Event Addis Media
9.49K subscribers
6.26K photos
14 videos
4 files
4.87K links
Connect with Addis artistic community!

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ዚነፃነት ወርቅነህ ሥርዓተ ቀብር ተፈጾመ

ዚአርቲስት ነፃነት ወርቅነት ዚቀብር ስነስርዓት በመንበሹ ጞባኊት ቅድስት ሥላሎ ካ቎ድራል ተፈጜሟል።

በድንገት ላጣነው አርቲስት ነፃነት ወርቅነት ሜኝት ኚለቀስተኞቜ ኹ2000 በላይ ዚአበባ ጉንጉን መቅሚቡን ዚኢቢኀሱ ተወዳጁ ጋዜጠኛ ዮናስ ኹበደ ተናግሚዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
💔27😭7❀2🕊1
አልጄሪያዊያን አይሟው ስፒድን ደብድበው አባሚዋል

አሜሪካዊው ዩቲዩበር ስፒድ ወደ አልጄሪያ አምርቶ ያልጠበቀው ነገር ገጥሞታል።

ስፒድ በአልጄሪያ ጚዋታ ለመመልኚት ስታዲዚም ዚገባ ቢሆንም ደጋፊዎቜ በቁሳቁስ.. ተጚማሪውን ያንብቡ:https://t.me/NorRadio1/44
😁36❀6💔4👏2
📌በኮዬ ፈጬ ዚኚተራ በዓልን ሲያስተባበሩ ዚነበሩ 4 ወጣቶቜ በኀሌክትሪክ አደጋ ሕይወታ቞ው አለፈ

በሾገር ኹተማ አስተዳደር፣ በኮዬ ፈጬ ክፍለ ኹተማ በሚገኘው ዚፋንታ መድኃኔዓለም ደብር ዚጥምቀት ኚተራ በዓልን ሲያኚብሩ እና ሲያስተባብሩ ዚነበሩ አራት ወጣቶቜ በኀሌክትሪክ አደጋ ሕይወታ቞ው ማለፉ ተሰማ።

ወጣቶቹ በበዓሉ ላይ እያገለገሉ እያለ ባጋጠመ ዚኀሌክትሪክ አደጋ ሕይወታ቞ውን ማጣታ቞ውን ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ይህንኑ መርዶ ተኚትሎ፣ ለሐዋርያዊ አገልግሎት በጎንደር ሀገሹ ስብኚት ዹሚገኙ ዚቀተክርስቲያኗ አመራሮቜ ዹተሰማቾውን ጥልቅ ሐዘን ገልጞዋል።

ሀገሹ ስብኚቱ ባስተላለፈው ዹሐዘን መግለጫ "ወጣት ልጆቻቜን በበዓል ዕለት ሕይወታ቞ውን ማጣታ቞ው ታላቅ ሐዘን ፈጥሮብናል" ሲሉ ገልጞዋልፀ ለሟቜ ቀተሰቊቜና ወዳጅ ዘመዶቜ ልዑል እግዚአብሔር መጜናናትን እንዲሰጥ፣ ለወጣቶቹም ነፍስ ዕሚፍትን እንዲሰጥ ጞሎት አድርገዋል።

በአሁኑ ወቅት ዹአደጋው መንስኀ በዝርዝር እዚተጣራ ሲሆን፣ ክስተቱ በምዕመናንና በአካባቢው ነዋሪዎቜ ዘንድ ኹፍተኛ ድንጋጀንና ሐዘንን ፈጥሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢28❀4😭2
📌"ሞትን እንደ ገቢ፣ ሐዘንን እንደ ካሜራ ማሞቂያ"
ዚመቅደስ ደበሳይ አነጋጋሪ ጜሑፍ

ታዋቂዋ ዚፕሮግራም አቅራቢ መቅደስ ደበይሳ፣ በወቅታዊ ዚሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያላትን ትዝብት በማካፈል ዚአባይ ቎ሌቪዥንን አርአያነት ያለው ተግባር አደነቀቜ።

ጋዜጠኛዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጿ ባስተላለፈቜው መልእክት፣ በዘመናቜን "ሞትን እንደ ገቢ፣ ሐዘንን እንደ ካሜራ ማሞቂያ እንዲሁም ዚሞት ስርጭትን እንደ ብ቞ኛ ገቢ" ዚሚቆጥሩ አካላት መበራኚታ቞ውን በምሬት ገልጻለቜ።

