🕊
[ † እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
††† መድኃኔ ዓለም †††
† ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ በዚሕ ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ ፫ ሰዓት [3:00] ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት:: ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::
ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::
በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት:: በሠለስት [ሦስት ሰዓት ላይ] አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ ፮ ሺህ ፮ መቶ ስድሳ ፮ [6,666] ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት::
ስድስት ሰዓት ላይ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት:: ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ::
ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ:: በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: አሥራ አንድ ሰዓት ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት::
በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ:: [ማቴ.፳፯፥፩ (27:1), ማር.፲፭፥፩ (15:1), ሉቃ.፳፫፥፩ (23:1), ዮሐ.፲፱፥፩ (19:1) ]
ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት ፳፯ [ 27 ] ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት
፳፯ [27] የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው::
ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም::
በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት
፳፯ [27] ሲመጣ: የመጋቢት ፭ [5] ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት ፭ [5] : የመጋቢት ፲ [10] መስቀል ወደ መስከረም ፲፯ [17] መጥቶ እንዲከበር ሆኗል::
🕊 † ቅዱስ መቃርስ ብጹዓዊ † 🕊
በዚህ ስም የሚጠሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው:: "ታላቁ መቃርዮስ": "መቃርስ እስክንድርያዊ": "መቃርስ ባሕታዊ"ን እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል:: ይህኛው ቅዱስ ደግሞ "መቃርስ ኤዺስ ቆዾስ: መቃርስ ብጹዓዊ: መቃርስ ዘሃገረ ቃው" ይባላል:: ሁሉም መጠሪያዎቹ ናቸው::
ቅዱሱ የ፭ኛው መቶ ክ/ዘመን ሰው ሲሆን የቅዱስ ቄርሎስና የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ተከታይ ነው:: ከሕይወቱ ማማርና ከቅድስናው መሥመር የተነሳ አበው አመስግነውት አይይጠግቡም:: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል" እንዳለው:: [መዝ.፺፩]
ዳግመኛ "ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ" [መዝ.፩፥፫] እንዳለው ቅዱስ መቃርስ እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን አፍርቷል:: ከሁሉ አስቀድሞ በበርሃ ኗሪ ከሆነበት ቀን ጀምሮ ስለ ጌታ ፍቅር እንባው እንደ ዥረት እየፈሰሰ:: ራሱን በብረት ዘንግ ይመታ ነበር::
