📌አሻም ቴሌቪዥን ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ
አሻም ቴሌቪዥን ስራውን ለመቀጠል አቅም ስለሌላው ሙሉ በሙሉ ስርጭቱን እንዳቋረጠ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ጣቢያው በቴሌቪዥንም ሆነ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ከዛሬ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በይፋ ስርጭቱን ማቆሙን ገልጿል።
አሻም ቴሌቪዥን ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ የአሻም ሚዲያ መታወቂያ በመያዝ ወይም የሚዲያዋን ሎጎ በመጠቀም በየትኛውም ሁነት (Event) ፣ በእቅድ ዜና ወይም ፕሮግራም ፣ በስልጠና መድረክ ፣ ቃለ-መጠይቅ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚገኙ (የሚሳተፉ) ባለሞያዎች የሚዲያ ተቋሙን እንደማይወክሉ ለሁሉም የግልና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ጭምር በትህትና ለማሳወቅ እንወዳለን ብሏል።
አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በዜናና ወቅታዊ እንዲሁም በመዝናኛ ዝግጅቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥን እና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አሻም ቴሌቪዥን ስራውን ለመቀጠል አቅም ስለሌላው ሙሉ በሙሉ ስርጭቱን እንዳቋረጠ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ጣቢያው በቴሌቪዥንም ሆነ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ከዛሬ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በይፋ ስርጭቱን ማቆሙን ገልጿል።
አሻም ቴሌቪዥን ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ የአሻም ሚዲያ መታወቂያ በመያዝ ወይም የሚዲያዋን ሎጎ በመጠቀም በየትኛውም ሁነት (Event) ፣ በእቅድ ዜና ወይም ፕሮግራም ፣ በስልጠና መድረክ ፣ ቃለ-መጠይቅ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚገኙ (የሚሳተፉ) ባለሞያዎች የሚዲያ ተቋሙን እንደማይወክሉ ለሁሉም የግልና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ጭምር በትህትና ለማሳወቅ እንወዳለን ብሏል።
አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በዜናና ወቅታዊ እንዲሁም በመዝናኛ ዝግጅቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥን እና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😭42❤6😢3🔥2👍1
📌"ጎላ ጉህ" ያሬድ ሹመቴ ነው
የድምጻዊት የማርያም ቸርነት "የደጋ ሰው" አልበም ላይ አብዛኞቹን ግጥሞች የጻፈውና ያስደመመን "ጎላ ጎህ" የተባለው ባለ ብዕር ስም ያሬድ ሹመቴ እንደሆነ ደጃፍ ፖድካስት ላይ ተናግሯል።
ይሄ ጎላ ጎህ የሚባለው ሰው ማነው ስትሉ ለከረማችሁ ሙሉ መልሱን ራሱ ያሬድ ሹመቴ ይነግራችኋል።
ሊንክ:https://youtu.be/tm9PercKdUI?si=8rUTaybnEUjzQQKM
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የድምጻዊት የማርያም ቸርነት "የደጋ ሰው" አልበም ላይ አብዛኞቹን ግጥሞች የጻፈውና ያስደመመን "ጎላ ጎህ" የተባለው ባለ ብዕር ስም ያሬድ ሹመቴ እንደሆነ ደጃፍ ፖድካስት ላይ ተናግሯል።
ይሄ ጎላ ጎህ የሚባለው ሰው ማነው ስትሉ ለከረማችሁ ሙሉ መልሱን ራሱ ያሬድ ሹመቴ ይነግራችኋል።
ሊንክ:https://youtu.be/tm9PercKdUI?si=8rUTaybnEUjzQQKM
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍25🔥12❤6😱3
📌አንባቢያን መጽሐፍ የሚቀያየሩበት ልዩ ዝግጅት
የአዲስ የሥነጽሑፍ ፌስቲቫል አካል የሆነ "ሥነ ጽሑፍ እና ነገረ ሐቲት" የተሰኘ መርሐግብር ተዘጋጅቷል።
