ቼልሲ እና በርንሌይ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቼልሲ እና በርንሌይ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የቼልሲን ግብ ጇ ፔድሮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር ፍሌሚንግ የበርንሌይን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ብራይተን ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ አስቶንቪላ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 1 አቻ ተለያይቷል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቼልሲ እና በርንሌይ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የቼልሲን ግብ ጇ ፔድሮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር ፍሌሚንግ የበርንሌይን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ብራይተን ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ አስቶንቪላ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 1 አቻ ተለያይቷል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሲሞን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ አስቆጥረዋል፡፡
ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቢንያም አይተን (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፏል፡፡
አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሲሞን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ አስቆጥረዋል፡፡
ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቢንያም አይተን (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፏል፡፡
አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ - የጨዋታ አሰላለፍ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሜዳው ኒውካስል ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ለማጥበብ ወደ ሜዳ የሚገባ ሲሆን፥ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቋሚ አሰላለፋቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በዚህም መሰረት ዶናሩማ፣ አይት-ኑሪ፣ ጉሂ፣ ሩበን ዲያዝ፣ ማታያስ ኑኔዝ፣ ኒኮ ኦሬሊ፣ ሮድሪ፣ በርናርዶ ሲልቫ፣ አንቱዋን ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሃላንድ በቋሚ አሰላለፍ ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡
በእንግዳው ቡድን ኒውካስል ዩናይትድ በኩል ኒክ ፖፕ፣ ትሪፒየር፣ ቲያው፣ በርን፣ ሀል፣ ዊሎክ፣ ቶናሊ፣ ጃኮብ ራምሴ፣ ኤላንጋ፣ ቮልትማደ እና ጎርደን በመጀመሪያው አሰላለፍ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሜዳው ኒውካስል ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ለማጥበብ ወደ ሜዳ የሚገባ ሲሆን፥ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቋሚ አሰላለፋቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በዚህም መሰረት ዶናሩማ፣ አይት-ኑሪ፣ ጉሂ፣ ሩበን ዲያዝ፣ ማታያስ ኑኔዝ፣ ኒኮ ኦሬሊ፣ ሮድሪ፣ በርናርዶ ሲልቫ፣ አንቱዋን ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሃላንድ በቋሚ አሰላለፍ ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡
በእንግዳው ቡድን ኒውካስል ዩናይትድ በኩል ኒክ ፖፕ፣ ትሪፒየር፣ ቲያው፣ በርን፣ ሀል፣ ዊሎክ፣ ቶናሊ፣ ጃኮብ ራምሴ፣ ኤላንጋ፣ ቮልትማደ እና ጎርደን በመጀመሪያው አሰላለፍ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
👍6
አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የአርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የነጌሌ አርሲን ግብ በመጀመሪያው አጋማሽ ዳዊት ተፈራ ሲያስቆጥር በፍቅር ግዛቸው ለአርባምንጭ ከተማ የአቻነቷን ግብ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው የሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
የሐዋሳ ከተማን ግብ ሽመልስ በቀለ ሲያስቆጥር የድሬዳዋ ከተማን ግብ ደግሞ ድልአዲስ ገብሬ ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ አቻ ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የአርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የነጌሌ አርሲን ግብ በመጀመሪያው አጋማሽ ዳዊት ተፈራ ሲያስቆጥር በፍቅር ግዛቸው ለአርባምንጭ ከተማ የአቻነቷን ግብ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው የሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
የሐዋሳ ከተማን ግብ ሽመልስ በቀለ ሲያስቆጥር የድሬዳዋ ከተማን ግብ ደግሞ ድልአዲስ ገብሬ ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሊቨርፑል ኖቲንግሃምን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸንፏል።
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሊቨርፑል 1 ለ 0 ነው ያሸነፈው።
የጨዋታው ሙሉ ጊዜ ተጠናቅቆ በተጨመረ የባከነ ደቂቃ ላይ አሌክሲስ ማካልስተር የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ወልቭስን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢቫን ጉሳንድ የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ አሳርፏል።
እንዲሁም ፉልሃምን ከሰንደርላንድ ባገናኘው ጨዋታ ፉልሃም 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ራውል ሂሚኔዝ በጨዋታና በፍጹም ቅጣት ምት እና አሌክስ ኢዎቢ የፉልሃምን ግቦች ሲያስቆጥሩ ኢንዞ ለፊ ደግሞ የሰንደርላንድን ብቸኛ ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 1:30 ላይ ቶተንሀምን ከአርሰናል የሚያገናኘው የሰሜን ደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸንፏል።
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሊቨርፑል 1 ለ 0 ነው ያሸነፈው።
የጨዋታው ሙሉ ጊዜ ተጠናቅቆ በተጨመረ የባከነ ደቂቃ ላይ አሌክሲስ ማካልስተር የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ወልቭስን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢቫን ጉሳንድ የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ አሳርፏል።
እንዲሁም ፉልሃምን ከሰንደርላንድ ባገናኘው ጨዋታ ፉልሃም 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ራውል ሂሚኔዝ በጨዋታና በፍጹም ቅጣት ምት እና አሌክስ ኢዎቢ የፉልሃምን ግቦች ሲያስቆጥሩ ኢንዞ ለፊ ደግሞ የሰንደርላንድን ብቸኛ ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 1:30 ላይ ቶተንሀምን ከአርሰናል የሚያገናኘው የሰሜን ደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል።
ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ።
ሁለቱ ቡድኖች አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ነው የተለያዩት።
በተመሳሳይ ሰዓት ሸገር ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ 1 አቻ ሲለያዩ÷ ሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ውጤት 1 አቻ መለያየታቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ።
ሁለቱ ቡድኖች አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ነው የተለያዩት።
በተመሳሳይ ሰዓት ሸገር ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ 1 አቻ ሲለያዩ÷ ሐዋሳ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ውጤት 1 አቻ መለያየታቸው ይታወሳል።
አርሰናል ቶተንሃምን 4 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርን 4 ለ 1 አሸንፏል
በመጀመርያው አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ወደ እረፍት ያመራው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ኤቤሪቼ ኤዜ (2) እና ዮኬሬሽ (2) አስቆጥረዋል።
ኮሎ ሙአኒ የቶተንሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርን 4 ለ 1 አሸንፏል
በመጀመርያው አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ወደ እረፍት ያመራው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ኤቤሪቼ ኤዜ (2) እና ዮኬሬሽ (2) አስቆጥረዋል።
ኮሎ ሙአኒ የቶተንሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።
👍20
ብራዚላዊው የማንቼስተር ዩናይትድ ኮከብ ካስሚሮ…
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት ምርጥ ብቃታቸውን እያሳዩ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ካስሚሮ፡፡
የእግር ኳስ ሕይወቱን በሀገሩ ክለብ ሳኦፖሎ የጀመረው ካስሚሮ የቡድኑን ሚዛን በመጠበቅ ችሎታው ይታወቃል፡፡