"ቃው" በምትባል ሃገር ዻዻስ ሆኖ በተሾመ ጊዜም ተጋድሎውን አልቀነሰም:: ዻዻስ ቢሆንም የሚለብሰው የበርሃዋን ደበሎ ነው:: ከብቅዓቱ የተነሳ የሕዝቡ ኃጢአት በግንባራቸው ላይ ተጽፎ እየታየው ስለ ወገኖቹ ያለቅስ ነበረ:: በቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሞ አንጀቱ ቅጥል እስኪል ድረስም ያለቅስ ነበር::
ሁልጊዜ ሲቀድስ ጌታችንን ከመላእክቱ ጋር ያየው ነበር:: አንድ ቀንም ጌታ ቅዱስ መቃርስን "ዻዻሱ ሆይ ሕዝቡን ገስጻቸው:: ብትገስጻቸውና ባይሰሙህ እዳው በእነርሱ ላይ ነው" አለው:: ቅዱስ መቃርስም ሕዝቡ ከኃጢአታቸው ይመለሱ ዘንድ ይመክራቸው: ይለምንላቸውም ነበር::
ከዚህ ሁሉ በሁዋላ በጉባኤ ኬልቄዶን [ጉባኤ አብዳን] ፮፻፴፮ ዻዻሳት ንጉሡን ፈርተው ሃይማኖታቸውን ሲክዱ ቅዱሳኑ ዲዮስቆሮስና መቃርስ "ተዋሐዶን አንክድም" በማለታቸው ዘበቱባቸው:: ብዙ አሰቃይተውም ወደ ጋግራ ደሴት አሳደዷቸው::
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ውስጥ ሲሞት ቅዱስ መቃርስ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ሕዝቡን ሲመክር ያዙት:: ከመሬት ላይ ጥለውም እየደጋገሙ ኩላሊቱን ረገጡት:: ከመከራው ብዛትም በዚህች ቀን ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ:: ቅዱሱ ሙታንን ማስነሳትን ጨምሮ ብዙ ተአምራትን ሠርቷል::
አበውም ስለ ቅዱስ መቃርስ ብሎ ጌታ እንዲምራቸው እንዲህ ይጸልዩ ነበር :-
"ሰላም ሰላም ለፈያታዊ ዘቀደሶ::
ሃገረ ጽጌ የአኀዝ ምስለ ጻድቃን በተዋርሶ::
ተዘከረኒ ክርስቶስ አመ ትመጽእ ለተዋቅሶ::
በእንተ መቃርስ ጻድቅ እንተ መጠወ ነፍሶ::
ወበበትረ መስቀል ዘይዘብጥ ርዕሶ::" [አርኬ ዘጥቅምት ፳፯]
🕊 † አቡነ መብዓ ጽዮን † 🕊
ሃገራችን ኢትዮዽያ እጅግ በርካታ ቅዱሳንን ስታፈራ አንዳንዶቹ ደግሞ የተለዩ ናቸው:: ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮን በ፲፭ኛው መቶ ክ ዘመን በሽዋ [ሻሞ] አካባቢ የተነሱ ጻድቅ ናቸው:: ገና ከልጅነታቸው የእመቤታችንና የጌታችን ፍቅር የሞላባቸው ነበሩ::
በ፫ ዓመታቸው ከእንግዳ የወሰዷት ስዕለ አድኅኖ ተለይታቸው አታውቅም ነበር:: በወጣትነታቸው ጊዜም ብሉያት ሐዲሳትን: ቅኔንም ጨምሮ ተምረው: ከቤተሰባቸው አስፈቅደው በምናኔ ገዳም ገቡ::
ከዚያ በሁዋላ ያለውን ገድላቸውን ማን ችሎ ይዘረዝረዋል!
በተለይ ዐርብ ዐርብ የጌታን ፲፫ ሕማማት ለማዘከር ሲቀበሉት የኖሩት መከራ እጅግ ብዙ ነው:: ድንጋይ ተሸክመው እንባና ላበታቸው እየተንጠፈጠፈ ይሰግዳሉ:: በድንጋይ ደረትና ጀርባቸውን ይደቃሉ:: ራሳቸውን ይገርፋሉ:: በዋንጫ ሐሞት [ኮሶ] ሞልተው ይጠጣሉ::
ከዚህ ሁሉ በሁዋላ ወር በገባ በ፳፯ ስለ መድኃኔ ዓለም ጠላ ጠምቀው: ንፍሮ ነክረው ወደ ገበያ ይወጡና ይዘክሩ ነበር:: ከዝክሩ የነካ ሁሉ ይፈወስ ነበር:: ከእንባ ብዛት ዓይናቸው ቢጠፋ ድንግል ማርያም መጥታ ብርሃናዊ ዓይንን ሰጠቻቸው:: ስለዚህም "ተክለ ማርያም [በትረ ማርያም]" ይባላሉ::
ጌታችንም ስለ ፍቅራቸው በአምሳለ ሕጻን ይገለጽላቸው: እርሳቸውም አቅፈው ይስሙት ነበር:: ጻድቁ ተናግረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ ተጋድለው ጌታ በዚህ ቀን ነፍሳትን ከሲዖል እንዲያወጡበት ስልጣንን ሰጣቸው:: አባታችን ቅዱሱና ጻድቁ መብዓ ጽዮን ከብዙ ትሩፋት በሁዋላ ዐርፈዋል::
🕊 † አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ † 🕊
