🔶አዲስ አበባ አንበሳ ባስን ልትዘክር ነው
አንበሳ ባስ ለረጅም ዘመናት የከተማውን ህዝብ አገልግለው በየገራጁ በስብሰው ቆመው የሚገኙት የዳፍ (DAF) አውቶብሶች አገልግሎት ሰጪ ብቻ ሳይሆን የብዙዎች ትዝታ ነበሩ::
የከተማ አስተዳደሩ በተመረጡ የአውቶብስ ፌርምታዎች እነዚህን ቀደምት የአንበሳ ባስ የከተማ አውቶብሶች የአውቶብስ መቆሚያ (ፌርማታ) ለማድረግ ዲዛይኑን አጠናቃል:: ይህም በቅርቡ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አንበሳ ባስ ለረጅም ዘመናት የከተማውን ህዝብ አገልግለው በየገራጁ በስብሰው ቆመው የሚገኙት የዳፍ (DAF) አውቶብሶች አገልግሎት ሰጪ ብቻ ሳይሆን የብዙዎች ትዝታ ነበሩ::
የከተማ አስተዳደሩ በተመረጡ የአውቶብስ ፌርምታዎች እነዚህን ቀደምት የአንበሳ ባስ የከተማ አውቶብሶች የአውቶብስ መቆሚያ (ፌርማታ) ለማድረግ ዲዛይኑን አጠናቃል:: ይህም በቅርቡ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍25❤8😁7👏3
🔶የዴማ ሆፕ ሪልስቴት እና የፋስትፔይ ስምምነት
ዴማ ሆፕ ሪልስቴት ከፋስትፔይ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
በሪልስቴት ዘርፍ ፈጣን እድገት እያስመዘገበ የሚገኘው ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት ከፋስትፔይ ጋር ስምምነት ማድረጉን ገልጿል።
ይህ ስምምነት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሕጋዊ እና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ የቤት ግዢ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ለማስቻል ያለመ ነው።
ደንበኞች የፋስትፔይን የክፍያ ስርዓት በመጠቀም ከዴማ ሆፕ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት እና የንግድ ሱቆችን ሲገዙ ክፍያዎችን በቀላሉ እና በአስተማማኝ ሁኔታ መፈጸም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ዴማ ሆፕ ሪልስቴት በአሁኑ ወቅት ስምንት የሚደርሱ ፕሮጀክቶች እንዳሉት ተገልጿል።
ኩባንያው ካርታ ያላቸውን ቤቶች በመሸጥ እና በግንባታ ፍጥነት ከመታወቁ ባለፈ፣ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመማሪያ ክፍሎችን በመገንባት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
ፋስትፔይ በበኩሉ ወደ ሀገር ውስጥ የሚላክ የውጭ ምንዛሬን ለማዘመን የተቋቋመ የቴክኖሎጂ ድርጅት ሲሆን፣ በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ ሕጋዊ እውቅና ያለው አገልግሎት ይሰጣል። ተቋሙ ከፍተኛ የምንዛሬ ዋጋ በማቅረብ፣ ከአነስተኛ የአገልግሎት ክፍያ ጋር ከየትኛውም ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ባንኮች ገንዘብ በፍጥነት ለማስተላለፍ የሚያስችል ስርዓት ዘርግቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ዴማ ሆፕ ሪልስቴት ከፋስትፔይ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
በሪልስቴት ዘርፍ ፈጣን እድገት እያስመዘገበ የሚገኘው ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት ከፋስትፔይ ጋር ስምምነት ማድረጉን ገልጿል።
ይህ ስምምነት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሕጋዊ እና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ የቤት ግዢ ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ለማስቻል ያለመ ነው።
ደንበኞች የፋስትፔይን የክፍያ ስርዓት በመጠቀም ከዴማ ሆፕ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት እና የንግድ ሱቆችን ሲገዙ ክፍያዎችን በቀላሉ እና በአስተማማኝ ሁኔታ መፈጸም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ዴማ ሆፕ ሪልስቴት በአሁኑ ወቅት ስምንት የሚደርሱ ፕሮጀክቶች እንዳሉት ተገልጿል።
ኩባንያው ካርታ ያላቸውን ቤቶች በመሸጥ እና በግንባታ ፍጥነት ከመታወቁ ባለፈ፣ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመማሪያ ክፍሎችን በመገንባት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
