቀቃል !!

    2. ለመንፈሳዊው አለም
 
             ማቴ 26÷31

  ፨ የፍቅርና የእምነት አቅም ነው / ወይም ፍቅርንና እምነትን ገልጦ ለመኖር ብቃት ነው !!

እምነትና ፍቅር በማይታየው አለም የመንፈሳዊ ብስለት መለኪያዎችና የክብር መንገድ መሰረቶች እንደመሆናቸው በአማኙ ህይወት ተፈላጊ እንቁዎች ናቸው። ኤፌ 1:15

እምነት ያለ ሀይል በክህደት ይደመደማል !!

II. ቅባት ምንድን ነው ?

1. የደህንነት መልህቅ ነው !! 

      ኤፌ 1:13        1 ዮሐ 2:20

     ኤፌ 4:30        ማቴ 25÷1-13

  ☆ ጠላት በእኛ ላይ ያለውን የእግዚአብሔር ቅባት ተከትሎ የሚነደውን እሳት ጥሶ ማለፍና እኛን መንካት አይችልም። ዘካ 2:5

  2. ልዩ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ነው !!
      
  1ሳሙ 16:13   ሉቃ3:22  ሐዋ 10:38

እግዚአብሔር በተለየ መንገድ ህልውናው በእኛ ውስጥ እንዲሰራ ሲፈልግና አጀንዳውን እንድፈፅምለት ሲመርጠን በቅባቱ ምርጫውን ይገልጣል !! 2 ነገ 9÷1-3

የተቀባ ሰው መንፈስ ቅዱስ በሀይል የመጣበት እንዲሁም መንፈስን በቆመበትና ባለበት ስፍራ ሁሉ የሚያመጣ ነው !


          ▶️  ይቀጥላል  ▶️


  ⭕️ ለሌሎች በማጋራት መንፈሳዊ አገልግሎታችንን ይደግፉ !!

Join here👉 @Hesedd @Hesedd


ጥያቄ ወይም አስተያየት ካለዎት ያነጋግሩን

          👇👇👇👇👇

             @JobYEp
#መንፈሳዊ_ብስለት

➡️ እግዚአብሔር ለመንፈሳዊ ብስለት ሁለት አብይ ደረጃዎችን አስቀምጧል። ይኸውም እርሱን ለመምሰል የሚሻ ሁሉ ይከተለውና ያደርገው ዘንድ በምላሹም ከእርሱ የሆነውን ዘላለማዊ ክብር እንዲያገኝ ወስኗል። ሮሜ 8÷29-30

⏩️ እግዚአብሔር የእርሱን አለም ምስጢራት እንድናውቅና እንድንካፈል የመገለጥ መንፈስን ሰጥቶናል እኛም ዕለት ተዕለትም በመንፈሱን የመገለጥ ወንዝ ህይወታችንን እንድናለማት ይሻል። #መገለጥ ለመንፈሳዊው እድገት ለደህንነት በር መከፈት ቀዳሚው አምላካዊ አቅርቦት ሲሆን ይኸውም የጊዜው የሆነውን መለኮታዊ ትጥቅ የምንቀበልበት የመንፈስ ቅዱስ አሰራር ነው።

▶️ጥበብ:- ለመንፈሳዊው ብስለት 'መሰረት' እንዲሁም ደግሞ የክብርን ዘውድ የምንጭንበት የሀይል እጅ ነው !! #ጥበብ እንደ መገለጥ በብዙሀኑ ዘንድ የምትገኝ ሳትሆን ዋጋዋ የገባቸውና ዋጋዋን ለመክፈል የሚጨክኑ የሚዋቡባት ታላቅ ሀብት ናት !!

#ጳውሎስ የጥበብና የመገለጥን ሚና በኤፌሶን መልዕክቱ ማስቀመጡ ከፍ ያለው የመንፈሳዊነት ክብርን ከዚሁ መርህ ጋር ለመያያዙ አመላካችና እግዚአብሔር ከመገለጥ በላይ በጥበብ ከእድገትም ይልቅ ብስለት ደስታን እንደሚሰጠውም የሚያሳይ ድንቅ መረዳት ነው !!