ጻድቁ አቡነ ጽጌ ድንግል በ፲፬ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ሊቅና ገዳማዊ ናቸው:: የዘር ሐረጋቸው ምንም ከቤተ እሥራኤል እንደሚመዘዝ ቢታወቅም ኢትዮዽያዊ ናቸው:: አስቀድመው አይሁዳዊ በመሆናቸው ኢየሱስ ክርስቶስንና ድንግል እናቱን አያምኑም ነበር::
የተማሩትም ብሉይ ኪዳንን ብቻ ነበር:: በጊዜውም "ክርስቶስ አልተወለደም:: ትክክለኛው እምነት ይሁዲ ነው::" እያሉ ከክርስቲያኖች ጋር ይከራከሩ ነበሩ:: አንድ ቀን ግን ከታላቁ ሊቅና ገዳማዊ አቡነ ዜና ማርቆስ ጋር ተገናኙ:: ጻድቁን ስላልቻሏቸው ተሸንፈው በክርስቶስ አመኑ:: አቡነ ዜና ማርቆስም አስተምረው ክርስትና ሲያነሷቸው [ሲያጠምቁዋቸው] "ጽጌ ድንግል" አሏቸው::
[ † እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
††† መድኃኔ ዓለም †††
† ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ በዚሕ ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ ፫ ሰዓት [3:00] ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት:: ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::
ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::
በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት:: በሠለስት [ሦስት ሰዓት ላይ] አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ ፮ ሺህ ፮ መቶ ስድሳ ፮ [6,666] ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት::
ስድስት ሰዓት ላይ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት:: ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ::
ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ:: በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: አሥራ አንድ ሰዓት ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት::
በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ:: [ማቴ.፳፯፥፩ (27:1), ማር.፲፭፥፩ (15:1), ሉቃ.፳፫፥፩ (23:1), ዮሐ.፲፱፥፩ (19:1) ]
ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት ፳፯ [ 27 ] ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት
፳፯ [27] የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው::
ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም::
በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት
፳፯ [27] ሲመጣ: የመጋቢት ፭ [5] ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት ፭ [5] : የመጋቢት ፲ [10] መስቀል ወደ መስከረም ፲፯ [17] መጥቶ እንዲከበር ሆኗል::
🕊 † ቅዱስ መቃርስ ብጹዓዊ † 🕊
በዚህ ስም የሚጠሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው:: "ታላቁ መቃርዮስ": "መቃርስ እስክንድርያዊ": "መቃርስ ባሕታዊ"ን እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል:: ይህኛው ቅዱስ ደግሞ "መቃርስ ኤዺስ ቆዾስ: መቃርስ ብጹዓዊ: መቃርስ ዘሃገረ ቃው" ይባላል:: ሁሉም መጠሪያዎቹ ናቸው::