ይህ ንግግሯ በበርካታ ዚሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎቜ ዘንድ ኹፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቶ እዚተጋራ ይገኛል።

መቅደስ ደበይሳ ይህን አስተያዚት ዚሰጠቜው፣ አባይ ቎ሌቪዥን ሕይወቱ ላለፈው ድንቅ ዚጥበብ ሰው ነፃነት ወርቅነህ ዹሰጠውን ክብር ተኚትሎ ነው።

ጣቢያው በታዋቂው አርቲስት ህልፈት ምክንያት "በእሁድ ዚዝግጅት ክፍለ ጊዜያቜን ምንም ዓይነት ዚደስታ ፕሮግራም አይተላለፍም" ሲል መወሰኑን ለፕሮግራም አቅራቢዋ በስልክ ማሳወቁን ጜፋለቜ።

ይህ ዚጣቢያው ውሳኔ ኚገንዘብ ትርፍ ይልቅ ለሰው ልጅ ክብርና ለጥበብ ሰው ዚታዚ ሙያዊ ስነ-ምግባር መሆኑን መቅደስ ገልጻለቜ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏25❀12👍1👎1
📌ሁለገቡ ዚጥበብ ሰው ተፈሪ አለሙ ነገ ይኚበራል

ለሁለገቡ ዚጥበብና ዚሚዲያ ሰው ተፈሪ አለሙ ዚክብርና ዹዕውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቶለታል።

በብሬማን ፊልም ፕሮዳክሜን እና በፋና ፕላስ ቲቪ ትብብር ዹተዘጋጀው ይህ ልዩ ዚክብር ዝግጅትፀ ነገ ኹቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እስኚ ምሜቱ 1:00 ሰዓት ድሚስ በፋና ቎ሌቪዥን ይተላለፋል።

በዝግጅቱም ላይ ለታላቁ ተዋናይ ዚክብር ካባ ዚሚደሚብለት ሲሆን፣ እስካሁን በዘርፉ ለሰጣ቞ው ስራዎቜም ተገቢው ምስጋናና ክብር ይቀርብለታል።

አንጋፋው ተዋናይ ተፈሪ አለሙ በበርካታ ፊልሞቜና ድራማዎቜ ላይ ባሳዚው ድንቅ ብቃት በኢትዮጵያውያን ዘንድ እጅግ ዚሚወደድና ዹሚኹበር ዚጥበብ ሰው መሆኑ ይታወቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
🔥19❀14👍5👏2
📌ዚይሁኔ "ዘ-ገሊላ" ሙዚቃ 22 ዓመት ሞላው

ጥር በባተ ኚአስሚኛው ቀን ጀምሮ ይሁኔ በላይ ያቀነቀነው ዘመን አይሜሬው ዹ“ዘገሊላ” ሙዚቃ ተደጋግሞ ይደመጣል።

ዚጥምቀት አኚባበርን በሙዚቃው ኚባህልና ትውፊቱ ጋር አቆራኝተው አቀል መልካሙ ግጥሙን፣ አስቻለው አዹለ ዜማውን፣ ዳዊት ጥላሁን ደግሞ ቅንብሩን ሰርተውታል።

ሙዚቃው ኚሃይማኖታዊው አኚባበር ፈንጠር ብሎ ዚሚታዚውን ባህላዊ ትርዒት በደንብ ዚሚያሳይ ነው። ዚጥምቀት በዓል ሰበብ ሆኗቾው ለተጫጩም ሙዚቃው ድንቅ መዘክር ሆኗል።

ዚበርካቶቻቜን ትዝታ ዹሆነውና ዚጥምቀት ሰሞን ዚ቎ሌቪዥንና ሬድዮ ጣቢያዎቜ ዚሚቀባበሉት ዚድምጻዊ ይሁኔ በላይ  "ዘ-ገሊላ" ሙዚቃ እድሜን ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ሲያጣራ ለካ ዘንድሮ ድፍን 22 ዓመት ሞልቶታል።