እዮባ ነኝ😇

ቸር እንሰንብት 🙏

Join us 👉 @Hesedd @Hesedd
👍2
🏥🏥🏥 የክርስቶስ ቤዛነት 🏥🏥🏥


ሮሜ 3:24         ቆላ 1÷13-14

I. የቤዛነት ምንነት

1. ቤዛነት እዳን መክፈል ነው !

-> ኢየሱስ የሀጥያታችንን እዳ ደሙን አፍስሶ ስጋውንም ቆርሶ ከፍሏል።

▶️ ይህም ሀጥያታችን በእኛ ላይ ያመጣውን ዘላለማዊ የሞት ቅጣት ያስወገደና ነፃ እንድንሆንም ያደረገ ነው !

ህዝ 18:4 ሮሜ 6:23 ኢሳ 53፡5

ቆላ 1÷13-14 ዕብ 2÷14-15

2. ለፅድቅ አርነት ማውጣት ነው !

• ይህ ደግሞ ኢየሱስ ከጠላት ሀይል እኛን ፈትቶ ነፃ ከማውጣት ባሻገር "የህይወታችን" ዋነኛ ግብ እንደቀየረና በአዲስ መንገድ ላይ ጉዞ እንደጀመርን የሚያሳይ ነው !!

1 ጴጥ 2:24 ሮሜ 6:19 - 23

ይህም ፅድቅን ለማድረግ ተነሳሽነትን ፣ ብቃትንና ድፍረትን ማግኘታችንን ያሳያል !!


II. የቤዛነቱ ትሩፋቶች

1. ከሰይጣን ሀይል ተፈታን

ኤፌ 1÷17-23 ዕብ 2÷14-15

2. ከሀጥያት ባርነት አርነት አወጣን

ሮሜ 8÷1-2

3. ትህትና ተገለጠ

ፊሊ 2÷5-11


4. የእግዚአብሔር ክብር ተመለሰ

ሐዋ 2÷1-4


🎇ለሌሎች አጫጭር መንፈሳዊ ፅሁፎች ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይቀላቀሉን🎇

👉 @Hesedd

👉@Hesedd

👉 @Hesedd
👍2
ያልፀለየ ጉዱ ፈላ 😳


ከእለታት አንድ ቀን ወንጌላዊ አለምነህ ጀምበሩ የገጠር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ ትውልድ ስፍራው ጎጀም ለመመለስ ከባለቤቱ ጋር ሆኖ በመንግስት ትራንስፓርት ይሳፈራል።ጉዞም ይጀምራሉ።

...ብዙ ከተሞችን በነፋስ ሽውታ እያለፉ ተጓዙ።አለምነህም በልቡ መፀለይ ጀመረ።ምን እየፀለየ እንዳለ ባለቤቱ ባታውቅም እየፀለየ እንደነበረ ግን አስተውላለች።ያው ልማዱ ነው ብላ ትታዋለች።
ከረጅም ጉዞ በኋላ አንድ ከተማ ደረሱ።

በዚህ ጊዜ አለምነህ ድንገት ወደ ባለቤቱ ዞሮ፦
" እዚህ መውረድ አለብን" ይላታል።

እሷም ግራ ተጋብታ " ለምን? ገና አልደረስንም እኮ!" ትለዋለች።

" አይ መንፈስ ቅዱስ እዚህ ውረዱ፤ የምታድሩትም እዚህ ከተማ ነው ብሎኛል" አላት በእርግጠኝነት መንፈስ ሆኖ።

የሱ ነገር ሁሌ እንግዳ ቢሆንባትም እግዚአብሔር ካለው እንደማይመለስ ስለምታውቅ "አይ አለምነህ! የምንወርድበትንስ ምክንያቱን ነግሮሃል?" አለችው።ለማወቅ በመፈለግ እና ትንሽም ግራ በመጋባት።

