Event Addis Media
9.43K subscribers
6.32K photos
15 videos
4 files
4.93K links
Connect with Addis artistic community!

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ዚመዝናኛው ዓለም እዚተነጋገሚበት ያለ ጉዳይ

በታዋቂዎቹ "ግሬይ አናቶሚ" እና "ዩፎሪያ" ተኚታታይ ድራማዎቜ ላይ በኹፍተኛ ብቃቱ ዚሚታወቀውና በሚሊዮኖቜ ዘንድ ተወዳጅነትን ያተሚፈው ተዋናይ ኀሪክ ዮን በ53 ዓመቱ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ኀሪክ ዮን ኹዚህ ዓለም ኚመለዚቱ በፊት ኚታዋቂው ዹፊልም አኹፋፋይ "ኔትፍሊክስ" ጋር ባደሚገው ልዩ ስምምነት መሠሚት፣ እርሱ እስኪያርፍ ድሚስ ተደብቆ ዹቆዹው ዚመጚሚሻ ቃለ-መጠይቁ ትናንት ምሜት አዹር ላይ ውሏል።

ባለፈው ኅዳር ወር ላይ ዹተቀሹጾውና ለሁለቱ ሎት ልጆቹ መታሰቢያ እንዲሆን ያዘጋጀው ይህ ቃለ-መጠይቅ፣ አባታዊ ምክሮቜንና አራት ዋና ዋና ዚሕይወት መልእክቶቜን ዚያዘ ነው።

ኀሪክ ዮን እንዲህ አለ:-

"ዛሬን ብቻ ኑሩ" ኀሪክ ባለፈው ጊዜ ላይ መቆዘም ትርፉ ፀፀት መሆኑንና ዚወደፊቱም ዚማይታወቅ በመሆኑ፣ ልጆቹ በያዙት ቅጜበትና በዛሬው ቀን ላይ ብቻ ትኩሚት አድርገው እንዲኖሩ መክሯል።

"ፍቅር ይያዛቜሁ" ፍቅር ዚግድ ኹሰው ጋር ብቻ መሆን እንደሌለበት ዹገለጾው ተዋናዩ፣ እርሱን በትወና ሕይወቱ ውስጥ ያጋጠሙትን አስ቞ጋሪ ፈተናዎቜ እንዲያልፍ ዚሚዳው ለሙያው ያለው ጥልቅ ፍቅር መሆኑን ጠቅሷል። "እናንተም ዚምታፈቅሩትን ነገር ፈልጉ" ሲልም አክሏል።

"ጓደኞቻቜሁን በጥንቃቄ ምሚጡ" እውነተኛ ጓደኞቜን ኚመሚጡ በኋላ ራስን አሳልፎ መስጠት እንደሚገባና እውነተኛ ጓደኞቜም በተመሳሳይ መልኩ ራሳ቞ውን አሳልፈው እንደሚሰጡ በቃለ-መጠይቁ አስገንዝቧል።

"እጅ አትስጡ" እስኚ መጚሚሻዋ ቅጜበት ድሚስ መታገል እንደሚገባ ዹገለጾው ኀሪክ፣ ዚጀናም ይሁን ሌላ ማንኛውም ዚሕይወት ቜግር ሲገጥም ለመሰበር መጣደፍ እንደሌለባ቞ውና በጜናት መታገል እንደሚገባ በስሜት ተውጩ ተናግሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀37👍9👏1
📌ዚአዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ፍቃድ ተሰሹዘ

ዚአዲስ ስታንዳርድ (Addis Standard) ዹበዹነ-መሚብ መገናኛ ብዙኃን ዚሥራ ፈቃድ መታገዱን ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል።

ኖር ሬድዮ እንደተመለኚተው ኹሆነ ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ኚአዲስ ስታንዳርድ ዹበዹነ-መሚብ መገናኛ ብዙኃን ጋር ዹነበሹው ዚምዝገባ ምስክር ወሚቀት ኚዛሬ ዚካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መሰሹዙን አስታውቋል።

ባለሥልጣኑ ለውሳኔው እንደ ምክንያት ያቀሚባ቞ው ነጥቊቜ ዚሚኚተሉት ናቾው፩

ሚዲያው ዚሚዲያ ሥነ-ምግባርንና ዚኢትዮጵያ ሕጎቜን ..ተጚማሪውን ያንብቡ:-
https://t.me/NorRadio1/141

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👎4👏3❀1
📌"ማስጠንቀቂያ ደርሶኝ አያውቅም "