ቅዳሜ ታህሳስ 4 ፣ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 – 12:00 ከቤት እስከ ከተማ ፡ የከተማ ማዕከል ውስጥ በተዘጋጀው በዚህ መሰናዶ የመጽሐፍ ወዳጆች አዳዲስ እና የቆዩ መጻሕፍትን የሚሸጡበት፣የመጻሕፍት ልውውጥ፣እንዲሁም ያነበቡትን መጽሐፍ በሌላ የሚቀያየሩበት እና ስለ ሥነ ጽሑፍ ጥልቅ ውይይት የሚያደርጉበት ይሆናል ስለመባሉ ኤቨንት አዲስ ሰምቷል።
በውይይቱ ላይ ከኢትዮጵያ ቡክ ፎረም ዳዊት ብርሃኑ ፣ ከኢትዮጵያ ሳይንክ አካዳሚ ሐያሲ ቴዎድሮስ አጥላው፣ ጸሐፌ ተውኔት መዓዛ ወርቁ እንዲሁም ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይገኙበታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የአዲስ የሥነጽሑፍ ፌስቲቫል አካል የሆነ "ሥነ ጽሑፍ እና ነገረ ሐቲት" የተሰኘ መርሐግብር ተዘጋጅቷል።
ቅዳሜ ታህሳስ 4 ፣ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 – 12:00 ከቤት እስከ ከተማ ፡ የከተማ ማዕከል ውስጥ በተዘጋጀው በዚህ መሰናዶ የመጽሐፍ ወዳጆች አዳዲስ እና የቆዩ መጻሕፍትን የሚሸጡበት፣የመጻሕፍት ልውውጥ፣እንዲሁም ያነበቡትን መጽሐፍ በሌላ የሚቀያየሩበት እና ስለ ሥነ ጽሑፍ ጥልቅ ውይይት የሚያደርጉበት ይሆናል ስለመባሉ ኤቨንት አዲስ ሰምቷል።
በውይይቱ ላይ ከኢትዮጵያ ቡክ ፎረም ዳዊት ብርሃኑ ፣ ከኢትዮጵያ ሳይንክ አካዳሚ ሐያሲ ቴዎድሮስ አጥላው፣ ጸሐፌ ተውኔት መዓዛ ወርቁ እንዲሁም ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይገኙበታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍5❤4
📌 የሮማን ተወለደ "ዮዲታ" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
ሮማን ተወልደብርሃን የጻፈችውና የክርስትና እናቴ በሰጠችኝ ሁለተኛ ስሜ "ዮዲታ" የተሰኘ ርዕስ ሰጥቼዋለሁ ያለችውን መጽሐፏን በዚህ ሳምንት ለንባብ አብቅታለች።
"ዮዲታ" የተሰኘው መጽሐፏ በይዘት ግለታሪክ ሲሆን ዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 4 ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ገሐር በሚገኘው በአዲሱ ጃፋር የመጽሐፍት መደብር ውስጥ ይመረቃል።
በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ለንባብ የበቃ መጽሐፏ በቀጣይ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንደሚሰራጭም ደራሲዋ ገልጻለች።
ደራሲ ሮማን ተወለደብርሃን አስቀድማ ጉራማይሌና የነፍስ እኩያዎች የተሰኙ መጽሐፍትን በቡድን እንዲህም ለታዳጊዎች ደናደን የተሰኙ መጽሐፍትን ለንባብ አብቅለታች።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ሮማን ተወልደብርሃን የጻፈችውና የክርስትና እናቴ በሰጠችኝ ሁለተኛ ስሜ "ዮዲታ" የተሰኘ ርዕስ ሰጥቼዋለሁ ያለችውን መጽሐፏን በዚህ ሳምንት ለንባብ አብቅታለች።
"ዮዲታ" የተሰኘው መጽሐፏ በይዘት ግለታሪክ ሲሆን ዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 4 ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ገሐር በሚገኘው በአዲሱ ጃፋር የመጽሐፍት መደብር ውስጥ ይመረቃል።
በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ለንባብ የበቃ መጽሐፏ በቀጣይ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንደሚሰራጭም ደራሲዋ ገልጻለች።
ደራሲ ሮማን ተወለደብርሃን አስቀድማ ጉራማይሌና የነፍስ እኩያዎች የተሰኙ መጽሐፍትን በቡድን እንዲህም ለታዳጊዎች ደናደን የተሰኙ መጽሐፍትን ለንባብ አብቅለታች።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤25
📌ኢትዮጵያዊው ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸነፈ
ኢትዮጵያዊው የፊልም ባለሙያ ቤዛ ኃይሉ 'አላዛር' በተሰኘ ፊልም ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸነፈ::
በፊልም ጽሁፍ አዘጋጁና ዳይሬክተሩ የተሠራው ፊልም፤ የ "ዳካር ኮርት የ2025 ዓለም አቀፍ የአጭር ፊልም ፌስቲቫል ግራንድ ፕሪ ሽልማት አሸናፊ ለመሆን በቅቷል፡፡