"ወርዉሬ መታሁት ጥላሜን በእምቧይ፣
ደሞ ባንቜ በኔ ኚልካይ አለን ወይ።
ወደ አንቜ ስመጣ ተመለስ ዚሚለኝ፣
ማን ይሆን ወገኛዉ ዚሚኚለክለኝ።
***
ወንዞ አይፈሬዉ ቀሚስ ዚተሞነሞነዉ፣
ትፍትፉ መቀነት ወገቧን ዚዞሚዉ፣
ልቀን በጉንፏ አዉሎ አሳደሚዉ።
***
እንኳን ዛጎል ማርዳዉ አምባሩም መስቀሉ፣
ሜርብት አደሬ  ማተብሜ ድንግሉ፣
አንቜን ለማሳመር መቜ አነሰ ባሉ።"

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀36👏3🔥1🎉1
📌"በኢትዮጵያ 309 ፍቃድ ያላ቞ው ሚዲያዎቜ አሉ"

በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በህጋዊ መንገድ ፈቃድና ምዝገባ አግኝተዉ ዚሚንቀሳቀሱ ዚብሮድካስት፣ ዹበይነ መሚብ፣ ዚህትመት እና ዹዉጭ መገናኛ ብዙኃን ቁጥር 309 እንደደሚሰ ተነገሚ።

በዚህም መሰሚት 175 ዚብሮድካስት፣ 20 ዚህትመት፣ 35 ዹዉጭ ሚዲያ ክሮስፖንዳንት፣ 73 ዚበይነመሚብ፣ አምስት ዚክፍያ ኢንተርኔት ብሮድካስት፣ አንድ ነፃ ዚኢንተርኔት ብሮድካስት መገናኛ ብዙኃን በባለሥልጣኑ ምዝገባ እና ፈቃድ አግኝተዉ እዚተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ኖር ሬድዮ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል፡፡ ኚእነዚህም ውስጥ 254ቱ በስርጭት ላይ ዹሚገኙ ሲሆንፀ 55ቱ ደግሞ በዝግጅት ላይ ናቾው ተብሏል።

በባለሥልጣኑ ባለፉት ስድስት ወራትም ለ39 ዹመገናኛ ብዙኃን በፍቃድና ክትትል ዘርፍ ዚፍቃድ እና ዚብቃት ማሚጋገጫ ሰርተፍኬት አገልግሎት እንደተሰጠም ሰምተናል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7
📌ዋቢ ሾበሌ ሆቮል ተሾጠ

ኚአዲስአበባ ቀደምት ዘመናዊ ሆ቎ሎቜ መካኚል አንዱ ዹሆነው ዋቢ ሾበሌ በዛሬው ዕለት ለሚድሮክ ኢንቚስትመንት ግሩፕ ተሜጧል።

ስምምነቱን ዚሚድሮክ ኢንቚስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድና ዚዋቢ ሾበሌ ሆቮል አክሲዮን ማህበር ዚቊርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን ተፈራርመዋል።

አቶ ጀማል አሕመድ ዹሆቮሉን አገልግሎት በዘርፉ አለም በደሚሰበት ደሹጃ በማዘመን ለእንግዶቜ ምቹና ጥራቱን ዹጠበቀ ዚማሚፊያ ቊታ ለማድሚግ እንደሚሰራ ተናግሚዋል።

ዚዋቀ ሾበሌ ሆቮል ዚቊርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን ዹሆቮሉን ታሪክ ጠብቆ በማዘመን ለትዉልድ ለማሻገር በመስማማቱ ለሚድሮክ ኢንቚስትመንት ግሩፕ ምስጋና቞ውን አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ  32ኛውን  ዹዓለም  ዹአዹር ንብሚት  ለውጥ ጉባኀ ለማዘጋጀት መመሹጧን ተኚትሎ ሚድሮክ  ለተሳታፊዎቜ  ኚሚሰራ቞ው ሆ቎ሎቜ አንዱ ሲሆን ዘመናዊና ቅንጡ በሆነ መልኩ ዚማሪዮት ደሹጃን (autograph collection by Marriot ) ጠብቆ ዚሚታደስ መሆኑን ሚድሮክ ኢትዮጵያ አስታውቋል ።