ፋስትፔይ በበኩሉ ወደ ሀገር ውስጥ የሚላክ የውጭ ምንዛሬን ለማዘመን የተቋቋመ የቴክኖሎጂ ድርጅት ሲሆን፣ በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ ሕጋዊ እውቅና ያለው አገልግሎት ይሰጣል። ተቋሙ ከፍተኛ የምንዛሬ ዋጋ በማቅረብ፣ ከአነስተኛ የአገልግሎት ክፍያ ጋር ከየትኛውም ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ባንኮች ገንዘብ በፍጥነት ለማስተላለፍ የሚያስችል ስርዓት ዘርግቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3
🔶የኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ምላሽ
ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ከቲክቶክ ዝነኛዋ ሀና ግዳይ (ባምቢ ሀበሻ) ጋር በገባው ውዝግብ ምክንያት በማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።
እሸቱ መለሰ "እንደዚህ ዓይነት ፕሮግራም ድሮ ነበር መጀመር የነበረብኝ፤ ስለዘገየሁ የተከበረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲል በይፋ መግለጫ ሰጥቷል።
ኮሜዲያኑ አክሎም ከዚህ በኋላ ወደ ኋላ እንደማይመለስና በሥራው እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
ውዝግቡ በሁለቱ ግለሰቦች መካከል ከፍተኛ የሃሳብ ልዩነት የፈጠረ ሲሆን፣ የብዙዎችን ትኩረት መሳቡም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ከቲክቶክ ዝነኛዋ ሀና ግዳይ (ባምቢ ሀበሻ) ጋር በገባው ውዝግብ ምክንያት በማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።
እሸቱ መለሰ "እንደዚህ ዓይነት ፕሮግራም ድሮ ነበር መጀመር የነበረብኝ፤ ስለዘገየሁ የተከበረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲል በይፋ መግለጫ ሰጥቷል።
ኮሜዲያኑ አክሎም ከዚህ በኋላ ወደ ኋላ እንደማይመለስና በሥራው እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
ውዝግቡ በሁለቱ ግለሰቦች መካከል ከፍተኛ የሃሳብ ልዩነት የፈጠረ ሲሆን፣ የብዙዎችን ትኩረት መሳቡም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤22👎6🤮5👍3
🔶የጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ
ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው ንጉሥ ተብሎ ለሚጠራው ለክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ የሚሆን ግርማ ሞገስ ያለው ሐውልት 6 ኪሎ አምበሳ ግቢ አጠገብ ተሠርቶ ዛሬ ሚያዝያ 27 2018 ዓ.ም በይፋ ተመርቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለታላቁ የጥበብ ሰው ያለውን አክብሮት ለመግለጽ ያስገነባው ይህ ሐውልት፣ በስድስት ኪሎ አካባቢ ወደ ምኒልክና ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ መገናኛ ላይ ቆሟል።
ጥላሁን ገሠሠ ስለ ሀገር፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ እናትና ስለ ጀግንነት ያልዘፈነበት ርዕስ የለም። በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞና በሱዳንኛ ዜማዎቹ ህዝብን ሲያቆራኝ የኖረ ባለውለታ ነው።
ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ቢለየንም፣ ዜማዎቹ ግን ከትውልድ ትውልድ ተሻግረው ዛሬም የነፍሳችን ምግብ ናቸው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው ንጉሥ ተብሎ ለሚጠራው ለክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ የሚሆን ግርማ ሞገስ ያለው ሐውልት 6 ኪሎ አምበሳ ግቢ አጠገብ ተሠርቶ ዛሬ ሚያዝያ 27 2018 ዓ.ም በይፋ ተመርቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለታላቁ የጥበብ ሰው ያለውን አክብሮት ለመግለጽ ያስገነባው ይህ ሐውልት፣ በስድስት ኪሎ አካባቢ ወደ ምኒልክና ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ መገናኛ ላይ ቆሟል።
ጥላሁን ገሠሠ ስለ ሀገር፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ እናትና ስለ ጀግንነት ያልዘፈነበት ርዕስ የለም። በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞና በሱዳንኛ ዜማዎቹ ህዝብን ሲያቆራኝ የኖረ ባለውለታ ነው።
ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ቢለየንም፣ ዜማዎቹ ግን ከትውልድ ትውልድ ተሻግረው ዛሬም የነፍሳችን ምግብ ናቸው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤18😁9
🔶የኢቲቪው አብዲ ከማል አረፈ
የቀድሞም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (etv) ጋዜጠኛ አብዲ ከማል ባጋጠው የጤና እክል ዛሬ ጧት በአዲስ አበባ እንዳረፈ ተሰምቷል። ሥርዓተ ቀብሩ ዛሬ (ማክሰኞ) ቀትር ላይ በኮልፌ የሙስሊም የመቃብር ስፍር እንደሚፈፀም የሥራ ባልደረባው ላሉ ኢታላ ጽፏል።
ጋዜጠኛ አብዲ ከማል በኢህአዴግ ጊዜ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን "አኬልዳማ" የተሰኘውን ዶክመንተሪ ጨምሮ የተለያዩ ዘጋቢ ፊልሞችን በማዘጋጀት ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የቀድሞም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (etv) ጋዜጠኛ አብዲ ከማል ባጋጠው የጤና እክል ዛሬ ጧት በአዲስ አበባ እንዳረፈ ተሰምቷል። ሥርዓተ ቀብሩ ዛሬ (ማክሰኞ) ቀትር ላይ በኮልፌ የሙስሊም የመቃብር ስፍር እንደሚፈፀም የሥራ ባልደረባው ላሉ ኢታላ ጽፏል።
ጋዜጠኛ አብዲ ከማል በኢህአዴግ ጊዜ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን "አኬልዳማ" የተሰኘውን ዶክመንተሪ ጨምሮ የተለያዩ ዘጋቢ ፊልሞችን በማዘጋጀት ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢17❤3😱2
🔶ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር
በ90ኛ ዓመት የልደት በዓሉ ተዘከረ
የ75ኛው የአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሚከበርበት በዛሬው ዕለት፣ ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የተወለደበት 90ኛ ዓመት የልደት በዓል በወዳጆቹ ተዘክሯል።
የደራሲው ህልፈት 14 ዓመታት ቢቆጠሩም፣ አድናቂዎቹና የጥበብ ወዳጆች በአዲስ አበባ ውቤ በረሃ አካባቢ በሚገኘው ሐውልቱ ስር በመሰብሰብ ለደራሲው ያላቸውን ፍቅር ገልጸዋል።
"እኔ የምሞተው በሰዎች ልብ ውስጥ ስሞት ነው" የሚለውን ንግግሩን በማስታወስ፣ ደራሲው ዛሬም በስራዎቹ እና በታሪኩ በብዙዎች ልብ ውስጥ ህያው ሆኖ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዚህ ዝግጅት ላይ ደራሲያኑ ዓለማየሁ ገላጋይ፥ዘነበ ወላ፣ኃይለመለኮት መዋዕል እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በ90ኛ ዓመት የልደት በዓሉ ተዘከረ
የ75ኛው የአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሚከበርበት በዛሬው ዕለት፣ ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የተወለደበት 90ኛ ዓመት የልደት በዓል በወዳጆቹ ተዘክሯል።
የደራሲው ህልፈት 14 ዓመታት ቢቆጠሩም፣ አድናቂዎቹና የጥበብ ወዳጆች በአዲስ አበባ ውቤ በረሃ አካባቢ በሚገኘው ሐውልቱ ስር በመሰብሰብ ለደራሲው ያላቸውን ፍቅር ገልጸዋል።
"እኔ የምሞተው በሰዎች ልብ ውስጥ ስሞት ነው" የሚለውን ንግግሩን በማስታወስ፣ ደራሲው ዛሬም በስራዎቹ እና በታሪኩ በብዙዎች ልብ ውስጥ ህያው ሆኖ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዚህ ዝግጅት ላይ ደራሲያኑ ዓለማየሁ ገላጋይ፥ዘነበ ወላ፣ኃይለመለኮት መዋዕል እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤34
🔶ድምጻዊ ሳሚ ዳን ለአርሰናል ዘፈነ
ታዋቂዉ የሬጌ አቀንቃኝ ሳሚ ዳን ከ22 ዓመታት በኃላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ላሸነፈው አርሰናል ክለብ ዘፈን ሰርቷል።
ዛሬ ምሸት 12:00 ሰዓት አርሰናልን የተመለከተ አዲስ ዘፈን እንደሚለቅም ይፋ አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ታዋቂዉ የሬጌ አቀንቃኝ ሳሚ ዳን ከ22 ዓመታት በኃላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ላሸነፈው አርሰናል ክለብ ዘፈን ሰርቷል።
ዛሬ ምሸት 12:00 ሰዓት አርሰናልን የተመለከተ አዲስ ዘፈን እንደሚለቅም ይፋ አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🤣53❤14👍2👎1
🔶ዳንኤል ክብረት ለባንዳና ባዕዳን መዝሙር ጋበዙ
የብልጽግና ፓርቲ እጩ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር የሆኑት ዳንኤል ክብረት ባንዳና ባዕዳን ላላቸው አካላት መዝሙር መጋበዛቸውን ኖር ሬድዮ ከፌስቡክ ገፃቸው ተመልክቷል።
አቶ ዳንኤል በፌስቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ፣ ምርጫውን ለማደናቀፍ ጥረት ላደረጉ የውስጥ "ባንዳዎች" እና የውጭ "ባዕዳን" በሚል የዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍን "እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ" የተሰኘውን መዝሙር ጋብዘዋል።
ዳንኤል "ይሄ ምርጫ እንዳይሳካ ለማደናቀፍ ሞክረው ለነበሩ የውስጥ ባንዳ እና የውጭ ባዳ ይሄንን ጋብዘናል" በማለት በፌስቡክ ገጻቸው ጽፈዋል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
የብልጽግና ፓርቲ እጩ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር የሆኑት ዳንኤል ክብረት ባንዳና ባዕዳን ላላቸው አካላት መዝሙር መጋበዛቸውን ኖር ሬድዮ ከፌስቡክ ገፃቸው ተመልክቷል።
አቶ ዳንኤል በፌስቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ፣ ምርጫውን ለማደናቀፍ ጥረት ላደረጉ የውስጥ "ባንዳዎች" እና የውጭ "ባዕዳን" በሚል የዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍን "እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ" የተሰኘውን መዝሙር ጋብዘዋል።
ዳንኤል "ይሄ ምርጫ እንዳይሳካ ለማደናቀፍ ሞክረው ለነበሩ የውስጥ ባንዳ እና የውጭ ባዳ ይሄንን ጋብዘናል" በማለት በፌስቡክ ገጻቸው ጽፈዋል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
😁37🖕29❤9🤬8🤣4😢3🥰1
🔶የዓለም ዋንጫን በዲኤስቲቪ
የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ 104ቱንም ጨዋታዎች በቀጥታ የሚያስተላልፈው ዲኤስቲቪ ልዩ ቅናሽ ማቅረቡን አስታወቀ
በአሜሪካ፣ በካናዳ እና በሜክሲኮ አስተናጋጅነት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረውን የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ ዲኤስቲቪ (ሱፐርስፖርት) ሁሉንም 104 ጨዋታዎች በቀጥታ እና በላቀ ጥራት እንደሚያስተላልፍ አስታውቋል።
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ትልቁ በሆነው በዚህ ውድድር ላይ 48 ብሔራዊ ቡድኖች በ12 ምድቦች ተከፋፍለው ለ39 ቀናት ብርቱ ፉክክርሚያደርጉ ሲሆን፣ ዲኤስቲቪ ስርጭቱን ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂና የዋጋ ቅናሽ አማራጮችን ይዞ ቀርቧል።
ልዩ የሱፐርስፖርት የሰርጭት አማራጮች፦
ቻናል 222 (World Cup Central)፦ ዋና ዋና ጨዋታዎች እና ትንተናዎች
ቻናል 223 (World Cup Extra)፦ በተመሳሳይ ሰዓት የሚደረጉ ተጨማሪ ወሳኝ ጨዋታዎች
ቻናል 225 (World Cup Pass)፦ አጫጭር ምስሎች (Highlights)፣ ድጋሚ ስርጭቶችና ዘጋቢ ፊልሞች (24/7)
DStv Stream መተግበሪያ፦ በስልክ፣ በታብሌትና በላፕቶፕ ባሉበት ቦታ ሆነው ለመከታተል።
የዲኮደር እና የፓኬጅ ልዩ ቅናሽ፦ ኩባንያው የዓለም ዋንጫውን ምክንያት በማድረግ ለአዳዲስ ደንበኞች ልዩ ቅናሽ ያቀረበ ሲሆን፣ የዲኮደር ዋጋን 999 ብር ብቻ ማድረጉን ገልጿል።
ደንበኞች በወር 569 ብር ብቻ የሚከፈለውን የ"ጎጆ ፓኬጅ" በመጠቀም ሁሉንም 104 ጨዋታዎች በቀጥታ መከታተል እንደሚችሉ ተቋሙ አስታውቋል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ 104ቱንም ጨዋታዎች በቀጥታ የሚያስተላልፈው ዲኤስቲቪ ልዩ ቅናሽ ማቅረቡን አስታወቀ
በአሜሪካ፣ በካናዳ እና በሜክሲኮ አስተናጋጅነት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረውን የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ ዲኤስቲቪ (ሱፐርስፖርት) ሁሉንም 104 ጨዋታዎች በቀጥታ እና በላቀ ጥራት እንደሚያስተላልፍ አስታውቋል።
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ትልቁ በሆነው በዚህ ውድድር ላይ 48 ብሔራዊ ቡድኖች በ12 ምድቦች ተከፋፍለው ለ39 ቀናት ብርቱ ፉክክርሚያደርጉ ሲሆን፣ ዲኤስቲቪ ስርጭቱን ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂና የዋጋ ቅናሽ አማራጮችን ይዞ ቀርቧል።
ልዩ የሱፐርስፖርት የሰርጭት አማራጮች፦
ቻናል 222 (World Cup Central)፦ ዋና ዋና ጨዋታዎች እና ትንተናዎች
ቻናል 223 (World Cup Extra)፦ በተመሳሳይ ሰዓት የሚደረጉ ተጨማሪ ወሳኝ ጨዋታዎች
ቻናል 225 (World Cup Pass)፦ አጫጭር ምስሎች (Highlights)፣ ድጋሚ ስርጭቶችና ዘጋቢ ፊልሞች (24/7)
DStv Stream መተግበሪያ፦ በስልክ፣ በታብሌትና በላፕቶፕ ባሉበት ቦታ ሆነው ለመከታተል።
የዲኮደር እና የፓኬጅ ልዩ ቅናሽ፦ ኩባንያው የዓለም ዋንጫውን ምክንያት በማድረግ ለአዳዲስ ደንበኞች ልዩ ቅናሽ ያቀረበ ሲሆን፣ የዲኮደር ዋጋን 999 ብር ብቻ ማድረጉን ገልጿል።
ደንበኞች በወር 569 ብር ብቻ የሚከፈለውን የ"ጎጆ ፓኬጅ" በመጠቀም ሁሉንም 104 ጨዋታዎች በቀጥታ መከታተል እንደሚችሉ ተቋሙ አስታውቋል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
❤4👍1🔥1
🔶“ሐጀር” እስላማዊ ፊልም ለዕይታ በቃ
በእስልምና ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣትን፣ ሐጀራን የውሃ ፍለጋ ታሪክ የሚያሳየው ይህ ፊልም፤ በተለይም በሶፋ እና በመረዋ ተራሮች መካከል ያደረገችውን ታሪካዊ ሩጫ በፊልም እይታ ያቀረበ ስራ ነው።
ፊልሙ ከአረፋ በዓል ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያለው ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑም ተገልጿል።
ይህንን ፈር-ቀዳጅ ስራ ልዩ ከሚያደርጉት ባህሪያቱ መካከል ፊልሙ ሙሉ በሙሉ ምንም አይነት የቃላት ንግግር የሌለበት (Mime) መሆኑ ሲሆን፣ አጠቃላይ የታሪኩን ይዘትና ልብ የሚነኩ ስሜቶችን በምልክትና በእንቅስቃሴ ብቻ በመግለጽ በ13 ደቂቃ ከፍታ አጭር ጊዜ ውስጥ የተቋጨ የጥበብ ስራ ነው። ይህ አይነቱ አቀራረብ ታሪኩን ያለምንም የቋንቋ ገደብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማንኛውም ተመልካች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተብራርቷል።
የፊልሙ አዘጋጅ ነጻ ዓለም አብዲ እንደተናገረው፤ ለዚህም በአፋር ክልል የሚገኙ ተራራማ ቦታዎችን 80 በመቶ ያህሉን በአካል በመዘዋወር ምልከታ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት የፊልሙ መቼት ሙሉ በሙሉ በአፋር ክልል በሚገኙ ተራራማና ምድረ-በዳ ቦታዎች ላይ ሊቀረጽ ችሏል።
የፊልሙ ባለሙያዎች ለነጃሺ ቲቪ በሰጡት ማብራሪያ፤ ስራው ልብ የሚነኩ የእስላማዊ ታሪክ ህያው ስሜቶችን በኪነ-ጥበብ መድረክ ለማንጸባረቅ በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ፈር ቀዳጅ መሆኑን ገልጸው፣ ፊልሙ የፊልም ስታንዳርዱን በአለም አቀፍ ደረጃ ጠብቆ በብቁ ባለሙያዎች የተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በእስልምና ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣትን፣ ሐጀራን የውሃ ፍለጋ ታሪክ የሚያሳየው ይህ ፊልም፤ በተለይም በሶፋ እና በመረዋ ተራሮች መካከል ያደረገችውን ታሪካዊ ሩጫ በፊልም እይታ ያቀረበ ስራ ነው።
ፊልሙ ከአረፋ በዓል ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያለው ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑም ተገልጿል።
ይህንን ፈር-ቀዳጅ ስራ ልዩ ከሚያደርጉት ባህሪያቱ መካከል ፊልሙ ሙሉ በሙሉ ምንም አይነት የቃላት ንግግር የሌለበት (Mime) መሆኑ ሲሆን፣ አጠቃላይ የታሪኩን ይዘትና ልብ የሚነኩ ስሜቶችን በምልክትና በእንቅስቃሴ ብቻ በመግለጽ በ13 ደቂቃ ከፍታ አጭር ጊዜ ውስጥ የተቋጨ የጥበብ ስራ ነው። ይህ አይነቱ አቀራረብ ታሪኩን ያለምንም የቋንቋ ገደብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማንኛውም ተመልካች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተብራርቷል።
የፊልሙ አዘጋጅ ነጻ ዓለም አብዲ እንደተናገረው፤ ለዚህም በአፋር ክልል የሚገኙ ተራራማ ቦታዎችን 80 በመቶ ያህሉን በአካል በመዘዋወር ምልከታ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት የፊልሙ መቼት ሙሉ በሙሉ በአፋር ክልል በሚገኙ ተራራማና ምድረ-በዳ ቦታዎች ላይ ሊቀረጽ ችሏል።
የፊልሙ ባለሙያዎች ለነጃሺ ቲቪ በሰጡት ማብራሪያ፤ ስራው ልብ የሚነኩ የእስላማዊ ታሪክ ህያው ስሜቶችን በኪነ-ጥበብ መድረክ ለማንጸባረቅ በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ፈር ቀዳጅ መሆኑን ገልጸው፣ ፊልሙ የፊልም ስታንዳርዱን በአለም አቀፍ ደረጃ ጠብቆ በብቁ ባለሙያዎች የተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤12🎉2😁1
🔶የሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ ሥዕል በ2ሺ ዩሮ ተሸጠ
በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ በተካሄደ የሥዕል ኤግዚቢሽን ላይ፣ ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ መድረክ ላይ በቀጥታ የሳለው ሥዕል በጨረታ ከ2 ሺህ ዩሮ በላይ መሸጡ ታወቀ።
በዕለቱ ከተካሄደው የሥዕል ሽያጭና የደጋፊዎች አስተዋጽኦ በተሰበሰበው የሕክምና ድጋፍ፣ በአጠቃላይ ከ8 ሺህ ዩሮ በላይ መገኘቱን ጋዜጠኛ መሳይ ወንድሜነህ ያጋራው መረጃ ያመላክታል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የሕፃናትና ታዳጊዎች የሥዕል ውድድር የተካሄደ ሲሆን፣ አሸናፊዎቹ ሽልማታቸውን ከሠዓሊ ብሩክ እጅ ተቀብለዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ በተካሄደ የሥዕል ኤግዚቢሽን ላይ፣ ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ መድረክ ላይ በቀጥታ የሳለው ሥዕል በጨረታ ከ2 ሺህ ዩሮ በላይ መሸጡ ታወቀ።
በዕለቱ ከተካሄደው የሥዕል ሽያጭና የደጋፊዎች አስተዋጽኦ በተሰበሰበው የሕክምና ድጋፍ፣ በአጠቃላይ ከ8 ሺህ ዩሮ በላይ መገኘቱን ጋዜጠኛ መሳይ ወንድሜነህ ያጋራው መረጃ ያመላክታል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የሕፃናትና ታዳጊዎች የሥዕል ውድድር የተካሄደ ሲሆን፣ አሸናፊዎቹ ሽልማታቸውን ከሠዓሊ ብሩክ እጅ ተቀብለዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤33👏5👍2
🔶ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው አረፈ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
😢40❤5💔5😱4🥰1
🔶ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ ታሰረች
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ ስለመታሰሯ ተሰምቷል።
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ በሙያዋ በሀገር ውስጥ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት ውስጥ የሠራች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በማኅበራዊ ሚዲያ በምታስተላልፋቸው ትምህርታዊ መልእክቶች በሰፊው ትታወቃለች።
ስለ ኢትዮጵያውያን አንድነት በርካታ ሐሳቦችን ታጋራ ነበር። ሰላምን፣ መደጋገፍንና የሀገርን ታሪክ የሚያንጸባርቁ መልእክቶችን በምትሠራቸው ቪዲዮዎቿ ትታወቃለች።
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ የታሰረችው ስለ አርሲ ክርስቲያኖች እልቂት በይፋ በመናገሯ ምክንያት እንደሆነ ተሰምቷል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ ስለመታሰሯ ተሰምቷል።
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ በሙያዋ በሀገር ውስጥ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት ውስጥ የሠራች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በማኅበራዊ ሚዲያ በምታስተላልፋቸው ትምህርታዊ መልእክቶች በሰፊው ትታወቃለች።
ስለ ኢትዮጵያውያን አንድነት በርካታ ሐሳቦችን ታጋራ ነበር። ሰላምን፣ መደጋገፍንና የሀገርን ታሪክ የሚያንጸባርቁ መልእክቶችን በምትሠራቸው ቪዲዮዎቿ ትታወቃለች።
ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ የታሰረችው ስለ አርሲ ክርስቲያኖች እልቂት በይፋ በመናገሯ ምክንያት እንደሆነ ተሰምቷል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
😢27❤16🤔4😱2👎1😁1
🔶የድምፃዊ ሰማኸኝ በለው የቀብር ሥነሥርዓት
የድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
የድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
😭13💔10
🔶ኮሜዲያኑ አልታሰረም !
ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል፣ በዚህ ሳምንት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን
የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል።
ነገር ግን ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል ታስሯል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ...ተጨማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/288
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል፣ በዚህ ሳምንት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን
የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል።
ነገር ግን ኮሜዲያን ምናለ ያረጋል ታስሯል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ...ተጨማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/288
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍9❤3
🔶የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ፊልም ፌስቲቫል
ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፊልም ፌስቲቫል ከዛሬ አርብ ሰኔ 12፣ እስከ እሁድ ሰኔ 14 ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል።
ፌስቲቫል ላይ በመታደም ከ25 በላይ አዳዲስ አጭር ፊልሞችን ይመልከቱ ተብላችኋል።
በተጨማሪም ዘርፉ ላይ ካሉ ታላላቅ ባለሙያዎች ጋር ግንኙነት ይፍጠሩ።
ቦታ - አአዩ - ዋናው ግቢ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ፤ ሼህ አላሙዲ አዳራሽ
ሰዓት - ከጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮ
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፊልም ፌስቲቫል ከዛሬ አርብ ሰኔ 12፣ እስከ እሁድ ሰኔ 14 ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል።
ፌስቲቫል ላይ በመታደም ከ25 በላይ አዳዲስ አጭር ፊልሞችን ይመልከቱ ተብላችኋል።
በተጨማሪም ዘርፉ ላይ ካሉ ታላላቅ ባለሙያዎች ጋር ግንኙነት ይፍጠሩ።
ቦታ - አአዩ - ዋናው ግቢ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ፤ ሼህ አላሙዲ አዳራሽ
ሰዓት - ከጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮ
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
❤4🔥1
🔶የሮቤል ሚዲቅሳ ኮንሰርት
የድምጻዊ ሮቤል ሚዲቅሳ "ከበር አፍ" የሙዚቃ ኮንሰርት ነገ ቅዳሜ ሰኔ 13 2018 ዓ.ም በቃና ዌርሃውስ በድምቀት ይካሄዳል።
ስለኮንሰርቱ ድምጻዊ ሮቤል በማህበራዊ ትስስር ገፁ "የመጀመርያ የሙዚቃ ኮንሰርቴን ለእናንተ ለተከበራችሁ አድማጮቼ እና አድናቂዎቼ ለማቅረብ ዝግጅታችንን ጨርሰናል። ከእናንተ ጋር በአካል የምንገናኝበት ቀን በመድረሱ ደስ እያለኝ ሰኔ 13 - June 20 በቃና ዌርሃውስ የማይረሳ ምሽት እንድናሳልፍ ሁላችሁንም እጋብዛለሁ"ብሏል።
.
ትኬቶቹን በM-PESA ላይ ማግኘት ይችላሉ
መደበኛ- 800
በር ላይ- 1000
ቪአይፒ- 2000
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
የድምጻዊ ሮቤል ሚዲቅሳ "ከበር አፍ" የሙዚቃ ኮንሰርት ነገ ቅዳሜ ሰኔ 13 2018 ዓ.ም በቃና ዌርሃውስ በድምቀት ይካሄዳል።
ስለኮንሰርቱ ድምጻዊ ሮቤል በማህበራዊ ትስስር ገፁ "የመጀመርያ የሙዚቃ ኮንሰርቴን ለእናንተ ለተከበራችሁ አድማጮቼ እና አድናቂዎቼ ለማቅረብ ዝግጅታችንን ጨርሰናል። ከእናንተ ጋር በአካል የምንገናኝበት ቀን በመድረሱ ደስ እያለኝ ሰኔ 13 - June 20 በቃና ዌርሃውስ የማይረሳ ምሽት እንድናሳልፍ ሁላችሁንም እጋብዛለሁ"ብሏል።
.
ትኬቶቹን በM-PESA ላይ ማግኘት ይችላሉ
መደበኛ- 800
በር ላይ- 1000
ቪአይፒ- 2000
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
❤9
🔶አንጋፋው ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሰ አረፈ
በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ለበርካታ ዓመታት ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አዘጋጅነት በተለያዩ የሙያ ደረጃዎች ያገለገሉት አንጋፋው ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሠ በህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሰ ታኅሣሥ 26 ቀን 1959 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከአባታቸው ታደሰ ዳምጠው እና ከእናታቸው ፈለቀች ዳኜ ተወልደዋል።
ከታኅሣሥ 18 ቀን 1994 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በተለይም በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ለ24 ዓመታት በሪፖርተርነት፣ በአዘጋጅነት እና በከፍተኛ የሙያ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።
የሟቹ ሥርዓተ ቀብር ነገ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5፡30 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ተገልጿል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ለበርካታ ዓመታት ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አዘጋጅነት በተለያዩ የሙያ ደረጃዎች ያገለገሉት አንጋፋው ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሠ በህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሰ ታኅሣሥ 26 ቀን 1959 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከአባታቸው ታደሰ ዳምጠው እና ከእናታቸው ፈለቀች ዳኜ ተወልደዋል።
ከታኅሣሥ 18 ቀን 1994 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በተለይም በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ለ24 ዓመታት በሪፖርተርነት፣ በአዘጋጅነት እና በከፍተኛ የሙያ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።
የሟቹ ሥርዓተ ቀብር ነገ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5፡30 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ተገልጿል።
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
😢13❤7🕊1💔1
🔶ተማሪዎቹ የመምህራቸውን መፅሐፍ አሳተሙ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ ድግሪ የጋዜጠኛኝነት ትምህርት ክፍል ተማሪዎቹ የመምህራቸውን መፅሐፍ አሳተሙ።
ተማሪዎቹ ያሳተሙት የመምራቸውን የዶ/ር ኣርካ አቦታ መጽሐፍ ነው።
“ኣርካ ኣቦታ፤ የሦስት ኮከቦች ንትርክ” መጽሐፍ ህትመት እየተጠናቀቀ ነው ሲሆን ፤ ሽያጩ በይፋ ተጀምሯል፡፡
የገጽ ብዛት ፡ 506 ፤ ዋጋ ፡ 998 ብር
በቀጥታ ለመግዛት
ዶ/ር ኣርካ ኣቦታ
የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር
1000290218415
ይህ መጽሐፍ በሁለት የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አንጋፋ የሚድያና ኮሚንኬሽን ት/ቤት መምህራን የተዘጋጀ ፖለቲካዊ የህይዎት ምልከታ ነው፡፡
ዶ/ር ኣርካ ኣቦታ ጽፈውት፣ ዶ/ር ተሻገር ሽፈራው አሰናድተውታል፡፡ ብዙ ባልተነገረላቸው ባህላዊ አውዶችና ፖለቲካዊ ተግዳሮቶች ውስጥ የሚጓዝ መሳጭ ታሪክ ነው፡፡
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ ድግሪ የጋዜጠኛኝነት ትምህርት ክፍል ተማሪዎቹ የመምህራቸውን መፅሐፍ አሳተሙ።
ተማሪዎቹ ያሳተሙት የመምራቸውን የዶ/ር ኣርካ አቦታ መጽሐፍ ነው።
“ኣርካ ኣቦታ፤ የሦስት ኮከቦች ንትርክ” መጽሐፍ ህትመት እየተጠናቀቀ ነው ሲሆን ፤ ሽያጩ በይፋ ተጀምሯል፡፡
የገጽ ብዛት ፡ 506 ፤ ዋጋ ፡ 998 ብር
በቀጥታ ለመግዛት
ዶ/ር ኣርካ ኣቦታ
የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር
1000290218415
ይህ መጽሐፍ በሁለት የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አንጋፋ የሚድያና ኮሚንኬሽን ት/ቤት መምህራን የተዘጋጀ ፖለቲካዊ የህይዎት ምልከታ ነው፡፡
ዶ/ር ኣርካ ኣቦታ ጽፈውት፣ ዶ/ር ተሻገር ሽፈራው አሰናድተውታል፡፡ ብዙ ባልተነገረላቸው ባህላዊ አውዶችና ፖለቲካዊ ተግዳሮቶች ውስጥ የሚጓዝ መሳጭ ታሪክ ነው፡፡
====================
አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/NorRadio1
https://t.me/NorRadio1
❤22👍1🙏1