"አልነገረኝም።" አላት።
ታዘው ወረዱ።ወደ አንድ ሆቴል ሄደው አልጋ ያዙ።ሻንጣቸውን አስቀምጠው ወክ ለማድረግ ወደ ከተማ ወጡ።

አለምነህ ግን በልቡ መፀለዩን ቀጠለ።
" ጌታ ሆይ!ለምንድን ነው እዚህ ከተማ ውረዱ ያልከን?እዚህ ከተማ ምን አለ? እያለ የእግዚአብሔርን ሃሳብ ለማወቅ ጠየቀ።ባለቤቱም የሚሆነው ባይገባትም በእርምጃ እና በፀሎት ዝም ብላ ተከተለችው።

ትንሽ እንደተጓዙ አንድ መናፈሻ ያለው ሆቴል ጋር ደረሱ።
መንፈስ ቅዱስም አለምነህን፦"ወደ ውስጥ ግባና የምነግርህን ታደርጋለህ" አለው።ድምፁን ተከትሎ ወደ ውስጥ ገባ።

መናፈሻው ውስጥ ትልቅ ሰርግ እየተደገሰ ነበር።ህዝቡም ግጥም ብሏል።አለምነህ አሻግሮ ወደ መድረኩ ተመለከተ።ሙሽራውን ያውቀው ነበር።የሚያውቀው ሰው ነው።

መንፈስ ቅዱስ መናገሩን ቀጠለ።
" ወደ ፊት ሂድና ሰርጉን አስቁም! " አለው።

አለምነህ በጣም ደነገጠ።ያልጠበቀው ድምፅ ነበር።
"ለምን" አለ።ክው እንዳለ።

መንፈስ ቅዱስም አለው፦" ከእኔ አይደለም።እሷ(ሙሽራይቱ) ፈፅሞ አትወደውም።ከጥቂት ጊዜ በኋላ ልትለየው አቅዳ የገባችበት ህይወቱንም አጥፍታ፣ንብረቱንም ዘርፋ ለመሄድ በጠላት የቴሴረ ሴራ ነው።የልጄን ቅንነት አይቼ ለማዳን ነው፤ አንተን የላኩህ" አለው።

በዚህ ጊዜ አለምነህ ወደ ጋብቻው መድረክ ቀረበ፤ምንም ሳይናገር በሙሽራይቱ ላይ ያለው መንፈስ እራሱን ገልጦ መጮህ ጀመረ።

አገኝህኝ፣ አዋረድከኝ፣ ነቃህብኝ! እረ ኡኡኡ እያለ ወደቀ።
ሰርጉም ቀረ!። ነፃነት ሆነ።
(ይህን ምስክርነት ከእራሱ ከወንጌላዊ አለምነህ ጀምበሩ አንደበት የሰማሁት ሲሆን።በጊዜ ርዝመት ቦታዎችን እና ከተሞችን ማስታወስ ባለመቻሌ ሳልጠቅሳቸው አልፌአቸዋለው።በተረፈ ምስክርነቱን ለፁሁፍ እንዲመች ከማድረግ ውጪ የጨመርኩት ምንም ነገር የለም።ተባረኩ።)

ከናትናኤል ገብረወልድ facebook ላይ የተገኘ

@Hesedd @Hesedd @Hesedd
👍73🔥3
🧶🧷🧷🧶መርፌው እና ክሩ🧶🧷🧷


➳መርፌና ክር በጣም የተቃረኑ ናቸው።ነገር ግን በጣም የተዋደዱና የተፈላለጉ ናቸው።ክሩ ልፍስፍስ በራሱ እንኳ መቆም የማይችል  ጥሶ ለማለፍ የማይሞክር ነው።🧶🧶🧶🧶
🧷🧷🧷መርፌው ላይ ሲታሰር ግን ውስብስቡን መንገድ እየጣሰ፤ከፊት ያለውን እየወጋ በመጨረሻ ብቅ ይላል።

🧶🧷መርፌው ብቅ ሲል የታዘለችው ክርም እንደጎበዝ ብቅ ትላለች ።ደካማዋ ክር ከመርፌው ጋር በመታሰርዋ አለመቻልዋ መቻል አግኝቶ የተቀደደውን ትሰለፋለች ፤የተበተነውን ትሰበስባለች ።