ለ36 ደቂቃዎች የሚዘልቀው “አላዛር” ፊልም፣ ለምርጥ ዳይሬክተር የሚሰጠውን “አባባካር ሳም ማክሃራም” የተሰኘውን ሽልማት መቀዳጀቱንም አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
ፊልሙ በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ የገበሬ ማህበረሰብ ሐይማኖት፣ አመክንዮና አምልኮ ዙሪያ በማጠንጠን ተመልካቾችን ስሜታዊ መዋዥቅ ውስጥ ሰቅዞ እንደሚይዝ ዳኞቹ ለምርጫቸው በሰጡት ማብራሪያ መናገራቸውን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ኢትዮጵያዊው የፊልም ባለሙያ ቤዛ ኃይሉ 'አላዛር' በተሰኘ ፊልም ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸነፈ::
በፊልም ጽሁፍ አዘጋጁና ዳይሬክተሩ የተሠራው ፊልም፤ የ "ዳካር ኮርት የ2025 ዓለም አቀፍ የአጭር ፊልም ፌስቲቫል ግራንድ ፕሪ ሽልማት አሸናፊ ለመሆን በቅቷል፡፡
ለ36 ደቂቃዎች የሚዘልቀው “አላዛር” ፊልም፣ ለምርጥ ዳይሬክተር የሚሰጠውን “አባባካር ሳም ማክሃራም” የተሰኘውን ሽልማት መቀዳጀቱንም አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
ፊልሙ በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ የገበሬ ማህበረሰብ ሐይማኖት፣ አመክንዮና አምልኮ ዙሪያ በማጠንጠን ተመልካቾችን ስሜታዊ መዋዥቅ ውስጥ ሰቅዞ እንደሚይዝ ዳኞቹ ለምርጫቸው በሰጡት ማብራሪያ መናገራቸውን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤42👍8👏3🔥1
📌"ከርቤ" ፊልም አርብ ይለቀቃል !
በሂስትሪ ፊልም ካምፓኒ ተሰርቶ የቀረበው "ከርቤ" ፊልም አርብ ታህሳስ 10 ልክ 12:00 ሲል በNahom_Multimedia ዩቲዩብ ቻናል በኩል ይለቀቃል።
ጭብጡን በጓደኛው ታላቅ በደልና ታላቅ ውለታ መሃል ገብቶ የተወጠረው አባት ነገሮችን ለመፍታት በሚከፍለው መስዋትነት እና በቀረው ቤተሰብ መካከል የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ልብ አንጠለጣይ ፊልም ነው።
በስዩም በላይ Produced የተደረገ ሲሆን ፊልሙን ዳይይሬክት ያደረገው አለባቸው አራጌ፣ ሲኒማቶግራፊውን ዳንኤል ግርማ፣ በትወና ደግሞ በሄኖክ ወንድሙ፣ መዓዛ ገ/ሕይወት ፣ የአብሥራ ታደሠ፣ ከድር ሁሴን፣ ይሁኔ ምንዋጋው፣ ሰርካለም ደምሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል፡፡
ፊልሙ አርብ ታህሳስ 10 ምሽት በNahom_Multimedia ዩቲዩብ በኩል ለተመልካች ይደርሳል።
ፊልሙ የሚለቀቅበት ቻናል ሊንክ ይኸው
https://youtube.com/@nahommultimedia?si=YqGl8THSPt1GIv7D
በሂስትሪ ፊልም ካምፓኒ ተሰርቶ የቀረበው "ከርቤ" ፊልም አርብ ታህሳስ 10 ልክ 12:00 ሲል በNahom_Multimedia ዩቲዩብ ቻናል በኩል ይለቀቃል።
ጭብጡን በጓደኛው ታላቅ በደልና ታላቅ ውለታ መሃል ገብቶ የተወጠረው አባት ነገሮችን ለመፍታት በሚከፍለው መስዋትነት እና በቀረው ቤተሰብ መካከል የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ልብ አንጠለጣይ ፊልም ነው።
በስዩም በላይ Produced የተደረገ ሲሆን ፊልሙን ዳይይሬክት ያደረገው አለባቸው አራጌ፣ ሲኒማቶግራፊውን ዳንኤል ግርማ፣ በትወና ደግሞ በሄኖክ ወንድሙ፣ መዓዛ ገ/ሕይወት ፣ የአብሥራ ታደሠ፣ ከድር ሁሴን፣ ይሁኔ ምንዋጋው፣ ሰርካለም ደምሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል፡፡
ፊልሙ አርብ ታህሳስ 10 ምሽት በNahom_Multimedia ዩቲዩብ በኩል ለተመልካች ይደርሳል።
ፊልሙ የሚለቀቅበት ቻናል ሊንክ ይኸው
https://youtube.com/@nahommultimedia?si=YqGl8THSPt1GIv7D
👍9❤8
📌የያንጎ ፌሎውሺፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት ተጀመረ
ይህም የቀጣዩን ትውልድ ዐቅም በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በምኅንድስና እና ሒሳብ ዘርፍ ለማጎልበት የሚያስችል ነው::
