በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በአቤቱታ እና ቅሬታ አፈታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
ነሀሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለባለሥልጣኑ ሠራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥ፣በአቤቱታ እና ቅሬታ አፈታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
የስልጠናው ዓላማ ከሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና ሠራተኞች የደንበኛ አያያዝ ክህሎታቸውን አዳብረው የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና የደንበኞች እርካታን በተግባር እንዲያሳድጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በባለሥልጣኑ የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ደንበኛን በፈገግታ፣ በትህትና እና በፍጥነት መቀበል የአገልግሎቱን ጥራት ግማሽ መንገድ የሚያሳካ መሆኑን ገልጸው አገልግሎት በሚሰጠበት ጊዜ ንቁ አዳማጭ መሆን ፤የተገልጋዩን ስሜት መረዳት ፤ግልጽ መረጃ መስጠት ፤ አዎንታዊ የአካል እንቅስቃሴ መገለጫ የሆኑትን ፈገግታና ትህትና ማሳየት፣ የሥራ ቦታን ለአገልግሎት ምቹና ዝግጁ ማድረግ ፣ ቀልጣፋ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲሁም ደንበኛን በአግባቡ የማስተናገጃ ደረጃዎች የሆኑትን አቀባበል፣ ፍላጎት መለየት፣አገልግሎትን በስታንዳርዱ ላይ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ፤አቅጣጫ መጠቆም እና ደንበኛን በአክብሮትና በፍቅር መሸኘት የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ፣ ቅሬታዎችን ለመፍታት እና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ስለደንበኛ አያያዝ መሠረቶች፤ ስለደንበኛን የማስተናገድ ደረጃዎች፤ ስለቅሬታዎችን የመደራደር ዘዴ፤ስለደንበኞች እርካታመለኪያ እና ስለአስቸጋሪ ግንኙነቶች ማስተዳደር ዙሪያ ሰፋ ያላ ማብራሪያና ገለጻ ተደርጓል፡፡
የቀረቡትን መነሻ ሀሳቦች መሠረት በማድረግ በተደረገው ውይይት ላይ ለተነሱ ሐሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች በባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት በአቶ ታምሩ መስፍን፣ የሥራ አዘመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ታደሰ እና የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ በሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
ነሀሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለባለሥልጣኑ ሠራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥ፣በአቤቱታ እና ቅሬታ አፈታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
የስልጠናው ዓላማ ከሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና ሠራተኞች የደንበኛ አያያዝ ክህሎታቸውን አዳብረው የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና የደንበኞች እርካታን በተግባር እንዲያሳድጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በባለሥልጣኑ የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ደንበኛን በፈገግታ፣ በትህትና እና በፍጥነት መቀበል የአገልግሎቱን ጥራት ግማሽ መንገድ የሚያሳካ መሆኑን ገልጸው አገልግሎት በሚሰጠበት ጊዜ ንቁ አዳማጭ መሆን ፤የተገልጋዩን ስሜት መረዳት ፤ግልጽ መረጃ መስጠት ፤ አዎንታዊ የአካል እንቅስቃሴ መገለጫ የሆኑትን ፈገግታና ትህትና ማሳየት፣ የሥራ ቦታን ለአገልግሎት ምቹና ዝግጁ ማድረግ ፣ ቀልጣፋ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲሁም ደንበኛን በአግባቡ የማስተናገጃ ደረጃዎች የሆኑትን አቀባበል፣ ፍላጎት መለየት፣አገልግሎትን በስታንዳርዱ ላይ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ፤አቅጣጫ መጠቆም እና ደንበኛን በአክብሮትና በፍቅር መሸኘት የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ፣ ቅሬታዎችን ለመፍታት እና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ስለደንበኛ አያያዝ መሠረቶች፤ ስለደንበኛን የማስተናገድ ደረጃዎች፤ ስለቅሬታዎችን የመደራደር ዘዴ፤ስለደንበኞች እርካታመለኪያ እና ስለአስቸጋሪ ግንኙነቶች ማስተዳደር ዙሪያ ሰፋ ያላ ማብራሪያና ገለጻ ተደርጓል፡፡
የቀረቡትን መነሻ ሀሳቦች መሠረት በማድረግ በተደረገው ውይይት ላይ ለተነሱ ሐሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች በባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት በአቶ ታምሩ መስፍን፣ የሥራ አዘመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ታደሰ እና የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ በሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
❤4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ አገልግሎት ለማግኘት እንዴት ማመልከት እንችላለን?