ቅዱሱ የ፭ኛው መቶ ክ/ዘመን ሰው ሲሆን የቅዱስ ቄርሎስና የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ተከታይ ነው:: ከሕይወቱ ማማርና ከቅድስናው መሥመር የተነሳ አበው አመስግነውት አይይጠግቡም:: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል" እንዳለው:: [መዝ.፺፩]
ዳግመኛ "ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ" [መዝ.፩፥፫] እንዳለው ቅዱስ መቃርስ እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን አፍርቷል:: ከሁሉ አስቀድሞ በበርሃ ኗሪ ከሆነበት ቀን ጀምሮ ስለ ጌታ ፍቅር እንባው እንደ ዥረት እየፈሰሰ:: ራሱን በብረት ዘንግ ይመታ ነበር::
"ቃው" በምትባል ሃገር ዻዻስ ሆኖ በተሾመ ጊዜም ተጋድሎውን አልቀነሰም:: ዻዻስ ቢሆንም የሚለብሰው የበርሃዋን ደበሎ ነው:: ከብቅዓቱ የተነሳ የሕዝቡ ኃጢአት በግንባራቸው ላይ ተጽፎ እየታየው ስለ ወገኖቹ ያለቅስ ነበረ:: በቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሞ አንጀቱ ቅጥል እስኪል ድረስም ያለቅስ ነበር::
ሁልጊዜ ሲቀድስ ጌታችንን ከመላእክቱ ጋር ያየው ነበር:: አንድ ቀንም ጌታ ቅዱስ መቃርስን "ዻዻሱ ሆይ ሕዝቡን ገስጻቸው:: ብትገስጻቸውና ባይሰሙህ እዳው በእነርሱ ላይ ነው" አለው:: ቅዱስ መቃርስም ሕዝቡ ከኃጢአታቸው ይመለሱ ዘንድ ይመክራቸው: ይለምንላቸውም ነበር::
ከዚህ ሁሉ በሁዋላ በጉባኤ ኬልቄዶን [ጉባኤ አብዳን] ፮፻፴፮ ዻዻሳት ንጉሡን ፈርተው ሃይማኖታቸውን ሲክዱ ቅዱሳኑ ዲዮስቆሮስና መቃርስ "ተዋሐዶን አንክድም" በማለታቸው ዘበቱባቸው:: ብዙ አሰቃይተውም ወደ ጋግራ ደሴት አሳደዷቸው::
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ውስጥ ሲሞት ቅዱስ መቃርስ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ሕዝቡን ሲመክር ያዙት:: ከመሬት ላይ ጥለውም እየደጋገሙ ኩላሊቱን ረገጡት:: ከመከራው ብዛትም በዚህች ቀን ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ:: ቅዱሱ ሙታንን ማስነሳትን ጨምሮ ብዙ ተአምራትን ሠርቷል::
አበውም ስለ ቅዱስ መቃርስ ብሎ ጌታ እንዲምራቸው እንዲህ ይጸልዩ ነበር :-
"ሰላም ሰላም ለፈያታዊ ዘቀደሶ::
ሃገረ ጽጌ የአኀዝ ምስለ ጻድቃን በተዋርሶ::
ተዘከረኒ ክርስቶስ አመ ትመጽእ ለተዋቅሶ::
በእንተ መቃርስ ጻድቅ እንተ መጠወ ነፍሶ::
ወበበትረ መስቀል ዘይዘብጥ ርዕሶ::" [አርኬ ዘጥቅምት ፳፯]
🕊 † አቡነ መብዓ ጽዮን † 🕊
ሃገራችን ኢትዮዽያ እጅግ በርካታ ቅዱሳንን ስታፈራ አንዳንዶቹ ደግሞ የተለዩ ናቸው:: ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮን በ፲፭ኛው መቶ ክ ዘመን በሽዋ [ሻሞ] አካባቢ የተነሱ ጻድቅ ናቸው:: ገና ከልጅነታቸው የእመቤታችንና የጌታችን ፍቅር የሞላባቸው ነበሩ::
በ፫ ዓመታቸው ከእንግዳ የወሰዷት ስዕለ አድኅኖ ተለይታቸው አታውቅም ነበር:: በወጣትነታቸው ጊዜም ብሉያት ሐዲሳትን: ቅኔንም ጨምሮ ተምረው: ከቤተሰባቸው አስፈቅደው በምናኔ ገዳም ገቡ::
ከዚያ በሁዋላ ያለውን ገድላቸውን ማን ችሎ ይዘረዝረዋል!
በተለይ ዐርብ ዐርብ የጌታን ፲፫ ሕማማት ለማዘከር ሲቀበሉት የኖሩት መከራ እጅግ ብዙ ነው:: ድንጋይ ተሸክመው እንባና ላበታቸው እየተንጠፈጠፈ ይሰግዳሉ:: በድንጋይ ደረትና ጀርባቸውን ይደቃሉ:: ራሳቸውን ይገርፋሉ:: በዋንጫ ሐሞት [ኮሶ] ሞልተው ይጠጣሉ::
