ማይክል ካሪክ የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ ተብሎ ተመረጠ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማይክል ካሪክ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት የጥር ወር ምርጥ አሰልጣኝ ተብሎ ተመርጧል፡፡
አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ማንቼስተር ዩናይትድን እየመራ በጥር ወር ያደረጋቸውን ሁለት ጨዋታዎች አሸንፏል፡፡
በጥር ወር ማንቼስተር ዩናይትድ የሊጉ መሪ አርሰናል እና ማንቼስተር ሲቲን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
በሌላ በኩል የብሬንትፎርዱ የፊት መስመር ተጫዋች ኢጎር ቲያጎ የጥር ወር ምርጥ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል፡፡
ኢጎር ቲያጎ በውድድር ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉ የወሩ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማይክል ካሪክ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት የጥር ወር ምርጥ አሰልጣኝ ተብሎ ተመርጧል፡፡
አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ማንቼስተር ዩናይትድን እየመራ በጥር ወር ያደረጋቸውን ሁለት ጨዋታዎች አሸንፏል፡፡
በጥር ወር ማንቼስተር ዩናይትድ የሊጉ መሪ አርሰናል እና ማንቼስተር ሲቲን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
በሌላ በኩል የብሬንትፎርዱ የፊት መስመር ተጫዋች ኢጎር ቲያጎ የጥር ወር ምርጥ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል፡፡
ኢጎር ቲያጎ በውድድር ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉ የወሩ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል።
👍2
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 16ቱን ለመቀላቀል የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ይጀምራሉ።
ምሽት 5 ሰዓት ላይ የፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ በሜዳው ስታዲዮ ዳ ሉዛ ሪያል ማድሪድን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ በስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተገናኝተው ቤኔፊካ 4 ለ 2 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ጁድ ቤሊንግሃም፣ ሮድሪጎ፣ ኤደር ሚሊታኦ እና ራውል አሴንሲዮ በዛሬው ጨዋታ ለሪያል ማድሪድ ግልጋሎት የማይሰጡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የወቅቱ የመድረኩ አሸናፊ ፒኤስጂ ከሞናኮ፣ ቦርሲያ ዶርትሙንድ ከአታላንታ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ጋላታሰራይ ከጁቬንቱስ ይገናኛሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 16ቱን ለመቀላቀል የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ይጀምራሉ።
ምሽት 5 ሰዓት ላይ የፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ በሜዳው ስታዲዮ ዳ ሉዛ ሪያል ማድሪድን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ በስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተገናኝተው ቤኔፊካ 4 ለ 2 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ጁድ ቤሊንግሃም፣ ሮድሪጎ፣ ኤደር ሚሊታኦ እና ራውል አሴንሲዮ በዛሬው ጨዋታ ለሪያል ማድሪድ ግልጋሎት የማይሰጡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የወቅቱ የመድረኩ አሸናፊ ፒኤስጂ ከሞናኮ፣ ቦርሲያ ዶርትሙንድ ከአታላንታ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ጋላታሰራይ ከጁቬንቱስ ይገናኛሉ፡፡
ቡካዮ ሳካ በአርሰናል የሚያቆየውን የረዥም ጊዜ ውል ተፈራረመ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ቡካዮ ሳካ በአርሰናል የሚያቆየውን የረዥም ጊዜ ውል ተፈራርሟል፡፡
የ24 ዓመቱ ተጫዋች በሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ ለመቆየት ነው ውሉን ያራዘመው፡፡
ቡካዮ ሳካ በአዲሱ ውል መሰረት በሳምንት 300 ሺ ፓውንድ የሚከፈለው ይሆናል፡፡
ሳካ በዚህ የውድድር ዘመን ለአርሰናል በሁሉም ውድድር ባደረጋቸው 33 ጨዋታዎች በሰባት ጎሎች ላይ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ቡካዮ ሳካ በአርሰናል የሚያቆየውን የረዥም ጊዜ ውል ተፈራርሟል፡፡