ዓለም አቀፋዊ የቴክኖሎጂ ተቋም የሆነው ያንጎ ግሩፕ፣ የያንጎ ፌሎውሺፕ ቀጣይ ምዕራፍ - በመላው አፍሪካ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የምኅንድስና እና ሒሳብ ዘርፍ ችሎታን ለማጎልበት ዓልሞ እንደተነደፈ አስታውቋል።
ያንጎ ፌሎውሺፕ፣ ወጣቶችን በማማከር እና አቅጣጫ በመጠቆም እንዲሁም ግብዓቶችን እና የግንኙነት መረቦችን በመዘርጋት፣ ተሳታፊዎች ማኅበረሰባቸውን የሚጠቅሙ ሐሳቦችን እንዲያመነጩ ብሎም ወደ ተግባር እንዲቀይሩ እገዛ ያደርጋል።
በዛምቢያ እና በአይቮሪኮስት በተሳካ ሁኔታ የተጀመረው የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም አድማሱን በማስፋት ወደ አራት ተጨማሪ ሀገራት፣ ማለትም ኢትዮጵያ፣ ሞዛምቢክ፣ ጋና እና ሴኔጋል ደርሷል።
መዳረሻዎቹን እያሰፋ የመጣው የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም፣ የገንዘብ ድጋፍን እና የባለሙያዎችን ሰፊ እገዛ ያካተተ ከመሆኑም ባሻገር፣ በድንበር ያልተገደበ ሰፊ የፌሎው ተጠቃሚ ማኅበረሰብ ግንኙነቶችን በማመቻቸት ተሳታፊዎች ለኅብረተሰባቸው መፍትሔ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ: https://url-shortener.me/460W
ይህም የቀጣዩን ትውልድ ዐቅም በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በምኅንድስና እና ሒሳብ ዘርፍ ለማጎልበት የሚያስችል ነው::
ዓለም አቀፋዊ የቴክኖሎጂ ተቋም የሆነው ያንጎ ግሩፕ፣ የያንጎ ፌሎውሺፕ ቀጣይ ምዕራፍ - በመላው አፍሪካ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የምኅንድስና እና ሒሳብ ዘርፍ ችሎታን ለማጎልበት ዓልሞ እንደተነደፈ አስታውቋል።
ያንጎ ፌሎውሺፕ፣ ወጣቶችን በማማከር እና አቅጣጫ በመጠቆም እንዲሁም ግብዓቶችን እና የግንኙነት መረቦችን በመዘርጋት፣ ተሳታፊዎች ማኅበረሰባቸውን የሚጠቅሙ ሐሳቦችን እንዲያመነጩ ብሎም ወደ ተግባር እንዲቀይሩ እገዛ ያደርጋል።
በዛምቢያ እና በአይቮሪኮስት በተሳካ ሁኔታ የተጀመረው የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም አድማሱን በማስፋት ወደ አራት ተጨማሪ ሀገራት፣ ማለትም ኢትዮጵያ፣ ሞዛምቢክ፣ ጋና እና ሴኔጋል ደርሷል።
መዳረሻዎቹን እያሰፋ የመጣው የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም፣ የገንዘብ ድጋፍን እና የባለሙያዎችን ሰፊ እገዛ ያካተተ ከመሆኑም ባሻገር፣ በድንበር ያልተገደበ ሰፊ የፌሎው ተጠቃሚ ማኅበረሰብ ግንኙነቶችን በማመቻቸት ተሳታፊዎች ለኅብረተሰባቸው መፍትሔ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ: https://url-shortener.me/460W
❤4👍1👎1
📌የአእላፋት ዝማሬ በመስቀል አደባባይ
የ2018 ዓ.ም 3ኛው የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ (ኢጃት) "የአእላፋት ሳምንት" የዝማሬ መርሐግብር ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይና በድሬ ለገሀር አደባባይ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ አሳውቋል።
በተጨማሪም የአእላፋት ሳምንት የተሰኘ ዐውደ ርዕይና የፎረም መድረክ ከታኅሣሥ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በግዮን ሆቴል ግራውንድስ ለማከናወን ዝግጅቱን መጨረሱን አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የ2018 ዓ.ም 3ኛው የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ (ኢጃት) "የአእላፋት ሳምንት" የዝማሬ መርሐግብር ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይና በድሬ ለገሀር አደባባይ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ አሳውቋል።
በተጨማሪም የአእላፋት ሳምንት የተሰኘ ዐውደ ርዕይና የፎረም መድረክ ከታኅሣሥ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በግዮን ሆቴል ግራውንድስ ለማከናወን ዝግጅቱን መጨረሱን አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤52👎8👍3👏2
📌አሜሪካ የ”ዲቪ” ሎተሪ እድልን አገደች!