አዲስ ስታንዳርድ ምላሜ ሰጠ 

ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ማምሻውን ፍቃዱ መሰሹዙን ዹገለጾው ዚአዲስ ስታንዳርድ ዹበዹነ-መሚብ መገናኛ ብዙኃን  ዋና አዘጋጅ ዮናስ ኚድር ባለስልጣኑ ያቀሚበውን ክስ ውድቅ አድርገዋል።

ዋና አዘጋጁ እንደገለጹትፀ ተቋሙ እስካሁን ድሚስ ምንም ዓይነት መደበኛ ዹሕግ ጥሰት እንደፈፀመ ዚሚያመለኚት ማስጠንቀቂያ ደርሶት እንደማያውቅ ኖር ሬድዮ ዘግቧል።

“አዲስ ስታንዳርድ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎቜ ደርሰውታል ዹሚለው ክስ ኚእውነት ዚራቀ ነው። ዚኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን ቀደም ሲል ስለነበሩ ዹሕግ ጥሰቶቜም ሆነ ስለተወሰዱ እርምጃዎቜ ለአዲስ ስታንዳርድ ዹዜና ክፍል በይፋ ያሳወቀው ነገር ዹለም” ብለዋል።

አክለውም ዚጋዜጣው አሳታሚ ዹሆነው ጃኬን ፐብሊሺንግ (JAKENN Publishing PLC) መብቱን ለማስኚበርና ዹሕግ ዚበላይነት መኚበሩን ለማሚጋገጥ ያሉትን ዹሕግ አማራጮቜ እዚገመገመ እንደሚገኝ áŒˆáˆáŒžá‹‹áˆá¢

ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አዲስ ስታንዳርድ ዹበዹነ-መሚብ መገናኛ ብዙኃን  “በሚዲያ ዘርፉ ላይ ዚሙያ ስነምግባር እና ዹሀገርና ዚህዝብ ብሔራዊ ጥቅም አክብሮ እንዲሰራ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ለመታሚም ፈቃደኛ አልሆነም” ሲል “በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሰሚት” ኚዛሬ ዚካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ  ፍቃዱ መሰሹዙን ገልጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6👍2
ዚባህል ጣዕም በቶቶት
ዹፆም ብፌ ድግስ ይጠብቃቜኋል!

​በኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቊቜ ዝግጅትና መስተንግዶ ስሙ ገኖ ዚሚጠራው ቶቶት ዚባህል ምግብ አዳራሜ፣ ለፆሙ ወቅት ልዩ ትኩሚት ዹሰጠ ዚብፌ ድግስ ይዞላቜሁ ቀርቧል። ለቀተሰብ፣ ለጓደኛሞቜ ወይም ለማንኛውም ድርጅታዊ ዝግጅት ምቹና ባህላዊ ድባብ ያለው ስፍራ ለሚፈልጉ ቶቶት ተመራጭ ነው።

​ለምን ቶቶትን ይመርጣሉ?

​ልዩ ዹፆም ብፌፊ
በልዩ ጣዕም ዹተዘጋጁ ዹፆም ምግቊቜ እንደ ልብዎ እንዲመገቡ ተኚሜነው ቀርበዋል።

​ሁልጊዜም ዝግጁ፩
ኹሰኞ እስኚ እሁድ ዚባህል ድግሱ አይቋሚጥም (ዚፍስክ አማራጮቜም እንደተጠበቁ ናቾው)።

​ባህላዊ ድባብፊ
ዚምግቡ ጣዕም ብቻ ሳይሆን ዚቊታው ድባብ ዚኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት በሚያንፀባርቅ መልኩ ዹተዋበ ነው።

ለበለጠ መሚጃ፣
ቊታ ለመያዝ ወይም ለትዕዛዝ በሚኚተሉት ስልኮቜ ይደውሉ፩

​📞 0116 46 07 18
​📞 0909 00 44 00

​ቶቶት — ዚኢትዮጵያ ባህልና ጣዕም መገናኛ!
❀10👍5
ዳናሜ ፊልም በናሆም መልቲሚዲያ !

በሲኒማ ቆይታው ብዙ ፍቅርና አድናቆት ያተሚፈው "ዳናሜ" ፊልም አሁን ኚአዲስ ጉልበት ጋር ወደ እናንተ ሊመለስ ነው።

ታዋቂው ተዋናይ ሄኖክ በሪሁን እና ኀደን አይሞሹም ዚተሳተፉበት፣ በአብርሃም ታደሰ ተፅፎና ተዘጋጅቶ ዹቀሹበው ድንቅ ዹፍቅር ፊልም—ዳናሜ!