🙄🙄🙄 ልክ እንደ ክሩ እኛም ደካሞች ፣ሳንጀምር የሚደክመን ልፍስፍሶች፣ውስብስቡን መንገድ መጓዝ የማይቻለን መንገድ ቀሪዎች ነን ።
     በክርስቶስ ላይ ስንታሰር ግን እንፀናለን🏋️‍♂️🏋🏻‍♀️ጥሰን የምንወጣ  ከፊታችን ያለውን ሁሉ የማንፈራ ፣ የማንችለውን ዉስብስብ መንገድ በመርፌው ጀርባ ላይ ሆነን ብቅ እንላለን ።
፡፡፡፡ዋናው አለመቻላችን አይደለም፣በሚችለው ጌታ ላይ በእምነት መታሰራችን ነው ።

።።።።።።ዲያቆን አሸናፊ እንደፃፈው ።።።

   ከ @maranatatube የተወሰደ

                  መልካም ቀን

                  Join Us
            👇👇👇👇👇👇
@Hesedd  @Hesedd   @Hesedd

@Hesedd  @Hesedd   @Hesedd
4👏1
ቅባቱን መረዳት 🤔


1. ቅባቱ ያስገዛል !

የበላይነትን ይሰጣል ! ( ስለዚህም በጠላት ላይ የፈለግነውን እናደርግበታለን !)

“እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤”
ሐዋ 10፥38

" ጠላት አይሰለጥንብንም "

2. ቅባቱ በሮችን ይከፍታል !

ቅባት በመያዝ ብቻ የሚከፈቱ በሮች አሉ ! ኢሳ 45:1

( በቅባት ስንመላለስ የሚከፈቱ በሮች ከፍ ያሉ ናቸው ! )

3. ቅባቱ መንገድን ያስተካክላል !

ቅባት ይዞ የመንገዱ አይነት ከመንገድ አያስቀርም (ሐዋ 5 መልአክ ከወህኒ አወጣቸው)

4. ቅባቱ የምድርን ብልፅግና ይሰጣል ! ኢሳ 45:1-3

ቅባት ይዘን ሳለ ድህነት ከመለኮታዊ ስራ አያስተጓጉለንም ! ( ቅባት ሀብትን ይስባል ነገር ግን መቼ እንዴትና ለምን ሀብትን/ብርና ወርቅ/ መጠቀም እንዳለብን ካላወቅን የሀብትን ሙላት ለማስተዳደር በጌታ ዘንድ favor ( ልዩ ሞገስ ) አይኖረንም ! {ለአንዱም አንድ መክሊት ሰጠው ይላልና } ማቴ 25:15


📌 በውስጣችን ያለውን ቅባት እናነሳሳ 💥

“ስለዚህ ምክንያት፥ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው፥ እጆቼን በመጫኔ በአንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታነሣሣ አሳስብሃለሁ።”  2 ጢሞ 1፥6


🙏መልካም ምሽት🙏

ይቀላቀሉን 👉 @Hesedd
6
Channel photo updated
ሰላም ውዶች እንደምን አላችሁ 👐

  📌  ለረጅም አመታት በዚህ ቻናል ትምህርታዊ ይዘት ያላቸውን ፅሁፎች ስንለቅ እንደነበርና ከዚያ በኃላ ግን በተለያዩ ምክንያቶች ያንን አገልግሎት ያቋረጥን እንደሆነ ይታወቃል። ከዚህ በኃላ ግን የቀደመውን አገልግሎት እንደምንጀምርና በተለያዩ ርዕሶች ላይም የእግዚአብሔርን ምክር አብረን የምንካፈል ይሆናል ።
              🙏መልካም ቆይታ 🙏
እሳቱን ጠብቅ !


የመንፈስ ቅዱስ እሳት ሊጠበቅ ያስፈልጋል !
ዘሌ 6:12 1ተሰ 5:19

ለምን እንጠብቀው

1. እሳቱ የትንቢት መንፈስ ነው !

ኢዮ 2÷28 ሐዋ 19÷6
ሐዋ 21÷9 ራዕ 19፡10

2. እሳቱ ብቁ የሚያደርግ ነው !

ማር 9:49 ኢሳ 41÷ 14-16 ዘካ 6:4

3. እሳቱ የእግዚአብሔር ክብር ነው !