ከዚህ ሁሉ በሁዋላ ወር በገባ በ፳፯ ስለ መድኃኔ ዓለም ጠላ ጠምቀው: ንፍሮ ነክረው ወደ ገበያ ይወጡና ይዘክሩ ነበር:: ከዝክሩ የነካ ሁሉ ይፈወስ ነበር:: ከእንባ ብዛት ዓይናቸው ቢጠፋ ድንግል ማርያም መጥታ ብርሃናዊ ዓይንን ሰጠቻቸው:: ስለዚህም "ተክለ ማርያም [በትረ ማርያም]" ይባላሉ::
ጌታችንም ስለ ፍቅራቸው በአምሳለ ሕጻን ይገለጽላቸው: እርሳቸውም አቅፈው ይስሙት ነበር:: ጻድቁ ተናግረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ ተጋድለው ጌታ በዚህ ቀን ነፍሳትን ከሲዖል እንዲያወጡበት ስልጣንን ሰጣቸው:: አባታችን ቅዱሱና ጻድቁ መብዓ ጽዮን ከብዙ ትሩፋት በሁዋላ ዐርፈዋል::
🕊 † አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ † 🕊
ጻድቁ አቡነ ጽጌ ድንግል በ፲፬ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ሊቅና ገዳማዊ ናቸው:: የዘር ሐረጋቸው ምንም ከቤተ እሥራኤል እንደሚመዘዝ ቢታወቅም ኢትዮዽያዊ ናቸው:: አስቀድመው አይሁዳዊ በመሆናቸው ኢየሱስ ክርስቶስንና ድንግል እናቱን አያምኑም ነበር::
የተማሩትም ብሉይ ኪዳንን ብቻ ነበር:: በጊዜውም "ክርስቶስ አልተወለደም:: ትክክለኛው እምነት ይሁዲ ነው::" እያሉ ከክርስቲያኖች ጋር ይከራከሩ ነበሩ:: አንድ ቀን ግን ከታላቁ ሊቅና ገዳማዊ አቡነ ዜና ማርቆስ ጋር ተገናኙ:: ጻድቁን ስላልቻሏቸው ተሸንፈው በክርስቶስ አመኑ:: አቡነ ዜና ማርቆስም አስተምረው ክርስትና ሲያነሷቸው [ሲያጠምቁዋቸው] "ጽጌ ድንግል" አሏቸው::
ሲመነኩሱም "ጽጌ ብርሃን" ተብለዋል:: ቀጥለውም በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ: እመቤታችንንም ሲለምኑ ምሥጢር ተገለጠላቸው::
የእመ ብርሃንን ስዕለ አድኅኖ በአበባ ተከባ: በብርሃንም ተውጣ ተመለከቱ:: በዚህ ምክንያትም ዛሬ በጣፋጭነቱ የሚታወቀውን ማኅሌተ ጽጌን ፩ መቶ ፶ ዓርኬ አድርገው ደረሱ:: እስከ ዕለተ ዕረፍታቸውም እመቤታችንና ልጇን በገዳማቸው [ወለቃ አካባቢ የሚገኝ] ሲያመሰግኑ ኑረዋል:: በዚህች ቀንም ዐርፈዋል::
አምላከ ቅዱሳን በአማኑኤል ስሙ: በማርያም እሙ: በፈሰሰ ደሙ: በተወጋ ጐኑ: በንጹሐን ቅዱሳኑ ይማረን:: ከመስቀሉና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
† መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን::
🕊
[ † መጋቢት ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮሐንስ [ፍቁረ እግዚእ]
፪. ቅዱሳት አንስት [ከእግረ መስቀሉ ያልተለዩ]
፫. ቅዱሳን ባልንጀሮች [በጌታ ስቅለት ጊዜ ከሞት የተነሱ]
፬. ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ
፭. ታላቁ ቅዱስ መቃርስ [የመነኮሳት አለቃ]
፮. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት [የኢትዮዽያ ንጉሥ]
፯. ቅዱስ ዕፀ መስቀል
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
፪. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
፫. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
፬. ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
† " የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" † [፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
የእመ ብርሃንን ስዕለ አድኅኖ በአበባ ተከባ: በብርሃንም ተውጣ ተመለከቱ:: በዚህ ምክንያትም ዛሬ በጣፋጭነቱ የሚታወቀውን ማኅሌተ ጽጌን ፩ መቶ ፶ ዓርኬ አድርገው ደረሱ:: እስከ ዕለተ ዕረፍታቸውም እመቤታችንና ልጇን በገዳማቸው [ወለቃ አካባቢ የሚገኝ] ሲያመሰግኑ ኑረዋል:: በዚህች ቀንም ዐርፈዋል::