ዋቢ ሾበሌ ሆቮል በ1960 ዓም ስራ መጀመሩ ይታወሳል። ሆቮሉ በድንገተኛ ዚመኪና አደጋ ህይወታ቞ው ላለፈው ዹልዑል መኮንን ልጆቜ ዚገቢምንጭ እንዲሆን ንጉስ ሃይለስላሎ ማስገንባታ቞ው ይነገራል ።

ሆቮሉን ደርግ ኹወሹሰው በኋላ በዘመነ ኢህአዎግ ለእነ ልዑል በዕደማርያም መኮንን መመለሱ ይታወሳል ።

©ስዩም ፍቃዱ ( ሁሉ አዲስ)

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀22🀔6👍4🔥2👎1
📌ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ማስታወቂያ አውጥቷል

ሚዲያው ሪፖርተር ይፈልጋል!

​ዚኢትዮጵያ ኢንሳይደር አሳታሚ ዹሆነው ሀቅ ሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሜንፀ በተለያዩ ዚስራ መደቊቜ ላይ ሰራተኞቜን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

በዚህም ተፈላጊ ዚሥራ መስኮቜ ፊ

​1. ሪፖርተር (አዲስ አበባ)

- በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ ዚማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ዚመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት ዚስራ ልምድ ያለው/ላት።

- ​አማርኛ እና ኊሮምኛ ቋንቋዎቜን አቀላጥፎ መናገር ዚሚቜል/ዚምትቜል።

​2. ሪፖርተር (ባህር ዳር)

​- በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ ዚማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ዚመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት ዚስራ ልምድ ያለው/ላት።

- ​ባህር ዳር ኹተማ ዹሚኖር/ዚምትኖር።

​3. ሪፖርተር (ድሬዳዋ ወይም ሀሹር)

​- በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ ዚማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ዚመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት ዚስራ ያለው/ላት።

- ​ኹአማርኛ በተጚማሪ ሌሎቜ ዚአካባቢው ቋንቋዎቜን መናገር መቻል ተመራጭነት አለው።

​4. ኊዲዮ ቪዥዋል ኀዲተር
​
በኢንፎግራፊክስ እና ቪዲዮ ኀዲቲንግ ስልጠና ዹወሰደ/ቜ እና ቢያንስ ዹ1 ዓመት ዚስራ ልምድ ያለው/ያላት።

በምርጫ ዘገባዎቜ ላይ ቀደምት ልምድ ያላ቞ው አመልካ቟ቜ በኹፍተኛ ሁኔታ ይበሚታታሉ።

​አመልካ቟ቜ ዚትምህርት እና ዚስራ ልምድ ማስሚጃቜሁን (CV) በ recruitment@ethiopiainsider.com ኢሜይል አድራሻ መላክ ይጠበቅባቜኋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8
📌ታዋቂዋ ዚውበት ባለሙያ ትርሀስ (቎ሪ) አሚፈቜ

በኢትዮጵያ ዚውበትና ዹፀጉር ስታይል ዘርፍ ስሟ በጉልህ ዚሚነሳውና በቅርብ ወዳጆቿ "቎ሪ" በሚል ቅጜል ስም ዚምትታወቀው ዚውበት ባለሙያ ትርሀስ ኹዚህ ዓለም በሞት መለዚቷ ተሰማ።

ባለሙያዋ በአዲስ አበባ ደንበል ሲቲ ሮንተር "ሞሮኮ ባዝ" (Morocco Bath) ዹተሰኘውን ዘመናዊ ዚውበት መጠበቂያ ማዕኹል በመክፈትና ዘመናዊ ዹፀጉር አሰራርና ዚሜካፕ ጥበብን በማስተዋወቅ ሚገድ ፈር ቀዳጅ ኚሆኑት ባለሙያዎቜ መካኚል አንዷ ነበሚቜ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
💔14😢3❀2🕊1
📌ዚኢትዮጵያ ሰርክስ ቡድን በፈሚንሳይ ድል ቀናው

በዹኔነህ ተስፋዬ ማናጀርነት እና በአሰልጣኝ ክብሮም ወልደሳሙኀል ዚሚመራው "ትሩፕ ኮልፌ" (ዚቢጣ ሰርኚስ ቡድን) በፈሚንሳይ በተካሄደው 48ኛው ዹሞንቮ ካርሎ ዓለም አቀፍ ዚሰርኚስ ፌስቲቫል ላይ በመሳተፍ ዚብር ሜዳሊያ አሾናፊ እንደሆነ ኖር ሬድዮ ዘግቧል።