ይህን ቪዲዮ ይከታተሉ👇👇
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
ይህን ቪዲዮ ይከታተሉ👇👇
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
❤15👍2
#ጳጉሜ_2018
“የኢትዮጵያ ማንሰራራት”
ጳጉሜን፦ የስኬት ማጠቃለያ፣ የአዲስ ተስፋ መነሻ!
እየተጠናቀቀ በሚገኘው የ2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን የሚያመላክቱ በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። እነዚህን ስኬቶች በማጠቃለል፣ የተገኙ ውጤቶችን በመገንዘብ እና ለቀጣይ የልማት ጉዞ በተስፋና በቁርጠኝነት ለመስካት የዘንድሮው ጳጉሜ በ**“የኢትዮጵያ ማንሰራራት” የጋራ መሪ መልዕክት ይከበራል።
የጳጉሜ ቀናት ልዩ መልዕክት
ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀን
የተመዘገቡ የእድገትና የእመርታ ውጤቶችን የምናከብርበት።
ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን
ኢትዮጵያ በልማትና በእድገት የምትራመድበትን የማንሰራራት ጉዞ የምናጎለብትበት።
ጳጉሜ 3 — የጽናት ቀን
በፈተናዎች ውስጥ በጽናት በመቆም፣ የሀገር ግንባታ ጉዟችንን በቁርጠኝነት የምናስቀጥልበት።
ጳጉሜ 4 — የኅብር ቀን
በአንድነት፣ በመተባበርና በመከባበር የጋራ ሀገራዊ አቅማችንን የምናጠናክርበት።
ጳጉሜ 5 — የነገ ቀን
የተሻለች፣ የበለጸገችና ለትውልድ የምትተላለፍ ኢትዮጵያን ለመገንባት የነገ ራዕያችንን የምናድስበት።
ጳጉሜ የሚያልፈውን ዓመት ብቻ የምንሰናበትበት ሳይሆን፣ የተሳካውን የምናጠናክርበት፣ ከተሳሳትነው የምንማርበት እና ለተሻለ ነገ በአዲስ ተስፋና በተጨማሪ ቁርጠኝነት የምንነሳበት ወሳኝ ወቅት ነው።
“የኢትዮጵያ ማንሰራራት”
ስኬታችንን እናክብር፤ ትብብራችንን እናጠናክር፤ ነገያችንን በጋራ እንገንባ!
#ጳጉሜ2018
#የኢትዮጵያ_ማንሰራራት
#የእመርታ_ቀን
#የማንሰራራት_ቀን
#የጽናት_ቀን
#የኅብር_ቀን
#የነገ_ቀን
#ኢትዮጵያ
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
“የኢትዮጵያ ማንሰራራት”
ጳጉሜን፦ የስኬት ማጠቃለያ፣ የአዲስ ተስፋ መነሻ!