አምላከ ቅዱሳን በአማኑኤል ስሙ: በማርያም እሙ: በፈሰሰ ደሙ: በተወጋ ጐኑ: በንጹሐን ቅዱሳኑ ይማረን:: ከመስቀሉና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
† መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን::
🕊
[ † መጋቢት ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮሐንስ [ፍቁረ እግዚእ]
፪. ቅዱሳት አንስት [ከእግረ መስቀሉ ያልተለዩ]
፫. ቅዱሳን ባልንጀሮች [በጌታ ስቅለት ጊዜ ከሞት የተነሱ]
፬. ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ
፭. ታላቁ ቅዱስ መቃርስ [የመነኮሳት አለቃ]
፮. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት [የኢትዮዽያ ንጉሥ]
፯. ቅዱስ ዕፀ መስቀል
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
፪. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
፫. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
፬. ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
† " የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" † [፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤4
🕊 💖 🕊
† 🕊 ክብርት ሰንበት 🕊 †
💛 💛
❝ በመብረቆች ብልጭታ [ ታጅቦ ] ንጉሥ በሚመጣበት ጊዜ ፣ የዕለታት ሁሉ አውራ [ አለቃ ] የሆነችው ሰንበት ለዘለዓለም ትሰጠናለች ፤ ያኔ ጨረቃ የለም ፣ ፀሐይም ቢሆን ክረምትና በጋም ቢሆን አይኖርም። ❞ [ ቅዱስ ያሬድ ]
🕊 💖 🕊
❝ እስከዚኽች ሰዓት ለአደረሰን ለክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል፡፡ የሰንበት ጌታዋ ነው፡፡ ለጌትነትህ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ ማነው ? ❞ [ ቅዱስ ያሬድ ]
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
† 🕊 ክብርት ሰንበት 🕊 †
💛 💛
❝ በመብረቆች ብልጭታ [ ታጅቦ ] ንጉሥ በሚመጣበት ጊዜ ፣ የዕለታት ሁሉ አውራ [ አለቃ ] የሆነችው ሰንበት ለዘለዓለም ትሰጠናለች ፤ ያኔ ጨረቃ የለም ፣ ፀሐይም ቢሆን ክረምትና በጋም ቢሆን አይኖርም። ❞ [ ቅዱስ ያሬድ ]
🕊 💖 🕊
❝ እስከዚኽች ሰዓት ለአደረሰን ለክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል፡፡ የሰንበት ጌታዋ ነው፡፡ ለጌትነትህ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ ማነው ? ❞ [ ቅዱስ ያሬድ ]
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
❤2
🕊 💖 🕊
[ ሆሣዕና በአርያም ! ]
💛 🕊 💛
❝ ነቢይ " እነሆ ባዕለ ጠጋ የሆነ ንጉሥሽ ወደ አንቺ መጥቷልና እጆችሽን በመጽፋት በደስታ አመስግኚው።" ያለሽን ስሚ፡፡ ወደ አንቺ በትሕትና እንጂ በክብር አይመጣምና፡፡ እንደ ነገሥታት ባለ ክብር የሚገለጥልሽ አይደለም:: በከበረ ሠረገላ ወይም በፈረሶች ተጭኖ ወደ አንቺ እንደማይመጣ አታምኝምን? ነገር ግን ጌታሽ ሲሆን በአህያ ውርንጭላ ላይ ተጭኖ ይመጣል እንጂ፡፡ ሠረገላ ከእስራኤል ፈረስም ከኤፍሬም አይጠፋምና፡፡ በትሕትናውም መኳንንቱን ያዋርዳቸዋል ፤ ነገራት መምጣቱንም ተረጎመላት።