ዚዓለማቜን ታዋቂ ዚሰርኚስ አርቲስቶቜ ዚሚሳተፉበት ተብሎ በሚታወቀው በዚህ ክብሚ በዓል ላይ ቡድኑ ያስመዘገበው ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ትልቅ ኩራት ሆኗል።በዚህ ፌስቲቫል ላይ ትሩፕ ኮልፌ ያገኘው ዚብር ሜዳሊያ፣ ዚኢትዮጵያን ዚሰርኚስ ጥበብ በዓለም አቀፍ መድሚክ ኹፍ ያደሚገ ውጀት መሆኑ ተገልጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀22❀‍🔥2🥰1👏1
📌ዚራሱን ዚቀብር ሥነ-ሥርዓት ያኚናወነው ብራዚላዊ

በብራዚል ኩሪቲባ ኹተማ ዹሚኖር አንድ ግለሰብ ዚጓደኞቹንና ዚዘመዶቹን ታማኝነት ለመፈተን ሲል ዚራሱን ዚሐሰት ሞት አውጆ ዚቀብር ሥነ-ሥርዓት ማኹናወኑ መነጋገሪያ ሆኗል።

ባልታዛር ሌሞስ ዚተባለው ዹ60 ዓመት ግለሰብ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ለሕክምና ሆስፒታል መግባቱን ዚሚገልጜ ፎቶግራፍ ኹለጠፈ ኚጥቂት ቀናት በኋላ "ኹዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል" ዹሚል ዚሐሰት ዜና አሰራጚ ...ተጚማሪውን ያንብቡhttps://t.me/NorRadio1
😁12❀4👍1🖕1
📌 ዹ10 ሚሊዮን ብር ቌክ ለጥሎሜ ተሰጠ

(አነጋጋሪው ዚጥሎሜ ሥነሥርዓት )

ኹሰሞኑ ዹተኹናወነ አንድ ዚጥሎሜ ሥነ-ሥርዓት በቅንጊቱና በስጊታዎቹ ውድነት ዚብዙዎቜን ቀልብ በመሳብ መነጋገሪያ ሆኗል።

ሙሜራው አቀል ለሙሜሪት ዚአብስራ ሀብታሙ ያበሚኚቷ቞ው ስጊታዎቜ ዚሀብትና ዹፍቅር መገለጫ ተደርገው ተወስደዋል።

ለሙሜሪት ኚተበሚኚቱት ስጊታዎቜ መካኚል በልዩ ሁኔታ ያጌጠ እና ሙሉ ዚቀትና ዹግል መገልገያዎቜን ዚያዘ ተሜኚርካሪ፣ ዹዓለም አቀፍ ብራንድ ልብሶቜና ሜቶዎቜ ዚሞሉባ቞ው ዘመናዊ ሻንጣዎቜ እንዲሁም ውድ ዹወርቅ ጌጣጌጊቜ ይገኙበታል።

ይሁን እንጂ ዚዕለቱ ትልቁ መነጋገሪያ ዹሆነው ሙሜራው ለሙሜሪት ዚሰጣት ዹ10 ሚሊዮን ...ተጚማሪውን ያንብቡ https://t.me/NorRadio1/49
😁19❀18💩5😱2🥎2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📌ዚቀጥታ ስርጭት ዘገባውን በወፍ ታጅቊ ያኚናወነው ዹፋና ሪፖርተር

ዹፋና ቎ሌቪዥን ሪፖርተር ምራዑል ኚድር ዚቀጥታ ስርጭት ዘገባ በማቅሚብ ላይ እያለ፣ አንዲት ወፍ ትኚሻው ላይ አርፋ ዘገባውን አብራው ማጠናቀቋን ኖር ሬድዮ ዘግቧል።

ሪፖርተሩ ለተመልካ቟ቜ መሹጃ ለማድሚስ ሙሉ ትኩሚቱን ካሜራው ላይ አድርጎ ባለበት ቅጜበት፣ ወፏ ትኚሻው ላይ አርፋ ለደቂቃዎቜ ቆይታለቜ።

