አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የአርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የነጌሌ አርሲን ግብ በመጀመሪያው አጋማሽ ዳዊት ተፈራ ሲያስቆጥር በፍቅር ግዛቸው ለአርባምንጭ ከተማ የአቻነቷን ግብ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው የሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
የሐዋሳ ከተማን ግብ ሽመልስ በቀለ ሲያስቆጥር የድሬዳዋ ከተማን ግብ ደግሞ ድልአዲስ ገብሬ ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የአርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የነጌሌ አርሲን ግብ በመጀመሪያው አጋማሽ ዳዊት ተፈራ ሲያስቆጥር በፍቅር ግዛቸው ለአርባምንጭ ከተማ የአቻነቷን ግብ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው የሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
የሐዋሳ ከተማን ግብ ሽመልስ በቀለ ሲያስቆጥር የድሬዳዋ ከተማን ግብ ደግሞ ድልአዲስ ገብሬ ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሊቨርፑል ኖቲንግሃምን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸንፏል።
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሊቨርፑል 1 ለ 0 ነው ያሸነፈው።
የጨዋታው ሙሉ ጊዜ ተጠናቅቆ በተጨመረ የባከነ ደቂቃ ላይ አሌክሲስ ማካልስተር የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ወልቭስን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢቫን ጉሳንድ የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ አሳርፏል።
እንዲሁም ፉልሃምን ከሰንደርላንድ ባገናኘው ጨዋታ ፉልሃም 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ራውል ሂሚኔዝ በጨዋታና በፍጹም ቅጣት ምት እና አሌክስ ኢዎቢ የፉልሃምን ግቦች ሲያስቆጥሩ ኢንዞ ለፊ ደግሞ የሰንደርላንድን ብቸኛ ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 1:30 ላይ ቶተንሀምን ከአርሰናል የሚያገናኘው የሰሜን ደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸንፏል።
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሊቨርፑል 1 ለ 0 ነው ያሸነፈው።
የጨዋታው ሙሉ ጊዜ ተጠናቅቆ በተጨመረ የባከነ ደቂቃ ላይ አሌክሲስ ማካልስተር የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ወልቭስን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢቫን ጉሳንድ የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ አሳርፏል።
እንዲሁም ፉልሃምን ከሰንደርላንድ ባገናኘው ጨዋታ ፉልሃም 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ራውል ሂሚኔዝ በጨዋታና በፍጹም ቅጣት ምት እና አሌክስ ኢዎቢ የፉልሃምን ግቦች ሲያስቆጥሩ ኢንዞ ለፊ ደግሞ የሰንደርላንድን ብቸኛ ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 1:30 ላይ ቶተንሀምን ከአርሰናል የሚያገናኘው የሰሜን ደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል።
ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ።
ሁለቱ ቡድኖች አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ነው የተለያዩት።
በተመሳሳይ ሰዓት ሸገር ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ 1 አቻ ሲለያዩ÷ ሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ውጤት 1 አቻ መለያየታቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ።
ሁለቱ ቡድኖች አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ነው የተለያዩት።
በተመሳሳይ ሰዓት ሸገር ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ 1 አቻ ሲለያዩ÷ ሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ውጤት 1 አቻ መለያየታቸው ይታወሳል።
አርሰናል ቶተንሃምን 4 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርን 4 ለ 1 አሸንፏል
በመጀመርያው አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ወደ እረፍት ያመራው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ኤቤሪቼ ኤዜ (2) እና ዮኬሬሽ (2) አስቆጥረዋል።
ኮሎ ሙአኒ የቶተንሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርን 4 ለ 1 አሸንፏል
በመጀመርያው አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ወደ እረፍት ያመራው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ኤቤሪቼ ኤዜ (2) እና ዮኬሬሽ (2) አስቆጥረዋል።
ኮሎ ሙአኒ የቶተንሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
👍20
ብራዚላዊው የማንቼስተር ዩናይትድ ኮከብ ካስሚሮ…
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት ምርጥ ብቃታቸውን እያሳዩ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ካስሚሮ፡፡
የእግር ኳስ ሕይወቱን በሀገሩ ክለብ ሳኦፖሎ የጀመረው ካስሚሮ የቡድኑን ሚዛን በመጠበቅ ችሎታው ይታወቃል፡፡
በወቅቱ በተከላካይ አማካይ ስፍራ ላይ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ የሪያል ማድሪድን ቀልብ የሳበ ሲሆን÷ በ2013 ሎስብላንኮቹን መቀላቀል ችሏል፡፡
ካስሚሮ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ በዋናው ቡድን ውስጥ የመጫወት ዕድል ባለማግኘቱ በውሰት ለፖርቶ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በፖርቶ ቆይታው ካስሚሮ አስደናቂ እንቅስቃሴ በማድረግ ቡድኑን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ለሩብ ፍፃሜ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡
ካስሚሮ በፖርቶ ባሳየው ምርጥ ብቃት ሪያል ማድሪድ በ2015 ተጫዋቹን ወደ ሳንቲያጎ ቤርናባው መልሶ አምጥቶታል፡፡
ካስሚሮ ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ለሪያል ማድሪድ ስኬት ወሳኝ ሚና በመጫወት ዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የተከላካይ አማካዮች አንዱ መሆን ችሏል፡፡
ብራዚላዊው ተጫዋች በሪያል ማድሪድ በነበረው ቆይታ አምስት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የዓለም ክለቦች፣ የኮፓ ዴል ሬይን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