የዩናይትድ ስቴትስ ብራውን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከተፈጸመ የተኩስ እሩምታ ግድያ በኋላ የ”ዲቪ” ሎተሪ እድልን ማገዷን አሳወቀች።
የሀገሪቱ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖዬም በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ “አሁን በተቋረጠው የዲቪ መርኀ-ግብር ተጠቃሚ ከሆነ አገር የመጣ ነው” ብለዋል።
ለኃላፊዋ የዲቪ ሎተሪ እድል መርኀ-ግብሩን እንዲያቋርጡ “አቋርጪ” ሲሉ ትናንት ሐሙስ ታኅሣሥ 9 /2018 ዓ.ም ማምሻውን ትእዛዝ ያስተላለፉላት የአገሪቱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ናቸው ብሏል ዶቸቬለ በዘገባው።
የዲቪ ሎተሪ መርኀ-ግብር በየዓመቱ 50,000 ፍልሰተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የሚያስችል እድል እንደነበር ነው የተገለፀ ሲሆን በዚህ እድል በርካታ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚ እንደነበሩ ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የዩናይትድ ስቴትስ ብራውን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከተፈጸመ የተኩስ እሩምታ ግድያ በኋላ የ”ዲቪ” ሎተሪ እድልን ማገዷን አሳወቀች።
የሀገሪቱ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖዬም በብራውን ዩኒቨርሲቲ የተኩስ እሩምታ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ “አሁን በተቋረጠው የዲቪ መርኀ-ግብር ተጠቃሚ ከሆነ አገር የመጣ ነው” ብለዋል።
ለኃላፊዋ የዲቪ ሎተሪ እድል መርኀ-ግብሩን እንዲያቋርጡ “አቋርጪ” ሲሉ ትናንት ሐሙስ ታኅሣሥ 9 /2018 ዓ.ም ማምሻውን ትእዛዝ ያስተላለፉላት የአገሪቱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ናቸው ብሏል ዶቸቬለ በዘገባው።
የዲቪ ሎተሪ መርኀ-ግብር በየዓመቱ 50,000 ፍልሰተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የሚያስችል እድል እንደነበር ነው የተገለፀ ሲሆን በዚህ እድል በርካታ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚ እንደነበሩ ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤7🤔2
📌ተጠባቂው "ከርቤ" ፊልም ተለቀቀ
በሂስትሪ ፊልም ካምፓኒ ተሰርቶ የቀረበው "ከርቤ" ፊልም በNahom_Multimedia ዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቀቀ።
ፊልሙን ለመመልከት ይኸው ሊንክ:https://youtu.be/CWE3vgB29uE?si=IgA67qcgs5Kp2HYD
ከርቤ ፊልም ጭብጡን በጓደኛው ታላቅ በደልና ታላቅ ውለታ መሃል ገብቶ የተወጠረው አባት ነገሮችን ለመፍታት በሚከፍለው መስዋትነት እና በቀረው ቤተሰብ መካከል የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ልብ አንጠለጣይ ፊልም ነው።
በስዩም በላይ Produced የተደረገ ሲሆን ፊልሙን ዳይይሬክት ያደረገው አለባቸው አራጌ፣ ሲኒማቶግራፊውን ዳንኤል ግርማ፣ በትወና ደግሞ በሄኖክ ወንድሙ፣ መዓዛ ገ/ሕይወት ፣ የአብሥራ ታደሠ፣ ከድር ሁሴን፣ ይሁኔ ምንዋጋው፣ ሰርካለም ደምሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል፡፡
በሂስትሪ ፊልም ካምፓኒ ተሰርቶ የቀረበው "ከርቤ" ፊልም በNahom_Multimedia ዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቀቀ።
ፊልሙን ለመመልከት ይኸው ሊንክ:https://youtu.be/CWE3vgB29uE?si=IgA67qcgs5Kp2HYD
ከርቤ ፊልም ጭብጡን በጓደኛው ታላቅ በደልና ታላቅ ውለታ መሃል ገብቶ የተወጠረው አባት ነገሮችን ለመፍታት በሚከፍለው መስዋትነት እና በቀረው ቤተሰብ መካከል የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ልብ አንጠለጣይ ፊልም ነው።