ህዝ 1 ዘፀ 40÷35-38 ሐዋ 2÷1-4

እሳቱን መጠበቅ

ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ ህያው ሆና ትገኝ ዘንድ እሳቱ ዘወትር መንደድ አለበት። 'ቅዱሱ' እሳት የእግዚአብሔርን ልዩ አቅርቦት ለቅዱሳን እውን የሚያደርግ ብቸኛው ሰማይ እና ስራውን ገላጭ እንደመሆኑ 'ልዩ' ጥንቃቄ ልናደርግለት ይገባናል። ዘሌ 6:13 ዘሌ 9:24 ዘሌ 10:1

1ተሰ 5÷19-24

1. በቅድስና ጠብቁ

ቅድስና:- ማለት ለእግዚአብሔርና ለሰው ለሁለቱም መመቸት ነው። ዕብ 12:24

ለእግዚአብሔር መመቸት 'ናዝራዊነትን' ሲያመጣልን ለሰው መመቸት ደግሞ ሰላምን ያጎናፅፋል። ለእግዚአብሔር የሆነ ሰላማዊም ሰው ካገኘን ይህ ሰው በቅድስና እየተመላለሰ እንደሆነ ልንመሰክር እንችላለን።

ቅድስና የእግዚአብሔርና የልጆቹ ባህሪይ በመሆኑ አለም ይህን ከእኛ ለማየት ይጓጓል።

( አንበሳ ለማየት ዙ የምንገባው ውሻ ፍለጋ
አይደለም ቤተክርስቲያንም በቅድስና በተዋቡ
ሰዎች ባትሞላ የምስበው ሰው አይኖራትም )

'ናዝራዊነት' የሚገለጠው እግዚአብሔር
እኛን ለሱ አላማ በመለየቱ ብቻ ሳይሆን እኛም
ደግሞ አላማውን አላማችን አርገን ስንለይለት ነው። ዘፀ 19÷5-6 ዘሁ 6÷1-5

በቅድስና ለመኖር ቁልፉ ነገር የመንፈስ ቅዱስ ታማኝነትና የእኛ እምነት ብቻ ነው።

፨ እግዚአብሔር ታማኝ ነው 1ቆሮ 1÷7-9

፨ ከእግዚአብሔር ለህይወት የሆነውን ሁሉ ተቀብለናልና እንደ 'ዘር' በውስጣችን ያለውን
ሁሉ እኛ ስንተጋ መገለጥ ፍሬ ሆኖ መታየት
ይጀምራል። 2 ጴጥ 1÷2 _ 5

በሰው ጋር ስንኖር የሚገጥመንን ጥሩ
ያልሆነ ነገር አምርሮ መያዝና 'መለየት' ለክፉ ምላሽም ደግሞ ቀን መጠበቅ በመንፈሳዊው ህይወታችን ስጋዊያንና ያላደግን የሰላም ሰው እንዳልሆንን በግልጥ ያሳያል።

በሰው አለመጎዳትና ሰውን አለመጉዳት ከፈለግን "ልከኛ"፣ ንግግራችን በፀጋ የተሞላና
ይቅር ማለትን የተማርን መሆን አለብን።

እግዚአብሔር "ተቀደሰ" የሚለን ከአለም ተለይተን ከእርሱ ጋር ህብረት ስናደርግና 'ደስ'
የሚያሰኘውን ስንፈፅም ብቻና ብቻ ነው። ይህን ስናደርግም እንደምንወደው ያረጋግጣል።

1ዮሐ 1:6 ዮሐ 5:20 ዮሐ 10:18

2. ለፀሎትና ለቃሉ በመትጋት ጠብቁ
ሐዋ 6÷4

ትጋት ብርቱ ትውልድን ይወልዳል 👉 እስጢፋኖስ
Channel photo updated
Hello guys - እቺን መልዕት ጀባ ብለናል !

💥 ዕለት ተለት የምንገስፀውና አልወድቅ ፍንክች አልል ያለን ጠላት በእውነተኛ ንስሀ በቀላሉ ይወድቃልና የደበቅነውን እርም እንድናወጣ ጌታ ይርዳን !

         Join here 👇👇
   @Hesedd     @Hesedd
           @Hesedd