የ24 ዓመቱ ተጫዋች በሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ ለመቆየት ነው ውሉን ያራዘመው፡፡
ቡካዮ ሳካ በአዲሱ ውል መሰረት በሳምንት 300 ሺ ፓውንድ የሚከፈለው ይሆናል፡፡
ሳካ በዚህ የውድድር ዘመን ለአርሰናል በሁሉም ውድድር ባደረጋቸው 33 ጨዋታዎች በሰባት ጎሎች ላይ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡
👏7😢4👎1
ዎልቭስ ከአርሰናል…
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ31ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ወደ ሞልኒው ስታዲየም በማቅናት ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል ምሽት 5 ሰዓት ወራጅ ቀጣና ላይ ከሚገኘው ወልቭስ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስፋት ቀደም ብሎ የቤት ስራውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡
በአርሰናል በኩል የክንፍ ተከላካዮቹ ካላፊዎሪ እና ቤን ኋይት ለዛሬው ጨዋታ ብቁ መሆናቸውን የጠቀሱት የቡድኑ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ÷ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ካይ ሀቨርትዝ ለእሁዱ የሰሜን ደርቢ ፍልሚያ ይደርሳሉ ብለዋል።
የዛሬው የዎልቭስ እና የአርሰናል ጨዋታ በፈረንጆቹ መጋቢት 21 ይካሄዳል ተብሎ በሊጉ መርሐ ግብር የወጣለት ቢሆንም፤ ለካራባኦ ካፕ ፍጻሜ የደረሰው አርሰናል ባለበት ጨዋታ ምክንያት ነው ዛሬ የሚካሄደው።
መድፈኞቹ በ57 ነጥብ ከተከታያቸው ማንቼስተር ሲቲ አራት ነጥብ በመብለጥ ሊጉን እየመሩ ይገኛሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ31ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ወደ ሞልኒው ስታዲየም በማቅናት ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል ምሽት 5 ሰዓት ወራጅ ቀጣና ላይ ከሚገኘው ወልቭስ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስፋት ቀደም ብሎ የቤት ስራውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡
በአርሰናል በኩል የክንፍ ተከላካዮቹ ካላፊዎሪ እና ቤን ኋይት ለዛሬው ጨዋታ ብቁ መሆናቸውን የጠቀሱት የቡድኑ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ÷ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ካይ ሀቨርትዝ ለእሁዱ የሰሜን ደርቢ ፍልሚያ ይደርሳሉ ብለዋል።
የዛሬው የዎልቭስ እና የአርሰናል ጨዋታ በፈረንጆቹ መጋቢት 21 ይካሄዳል ተብሎ በሊጉ መርሐ ግብር የወጣለት ቢሆንም፤ ለካራባኦ ካፕ ፍጻሜ የደረሰው አርሰናል ባለበት ጨዋታ ምክንያት ነው ዛሬ የሚካሄደው።
መድፈኞቹ በ57 ነጥብ ከተከታያቸው ማንቼስተር ሲቲ አራት ነጥብ በመብለጥ ሊጉን እየመሩ ይገኛሉ፡፡
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 16 ውስጥ ለመግባት የሚደረጉ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ፡፡
በዚህም መሰረት ካራባግ ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ቦዶ ግሊምት ከኢንተርሚላን፣ ክለብ ብሩዥ ከአትሌቲኮ ማድሪድ እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሊቨርኩሰን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ትናንት በተደረጉ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ቤንፊካን 1 ለ 0፣ ፒኤስጂ ሞናኮን 3 ለ 2፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ አታላንታን 2 ለ 0 እንዲሁም ጋላታሳራይ ጁቬንቱስን 5 ለ 2 አሸንፈዋል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 16 ውስጥ ለመግባት የሚደረጉ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ፡፡
በዚህም መሰረት ካራባግ ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ቦዶ ግሊምት ከኢንተርሚላን፣ ክለብ ብሩዥ ከአትሌቲኮ ማድሪድ እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሊቨርኩሰን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ትናንት በተደረጉ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ቤንፊካን 1 ለ 0፣ ፒኤስጂ ሞናኮን 3 ለ 2፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ አታላንታን 2 ለ 0 እንዲሁም ጋላታሳራይ ጁቬንቱስን 5 ለ 2 አሸንፈዋል።