🗓 መቌ?ፊ አርብ ዚካቲት 20

📍 ዚት?ፊ በናሆም መልቲሚዲያ (Nahom Multimedia) ዩቲዩብ ቻናል

ስሜት፣ ፍቅር እና አስደናቂ ትሚካ ዚተዋሃደበትን ይህን ፊልም ለማዚት ዝግጁ ናቜሁ? ቀኑን አትርሱ!

ፊልሙ ዚሚለቀቅበት ቻናል ሊንክ ይኾው

https://youtube.com/@nahommultimedia?si=YqGl8THSPt1GIv7D
❀8👍2👎2
📌 ዳናሜ ፊልም በናሆም መልቲሚዲያ ተለቀቀ

ታዋቂው ተዋናይ ሄኖክ በሪሁን እና ኀደን አይሞሹም ዚተሳተፉበት፣ በአብርሃም ታደሰ ተፅፎና ተዘጋጅቶ ዹቀሹበው ዳናሜ በናሆም መልቲሚዲያ ዚዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቋል።

ፊልሙን ይመልኚቱ ሊንክ ይኾው:-

https://youtu.be/Tyl5PGNU4Sc?si=PMhQENnEu--BrQSG
👍2
📌ዓድዋ ዚሥዕል አውደርዕይ

130ኛውን ዚዓድዋ ድል በዓልን በኪነ-ጥበብ ሥራዎቜ ለማዘኹር ዚታለሙ ሁለት ዚሥዕል አውደርዕዮቜ በጣይቱ ዚባህል እና ትምህርት ማዕኹል እንዲሁም በፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል በድምቀት ተኚፈቱ።

በጣይቱ ዚባህል እና ትምህርት ማዕኹል ኚሕብር ሰዓልያን ቡድን ጋር በመተባበር ዚተሰናዳውና "ዚድል አርማ" ዹተሰኘው 8ኛው ዝክሹ ዓድዋ ዚሥዕል አውደርዕይፀ ዚካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለተመልካቜ ክፍት ሆኗል። በዚህ አውደርዕይ ላይ ዚሕብር ሰዓልያን ቡድን አባላትና ተጋባዥ ታዋቂ ሰዓልያን ስለ ዓድዋ ድል፣ ስለ ኢትዮጵያዊነትና ስለ ጀግንነት ዚሳሏ቞ው ድንቅ ሥራዎቜ ዚቀሚቡ ሲሆን፣ አውደርዕዩ ለአንድ ወር ያህል ለጎብኚዎቜ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል።

በተመሳሳይ ዜና፣ ሐያት ሪጀንሲ ሆቮል በሚገኘው ዚፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል "ዓድዋ" ዹተሰኘ ሌላ ዚሥዕል አውደርዕይ ባሳለፍነው ዚካቲት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. ተኚፍቷል። ሰባት ታዋቂና ወጣት ሠዓሊያን ዚተሳተፉበት ይህ አውደርዕይፀ ዚድሉን ታላቅነት በሠዓሊያኑ ዚፈጠራ ክህሎትና ታሪካዊ እይታ በማጣመር ዹቀሹበ ድግስ ነው። ይህ አውደርዕይ እስኚ ዚካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ድሚስ ለተኚታታይ ሳምንታት ለጎብኚዎቜ ክፍት ሆኖ ዹሚቆይ ይሆናል።

ዚሁለቱም አውደርዕዮቜ አዘጋጆቜ እንደገለጹትፀ ዚዝግጅቶቹ ዋነኛ ዓላማ ዚዓድዋን ድል በሥነ-ጥበብ ሥራዎቜ በማዘኚር፣ ዚድሉን ፋይዳና ሀገራዊ ክብር ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሆነ ገልጞዋል።

For more: https://t.me/EventAddis1

For more: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀3👍2
📌ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ በሚራዎቜን አቋሹጠ

ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ በመካኚለኛው ምስራቅ ባለው ዚፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ወደ አንዳንድ ኚተሞቜ ዹሚደሹጉ በሚራዎቜን በጊዜያዊነት ዚሚያቋርጥ መሆኑን አስታውቋል።

በመካኚለኛው ምስራቅ ቀጠና በተቀሰቀሰው አለመሚጋጋት እና ዚፀጥታ ስጋት ፣ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ወደ አንዳንድ ኚተሞቜ ዚሚያደርጋ቞ውን በሚራዎቜ ለጊዜው ዚሚያቋርጥ መሆኑን አዹር መንገዱ አሚጋግጧል።