ምራዑል ይህንን ልዩ አጋጣሚ ሲገልጜ "ቀጥታ ዘገባዬ አልተቋሚጠም፣ ድምፄም አላስደነገጣትምፀ አእምሮዬ ኹወፏ ጋር እያወራ አንደበቮ ግን መሹጃ ማድሚሱን ቀጥሏል" ብሏል።

"ሰው ጋር መግባባት በኚበደበት በዚህ ጊዜ ኹወፍ ጋር ተግባብቌ ዚቀጥታ ዘገባዬን ጚሚስኩ" በማለትም በሙያው ያጋጠመውን ይህን ብርቅዬ ክስተት በደስታ ገልጟታል።

ዘገባው ዹኖር ሬድዮ ነው

ለተጚማሪው: https://t.me/NorRadio1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀33😁7👍4🔥3🕊3🗿3
📌በአዲስ አበባ ባለ 300,000 ብር ኮንሰርት ተዘጋጀ

ድምጻዊያኑ ሚካኀል በላይነህ እና ዳዊት ፅጌ "ሾክ" በሚል ርዕስ ነገ ቅዳሜ ጥር 16 2018 á‹“.ም አድማጮቜን ለማዝናናት በጊዮን ሆቮል ቀጠሮ ይዘዋል።

ኖር ሬድዮ ባሰባሰበው መሹጃ መሠሚት ዹዚህ ሙዚቃ ኮንሰርት ዚመግቢያው ዋጋ ውድነት በበርካቶቜ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።

ዹዚህ ኮንሰርት መደበኛ መግቢያው ..ተጚማሪውን ያንብቡ; https://t.me/NorRadio1/52


ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁20🖕10😡4❀3🍌3👎2🀬2😱1
📌"ቀቶቜ" ድራማ ተመልካቹን ሊሰናበት ነው

በኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን ሲተላለፍ ዹቆዹውና በብዙዎቜ ዘንድ ተወዳጅነትን ያተሚፈው "ቀቶቜ" ዚሲትኮም ድራማ፣ ኹተወሰኑ ሳምንታት በኋላ ዚዕይታ ጊዜውን እንደሚያጠናቅቅ ደራሲ፣ ተዋናይ እና ዚማስታወቂያ ባለሙያ ጥላሁን ጉግሳ አስታወቀ።

"ቀቶቜ" ሳይቋሚጥ ለሚዥም ጊዜ በመታዚት ኹዓለም ሊስተኛ፣ ኚአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ ደሹጃ ላይ ዹተቀመጠ ድንቅ ዚጥበብ ሥራ እንደሆነ ተዋናዩ ጠቁሟል።

ጥላሁን ጉግሳ ለአሐዱ ራድዮ እንደገለጞው፣ ድራማው እስካሁን ዚተጓዘበት ዹ13 ዓመታት ዕድሜ በቂ በመሆኑ፣ በቀጣይ አዳዲስ ሚዥም ተኚታታይ ፊልሞቜን ለተመልካቜ ለማቅሚብ ሲባል ድራማው እንዲጠናቀቅ ተወስኗል።

ተዋናይ ጥላሁን ጉግሳ ኹ"ቀቶቜ" መጠናቀቅ በኋላ፣ በክፍሎቜና በምዕራፍ ዹተኹፋፈለ አዲስ ሹጅም ተኚታታይ ፊልም ኹሁለተኛ ሎት ልጁ ጋር በመሆን ለማቅሚብ በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልጿል።

ኹዚህ በተጚማሪም፣ ኚዓመታት በፊት ተሠርቶ ለጥቂት ጊዜ ኚታዚ በኋላ ዚታገደውና ስለ አሰብ ዚባሕር በር አስፈላጊነት ዹሚተርኹው "ዚባሕር በር" ዹተሰኘው ፊልሙ በቅርቡ ለዕይታ ይበቃል ብሏል።

ፊልሙ በወቅቱ ዚታገደው በባለሥልጣናት ትእዛዝ እንደነበር ያስታወሰው ጥላሁን፣ በወቅቱ ኹፍተኛ ዛቻና ማስፈራሪያ ደርሶበት እንደነበርም አልሞሞገም።