እየተጠናቀቀ በሚገኘው የ2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን የሚያመላክቱ በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። እነዚህን ስኬቶች በማጠቃለል፣ የተገኙ ውጤቶችን በመገንዘብ እና ለቀጣይ የልማት ጉዞ በተስፋና በቁርጠኝነት ለመስካት የዘንድሮው ጳጉሜ በ**“የኢትዮጵያ ማንሰራራት” የጋራ መሪ መልዕክት ይከበራል።
የጳጉሜ ቀናት ልዩ መልዕክት
ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀን
የተመዘገቡ የእድገትና የእመርታ ውጤቶችን የምናከብርበት።
ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን
ኢትዮጵያ በልማትና በእድገት የምትራመድበትን የማንሰራራት ጉዞ የምናጎለብትበት።
ጳጉሜ 3 — የጽናት ቀን
በፈተናዎች ውስጥ በጽናት በመቆም፣ የሀገር ግንባታ ጉዟችንን በቁርጠኝነት የምናስቀጥልበት።
ጳጉሜ 4 — የኅብር ቀን
በአንድነት፣ በመተባበርና በመከባበር የጋራ ሀገራዊ አቅማችንን የምናጠናክርበት።
ጳጉሜ 5 — የነገ ቀን
የተሻለች፣ የበለጸገችና ለትውልድ የምትተላለፍ ኢትዮጵያን ለመገንባት የነገ ራዕያችንን የምናድስበት።
ጳጉሜ የሚያልፈውን ዓመት ብቻ የምንሰናበትበት ሳይሆን፣ የተሳካውን የምናጠናክርበት፣ ከተሳሳትነው የምንማርበት እና ለተሻለ ነገ በአዲስ ተስፋና በተጨማሪ ቁርጠኝነት የምንነሳበት ወሳኝ ወቅት ነው።
“የኢትዮጵያ ማንሰራራት”
ስኬታችንን እናክብር፤ ትብብራችንን እናጠናክር፤ ነገያችንን በጋራ እንገንባ!
#ጳጉሜ2018
#የኢትዮጵያ_ማንሰራራት
#የእመርታ_ቀን
#የማንሰራራት_ቀን
#የጽናት_ቀን
#የኅብር_ቀን
#የነገ_ቀን
#ኢትዮጵያ
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
❤15👎2
#ጳጉሜ_1
#የእመርታ_ቀን
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
#የእመርታ_ቀን
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
❤1
ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የምሁራን እና ባለሙያዎች ምክክር ተካሄደ
የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ጥራትን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማረጋገጥና የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱን ይበልጥ ወጥና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከባለሙያዎች፥ከዘርፉ ተመራማሪዎች እና ምሁራን ጋር ምክክር ተካሄደ።
የምክክር መድረኩ ከነሐሴ 26-28/2018 ዓ.ም አዳማ ከተማ በሚገኘው በመልካ አዳማ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን፣ ከተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ ከፌዴራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ቁጥር ባለሥልጣን የተውጣጡ ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና የጥራት አረጋጋጭ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የምክክሩ ዋና ዓላማ እና የሦሥት ቀን የቆይታ ዝርዝር መርሃ-ግብ በዶ/ር ሀብታሙ ተሾመ የባለስልጣኑ ስታንደርዳይዜሽንና ብሄራዊ ብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ቀርቧል። ዶ/ር ሀብታሙ በገለጹት መሠረት የምክክሩ ዋና ዓላማ እስከ አሁን ሲከናወን በነበረው በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት የማረጋገጫ ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ ከምሁራን እና ባለድርሻ አካላት ጋር የመጀመሪያውን ምክክር በማካሄድ ብሔራው የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ቅድመ ሁኔታን ማመቻችት ነው።
በመቀጠል የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው የምክክር መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የትምህርትና ስልጠና ጥራት የሀገሪቱን የሰው ኃይል ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገትና የሀገር ግንባታ ውጤታማነት ከሚወስኑ ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ ጥራትን ማረጋገጥ የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም የትምህርትና ስልጠና ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። ዶ/ር አህመድ በተለይም የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በግልጽ መርሆዎች፣ በተወሰኑ መመዘኛዎችና በተቀናጀ አሠራር ላይ መመሥረት እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም በሀገሪቱ የሚተገበረውን የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት በማጠናከር የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሚያቀርቡት ትምህርትና ስልጠና የሀገሪቱን ፍላጎትና የሥራ ዓለም ተጠቃሚነት የሚያሟላ እንዲሆን የሚያግዝ ማዕቀፍ መዘጋጀቱ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።
በመድረኩ የባለሥልጣኑ የእውቅናና ስታንዳርዳይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሑፍ አቅርበዋል። በጽሑፋቸውም ባለሥልጣኑ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ እስካሁን የሠራቸውን የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች፣ በሂደቱ የታዩ ልምዶችና ክፍተቶች እንዲሁም በቀጣይ ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎች በስፋት ቀርበዋል።
የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማሻሻል የሚጫወተውን ሚና በማጠናከር የተማሪዎችና የሰልጣኞች ብቃት፣ የተቋማት አፈጻጸም እና ከሥራ ዓለም ጋር ያለው ትስስር እንዲሻሻል ማድረግ ከሚጠበቁት ዋና ተግባራት መካከል መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል።
ጽሑፉ ከቀረበ በኋላ የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረቡት ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን፣ ምልከታዎችንና የመፍትሔ ሃሳቦችን አንስተዋል። ተሳታፊዎቹ በተለይም የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በተግባር ሲተገበር የሚያጋጥሙ ችግሮች፣ የተቋማት የጥራት ደረጃ አመዳደብ፣ የጥራት መለኪያዎች ግልጽነት፣ የተቋማት ተጠያቂነትና የባለድርሻ አካላት ሚና የመሳሰሉ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ለተሳታፊዎቹ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው እና ም/ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። የተነሱት ሃሳቦችም በማዕቀፉ ዝግጅት ወቅት በጥንቃቄ እንደሚታዩ ተገልጿል።
ዶ/ር አህመድ በበኩላቸው በምክክሩ የተሳተፉ ምሁራን ባቀረቡት ሙያዊ እውቀት፣ ልምድና ምልከታ ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት ጠቃሚ ግብዓት እንደሚገኝ ገልጸዋል። ምሁራንና ባለሙያዎች በተግባራዊ ልምዳቸውና በሙያዊ እውቀታቸው ላይ በመመሥረት የሚያቀርቡት ግብዓት ማዕቀፉ ተግባራዊ፣ ዘላቂና የሀገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስረድተዋል።
ከጋራ ውይይቱ በኋላ ተሳታፊዎች በአራት ቡድን ተከፋፍለው ቀድሞ በተዘጋጁ ስምንት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል። ቡድኖቹ በተመደቡላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት፣ የችግሮችን መነሻ ምክንያቶችና ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በመለየት በየቡድኑ የተነሱ ሃሳባቸውን በጋራ መድረክ ላይ አቅርበዋል።
የቡድን ውይይቱም በሁለት ቀናት በስፋት የተካሄደ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ በተለያዩ አቅጣጫዎች የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ እንዴት ሊጠናከር እንደሚችል የራሳቸውን ሙያዊ ሃሳብ አቅርበዋል። በቡድኖቹ የቀረቡት ሃሳቦችም በጋራ ውይይት ተገምግመውና ተጠናክረው ለማዕቀፉ ዝግጅት የሚያገለግሉ ግብዓቶች ተሰብስበዋል።
በመድረኩ የተነሱት ሃሳቦች እና የቀረቡት ምክረ ሃሳቦች ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉን ለማዘጋጀት ጠንካራ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም ከተለያዩ የሙያ መስኮች የመጡ ምሁራን የተለያዩ አመለካከቶችን ማቅረባቸው ማዕቀፉ በሰፊ ሙያዊ ምክክርና በተጨባጭ ልምድ ላይ እንዲመሠረት ያግዛል ተብሏል።
የባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥር ኢንስፔክሽንና የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሺሻይ አማረ በመድረኩ መጠናቀቂያ ላይ ከምሁራንና ከባለሙያዎች ጋር የተካሄደውን ውይይት አድንቀው፣ በውይይቱ የተገኙ ግብዓቶች ወደ ቀጣይ የማዕቀፍ ዝግጅት ሥራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል።
በቀጣይም በምክክሩ የተሰበሰቡ ሃሳቦችንና ምክረ ሃሳቦችን በማደራጀት፣ በማጠናቀርና በመተንተን ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅት እንደሚውሉ ተገልጿል። ይህም በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን በመቅረፍ፣ የጥራት ማረጋገጫ አሠራሩን ይበልጥ ወጥ፣ ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
የሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት የትምህርትና ስልጠና ጥራትን በተቀናጀ መልኩ ለማሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን የጥራት ባህል ለማጠናከር እና ተማሪዎችና ሰልጣኞች በጥራት የተማሩና በብቃት የተሰለጠኑ የሰው ኃይል እንዲሆኑ ለማስቻል ጠቃሚ እርምጃ እንደሚሆን ይጠበቃል።
በመሆኑም በአዳማ የተካሄደው የምሁራን ምክክር ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅቱን ከሙያዊ እውቀት፣ ከተጨባጭ ልምድና ከባለድርሻ አካላት ምክረ ሃሳብ ጋር በማጣመር ለመተግበር የሚያስችል ጠንካራ መነሻ መፍጠሩ ተገልጿል።
የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ጥራትን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማረጋገጥና የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱን ይበልጥ ወጥና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከባለሙያዎች፥ከዘርፉ ተመራማሪዎች እና ምሁራን ጋር ምክክር ተካሄደ።
የምክክር መድረኩ ከነሐሴ 26-28/2018 ዓ.ም አዳማ ከተማ በሚገኘው በመልካ አዳማ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን፣ ከተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ ከፌዴራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ቁጥር ባለሥልጣን የተውጣጡ ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና የጥራት አረጋጋጭ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የምክክሩ ዋና ዓላማ እና የሦሥት ቀን የቆይታ ዝርዝር መርሃ-ግብ በዶ/ር ሀብታሙ ተሾመ የባለስልጣኑ ስታንደርዳይዜሽንና ብሄራዊ ብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ቀርቧል። ዶ/ር ሀብታሙ በገለጹት መሠረት የምክክሩ ዋና ዓላማ እስከ አሁን ሲከናወን በነበረው በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት የማረጋገጫ ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ ከምሁራን እና ባለድርሻ አካላት ጋር የመጀመሪያውን ምክክር በማካሄድ ብሔራው የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ቅድመ ሁኔታን ማመቻችት ነው።
በመቀጠል የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው የምክክር መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የትምህርትና ስልጠና ጥራት የሀገሪቱን የሰው ኃይል ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገትና የሀገር ግንባታ ውጤታማነት ከሚወስኑ ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ ጥራትን ማረጋገጥ የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም የትምህርትና ስልጠና ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። ዶ/ር አህመድ በተለይም የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በግልጽ መርሆዎች፣ በተወሰኑ መመዘኛዎችና በተቀናጀ አሠራር ላይ መመሥረት እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም በሀገሪቱ የሚተገበረውን የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት በማጠናከር የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሚያቀርቡት ትምህርትና ስልጠና የሀገሪቱን ፍላጎትና የሥራ ዓለም ተጠቃሚነት የሚያሟላ እንዲሆን የሚያግዝ ማዕቀፍ መዘጋጀቱ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።
በመድረኩ የባለሥልጣኑ የእውቅናና ስታንዳርዳይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሑፍ አቅርበዋል። በጽሑፋቸውም ባለሥልጣኑ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ እስካሁን የሠራቸውን የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች፣ በሂደቱ የታዩ ልምዶችና ክፍተቶች እንዲሁም በቀጣይ ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎች በስፋት ቀርበዋል።
የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማሻሻል የሚጫወተውን ሚና በማጠናከር የተማሪዎችና የሰልጣኞች ብቃት፣ የተቋማት አፈጻጸም እና ከሥራ ዓለም ጋር ያለው ትስስር እንዲሻሻል ማድረግ ከሚጠበቁት ዋና ተግባራት መካከል መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል።
ጽሑፉ ከቀረበ በኋላ የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረቡት ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን፣ ምልከታዎችንና የመፍትሔ ሃሳቦችን አንስተዋል። ተሳታፊዎቹ በተለይም የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በተግባር ሲተገበር የሚያጋጥሙ ችግሮች፣ የተቋማት የጥራት ደረጃ አመዳደብ፣ የጥራት መለኪያዎች ግልጽነት፣ የተቋማት ተጠያቂነትና የባለድርሻ አካላት ሚና የመሳሰሉ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ለተሳታፊዎቹ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው እና ም/ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። የተነሱት ሃሳቦችም በማዕቀፉ ዝግጅት ወቅት በጥንቃቄ እንደሚታዩ ተገልጿል።
ዶ/ር አህመድ በበኩላቸው በምክክሩ የተሳተፉ ምሁራን ባቀረቡት ሙያዊ እውቀት፣ ልምድና ምልከታ ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት ጠቃሚ ግብዓት እንደሚገኝ ገልጸዋል። ምሁራንና ባለሙያዎች በተግባራዊ ልምዳቸውና በሙያዊ እውቀታቸው ላይ በመመሥረት የሚያቀርቡት ግብዓት ማዕቀፉ ተግባራዊ፣ ዘላቂና የሀገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስረድተዋል።
ከጋራ ውይይቱ በኋላ ተሳታፊዎች በአራት ቡድን ተከፋፍለው ቀድሞ በተዘጋጁ ስምንት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል። ቡድኖቹ በተመደቡላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት፣ የችግሮችን መነሻ ምክንያቶችና ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በመለየት በየቡድኑ የተነሱ ሃሳባቸውን በጋራ መድረክ ላይ አቅርበዋል።
የቡድን ውይይቱም በሁለት ቀናት በስፋት የተካሄደ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ በተለያዩ አቅጣጫዎች የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ እንዴት ሊጠናከር እንደሚችል የራሳቸውን ሙያዊ ሃሳብ አቅርበዋል። በቡድኖቹ የቀረቡት ሃሳቦችም በጋራ ውይይት ተገምግመውና ተጠናክረው ለማዕቀፉ ዝግጅት የሚያገለግሉ ግብዓቶች ተሰብስበዋል።
በመድረኩ የተነሱት ሃሳቦች እና የቀረቡት ምክረ ሃሳቦች ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉን ለማዘጋጀት ጠንካራ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም ከተለያዩ የሙያ መስኮች የመጡ ምሁራን የተለያዩ አመለካከቶችን ማቅረባቸው ማዕቀፉ በሰፊ ሙያዊ ምክክርና በተጨባጭ ልምድ ላይ እንዲመሠረት ያግዛል ተብሏል።
የባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥር ኢንስፔክሽንና የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሺሻይ አማረ በመድረኩ መጠናቀቂያ ላይ ከምሁራንና ከባለሙያዎች ጋር የተካሄደውን ውይይት አድንቀው፣ በውይይቱ የተገኙ ግብዓቶች ወደ ቀጣይ የማዕቀፍ ዝግጅት ሥራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል።
በቀጣይም በምክክሩ የተሰበሰቡ ሃሳቦችንና ምክረ ሃሳቦችን በማደራጀት፣ በማጠናቀርና በመተንተን ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅት እንደሚውሉ ተገልጿል። ይህም በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን በመቅረፍ፣ የጥራት ማረጋገጫ አሠራሩን ይበልጥ ወጥ፣ ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
የሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት የትምህርትና ስልጠና ጥራትን በተቀናጀ መልኩ ለማሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን የጥራት ባህል ለማጠናከር እና ተማሪዎችና ሰልጣኞች በጥራት የተማሩና በብቃት የተሰለጠኑ የሰው ኃይል እንዲሆኑ ለማስቻል ጠቃሚ እርምጃ እንደሚሆን ይጠበቃል።
በመሆኑም በአዳማ የተካሄደው የምሁራን ምክክር ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅቱን ከሙያዊ እውቀት፣ ከተጨባጭ ልምድና ከባለድርሻ አካላት ምክረ ሃሳብ ጋር በማጣመር ለመተግበር የሚያስችል ጠንካራ መነሻ መፍጠሩ ተገልጿል።
❤11