ዹአዹር መንገዱ ኹፍተኛ ሃላፊ " በክልሉ ባለው ዚፀጥታ ሁኔታ ምክንያት፣ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኚኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሜን ባለስልጣን እና ኚሚመለኚታ቞ው አውሮፕላን ማሚፊያዎቜ ካሉ ዚሲቪል አቪዬሜን ባለስልጣናት ጋር ዚሚመካኚር መሆኑን " ገልጞዋል።

በምክክሩም መሰሚት " በመሬት ላይ ያለውን ተጚባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ወደ አንዳንድ ዚመካኚለኛው ምስራቅ ኚተሞቜ ዚሚያደርገውን በሚራ ለጊዜው ያቋርጣል " ብለዋል።

በተጚማሪም " በአሁኑ ሰዓት፣ በመካኚለኛው ምስራቅ ቀጠና ውስጥ (በአውሮፕላን ማሚፊያ) ዹቆመ ምንም ዓይነት ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ አውሮፕላን ዹለም " ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4👍1
📌ሠዓሊና ቀራጺ በቀለ መኮንን ሀሳቡን ያጋራል

79ኛው ዙር አውደ ፋጎስ ዚውይይት መድሚክ ነገ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር በቀለ መኮንን(ፕ/ር) "ዚቶሪኖው ግብዣና ዚሚጀሰው ጠሹንጮዛ " በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያጋራል።ይህም ውይይት እሁድ ዚካቲት 22 2018 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቀተመዛግብት እና ቀተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሜ ውስጥ ይካሄዳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8👍5
📌“ኊዛና ምኒልክ” መፅሐፍ ላይ ውይይት አለ

በደራሲ ንጉሀ አዹለ ተካ ዚተፃፈው፣ ኹፍተኛ ምርምር ዚተደሚገበት "ኩዛና ምኒልክ" ዹተሰኘ መፅሐፍ ዛሬ ቅዳሜ  ዚካቲት 28 2018 ዓ.ም ኹቀኑ 4 ሰዓት በወመዘክር፡ ዚብላ቎ን ጌታ ህሩይ አዳራሜ ውይይት ይደሚጋል።

ኹዚህ ቀደም "ታላቁ ጥቁር" ዹተሰኘውን ኹፍተኛ ተነባቢነትን ያገኘ በዳግማዊ ምኒልክ ዙሪያ ላይ ያተኰሚ መፅሐፍ አሳትሞ ለንባብ ያቀሚበው ንጉሀ አዹለ አሁን ደግሞፀ ቀጣይ ክፍልፀ "ኩዛና ምኒልክን" ለንባብ አብቅቷል፡፡

"ኩዛና ምኒልክ" ስለ ዳግማዊ ምኒልክ ያልተነገሩ ዕውነታዎቜን  በዝርዝር ዚሚያስሚዳ ጥልቅ ዹምርምር ሥራ ሲሆን 460 ገፆቜንም ይዟል፡፡በተለይም ደግሞፀ ዚአድዋ ድልፀ በመላው ዓለም ለሚገኙ ጥቁሮቜፀ ዚባርነትና ዹቅኝ ግዛትን ቀንበር ለመስበር ለሚያደርጉት ተጋድሎ እንደ አንጞባራቂ ኮኚብ ሆኗቾው እንደነበር በዝርዝር ያትታል። በደቡባዊ አሜሪካ አገሮቜ ዹነበሹውን ሰፊ እንቅስቃሎ በስፋት ያሳያል።

ደራሲ ንጉሀ አዹለ ተካ ፣በሚኖርበት አሜሪካን አገርፀ በሚገኙ ታላላቅ ቀተ መጻሕፍት ውስጥ ጊዜውን በማሳለፍ አዳዲስ ዚታሪክ ዕውነቶቜን ለመጀመሪያ ጊዜ ለአንባቢ ፅፎ አቅርቧል።

ደራሲ ንጉሀ አዹለ ተካ፣ ኹዚህ ቀደም ሐኖስ ፣ዚገራዶ ዋሜንት፣ ጣዝማ እና ሌሎቜ 7 መጻሕፍትን ለንባብ ያበቃ ሲሆን በ1970ዎቹ አጋማሜ ኚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲፀ ዚኢትዮጵያ ቋንቋዎቜና ሥነ- ፅሑፍ ክፍልም ተመርቋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7👍2
📌ዚኢትዮጵያውያን ሠዓልያን ሥራ ዚት ገባ?

አዘርባጃን ኀምባሲ ላይ ዹቀሹበው ቅሬታ

በኢትዮጵያ ዹሚገኘው ዚአዘርባጃን ኀምባሲ፣ ኚዛሬ አንድ ዓመት ተኩል በፊት ለውድድርና ለአውደ ርዕይ በሚል ዚወሰዳ቞ውን ዚኢትዮጵያውያን ሠዓልያን ዚፈጠራ ሥራዎቜን አልመለሰም ስለመባሉ ተዘገበ።

ኀምባሲው ኹአለላ መልቲሚዲያ እና ኹፕላንና ልማት ሚኒስ቎ር ጋር በመተባበር "ተጓዥ ኪነ-ጥበባት" በሚል ዹሰዹመውንና በአዹር ንብሚት ለውጥ ላይ ግንዛቀ ለመፍጠር ያለመ ውድድር ማዘጋጀቱ ይታወሳል።

በውድድሩም 17 ኢትዮጵያውያን ሠዓልያን ዚተሳተፉ ሲሆን፣ አሾናፊ ለሚሆኑ አራት ባለሙያዎቜ ዚገንዘብ ሜልማትና ወደ አዘርባጃን ዹጉዞ ዕድል ቃል ተገብቶላ቞ው እንደነበር ተገልጿል።

ይሁንና አሾናፊ ያልሆኑ ሠዓልያን ሥራዎቻ቞ው እንዲመለሱላ቞ው ደጋግመው ቢጠይቁም ምላሜ አለማግኘታ቞ውን ገልጞዋል። ኹነዚህም መካኚል አርቲስት ምህሚቱ ዋሎ፣ በአዝራር ዚሰራው ዹኔልሰን ማንዮላ ምስል ያለፈቃዱ ለአፍሪካ ህብሚት ኮሚሜን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት በስጊታ መበርኚቱን በሚዲያ መመልኚቱን በመጥቀስ ቅሬታውን አቅርቧል።

አሾናፊ ተብለው ዚተለዩት ሠዓልያንም ቢሆኑ ዚተገባላ቞ው ዚገንዘብ ሜልማትም ሆነ ዹጉዞ ዕድል እስካሁን አልተፈጞመላ቞ውም።

ሠዓልያኑ ሥራዎቻ቞ውን በራሳ቞ው ወጪ ማዘጋጀታ቞ውን ጠቅሰው፣ ዚፈጠራ ውጀቶቻ቞ው ያለ እውቅና ለሊስተኛ ወገን መሰጠታ቞ው "ማጭበርበር ነው" ሲሉ ተናገሚዋል።

ኀምባሲውን ለማነጋገር ቢሞክርም፣ ኀምባሲው ጥያቄውን ወደ አለላ መልቲሚዲያ መርቷል። ዹአለላ መልቲሚዲያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አደራጀው አስፋው በበኩላ቞ው ድርጅታ቞ው ሥራዎቹን በአዘርባጃን ለነበሹው "ኮፕ 29" ጉባኀ ዚመውሰድ ዕቅድ እንደነበሚ አስሚድተዋል።ነገር ሀሳብ አልተሳካም።

©መሠሚት ሚዲያ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀5🀔4🀬1
📌ዚሙዚቀኛ ጣሰው ወንድም ዚዋሜንት አልበም

በመሶብ ባህላዊ ዹሙዚቃ ባንድ ውስጥ በዋሜንት ተጫዋቜነቱ ዹምናውቀው ጣሰው ወንድም "ምናባዊ" ቁጥር ሁለት ዹተሰኘ ዚዋሜንት ዹሙዚቃ አልበሙን ዛሬ ለአድማጮቜ ያቀርባል።

ዹ"ምናባዊ" ቁጥር ሁለት አልበም ምርቃቱና ዹሙዚቃ ዝግጅቱ ዛሬ ዚካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ኚምሜቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በሞሶብ ዹሙዚቃ ማዕኹል በደመቀ ሁኔታ እንደሚኚናወን ተገልጿል።

በዚህ ዹሙዚቃ ምሜት ላይ ሙዚቀኛ ጣሰው ወንድም በዋሜንት ጥበቡ ታዳሚውን ዚሚያዝናና ሲሆን፣ ስመ-ጥሩው ዚፒያኖ ተጫዋቜ አብይ ወልደማርያምም አብሮት በመሆን ጥበባዊ ስራዎቹን እንደሚያቀርብ ተገልጿል።