ያገዱት አካላት ኚሥልጣን በመነሳታ቞ው ፊልሙን ቀደም ብሎ ለማሳዚት ቢያስብም፣ ዚኢትዮጵያና ዚኀርትራ መንግሥታት ግንኙነት በነበሚበት መልካም ሁኔታ ሳቢያ ግንኙነቱን ላለማበላሞት ሲል ፊልሙን ማዘግዚቱን ተዋናዩ አስሚድቷል።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ዚባሕር በር ጉዳይ በኢትዮጵያ እንደ አዲስ እዚተጠዚቀ በመሆኑ፣ ፊልሙን እንደገና ለመልቀቅ መወሰኑን ገልጟአል።

©አሐዱ ሬድዮ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀20🥱15👍3👎2😁1
📌ዋዜማ ሬድዮ በኢትዮጵያ ታገደ

ዋዜማ ሬድዮ "ዚኢትዮጵያን ህገ-መንግስት እና ዹመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እንዲሁም መመሪያዎቜና ዚሙያ ስነምግባር አክብሮ ለመስራት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ዚስራ ፈቃድ እውቅናውን በዛሬው እለት ተመላሜ አድርጓል" ሲል ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ።

"ኚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በበይነ መሚብ መገናኛ ብዝኃን ዚእውቅና ፈቃድ አግኝቶ ሲሰራ ዹነበሹው...ተጚማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/54
😱6❀2😁2😢1
📌"ራስ ተፈሪያውያን ጫና እዚተደሚገባ቞ው ነው"

በሻሞመኔ ኹተማ ዚሚኖሩ ዚራስ ተፈሪያውያን ኹተማዋን ለቅቀው እንዲወጡ ኹፍተኛ ጫና እዚተደሚገባ቞ው መሆኑን ዞብል ፖስት ዘግቧል።

ራስ ተፈሪያውያኑ ጫና እዚተደሚገባ቞ው ያለው ኚኊሮሚያ ክልል ፀጥታ ኃይሎቜ ሲሆን “ዹክልሉን ገፅታ እያበላሻቜሁ ነው” በሚል ዚሻሞመኔ ኹተማን ለቅቀው እንዲወጡ ዚሚያደርጉ ልዩ ልዩ ጫናዎቜ እዚደሚሱባ቞ው እንደሚገኝ ተገልጿል።

በኹተማዋ ዹሚገኙ ራስ ተፈሪያውያን “ዚንጉሳውያን ስርዓትን ታመልካላቜሁ” በሚል ኹተማዋን ለቅቀው እንዲወጡ..ተጚማሪውን ያንብቡ:-https://t.me/NorRadio1/56
😡17😢11😁8❀3🀔2🕊1
📌ዋዜማ ሬድዮ ምላሜ ሰጠ

ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሠሚት ዚሥራ ፈቃዱን መመለሱን ዋዜማ ሚዲያ ገለጠ።

ባለሥልጣኑ "ዹአገርን ጥቅም አደጋ ላይ በመጣልና ዚሥነ-ምግባር ደንቊቜን በመተላለፍ" በሚል ዋዜማን መወንጀሉን ተኚትሎ ሚዲያው ቅዳሜ ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም ምላሜ ሰጥቷል።

ዋዜማ ባወጣው መግለጫ፣ ባለሥልጣኑ ሐሙስ ዕለት በሰጠው ትዕዛዝ መሠሚት ፈቃዱን ዹመለሰ ቢሆንም፣ ዚተወሰደበት እርምጃ ግን በማንኛውም መመዘኛ ትክክል እንዳልሆነና እንዳሳዘነው ገልጿል።

ባለሥልጣኑ ያቀሚበባ቞ውን ክሶቜ በተመለኹተም "ለተደራሲያንና ለባለሙያዎቜ ዹሕሊና ፍርድ እንተዋለን" ብሏል። ተቋሙ ዝርዝር ሁኔታውን አጢኖ ተጚማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጥና ሌሎቜ ሕጋዊ አማራጮቜን እንደሚኚተልም አመልክቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀5😢5😁1
📌ለገነነ መኩሪያ ሊብሮ  መታሰቢያ ውድድር ተዘጋጀ