በሪያል ማድሪድ ቤት በቆየባቸው ዓመታት ከክሮሺያዊው ሉካ ሞድሪች እና ከጀርመናዊው ቶኒ ክሩስ ጋር የነበረው ጥምረት አስደናቂ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በሦስቱ ተጫዋቾች አስገራሚ ጥምረት የሪያል ማድሪድ የመሀል ሜዳ ክፍል ለዓመታት አስፈሪ ሆኖ መቆየት... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02CXDLZHsvh1kdENwrbC3DYV1Ep67H1u27QqKhDpMBUWMEeBCQhyyMHpLvG8Tdp4tNl
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት ምርጥ ብቃታቸውን እያሳዩ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ካስሚሮ፡፡
የእግር ኳስ ሕይወቱን በሀገሩ ክለብ ሳኦፖሎ የጀመረው ካስሚሮ የቡድኑን ሚዛን በመጠበቅ ችሎታው ይታወቃል፡፡
በወቅቱ በተከላካይ አማካይ ስፍራ ላይ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ የሪያል ማድሪድን ቀልብ የሳበ ሲሆን÷ በ2013 ሎስብላንኮቹን መቀላቀል ችሏል፡፡
ካስሚሮ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ በዋናው ቡድን ውስጥ የመጫወት ዕድል ባለማግኘቱ በውሰት ለፖርቶ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በፖርቶ ቆይታው ካስሚሮ አስደናቂ እንቅስቃሴ በማድረግ ቡድኑን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ለሩብ ፍፃሜ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡
ካስሚሮ በፖርቶ ባሳየው ምርጥ ብቃት ሪያል ማድሪድ በ2015 ተጫዋቹን ወደ ሳንቲያጎ ቤርናባው መልሶ አምጥቶታል፡፡
ካስሚሮ ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ለሪያል ማድሪድ ስኬት ወሳኝ ሚና በመጫወት ዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የተከላካይ አማካዮች አንዱ መሆን ችሏል፡፡
ብራዚላዊው ተጫዋች በሪያል ማድሪድ በነበረው ቆይታ አምስት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የዓለም ክለቦች፣ የኮፓ ዴል ሬይን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
በሪያል ማድሪድ ቤት በቆየባቸው ዓመታት ከክሮሺያዊው ሉካ ሞድሪች እና ከጀርመናዊው ቶኒ ክሩስ ጋር የነበረው ጥምረት አስደናቂ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በሦስቱ ተጫዋቾች አስገራሚ ጥምረት የሪያል ማድሪድ የመሀል ሜዳ ክፍል ለዓመታት አስፈሪ ሆኖ መቆየት... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02CXDLZHsvh1kdENwrbC3DYV1Ep67H1u27QqKhDpMBUWMEeBCQhyyMHpLvG8Tdp4tNl
ማንቼስተር ዩናይትድ ከኤቨርተን
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ከአራት ተከታታይ ድል በኋላ የአቻ ውጤት ያስመዘገበው ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሁለቱን ሲያሸንፍ ኤቨርተን በአንዱ ድል አድርጎ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 48 ከፍ በማድረግ 4ኛ ደረጃን ከቼልሲ የሚረከብ ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ከአራት ተከታታይ ድል በኋላ የአቻ ውጤት ያስመዘገበው ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሁለቱን ሲያሸንፍ ኤቨርተን በአንዱ ድል አድርጎ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 48 ከፍ በማድረግ 4ኛ ደረጃን ከቼልሲ የሚረከብ ይሆናል፡፡
መቐለ 70 እንደርታ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ስንታየሁ መንግሥቱ አስቆጥሯል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ስንታየሁ መንግሥቱ አስቆጥሯል፡፡
በሜክሲኮ ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሜክሲኮ ጓዋዳላሀራ የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በወንዶች ግማሽ ማራቶን አትሌት ገመቹ ዲዳ ርቀቱን 1 ሰዓት 3 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆኗል፡፡
በሴቶች ምድብ ደግሞ ኮሎሌ መካሹ 1 ሰዓት 12 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቅቃለች፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሜክሲኮ ጓዋዳላሀራ የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በወንዶች ግማሽ ማራቶን አትሌት ገመቹ ዲዳ ርቀቱን 1 ሰዓት 3 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆኗል፡፡
በሴቶች ምድብ ደግሞ ኮሎሌ መካሹ 1 ሰዓት 12 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቅቃለች፡፡
👍4😢1
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 16ቱን ለመቀላቀል የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ አትሌቲኮ ማድሪድ በሜዳው ክለብ ብሩዥን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን ሦስት አቻ በሆነ ውጤት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ምሽት 5 ሰዓት ላይ የጣሊያኑ ክለብ ኢንተር ሚላን በጁሴፔ ሜዛ ከቦዶ ግሊምት ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ኢንተር ሚላን ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 መሸነፉ አይዘነጋም፡፡
በዚህም የአምና መድረኩ የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተርሚላን 16ቱን ለመቀላቀል በሚያደርገው ጉዞ ዛሬ ምሽት ትልቅ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡
በሌላ ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ኒውካስል ዩናይትድ ከካራባግ እንዲሁም ባየር ሊቨርኩሰን ከኦሎምፒያኮስ ይገናኛሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 16ቱን ለመቀላቀል የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ አትሌቲኮ ማድሪድ በሜዳው ክለብ ብሩዥን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን ሦስት አቻ በሆነ ውጤት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ምሽት 5 ሰዓት ላይ የጣሊያኑ ክለብ ኢንተር ሚላን በጁሴፔ ሜዛ ከቦዶ ግሊምት ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ኢንተር ሚላን ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 መሸነፉ አይዘነጋም፡፡
በዚህም የአምና መድረኩ የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተርሚላን 16ቱን ለመቀላቀል በሚያደርገው ጉዞ ዛሬ ምሽት ትልቅ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡
በሌላ ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ኒውካስል ዩናይትድ ከካራባግ እንዲሁም ባየር ሊቨርኩሰን ከኦሎምፒያኮስ ይገናኛሉ፡፡
👍4