👎1
አርሰናል ከዎልቭስ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከሜዳው ውጭ ከዎልቭስ ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል።
የሊጉ መሪ አርሰናል በቡካዮ ሳካ እና ሂንካፒ ግቦች 2 ለ ዐ ሲመራ ቢቆይም፥ በሊጉ መጨረሻ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ዎልቭስ ቡዪኖ እና ካላፊዮሪ (በራሱ ላይ) ባስቆጠሯቸው ግቦች ሁለቱ ቡድኖች ነጥብ ተጋርተዋል።
ውጤቱን ተከትሎ 27 ጨዋታዎችን ያደረገው አርሰናል በ58 ነጥብ ሊጉን ሲመራ፥ 26 ጨዋታዎችን ያደረገው ማንቼስተር ሲቲ በ5 ነጥብ ልዩነት ይከተላል።
አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከሜዳው ውጭ ከዎልቭስ ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል።
የሊጉ መሪ አርሰናል በቡካዮ ሳካ እና ሂንካፒ ግቦች 2 ለ ዐ ሲመራ ቢቆይም፥ በሊጉ መጨረሻ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ዎልቭስ ቡዪኖ እና ካላፊዮሪ (በራሱ ላይ) ባስቆጠሯቸው ግቦች ሁለቱ ቡድኖች ነጥብ ተጋርተዋል።
ውጤቱን ተከትሎ 27 ጨዋታዎችን ያደረገው አርሰናል በ58 ነጥብ ሊጉን ሲመራ፥ 26 ጨዋታዎችን ያደረገው ማንቼስተር ሲቲ በ5 ነጥብ ልዩነት ይከተላል።
🙏10👎3
ወላይታ ድቻ መቻልን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግቦች ቴዎድሮስ ሀይለማሪያም፣ ካርሎስ ዳምጠው እና ዮናታን ኤልያስ (2) አስቆጥረዋል፡፡
መቻልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ቸርነት ጉግሳ(2) እና በረከት ደስታ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የባህርዳር ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ግርማ ዲሳሳ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ በተመሳሳይ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግቦች ቴዎድሮስ ሀይለማሪያም፣ ካርሎስ ዳምጠው እና ዮናታን ኤልያስ (2) አስቆጥረዋል፡፡
መቻልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ቸርነት ጉግሳ(2) እና በረከት ደስታ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የባህርዳር ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ግርማ ዲሳሳ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ በተመሳሳይ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ አዲስ ታሪክ የጻፈው ጀምስ ሚልነር…
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብራይተኑ ተጫዋች ጀምስ ሚልነር በፕሪሚየር ሊጉ ብዙ ጨዋታዎችን ያደረገ ተጫዋች በሚል በሊጉ የታሪክ መዝገብ ስሙን አስፍሯል፡፡
ሚልነር በአሁኑ ሰዓት ክለቡ ብራይተን ከብሬንትፎርድ ጋር እያደረገው በሚገኘው የ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ በቋሚነት በመሰለፍ 654ኛ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን አድርጓል፡፡
በዚህም መሰረት የ40 ዓመቱ እንግሊዛዊ የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ በብራይተን፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ ሊቨርፑል፣ ኒውካስል ዩናይትድ፣ አስቶን ቪላ እና ሊድስ ዩናይትድ በአጠቃላይ በ654 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡
ይህን ተከትሎም በሊጉ 653 ጨዋታዎችን በማድረግ ቀዳሚ የነበረውን የቀድሞ የማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ እና ዌስትብሮሚች ተጫዋች ጋሪዝ ባሪ ክብረወሰን በመብለጥ አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡
በፈረንጆቹ 2002 የመጀመሪያ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን በ16 ዓመቱ ለሊድስ ዩናይትድ ያደረገ ሲሆን፥ በወቅቱ በሊጉ መሰለፍ የቻለ 2ኛው በእድሜ ትንሹ ተጫዋች ነበር፡፡
ከሊቨርፑል ጋር አንድ የሻምፒየንስ ሊግ እና አንድ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን ያሳካው ጀምስ ሚልነር ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ሁለት ጊዜ የሊጉ ባለክብር መሆን ችሏል፡፡