በስዩም በላይ Produced የተደረገ ሲሆን ፊልሙን ዳይይሬክት ያደረገው አለባቸው አራጌ፣ ሲኒማቶግራፊውን ዳንኤል ግርማ፣ በትወና ደግሞ በሄኖክ ወንድሙ፣ መዓዛ ገ/ሕይወት ፣ የአብሥራ ታደሠ፣ ከድር ሁሴን፣ ይሁኔ ምንዋጋው፣ ሰርካለም ደምሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል፡፡
❤8🔥1
📌የተደለዙ ገጾች መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል
በጋዜጠኛ ተስፋዬ ወልደዮሐንስ የተዘጋጀው "የተደለዙ ገጾች " መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
የተደለዙ ገጾች ዐሥር አጫጭር እውነተኛ ታሪኮችን የያዘ መፅሐፍ ነው። ትኩረት የተነፈጉ ቁም ነገሮች፣ እንደዋዛ የታለፉ ውልብታዎች፣ የተኖሩ የሕይወት ገጽታዎች ናቸው።
ዐጭር ቢሆኑም በዝርዝር የሚታወሱን፣ ፈገግ የሚያደርጉን፣ የሚያሳዝኑን፣ የሚወቅሱን ግን ዘንግተን ያለፍናቸው የታሪካችን አካል ናቸው።
መጽሐፉ በጃዕፋርና ክብሩ መፅሐፍት መደብር ይገኛል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በጋዜጠኛ ተስፋዬ ወልደዮሐንስ የተዘጋጀው "የተደለዙ ገጾች " መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
የተደለዙ ገጾች ዐሥር አጫጭር እውነተኛ ታሪኮችን የያዘ መፅሐፍ ነው። ትኩረት የተነፈጉ ቁም ነገሮች፣ እንደዋዛ የታለፉ ውልብታዎች፣ የተኖሩ የሕይወት ገጽታዎች ናቸው።
ዐጭር ቢሆኑም በዝርዝር የሚታወሱን፣ ፈገግ የሚያደርጉን፣ የሚያሳዝኑን፣ የሚወቅሱን ግን ዘንግተን ያለፍናቸው የታሪካችን አካል ናቸው።
መጽሐፉ በጃዕፋርና ክብሩ መፅሐፍት መደብር ይገኛል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5👍2
📌የመጀመሪያዋ ሴት የረዥም ልቦለድ ደራሲ ፀሐይ መልአኩ አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
የደራሲዋ አዲስ መጽሐፍ ርዕስ "ዘባሲል" ይሰኛል።
"ዘባሲል” መጽሐፍ በ399 ገፆች የተቀነበበ ታሪክ ለበስ ልብ ወለድ ነው።
መፅሐፉ ዛሬ ቅዳሜ ታኅሣሥ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሚገኙበት በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትያና ቤተመጻፍት አገልግሎት (ወመዘክር( አዳራሽ ይመረቃል።
“ዘባሲል” መፅሐፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ደምና አጥንት ተከፍሎባት የተረከባትን ሃገር ባለአደራ ሆኖ ለቀጣዩ ትውልድ እንዴት ማስተላለፍ እንዳለበት እንደሚጠቁም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የደራሲዋ አዲስ መጽሐፍ ርዕስ "ዘባሲል" ይሰኛል።
"ዘባሲል” መጽሐፍ በ399 ገፆች የተቀነበበ ታሪክ ለበስ ልብ ወለድ ነው።
መፅሐፉ ዛሬ ቅዳሜ ታኅሣሥ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሚገኙበት በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትያና ቤተመጻፍት አገልግሎት (ወመዘክር( አዳራሽ ይመረቃል።
“ዘባሲል” መፅሐፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ደምና አጥንት ተከፍሎባት የተረከባትን ሃገር ባለአደራ ሆኖ ለቀጣዩ ትውልድ እንዴት ማስተላለፍ እንዳለበት እንደሚጠቁም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤7🙏6👍2
📌ትውልደ ኢትዮጵያዊው ደራሲ በአሜሪካ
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ደራሲና ፀሀፊ ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውን ፔን አሜሪካን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመረጡ።
ከትናንት በስቲያ ረቡዕ የፔን አሜሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ በተደረገ ምርጫ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዲናው መንግስቱ ድርጅቱን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመርጠዋል።
የ103 ዓመት እድሜ ያለው ታዋቂው ተቋም "ፔን አሜሪካ" ዋና መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገና ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው፡፡
