ኮሌጁ የአየር ንብረት ለውጥ ፍትሐዊነት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አዘጋጀ።
5/9/2017 ዓ/ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ ከዩኒቨርሲቲው የህግ ተማሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና ስነ-ምህዳር ለውጥ ፍትሐዊነት ላይ አተኩሮ የማይበሰብሱ የፕላስቲክ ምርቶች አያያዝና አወጋገድ ላይ ለተማሪዎች ክፍት የሆነ የትምህርትና ውይይት መድረክ ተካሂዷል።
የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ደብረወርቅ ደበበ በመክፈቻ ንግግራቸው የአየር ንብረት ለውጥ ሁሉንም የአለም ክፍል የሚጎዳ ቢሆንም ለለውጡ ዋነኛ አስተዋጽኦ ካላቸው የበለጸጉት ሀገራት ይልቅ የከፋ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ የሚገኘው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ እየተበራከተ ያለውን የጎርፍ፣ ድርቅ፣ የሙቀት መጨመርና የበረሃማነት መስፋፋት አደጋ ለመከላከል ፍትሐዊ አሰራር ሊዘረጋ እንደሚገባውም ዶ/ር ደብረወርቅ አክለዋል።
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና አደጋዎቹን ለመቀልበስ በአመለካከት ላይ የሚሰራው ስራ ቀዳሚ መሆኑን ያነሱት ትምህርታዊ መድረኩ ላይ ተገኝተው ስልጠናውን የሰጡት ጆዳሄ ጴጥሮስ በተለይም በማይበሰብሱት የፕላስቲክ ግብአቶች አጠቃቀምና አወጋገድ ላይ የሚታየው ድክመት ሊሻሻል ይገባል ብለዋል።
የህግ ተማሪዎች ማህበር ፕሬዚደንት እና የ3ኛ አመት ህግ ተማሪው አንዋር ኑርበገን በበኩሉ ማህበሩ በየጊዜው በሚያከናውናቸው ወቅታዊ የአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያተኮሩ ዝግጅቶች አማካኝነት የስርአተ ምህዳር ፍትሕ-ኢትዮጵያ እና Influencers initiative ከመሳሰሉ ተቋማት ጋር ተቀራርቦ የመስራት እድል ማግኘቱን ገልጾ በቀጣይ ይህንን በማጠናከር ተደራሽነቱንና ተጽዕኖውን የማሳደግ ስራ እንደሚሰራ ጠቁሟል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
5/9/2017 ዓ/ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ ከዩኒቨርሲቲው የህግ ተማሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና ስነ-ምህዳር ለውጥ ፍትሐዊነት ላይ አተኩሮ የማይበሰብሱ የፕላስቲክ ምርቶች አያያዝና አወጋገድ ላይ ለተማሪዎች ክፍት የሆነ የትምህርትና ውይይት መድረክ ተካሂዷል።
የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ደብረወርቅ ደበበ በመክፈቻ ንግግራቸው የአየር ንብረት ለውጥ ሁሉንም የአለም ክፍል የሚጎዳ ቢሆንም ለለውጡ ዋነኛ አስተዋጽኦ ካላቸው የበለጸጉት ሀገራት ይልቅ የከፋ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ የሚገኘው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ እየተበራከተ ያለውን የጎርፍ፣ ድርቅ፣ የሙቀት መጨመርና የበረሃማነት መስፋፋት አደጋ ለመከላከል ፍትሐዊ አሰራር ሊዘረጋ እንደሚገባውም ዶ/ር ደብረወርቅ አክለዋል።
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና አደጋዎቹን ለመቀልበስ በአመለካከት ላይ የሚሰራው ስራ ቀዳሚ መሆኑን ያነሱት ትምህርታዊ መድረኩ ላይ ተገኝተው ስልጠናውን የሰጡት ጆዳሄ ጴጥሮስ በተለይም በማይበሰብሱት የፕላስቲክ ግብአቶች አጠቃቀምና አወጋገድ ላይ የሚታየው ድክመት ሊሻሻል ይገባል ብለዋል።
የህግ ተማሪዎች ማህበር ፕሬዚደንት እና የ3ኛ አመት ህግ ተማሪው አንዋር ኑርበገን በበኩሉ ማህበሩ በየጊዜው በሚያከናውናቸው ወቅታዊ የአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያተኮሩ ዝግጅቶች አማካኝነት የስርአተ ምህዳር ፍትሕ-ኢትዮጵያ እና Influencers initiative ከመሳሰሉ ተቋማት ጋር ተቀራርቦ የመስራት እድል ማግኘቱን ገልጾ በቀጣይ ይህንን በማጠናከር ተደራሽነቱንና ተጽዕኖውን የማሳደግ ስራ እንደሚሰራ ጠቁሟል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