እርሷ ግን በምስጋና የሚዘምሩትን የሕፃናትን ድምፅ ሰምታ ደነገጠች፡፡ ነቢዩ ዳዊት ከሕፃናትና ከሚጠቡት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ ያለውን አላስተዋለችምና፡፡ እነሆ እኔ የነቢያትን መንገድ እከተላለሁ። የቃላቸውን ምሥጢርም እተረጕማለሁ፡፡ ምድርን ሁሉን በየ ወገኑ ታስገኝ ዘንድ ያዘዛት የሁሉ ጌታ እንደ ሆነም እናገራለሁ። በኃይሉም እንስሳትን ሁሉ ፈጠረ።
እርሱ ግን ከልዑል መንበሩ ሳይጎድል በአህያ ውርንጭላ ተቀመጠ፡፡ ወደ ፈረሰች ከተማ በገባ ጊዜ በትሕትናው ፊትም ልብሳቸውን አነጠፉ፡፡ እርሷ ግን አልተቀበለችውም፡፡ ከፍ ከፍም አላደረገችውም፡፡ ለክብሩም አልተገዛችም፡፡ በኃይሉም እንስሳትን ሁሉ ፈጠረ፡፡
ሕፃናቱ ግን ሰማያዊ ክብሩን ዐወቁ፡፡ ሆሳዕና በአርያም በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነውም አሉ። ይኸውም በአህያ ውርንጭላ የተጫነው የዓለም ሁሉ መድኃኒት ነው፡፡ በኪሩቤል ላይ የሚቀመጥ እሱ በትሕትና ወደ ምድር ወረደ፡፡ በምድር በዘንባባ ዝንጣፊ ይመሰገናል፡፡ በሰማይ በመንፈሳውያን መላእክት ክንፍ ይጋረዳል።
ከግርማው የተነሣ ልዑላን የሚንቀጠቀጡለት ይህ ነው፡፡ በአርያም የሚመሰገን እርሱ በሕፃናት አንደበት በጽዮን ገበያዎች ተመሰገነ፡፡ በእሳት መንበሮች የሚቀመጥ በቅዱሳን መላእክትም የሚመሰገን እርሱ እንደ ችግረኛ ያዳናትን ጠላችው ናቀችውም᎓᎓ የሥራዋ ክፋትና ጕስቁልናዋም ተገለጠ፡፡ አብን አስቆጣችው ወልድንም አልወደደችውም፡፡ ልቧ ኃጢአትን ጠገበ፡፡ ከነቢያት ስብከትም ራቀች፡፡ ሕፃናቱንም የምስጋናን ቃል እንዳይናገሩ ዝም ታሰኛቸው ዘንድ ወደደች:: አመፃን እየወደደች እንዴት እውነትን መጠበቅ ይቻላታል? ሕፃናቱ በዘንባባ ዝንጣፊ ሲያመሰግኑ በሰማች ጊዜ በቅናት ነደደች። ተከዘችም፡፡ ❞ [ ቅዱስ ኤፍሬም ]
[ 🩵 ሆሣዕና በአርያም 🩵 ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
[ ሆሣዕና በአርያም ! ]
💛 🕊 💛
❝ ነቢይ " እነሆ ባዕለ ጠጋ የሆነ ንጉሥሽ ወደ አንቺ መጥቷልና እጆችሽን በመጽፋት በደስታ አመስግኚው።" ያለሽን ስሚ፡፡ ወደ አንቺ በትሕትና እንጂ በክብር አይመጣምና፡፡ እንደ ነገሥታት ባለ ክብር የሚገለጥልሽ አይደለም:: በከበረ ሠረገላ ወይም በፈረሶች ተጭኖ ወደ አንቺ እንደማይመጣ አታምኝምን? ነገር ግን ጌታሽ ሲሆን በአህያ ውርንጭላ ላይ ተጭኖ ይመጣል እንጂ፡፡ ሠረገላ ከእስራኤል ፈረስም ከኤፍሬም አይጠፋምና፡፡ በትሕትናውም መኳንንቱን ያዋርዳቸዋል ፤ ነገራት መምጣቱንም ተረጎመላት።
እርሷ ግን በምስጋና የሚዘምሩትን የሕፃናትን ድምፅ ሰምታ ደነገጠች፡፡ ነቢዩ ዳዊት ከሕፃናትና ከሚጠቡት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ ያለውን አላስተዋለችምና፡፡ እነሆ እኔ የነቢያትን መንገድ እከተላለሁ። የቃላቸውን ምሥጢርም እተረጕማለሁ፡፡ ምድርን ሁሉን በየ ወገኑ ታስገኝ ዘንድ ያዘዛት የሁሉ ጌታ እንደ ሆነም እናገራለሁ። በኃይሉም እንስሳትን ሁሉ ፈጠረ።
እርሱ ግን ከልዑል መንበሩ ሳይጎድል በአህያ ውርንጭላ ተቀመጠ፡፡ ወደ ፈረሰች ከተማ በገባ ጊዜ በትሕትናው ፊትም ልብሳቸውን አነጠፉ፡፡ እርሷ ግን አልተቀበለችውም፡፡ ከፍ ከፍም አላደረገችውም፡፡ ለክብሩም አልተገዛችም፡፡ በኃይሉም እንስሳትን ሁሉ ፈጠረ፡፡
ሕፃናቱ ግን ሰማያዊ ክብሩን ዐወቁ፡፡ ሆሳዕና በአርያም በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነውም አሉ። ይኸውም በአህያ ውርንጭላ የተጫነው የዓለም ሁሉ መድኃኒት ነው፡፡ በኪሩቤል ላይ የሚቀመጥ እሱ በትሕትና ወደ ምድር ወረደ፡፡ በምድር በዘንባባ ዝንጣፊ ይመሰገናል፡፡ በሰማይ በመንፈሳውያን መላእክት ክንፍ ይጋረዳል።