ዝግጅቱ ዚኢትዮጵያን ባህላዊ ዚዋሜንት ዜማ ኹዘመናዊ ዹሙዚቃ ቅንብር ጋር አዋህዶ ዚሚያቀርብ እንደሆነም ይጠበቃል።

"ምናባዊ "ቁጥር ሁለት ለኢትዮጵያ ዹሙዚቃ ዘርፍ አዲስ ዚጥበብ ቀለም እንደሚጚምር ተነግሮለታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8👍2🙏1
📌"ዐውደ ፋጎስ" ዚውይይት መሰናዶ ነገ ይካሄዳል

ዚዕውቀትና ዚውይይት መድሚክ "ዐውደ ፋጎስ" 80ኛ ዙር ዝግጅቱን ነገ እሁድ ዚካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በሥነ-አመክንዮ ርዕሰ-ጉዳይ ላይ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።

በዕለቱ ዚሥነ-አመክንዮ መጜሐፍ አዘጋጅ ዚሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ትንታኔና ዚመነሻ ጜሑፍ ለታዳሚው ዚሚያቀርቡ ይሆናል።

መድሚኩ በአገራቜን ዚምሁራን ውይይት ባህልን ለማሳደግና ሹቂቅ ዹሆኑ ዚፍልስፍናና ዚዕውቀት ዘርፎቜን ለሰፊው ማህበሚሰብ ተደራሜ ለማድሚግ አልሞ ዚሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል።

ይህ መርሃ-ግብር ነገ ኹቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀተ-መዛግብትና ቀተ-መጻሕፍት (ወመዘክር) በሚገኘው በመርስዔ ኃዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሜ ዹሚኹናወን ሲሆን፣ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜና ዚጥበብ አፍቃሪያን በሰዓቱ ተገኝተው እንዲሳተፉ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3👍2
ዹዓለማዹሁ ገላጋይ አዲስ መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው

በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ-ጜሑፍ ውስጥ በሥራዎቹ ስም ያተሚፈው ደራሲ ዓለማዹሁ ገላጋይ፣ "ፈሪሳ" በሚል ርዕስ ያዘጋጀው አዲስ መጜሐፍ በቅርቡ ለንባብ እንደሚበቃ ኀቚንት አዲሰሰ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመልክታል።

ይህ አዲስ መጜሐፍ ለደራሲው አሥሚኛ ዚልብ-ወለድ ሥራው መሆኑ ተገልጿል። ደራሲ ዓለማዹሁ ገላጋይ ኹዚህ ቀደም "ወሪሳ"፣ "በፍቅር ስም"፣ "ታለ በእውቀት ስም"፣ "ሀሰተኛው በእምነት ስም" እና "ውልብታ"ን ዚመሳሰሉ በአንባቢያን ዘንድ ኹፍተኛ ተወዳጅነትን ያተሚፉ ዚልብ-ወለድ መጻሕፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል።

አዲሱ መጜሐፍ "ፈሪሳ" ምን ዓይነት ጭብጥና ዚሥነ-ጜሑፍ ጣዕም ይዞ እንደሚመጣ በጉጉት እዚተጠበቀ ሲሆን፣ በቅርቡ ለገበያ እንደሚቀርብ ሰምተናል።

ደራሲው በሹቂቅ ዹቋንቋ አጠቃቀሙና በጥልቅ ማህበራዊ ትቜቶቹ ዚሚታወቅ በመሆኑ፣ ይህ አሥሚኛ ሥራው በሥነ-ጜሑፍ አፍቃሪያን ዘንድ ትልቅ ትኩሚት ስቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀23👍3🥰2🀗2👎1🙏1
📌ኢዜማ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋን ኚመሪነት አሰናበተ

አዜማ ፓርቲ በዛሬው ዕለት ባካሄደው አስ቞ኳይ ስብሰባ ዹ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማኒፌስቶውን ያስተዋወቀ ሲሆን፥ በቀጣይ ዚሚመራበትን 50 ፖሊሲዎቜንም ለአባላቱ ይፋ አድርጓል፡፡

ፖሊሲዎቹ በተለይም በሀገር መንግስት ግንባታ፣ በብሔራዊ ጥቅም፣ ልማትና ኢኮኖሚ እንዲሁም በአካታቜነትና ሌሎቜ ጉዳዮቜ ላይ ዚሚያተኩሩ መሆናቾው ተገልጿል፡፡

ኢዜማ በአስ቞ኳይ ስብሰባው በቀጣይ መሪውን መርጧል...ተጚማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/154


ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3😁2
📌“ሄር ስቶሪ” ዚሥዕል አውደርዕይ ተኹፈተ