በወቅቱ በተከላካይ አማካይ ስፍራ ላይ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ የሪያል ማድሪድን ቀልብ የሳበ ሲሆን÷ በ2013 ሎስብላንኮቹን መቀላቀል ችሏል፡፡
ካስሚሮ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ በዋናው ቡድን ውስጥ የመጫወት ዕድል ባለማግኘቱ በውሰት ለፖርቶ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በፖርቶ ቆይታው ካስሚሮ አስደናቂ እንቅስቃሴ በማድረግ ቡድኑን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ለሩብ ፍፃሜ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡
ካስሚሮ በፖርቶ ባሳየው ምርጥ ብቃት ሪያል ማድሪድ በ2015 ተጫዋቹን ወደ ሳንቲያጎ ቤርናባው መልሶ አምጥቶታል፡፡
ካስሚሮ ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ለሪያል ማድሪድ ስኬት ወሳኝ ሚና በመጫወት ዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የተከላካይ አማካዮች አንዱ መሆን ችሏል፡፡
ብራዚላዊው ተጫዋች በሪያል ማድሪድ በነበረው ቆይታ አምስት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የዓለም ክለቦች፣ የኮፓ ዴል ሬይን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
በሪያል ማድሪድ ቤት በቆየባቸው ዓመታት ከክሮሺያዊው ሉካ ሞድሪች እና ከጀርመናዊው ቶኒ ክሩስ ጋር የነበረው ጥምረት አስደናቂ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በሦስቱ ተጫዋቾች አስገራሚ ጥምረት የሪያል ማድሪድ የመሀል ሜዳ ክፍል ለዓመታት አስፈሪ ሆኖ መቆየት... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02CXDLZHsvh1kdENwrbC3DYV1Ep67H1u27QqKhDpMBUWMEeBCQhyyMHpLvG8Tdp4tNl
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት ምርጥ ብቃታቸውን እያሳዩ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ካስሚሮ፡፡
የእግር ኳስ ሕይወቱን በሀገሩ ክለብ ሳኦፖሎ የጀመረው ካስሚሮ የቡድኑን ሚዛን በመጠበቅ ችሎታው ይታወቃል፡፡
በወቅቱ በተከላካይ አማካይ ስፍራ ላይ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ የሪያል ማድሪድን ቀልብ የሳበ ሲሆን÷ በ2013 ሎስብላንኮቹን መቀላቀል ችሏል፡፡
ካስሚሮ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ በዋናው ቡድን ውስጥ የመጫወት ዕድል ባለማግኘቱ በውሰት ለፖርቶ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በፖርቶ ቆይታው ካስሚሮ አስደናቂ እንቅስቃሴ በማድረግ ቡድኑን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ለሩብ ፍፃሜ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡
ካስሚሮ በፖርቶ ባሳየው ምርጥ ብቃት ሪያል ማድሪድ በ2015 ተጫዋቹን ወደ ሳንቲያጎ ቤርናባው መልሶ አምጥቶታል፡፡
ካስሚሮ ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ለሪያል ማድሪድ ስኬት ወሳኝ ሚና በመጫወት ዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የተከላካይ አማካዮች አንዱ መሆን ችሏል፡፡
ብራዚላዊው ተጫዋች በሪያል ማድሪድ በነበረው ቆይታ አምስት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የዓለም ክለቦች፣ የኮፓ ዴል ሬይን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
በሪያል ማድሪድ ቤት በቆየባቸው ዓመታት ከክሮሺያዊው ሉካ ሞድሪች እና ከጀርመናዊው ቶኒ ክሩስ ጋር የነበረው ጥምረት አስደናቂ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በሦስቱ ተጫዋቾች አስገራሚ ጥምረት የሪያል ማድሪድ የመሀል ሜዳ ክፍል ለዓመታት አስፈሪ ሆኖ መቆየት... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02CXDLZHsvh1kdENwrbC3DYV1Ep67H1u27QqKhDpMBUWMEeBCQhyyMHpLvG8Tdp4tNl
ማንቼስተር ዩናይትድ ከኤቨርተን
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ከአራት ተከታታይ ድል በኋላ የአቻ ውጤት ያስመዘገበው ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሁለቱን ሲያሸንፍ ኤቨርተን በአንዱ ድል አድርጎ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 48 ከፍ በማድረግ 4ኛ ደረጃን ከቼልሲ የሚረከብ ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ከአራት ተከታታይ ድል በኋላ የአቻ ውጤት ያስመዘገበው ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሁለቱን ሲያሸንፍ ኤቨርተን በአንዱ ድል አድርጎ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 48 ከፍ በማድረግ 4ኛ ደረጃን ከቼልሲ የሚረከብ ይሆናል፡፡