ከግርማው የተነሣ ልዑላን የሚንቀጠቀጡለት ይህ ነው፡፡ በአርያም የሚመሰገን እርሱ በሕፃናት አንደበት በጽዮን ገበያዎች ተመሰገነ፡፡ በእሳት መንበሮች የሚቀመጥ በቅዱሳን መላእክትም የሚመሰገን እርሱ እንደ ችግረኛ ያዳናትን ጠላችው ናቀችውም᎓᎓ የሥራዋ ክፋትና ጕስቁልናዋም ተገለጠ፡፡ አብን አስቆጣችው ወልድንም አልወደደችውም፡፡ ልቧ ኃጢአትን ጠገበ፡፡ ከነቢያት ስብከትም ራቀች፡፡ ሕፃናቱንም የምስጋናን ቃል እንዳይናገሩ ዝም ታሰኛቸው ዘንድ ወደደች:: አመፃን እየወደደች እንዴት እውነትን መጠበቅ ይቻላታል? ሕፃናቱ በዘንባባ ዝንጣፊ ሲያመሰግኑ በሰማች ጊዜ በቅናት ነደደች። ተከዘችም፡፡ ❞ [ ቅዱስ ኤፍሬም ]
[ 🩵 ሆሣዕና በአርያም 🩵 ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
❤2
🕊 💖 🕊
[ 🕊 መድኃኔ ዓለም 🕊 ]
† እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †
🕊 💖 🕊
❝ ይትፌሣሕ ሰማይ ወትትሐሠይ ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ሕምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዓባይ ፍሥሐ በሰማያት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ ፤ ❞
ትርጉም ፦ [ ሰማይ ደስ ይለዋል ፣ ምድር ፍስሐን ታደርጋለች የምድር መሠረቶችም መለከትን ይነፋሉ ፣ ተራሮችና ኮረብቶችም ይነዋወጣሉ ፣ ሁሉም የበረሃ ዛፎችም [ ይነዋወጣሉ ] በሰማያትም ዛሬ እጅግ ትልቅ ደስታ ይደረጋል፣ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን [ በከርስቶስ ደም በተገኘ ማዕዶት የተገኘ ደስታን ] ታደርጋለች። ] [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊 💖 🕊
❝ ብርሃን ዘመጽአ ውስተ ዓለም ዘያበርህ ላዕለ ጻድቃን መርአዊሃ ለቤተ ክርስቲያን ይርዳዕ ዘተኃጕለ ያስተጋብእ ዝርዋነ መጽአ ኀቤነ ፤ ❞
ትርጉም ፦ [ ወደ ዓለም የመጣው ብርሃን በጻድቃን ላይ የሚያበራ ነው ፣ የቤተ ክርስቲያን ሙሽራዋ ነው ፣ የጠፋው ይረዳ ዘንድ የተበተኑትን ይሰበስብ ዘንድ ወደ እኛ መጣ [ ሰው ሆነ ] ] [ ድጓ ዘአስተምህሮ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
[ 🕊 መድኃኔ ዓለም 🕊 ]
† እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †
🕊 💖 🕊
❝ ይትፌሣሕ ሰማይ ወትትሐሠይ ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ሕምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዓባይ ፍሥሐ በሰማያት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ ፤ ❞
ትርጉም ፦ [ ሰማይ ደስ ይለዋል ፣ ምድር ፍስሐን ታደርጋለች የምድር መሠረቶችም መለከትን ይነፋሉ ፣ ተራሮችና ኮረብቶችም ይነዋወጣሉ ፣ ሁሉም የበረሃ ዛፎችም [ ይነዋወጣሉ ] በሰማያትም ዛሬ እጅግ ትልቅ ደስታ ይደረጋል፣ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን [ በከርስቶስ ደም በተገኘ ማዕዶት የተገኘ ደስታን ] ታደርጋለች። ] [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊 💖 🕊
❝ ብርሃን ዘመጽአ ውስተ ዓለም ዘያበርህ ላዕለ ጻድቃን መርአዊሃ ለቤተ ክርስቲያን ይርዳዕ ዘተኃጕለ ያስተጋብእ ዝርዋነ መጽአ ኀቤነ ፤ ❞
ትርጉም ፦ [ ወደ ዓለም የመጣው ብርሃን በጻድቃን ላይ የሚያበራ ነው ፣ የቤተ ክርስቲያን ሙሽራዋ ነው ፣ የጠፋው ይረዳ ዘንድ የተበተኑትን ይሰበስብ ዘንድ ወደ እኛ መጣ [ ሰው ሆነ ] ] [ ድጓ ዘአስተምህሮ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
❤4