ማስታወቂያ
በ2017 ዓ.ም በሰኔ ወር የሚሰጠው የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ብቻ የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፡-
1. እስከ አሁን ያልተመዘገባችሁ የድጋሚ ተፈታኞች (resitters) ከዚህን በፊት ለምዝገባ በተከፈተውና በተገለጸው መመዝገቢያ ፕላትፎረም (registration link) በኩል ገብታችሁ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ፣
2. ለመጀመሪያ ጊዜ ለመውጫ ፈተና የምትቀመጡ ተፈታኞች በተቋሞቻችሁ በኩል መመዝገባችሁን እንድታረጋግጡ እያሳሰብን፤
3. ፈተናው የሚሰጠው ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ
ለፈተናው የምታመለክቱ አመልካቾች ለመመዝገብ የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ሊኖራችሁ ይገባል፡፡
ከግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ቦኋላ ምዝገባ አይስተናገድም፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር
በ2017 ዓ.ም በሰኔ ወር የሚሰጠው የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ብቻ የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፡-
1. እስከ አሁን ያልተመዘገባችሁ የድጋሚ ተፈታኞች (resitters) ከዚህን በፊት ለምዝገባ በተከፈተውና በተገለጸው መመዝገቢያ ፕላትፎረም (registration link) በኩል ገብታችሁ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ፣
2. ለመጀመሪያ ጊዜ ለመውጫ ፈተና የምትቀመጡ ተፈታኞች በተቋሞቻችሁ በኩል መመዝገባችሁን እንድታረጋግጡ እያሳሰብን፤
3. ፈተናው የሚሰጠው ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ
ለፈተናው የምታመለክቱ አመልካቾች ለመመዝገብ የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ሊኖራችሁ ይገባል፡፡
ከግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ቦኋላ ምዝገባ አይስተናገድም፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር
ኮሌጁ የአድባራትና ገዳማት ደን አጠባበቅና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያተኮረ ስልጠና መሰጠት ጀመረ።
**//**
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልማት ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን (EOC-DICAC) ጋር በመተባበር የአየር ንብረት ለውጥ ፍትሐዊነት፣ የተጋላጭነት ዳሰሳ እና ስልታዊ የመቋቋም ስትራቴጂዎች ላይ ያዘጋጀው ለአምስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና የማስጀመሪያ መድረክ ሚያዝያ 5/2017 ዓ.ም በሴንትራል ሐዋሳ ሆቴል ተካሂዷል።
የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ተሻለ ወ/አማኑኤል ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት የቤተክርስቲያኗ አድባራትና ገዳማት ሀገር በቀል ዛፎችንንና እጽዋቶችን ለዘመናት ጠብቀው በማቆየትና ስነ-ምህዳሩን በማስጠበቅ ደረጃ የተጫወቱት ሚና በጎላ መልኩ የሚነሳ መሆኑን ጠቁመው ይህንን ጠብቆ ለመቀጠል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቋቋም የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል። ስልጠናው በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ሚና ይኖራቸዋል ተብለው የታመነባቸውን የመንግስትና የጥናት ቡድኑን አባላት፣ የኃይማኖት አባቶች እና የማህበረሰብ ተወካዮችን ያቀፈ በመሆኑ ለውጥ ያመጣል ብለው እንደሚጠብቁ ዶ/ር ተሻለ ተናግረዋል።
ጥናቱ በዘጠኝ አብያተ ቤተክርስቲያናት ቅጥር ግቢዎች ውስጥ በሚገኙ ደኖችና በአካባቢያቸው ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት እንደሚዳስስ የገለጹት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር በየነ ተክሉ በጥናቱ የተገኙ ውጤቶችን በመቀመር ማህበረሰቡ አካባቢውን ሳይጎዳ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በመጠቀም፣ ዘመናዊ ውሃ ማቆርና የመስኖ ስራን የሚያስፋፋበት አሰራር እንደሚበጅ ተናግረዋል።
**//**
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልማት ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን (EOC-DICAC) ጋር በመተባበር የአየር ንብረት ለውጥ ፍትሐዊነት፣ የተጋላጭነት ዳሰሳ እና ስልታዊ የመቋቋም ስትራቴጂዎች ላይ ያዘጋጀው ለአምስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና የማስጀመሪያ መድረክ ሚያዝያ 5/2017 ዓ.ም በሴንትራል ሐዋሳ ሆቴል ተካሂዷል።
የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ተሻለ ወ/አማኑኤል ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት የቤተክርስቲያኗ አድባራትና ገዳማት ሀገር በቀል ዛፎችንንና እጽዋቶችን ለዘመናት ጠብቀው በማቆየትና ስነ-ምህዳሩን በማስጠበቅ ደረጃ የተጫወቱት ሚና በጎላ መልኩ የሚነሳ መሆኑን ጠቁመው ይህንን ጠብቆ ለመቀጠል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቋቋም የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል። ስልጠናው በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ሚና ይኖራቸዋል ተብለው የታመነባቸውን የመንግስትና የጥናት ቡድኑን አባላት፣ የኃይማኖት አባቶች እና የማህበረሰብ ተወካዮችን ያቀፈ በመሆኑ ለውጥ ያመጣል ብለው እንደሚጠብቁ ዶ/ር ተሻለ ተናግረዋል።
ጥናቱ በዘጠኝ አብያተ ቤተክርስቲያናት ቅጥር ግቢዎች ውስጥ በሚገኙ ደኖችና በአካባቢያቸው ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት እንደሚዳስስ የገለጹት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር በየነ ተክሉ በጥናቱ የተገኙ ውጤቶችን በመቀመር ማህበረሰቡ አካባቢውን ሳይጎዳ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በመጠቀም፣ ዘመናዊ ውሃ ማቆርና የመስኖ ስራን የሚያስፋፋበት አሰራር እንደሚበጅ ተናግረዋል።
የኮሚሽኑ የቤተክርስቲያን ደን አያያዝ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ምትክ ከተማ በበኩላቸው ኮሚሽኑ ከተቋቋመ ከ50 አመት በላይ ያስቆጠረና ዘርፈ ብዙ ልማታዊና ሰብአዊ አገልግሎቶችን በመላ ሀገሪቱ ያከናወነ መሆኑን አስታውቀው ወቅታዊ በሆነውና የቤተክርስቲያኗ ሀብቶች በሆኑት ደኖች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ በሚገኘው የአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ከኮሌጁ ጋር ጥናቶችን ለማካሄድ ቅንጅታዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል።
የመንግስት ኃላፊዎችና የቤተክርስቲያን አባቶች ያላቸውን ተሰሚነትና ተቀባይነት በመጠቀም ከችግኝ ተከላና ጽድቀት እስከ ዘላቂ እንክብካቤ ድረስ ባሉ የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋሚያ መንገዶች ላይ ማህበረሰቡን የማንቃት ሚና እንዲወጡ በመድረኩ መልዕክት ተላልፏል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
የመንግስት ኃላፊዎችና የቤተክርስቲያን አባቶች ያላቸውን ተሰሚነትና ተቀባይነት በመጠቀም ከችግኝ ተከላና ጽድቀት እስከ ዘላቂ እንክብካቤ ድረስ ባሉ የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋሚያ መንገዶች ላይ ማህበረሰቡን የማንቃት ሚና እንዲወጡ በመድረኩ መልዕክት ተላልፏል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!