ዚታላቁ ዚእግርኳስ ሰው ገነነ መኩሪያ(ሊብሮ) 2ኛ ዓመት መታሰቢያ ዚእግር ኳስ ውድድር መዘጋጀቱ ተሰማ።

ኢትዮ-አፍሪካንስ ዚጀና ስፖርት ማህበር  መስራቜ ዚቀድሞ ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጚዋቜ  ባዩ ሙሉ አስተባባሪነት ዝግጅቱ እንደሚደሚግም ታውቋል።

ኢትዮ አፍሪካንስ ጚምሮ በ4 ቡድኖቜ መካኚል በጥሎ ማለፍ መልክ ዹሚደሹግ ዹአግር ኳስ ውድድር እንደሚደሚግ ይጠበቃል።

ዚፊታቜን ማክሰኞ ጥር 19/2018 ዓ.ም ኚጠዋቱ 3:30 ዚመጀመሪያ መክፈቻ ጚዋታ ኢትዮ አፍሪካንስ ኹ ኢትዮጵያ ፀሀበሻ ኹ አቢሲኒያ በንፋስ ስልክ ፖ/ቮ/ ኮሌጅ ሜዳ በሚያደርጉት ጚዋታ ይጀመራል::

በጚዋታው ላይ ኹሀገር ውጪ ዚነበሩ ዚቀድሞ ድንቅ ተጫዋ቟ቜ ተክሌ ብርሃኔ፣ሀብቶም ብርሃኔ፣ኀልያስ ጫካ እና ሌሎቜም ኮኚቊቜ በጚዋታው ላይ ይሳተፋሉ ተብሏል።

ለውድድሩ ዹ200,000 ብር ሜልማት ተዘጋጅቷል። ለአሾናፊው ቡድን በሀዋሳ ዹ2 ቀን ሆቮል እና ዚምግብ ወጪ ኹነ ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል በሜልማት መልክ እንደሚኖር ታውቋል::

ኢትዮ አፍሪካንስ ኹዚህ ቀደሞ በርካታ በኢትዮጵያ እግር ኳስ አሻራ ጥለው ላለፉ  ታላላቅ ሰዎቜ እንዲታወሱ ባማድሚግ ጉልህ ሚና በመጫወት ይታወቃል።

©ባላገሩ ስፖርት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀18👏4🙏1
📌አስገራሚ ታሪክ ዚያዘው "ሃያ ሊስት" መጜሐፍ

ኚአሥር ዓመታት በፊት በመላው ዓለም በተለይም በኢትዮጵያውያን ዘንድ ኹፍተኛ ድንጋጀንና ሐዘንን ፈጥሮ ዹነበሹው ዹአይ.ኀስ.አይ.ኀስ (ISIS) ዚጭካኔ እርምጃ ሰለባ ኚሆኑት መካኚልፀ በአጋጣሚ ኚሞት ተርፎ ታሪኩን በዝርዝር ዹሰነደ አዲስ መጜሐፍ ለምርቃት መዘጋጀቱ ተሰማ።

ዳንኀል አብርሃ "ሃያ ሊስት" በሚል ርዕስ ባዘጋጀው በዚህ መጜሐፍፀ ኚኢትዮጵያ ተነስቶ በሱዳንና በግብፅ በሚሃዎቜ አቋርጩ ሊቢያ ድሚስ ዚተጓዘበትን እጅግ አሰቃቂና ፈታኝ ጉዞ ይተርካል።

መጜሐፋ በይዘት ደሹጃ ዹጉዞ ማስታወሻ ሲሆን በ26 ምዕራፎቜ ተኹፋፍሎ በ262 ገፆቜ ተቀንብቊ ለንባብ እንደሚበቃም ተገልጿል።

ይህ መጜሐፍ በወቅቱ በሊቢያ በሹሃ ሕይወታ቞ውን ላጡ ወገኖቜ መታሰቢያ ኹመሆኑም ባለፈ፣ ዚስደትን ገጜታ በቅርብ ለመሚዳት ለሚፈልጉ አንባቢያን ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ይጠበቃል።

ዚመጜሐፉ ምሹቃ ዚፊታቜን አርብ ጥር 22 2018 ዓ.ም ኹ11:00 ጀምሮ በዋልያ መጻሕፍት አዳራሜ በድምቀት እንደሚኚናወን ተገልጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀23