FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
31.4K subscribers
20.2K photos
8 videos
9 files
5.33K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
የዕዙ ስታፍ ሴት የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የስራ አፈፃፀም ውጤታማ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አጠቃላይ የስራ አፈፃፀሙን አስመልክቶ ባካሄደው ውይይት የጠቅላይ መምሪያው ሴት የሠራዊት አባላት የተሰጣቸውን ግዳጅና ተልዕኮ በውጤታማነት መፈፀማቸውን የዕዙ ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ተወካይ ሌተናል ኮሎኔል ሸዋዬ ካህሳይ ተናግረዋል።

እንደ ዕዝ ሴቶችን በሁለንተናዊ መስክ ለማብቃት የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች የተሻለ አፈፃፀም ነበራቸው ያሉት ሌተናል ኮሎኔል ሸዋዬ ካህሳይ የሴቶችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣አሠራርና መመሪያው በሚፈቅደው መሠረት የመብቶቻቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በየደረጃው ያለ አመራር ያሳየው ተነሳሽነት፣ ቁርጠኝነትና ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል።

ከውይይቱ ማጠቃለያ በኋላ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ውይይት የተደረገ ሲሆን  ለዕቅዱ መሳካት  የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

ዘጋቢ አለምፀሃይ ተሾመ
ፎቶግራፍ  አንዷለም ከፍያለው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የሁሉም ዕዞች ጤና መምሪያ ሃላፊዎችና የደረጃ -3 ሆስፒታል አዛዦች ቢሾፍቱ ከተማ የሚገኘውን የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ በአዳማ ከተማ ባዘጋጀው የ2016 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የአዲሡን በጀት ዓመት የስራ እቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ ላይ የተሳተፉ የሁሉም ዕዞች ጤና መምሪያ ሃላፊዎችና የደረጃ-3 ሆስፒታል አዛዦች ቢሾፍቱ ከተማ ተገኝተው የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።

በዕለቱም ለጎብኝዎች እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቀበሉትና ስለ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታሉ የስራ እንቅስቃሴ ገለፃ ያደረጉት የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሸዋዬ ሃይሌ መከላከያ ተቋማዊ ሪፎርሙን መነሻ በማድረግ የሠራዊቱን ተልዕኮ የሚመጥን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግና የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ ሂደትን የሚያሳልጡ የጤና መሠረተ-ልማቶችን ለማስፋፋት ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

ሠራዊታችን ዘመኑን የሚመጥን፤ የተሟላ እና ተደራሽ የሆነ የጤና አገልግሎት ማግኘት ይገባዋል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ሸዋዬ ሃይሌ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ከሠራዊታችን ጤና መበልፀግና የተሟላ ፈውስና እንክብካቤ ማግኘት ባሻገር እንደ ሃገር የጤናውን ዘርፍ አንድ እርምጃ የማራመድ አቅምን የተጎናፀፈ እጅግ ዘመናዊ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሆስፒታሉ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር አብይ አህመድ ተመርቆ በይፋ ስራ መጀመሩን ያስታወሡት የሆስፒታሉ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሸዋዬ በአሁኑ ወቅትም ታካሚ የሠራዊት አባላትን ተቀብሎ አገልግሎት መስጠት መጀመሩንና በሂደትም የመጨረሻ አቅሙን ሙሉ በሙሉ አሟጦ ግልጋሎት መስጠት እንዲችል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

ሆስፒታሉን ተዘዋዉረው ከጎበኙ የጤናው ዘርፍ ስራ አመራሮች መካከል
በጦር ሃይሎች ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሜዲካል ሎጀስቲክስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል ሙሉ ተስፋዬ እና የሠሜን ምዕራብ ዕዝ ደረጃ-3 ሆስፒታል አዛዥ ኮሎኔል ዶክተር ታደገ አበራ በሠጡት አስተያየት በተቋማዊ ሪፎርም ትግበራው የሠራዊቱ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ መሆኑን ጠቁመው በማናቸውም ግዳጅ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት ቢደርስብኝ ታክሜ መዳን እችላለሁ የሚል መተማመንን የሚፈጥር ተቋም ተገንብቶ በማየታችን ክብር ተሠምቶናል ብለዋል።

መከላከያ በጤናው አገልግሎት ዘርፍ እያሳየ ያለው እምርታ ዛሬን ብቻ ሳይሆን መጪውን ዘመን እና ትውልድን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የተመለከቱት የተራቀቀ ቴክኖሎጂን የታጠቀው ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አረጋግጦልናል ያሉት ከፍተኛ መኮንኖቹ እነዚህ ጅምሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በየተመደቡበት የስራ ሃላፊነት ጠንክረው እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ በአዳማ ያካሄደውን የ2016 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የመጪውን አዲስ በጀት ዓመት የስራ እቅድ ትውውቅ መድረክ ሲያጠናቅቅ የስራ መመሪያ የሠጡት የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ በመጪዎቹ ስምንት እና ሰባት ዓመታት ከአፍሪካ ቀዳሚ እና ተመራጭ የሆነ የጤና አገልግሎትን ዕውን ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ ስለመሆኑ መግለፃቸው የሚታወስ ነው።

ዘጋቢ ሲሳይ ደመቀ
ፎቶ ግራፍ እንደሻው ስሜ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
ስልጠና ለፕሮፌሽናል ሠራዊት ግንባታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

የማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ በህዳሴ ኮር ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙ የመቶ አመራሮች በሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ እና የታችኛው አመራር ሚናን በሚመለከት ትምህርት ሠጥተዋል።

ሠራዊት በየጊዜው ስልጠናዎችን በማከናወን ዘመኑ ከሚጠይቀው ቴክኖሎጂ  ጋር ራሱን እያስተዋወቀ በጠንካራ መሰረት ላይ የተገነባ ሰራዊት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

በስልጠና የሚገኘውን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር  የምትመሩትን ሰራዊት መመሪያ እና አሰራርን ብቻ በመከተል ለጠንካራ አሃድ ግንባታ ስራ ማዋል ይገባችኋል ሲሉ አሥገንዝበዋል።

የኮሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ደስታው ተመስገን በበኩላቸው የኮሩ የሰራዊት አባላት ከግዳጅ ጎን ለጎን  ስልጠናዎችን እያደረገ የቆየ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም የሰራዊቱን ስነ ልቦና የሚያጠናክሩ ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።
  
ዘጋቢ ቃኘው  ካሳሁን
ፎቶግራፍ ቃኘው ካሳሁን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
              የሠራዊቱ ህይወት 
የምስራቅ ዕዝ ሠራዊት አገር የማፅናት ተጋድሎ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም                                                                              
ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ኢትዮጵያ ዘመናዊና ጠንካራ የጦር ኃይል እንዲኖራት ከነበራቸው ፍላጎት በመነሳት በ1935 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ 11 ሻለቆችን የያዘ መደበኛ ሠራዊት አቋቋሙ።

ከነዚህ ሻለቆች መሃከልም የአሁኑ ምስራቅ ዕዝ የያኔው 3ኛ ሻለቃ በኋላም ወደ ክፍለ ጦር በማደጉ ብርጋዲየር ጀኔራል አሰፋው ወልደ ጊዮርጊስ የ3ኛ ክፍለጦር አዛዥ ሆነው ተመደቡ፡፡

በ180 ወታደሮች የተመሰረተው 3ኛ አንበሳው ክፍለጦር አደረጃጀቱን በማስፋት 2ኛና 5ኛ ሚሊሺያ ክፍለጦር የተባሉ ተጨምረው የዚያድ ባሬን ወረራ ለመከላከልና የተጋረጠብንን አገራዊ የደህንነት ስጋት ለመቀልበስ እንደ አዲስ በማደራጀት ምስራቅ ዕዝ ነሃሴ 21 ቀን 1969 ዓ.ም በሐረር  ከተማ ተመሠረተ፡፡

ምስራቅ ዕዝ እንደተቋም የተሰጠው ግዳጅ ግልፅ እና ወቅታዊ ነበር ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ወረራውን እያስፋፋ የመጣውን የሶማሊያ ወራሪ ኃይል በመልሶ ማጥቃት በወረራ ተይዘው የነበሩ የኢትዮጵያን ግዛቶች ማስመለስና ሉዓላዊነትን ማስከበር ነው፡፡
 
ምስራቅ ዕዝ የነበረው ሃይል እና የታጠቀው መሳሪያ ከሶማሊያ ዝግጅት አንፃር እጅግ በጣም አነስተኛ ስለነበር በጎዴ ይገኝ የነበረውን አነስተኛ የወገን ሃይል ለማጠናከር የ79ኛ ሚሊሺያ ብርጌድ ከ219ኛ ነበልባል ጦር ጋር ተደርቦለት የጠላትን እንቅስቃሴ ሊገታ ችሏል፡፡
በመስዋዕትነቱም ደማቅ ታሪክን ፅፏል፡፡