“ሄር ስቶሪ” ዹተሰኘ ዚጋራ ዚሥነ-ጥበብ ዐውደርዕይ ባሳለፍነው ቅዳሜ ዚካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ዘ ስፔስ ኢትዮጵያ” ጋለሪ ውስጥ áˆˆá‰°áˆ˜áˆáŠ«á‰Ÿá‰œ ክፍት ሆኗል። እስኚ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድሚስም ይቆያል።

ዓለም አቀፍ ዚሎቶቜ ቀንን ምክንያት በማድሚግ በተዘጋጀው በዚህ ዐውደርዕይ ላይፀ አሌክሳንድራ ምትኩ፣ ብሌን ደሚሰ፣ ፍቅርተ አያና፣ ምሕሚት እሞቱ፣ ኒና ኡርጌሳ፣ ራፋኀላ ፍቃዱ፣ ሩት አስክንድር እና ሩት ጌታ቞ው ዚፈጠራ ሥራዎቻ቞ውን ለታዳሚ አቅሚበዋል።

ይህ ዐውደርዕይ ለቀድሞዋ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ መታሰቢያነት ዹተበሹኹተ መሆኑ ተነግሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7👍1🙏1
📌"ዥዋዥዌ ዚአዲስ አበባ መድበል"

ዓለም አቀፍ ዚሎቶቜ ቀንን ምክንያት በማድሚግ ስድስት ሎት ኚያንያን ሥራዎቻ቞ውን ዚሚያቀርቡበት "ዥዋዥዌ - ዚአዲስ አበባ መድበል" ዹተሰኘ ልዩ ዚሥነ-ጥበብ ዐውደ-ርዕይ በመጪው ቅዳሜ መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚኚፈት ተገለጠ።

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ፣ ብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሎ ሥነ-ጥበባት ማዕኹል ዹሚቀርበው ይህ ዐውደ-ርእይፀ በታዋቂዋ ፎቶ አንሺ ማህደር ኃይለሥላሎ አሰናጅነት ዹተዘጋጀ ነው። በኀግዚቢሜኑ ላይ ሳሌም መኩሪያ፣ ዓይናለም ገብሚማርያም፣ ጜዮን ኃይለሥላሎ፣ ሄለን ዘሩ፣ ነፃነት ገብሚሚካኀል እና ማህደር ኃይለሥላሎ ኚአዲስ አበባ ኹተማ ጋር ያላ቞ውን ዹግል እና ዚጋራ ትስስር በፈጠራ ሥራዎቻ቞ው ዚሚዳስሱበት ይሆናል።

ዚሥነ-ጥበባት ማዕኹሉ እንዳስታወቀው፣ ዹዐውደ-ርእዩ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ቅዳሜ ኹቀኑ 8፡30 ላይ ዹሚኹናወን ሲሆን ማንኛውም ዚጥበብ አፍቃሪ በዝግጅቱ ላይ እንዲታደም ግብዣ ቀርቧል።

ማዕኹሉ ዹሚገኘው በጉለሌ ክፍለ ኚተማ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው ዚኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንደሆነ ታውቋል።

ይህ ዐውደ-ርእይ በሎቶቜ ላይ ትኩሚት ኚማድሚጉም ባለፈ፣ ዚአዲስ አበባን ሁለንተናዊ ገጜታ በሎት ኚያንያን እይታ ለመመልኚት ዕድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3
📌 "ሐሹግ" ቎አትር ወደ መድሚክ ተመለሰ

ተቋርጩ ዹነበሹውና "ሐሹግ" ዹተሰኘው ዚአንድ ሰው ዹሙሉ ጊዜ ተውኔት ዛሬ አመሻሹን በድጋሚ ወደ መድሚክ እንደሚመለስ አዘጋጆቹ ለኀቚንት ሚዲያ አስታውቀዋል።

ይህ በደራሲና አዘጋጅ ክብይናድ አሰፋ ዹተዘጋጀው ተውኔትፀ በትያትር አፍቃሪያን ዘንድ ኹፍተኛ አድናቆትን ያተሚፈ ሲሆን፣ አሁን ላይ በቋሚነት ለዕይታ ዝግጁ መሆኑ ተሚጋግጧል።

ተውኔቱ ዘወትር ማክሰኞ ኹቀኑ 11፡30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ለታዳሚ እንደሚቀርብ ታውቋል።

በአንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር መድሚክ ላይ በሚቀርበው በዚህ ሥራ፣ ተዋናይት ሃና ጌትነት በብ቞ኝነት ትተውናለቜ።

ዚዝግጅቱ አስተባባሪዎቜ እንደገለጹት፣ ተውኔቱ ማህበራዊና ስነ-ልቩናዊ ጉዳዮቜን በጥልቀት ዚሚዳስስ ሲሆን፣ በትያትር ጥበብ ውስጥ ኹፍተኛ አቅም ዹሚጠይቀውን ዚአንድ ሰው ትወና በልዩ ሁኔታ እንደሚያቀርብ ተገልጿል።

ማንኛውም ዚጥበብ አፍቃሪ ዘወትር ማክሰኞ በብሔራዊ ቎አትር በመገኘት ዝግጅቱን መታደም እንደሚቜል ተመልክቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6
📌ዚ35 ሚሊዮን ብር ልዩነት በአንድ ዓመት ብቻ ?