ጀምስ ሚልነር 27ኛ ሳምንቱ ላይ በሚገኘው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጨማሪ ጨዋታዎችን በማድረግ ቁጥሩን ከዚህም ከፍ የማድረግ እድል አለው፡፡
የቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ሪያን ጊግስ (632) እንዲሁም ፍራንክ ላምፓርድ (609) በሊጉ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብራይተኑ ተጫዋች ጀምስ ሚልነር በፕሪሚየር ሊጉ ብዙ ጨዋታዎችን ያደረገ ተጫዋች በሚል በሊጉ የታሪክ መዝገብ ስሙን አስፍሯል፡፡
ሚልነር በአሁኑ ሰዓት ክለቡ ብራይተን ከብሬንትፎርድ ጋር እያደረገው በሚገኘው የ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ በቋሚነት በመሰለፍ 654ኛ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን አድርጓል፡፡
በዚህም መሰረት የ40 ዓመቱ እንግሊዛዊ የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ በብራይተን፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ ሊቨርፑል፣ ኒውካስል ዩናይትድ፣ አስቶን ቪላ እና ሊድስ ዩናይትድ በአጠቃላይ በ654 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡
ይህን ተከትሎም በሊጉ 653 ጨዋታዎችን በማድረግ ቀዳሚ የነበረውን የቀድሞ የማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ እና ዌስትብሮሚች ተጫዋች ጋሪዝ ባሪ ክብረወሰን በመብለጥ አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡
በፈረንጆቹ 2002 የመጀመሪያ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን በ16 ዓመቱ ለሊድስ ዩናይትድ ያደረገ ሲሆን፥ በወቅቱ በሊጉ መሰለፍ የቻለ 2ኛው በእድሜ ትንሹ ተጫዋች ነበር፡፡
ከሊቨርፑል ጋር አንድ የሻምፒየንስ ሊግ እና አንድ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን ያሳካው ጀምስ ሚልነር ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ሁለት ጊዜ የሊጉ ባለክብር መሆን ችሏል፡፡
ጀምስ ሚልነር 27ኛ ሳምንቱ ላይ በሚገኘው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጨማሪ ጨዋታዎችን በማድረግ ቁጥሩን ከዚህም ከፍ የማድረግ እድል አለው፡፡
የቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ሪያን ጊግስ (632) እንዲሁም ፍራንክ ላምፓርድ (609) በሊጉ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
ቼልሲ እና በርንሌይ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቼልሲ እና በርንሌይ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የቼልሲን ግብ ጇ ፔድሮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር ፍሌሚንግ የበርንሌይን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ብራይተን ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ አስቶንቪላ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 1 አቻ ተለያይቷል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቼልሲ እና በርንሌይ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የቼልሲን ግብ ጇ ፔድሮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር ፍሌሚንግ የበርንሌይን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ብራይተን ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ አስቶንቪላ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 1 አቻ ተለያይቷል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሲሞን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ አስቆጥረዋል፡፡
ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቢንያም አይተን (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፏል፡፡
አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሲሞን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ አስቆጥረዋል፡፡
ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቢንያም አይተን (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፏል፡፡
አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