የሶማሊያ ጦር የጦርነት ቀጠናውን እያሰፋ በዋርደር፣ በደገሃቡር፣ በቀብሪደሃርና በሌሎችም ስፍራዎች የነበሩት የወገን አነስተኛ የሰራዊት ክፍሎች በርካታ ሃይል ተጠቅሞ ለመደምስስ ቢሞክርም አልተሳካለትም።

ጀግኗቻችን እየተጣደፈ የሚመጣውን የጠላት ሃይል በመጋፈጥ ግንባራቸውን ለጥይት ሰጥተው በከፈሉት መስዋዕትነት የጠላትን ሃይል በማዳከምና መሳሪያዎቹን በማውደም እስከ መጨረሻዋ የህይወት ፍፃሜ ድረስ ተዋግተዋል፡፡ ድልም አምጥተዋል።

በዳንኤል አወል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
"ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን ለማተራመስ የሚደረግን እርምጃ በዝምታ አትመለከትም" ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ቀጣናዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) በቀጣይ የሚኖረው አዲስ የሰላም ተልዕኮ አወቃቀር ሁኔታ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ላይ አዲስ ስጋት ይዞ መምጣቱ ኢትዮጵያን የሚያሳስብ ሆኗል፡፡

የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለዚሁ አዲስ ሽግግር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፣ ቀጠናው ሊተነበይ ወደማይቻል ፈተና ውስጥ እየገባ ይገኛል፡፡ በሁኔታው ላይ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ ወታደር ያዋጡ አገሮች ተደጋጋሚ ጥሪዎችና አስተያየቶች ትኩረት አልተሰጣቸውም፡፡

የመከላከያ ሠራዊታችንን መልካም ስምና ዝናን እንዲሁም መስዋዕትነት የሚያጠለሹ ተከታታይ መግለጫዎች ሲወጡ ኢትዮጵያ በዝምታ እንድታልፍ ከአንዳንድ ወገኖች በኩል ፍላጐት መኖሩ ይታያል፡፡ ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ ኢትዮጵያ በዝምታ አትመለከትም፡፡ ይህም በመሆኑ በቀጣናው የብሄራዊ ደህንነቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሁሉ በንቃት እየተከታተለች ትገኛለች፡፡

ኢትዮጵያ ለሶማሊያና ለአካባቢው ሰላምና ፀጥታ መስፈን፣ ለጋራ ዕድገት እና በክልሉ ያሉ ህዝቦች መካከል ያለውን የጠበቀ የእርስ በርስ ትስስር ይበልጥ እንዲጎለብት ያላሰለሰ ጥረት ስታደርግ ቆይታለች፡፡

ኢትዮጵያ ከሶማሊያ መንግስት ጋር ያለውን ወቅታዊ አለመግባባት ለመፍታት እንዲያስችል በተዘጋጁ የውይይት መድረኮች ላይም በንቃት ተሳትፎ አድርጋለች፡፡ በእነዚህ ንግግሮች ተጨባጭ ውጤቶችም ታይተዋል። የሶማሊያ መንግስት እነዚህን ሰላም ለማስፈን የሚደረጉ ጥረቶች  ከማጠናከር ይልቅ ቀጠናውን ለማተራመስ ከሚሹ የውጭ ኃይሎች ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡

በሶማሊያ ለማሰማራት የታቀደውን አዲስ የሰላም ተልዕኮ የማዘጋጀት እና የመፍቀድ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ሁሉ በቀጠናው የሚገኙና ቀደም ሲል ወታደር አዋጭ የሆኑ አገራትን ተገቢ የሆኑ ስጋቶች ሁሉ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል፡፡ ለአጭር ጊዜ ፍላጎታቸው እና ከንቱ አላማቸው ሲሉ በክልሉ ውጥረትን ለማቀጣጠል የሚሞክሩ ኃይሎች ዕኩይ ተግባራቸው የሚያስከትሏቸዉን መዘዞች መሸከም ይኖርባቸዋል፡፡ ቀደም ሲል አህጉራዊ እና አለምአቀፋዊ አሸባሪ ቡድኖች ላይ የተገኘውን አበረታች ውጤት አደጋ ላይ የሚጥሉና የሚቀለብሱ ድርጊቶች ኢትዮጵያ አትታገስም።
 
ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ከሶማሊያ ህዝብ እና ከአለምአቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል አሁንም ቁርጠኛ አቋም አላት፡፡

ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቀባይ ጽ/ቤት  
አዲስ አበባ፤ኢትዮጵያ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official