ዘንድሮ ኢትዮጵያ ፕሪምዚር ሊግ አሾናፊ ሜልማቱ ስንት ነው?

በዘንድሮው ዚኢትዮጵያ ፕሪምዚር ሊግ ተሳታፊ ዹሆኑ ክለቊቜ ዚሚያገኙት ዚሜልማት እና ዚጥቅማጥቅም መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር እጅግ ዹወሹደ መሆኑ ተሰማ።

ዹሊጉን ዚሥርጭት መብት ዹወሰደው ኊቢኀን (OBN) ቎ሌቪዥን ለኢትዮጵያ ፕሪምዚር ሊግ አክሲዮን ማህበር በዓመቱ መጚሚሻ ዹሚኹፍለው ጠቅላላ ክፍያ 200 ሚሊዮን ብር ብቻ መሆኑ ተገልጿል። ይህም በሊጉ ተሳታፊ ዹሆኑ 16 ክለቊቜ ዚሚያገኙትን ዚገቢ ድርሻ በኹፍተኛ ሁኔታ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።

ባለፈው ዚውድድር ዘመን ዚዲኀስቲቪ (DSTV) ዚሥርጭት ስምምነት በነበሚበት ወቅት፣ ለክለቊቜ ዹተኹፋፈለው ዚገንዘብ መጠን 406 ሚሊዮን ብር ዹነበሹ ሲሆንፀ ዘንድሮ ግን ይህ መጠን ኹ50 ሚሊዮን ብር በታቜ ሊወርድ እንደሚቜል ተመልክቷል።

ዚሜልማት መጠኑን አስመልክቶ በወጣው መሹጃ መሠሚትፀ ባለፈው ዓመት ዹሊጉ ሻምፒዮን ዹሆነው ኢትዮጵያ መድን 40 ሚሊዮን ብር ዹተሾለመ ቢሆንም፣ ዚዘንድሮው ዹሊጉ አሾናፊ ግን ...ተጚማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/156


ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀2👍2😁1
📌እንዳልክ አሰፋ ትቜት ቀሚበበት

ዹ"ዕርቅ ማዕድ" ፕሮግራም አዘጋጅ ዹነበሹው እንዳልክ አሰፋ፣ በቅርቡ በዩቲዩብ ቻናሉ ባቀሚበው ዝግጅት ዚባለታሪኮቜን ሰብአዊ ክብር ዚሚነኩ አቀራሚቊቜን ተጠቅሟል በሚል ኚጋዜጠኞቜና ኚሰብአዊ መብት ተሟጋ቟ቜ ጥብቅ ትቜት እዚቀሚበበት ይገኛል።

ትቜቱን ካቀሚቡት መካኚል ጋዜጠኛ ቃልኪዳን እና እመቀት ደመቀ ዚሚጠቀሱ ሲሆን፣ ጋዜጠኛው በፕሮግራሙ ላይ ዚቀሚቡ ሁለት ሎቶቜን ፊት ለፊት በማጋጠም እርስ በእርስ እንዲናናቁና እንዲሰዳደቡ መንገድ ኚፍቷል ሲሉ ወቅሰዋል።

በተለይም ዚሊስት ልጆቜ እናት ዚሆነቜን ባለታሪክ “ራስሜን አትጠብቂም፣ ዝርክርክ ነሜ” ዹሚሉ ዹግል ክብሯን ዚሚነኩ ንግግሮቜን በአደባባይ በማንሳቱ፣ ዝግጅቱ ኹዕርቅ ይልቅ ዚሞራል ስብራትን ዚሚያስኚትል ነው ተብሏል።

ተቺዎቹ አክለውም፣ ጋዜጠኛው ዚዲኀንኀ (DNA) ምርመራ ውጀቶቜን እንደ ውድድር ውጀት “ልብ አንጠልጣይ” ለማድሚግ ጊዜ መውሰዱ እና በሰው ስቃይ ....ተጚማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/159

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍8😁5❀4👎1👏1