ተግባሩም ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን መደገፍ ፣ ለስነ ፅሁፍ እድገትና ነፃነት መታገል፣እንዲሁም በአጠቃላይ በአለም ዙሪያ ሰብአዊ መብት እንዲከበር መስራት መሆኑ ይነገራል፡፡
ይህንን ግዙፍ ተቋም በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ነው ትውልድ ኢትዮጵያዊው ፀሐፊና ደራሲ ዲናው መንግስቱ የተመረጡት።
ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውና የኪነ ጥበብ ኮሌጅ የሆነው ባርድ ኮሌጅ የሪትን አርት ፕሮግራም ዳይሬክተር ሆነውም ይሰራሉ።
ኢትዮጵያ አሜሪካዊው ደራሲ ዲናው መንግስቱ ትውልዳቸው በአዲስ አበባ ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኙ መፅሐፍትን ለንባብ አብቅተዋል።
©️ሸገር 102.1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ደራሲና ፀሀፊ ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውን ፔን አሜሪካን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመረጡ።
ከትናንት በስቲያ ረቡዕ የፔን አሜሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ በተደረገ ምርጫ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዲናው መንግስቱ ድርጅቱን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመርጠዋል።
የ103 ዓመት እድሜ ያለው ታዋቂው ተቋም "ፔን አሜሪካ" ዋና መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገና ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው፡፡
ተግባሩም ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን መደገፍ ፣ ለስነ ፅሁፍ እድገትና ነፃነት መታገል፣እንዲሁም በአጠቃላይ በአለም ዙሪያ ሰብአዊ መብት እንዲከበር መስራት መሆኑ ይነገራል፡፡
ይህንን ግዙፍ ተቋም በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ነው ትውልድ ኢትዮጵያዊው ፀሐፊና ደራሲ ዲናው መንግስቱ የተመረጡት።
ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውና የኪነ ጥበብ ኮሌጅ የሆነው ባርድ ኮሌጅ የሪትን አርት ፕሮግራም ዳይሬክተር ሆነውም ይሰራሉ።
ኢትዮጵያ አሜሪካዊው ደራሲ ዲናው መንግስቱ ትውልዳቸው በአዲስ አበባ ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኙ መፅሐፍትን ለንባብ አብቅተዋል።
©️ሸገር 102.1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤14👏4
📌ቤቲንግ ቢከለከልም ብሔራዊ ሎተሪ ግን የቤቲንግ ቁማር እያጫወተ መሆኑ ተሰምቷል። የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁሉንም የስፖርት ውርርድ (Betting) ድርጅቶች የሥራ ፈቃድ ሙሉ በሙሉ መሰረዙ ይታወሳል።ራሱ ተቋሙ በድረ-ገጽ አማካኝነት የ"ቨርችዋል" ጨዋታዎችን ማጫወት መጀመሩን ካፒታል ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁18👍2🥱1
📌በስንቱ ድራማ የኢቤኤስ ቆይታው ተጠናቀቀ
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሲተላለፍ የነበረው ተወዳጁ በስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ፕሮዲዩሰር የሆነው አብሪኮም መልቲሚዲያ፤ ከጣቢያው ጋር የነበረውን የሥራ ውል ማጠናቀቁን መልቲሚዲያው አሳውቋል።
አብሪኮም መልቲሚዲያ ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር የነበረው የሥራ ቆይታ መጠናቀቁን ተከትሎ፤ ተወዳጁ በስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ድራማ ከታህሳስ 03 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን እንደማይተላለፍ እና በበስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ዙሪያ የሚኖሩ ተጨማሪ መረጃዎችን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ መልቲሚዲያው ገልጿል።
ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ሰላማዊ እና ጥሩ የሥራ ቆይታ እንደነበራቸው የገለጸው አብሪኮም፤ ለጣቢያው ባለቤቶች እና ሠራተኞች የቀና ምሥጋና አቅርበዋል።
©️ይትባረክ ዋለልኝ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሲተላለፍ የነበረው ተወዳጁ በስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ፕሮዲዩሰር የሆነው አብሪኮም መልቲሚዲያ፤ ከጣቢያው ጋር የነበረውን የሥራ ውል ማጠናቀቁን መልቲሚዲያው አሳውቋል።
አብሪኮም መልቲሚዲያ ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር የነበረው የሥራ ቆይታ መጠናቀቁን ተከትሎ፤ ተወዳጁ በስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ድራማ ከታህሳስ 03 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን እንደማይተላለፍ እና በበስንቱ የቤተሰብ ሲትኮም ዙሪያ የሚኖሩ ተጨማሪ መረጃዎችን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ መልቲሚዲያው ገልጿል።
ከኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ሰላማዊ እና ጥሩ የሥራ ቆይታ እንደነበራቸው የገለጸው አብሪኮም፤ ለጣቢያው ባለቤቶች እና ሠራተኞች የቀና ምሥጋና አቅርበዋል።
©️ይትባረክ ዋለልኝ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢19❤7👍5🔥3👏3
📌ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ተዘጋጅቷል።
ደራሲ አዳም ረታ ከነገ በስቲያ ሐሙስ ታህሥሣ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በአዲሱ የጃዕፋር መፅሐፍት መደብር የመጽሐፍት የፊርማ ሥነሥርዓት ያከናውናል።
በተጨማሪም ከአድናቂዎቹ ጋር ስለ ስራዎች በተናጥል ይጨዋወታል። የፎቶግራፍ መርሐግብርም እንደሚያካሂድ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ተዘጋጅቷል።
ደራሲ አዳም ረታ ከነገ በስቲያ ሐሙስ ታህሥሣ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በአዲሱ የጃዕፋር መፅሐፍት መደብር የመጽሐፍት የፊርማ ሥነሥርዓት ያከናውናል።
በተጨማሪም ከአድናቂዎቹ ጋር ስለ ስራዎች በተናጥል ይጨዋወታል። የፎቶግራፍ መርሐግብርም እንደሚያካሂድ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤37🔥10
📌ደራሲ አዳም ረታን የምታገኙት ዛሬ ነው
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል !
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ተዘጋጅቷል።
ደራሲ አዳም ረታ ዛሬ ሐሙስ ታህሥሣ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በአዲሱ የጃዕፋር መፅሐፍት መደብር የመጽሐፍት የፊርማ ሥነሥርዓት ያከናውናል።
በተጨማሪም ከአድናቂዎቹ ጋር ስለ ስራዎች በተናጥል ይጨዋወታል። የፎቶግራፍ መርሐግብርም እንደሚያካሂድ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል !
ደራሲ አዳም ረታን በአካል የምታገኙበት እድል በጃፋር መጽሐፍት መደብር በኩል ተዘጋጅቷል።
ደራሲ አዳም ረታ ዛሬ ሐሙስ ታህሥሣ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በአዲሱ የጃዕፋር መፅሐፍት መደብር የመጽሐፍት የፊርማ ሥነሥርዓት ያከናውናል።
በተጨማሪም ከአድናቂዎቹ ጋር ስለ ስራዎች በተናጥል ይጨዋወታል። የፎቶግራፍ መርሐግብርም እንደሚያካሂድ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤11👍8
📌የአእላፋት ሳምንት አውደርዕይ ዛሬ ይጀምራል
የመጀመሪያው የአእላፋት ሳምንት አውደርዕይ እና ፎረም ዛሬ አርብ ታህሥሣ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 በጊዮን ሆቴል ግራውንድስ በይፋ ይጀምራል።
ከታህሣሥ 18 እስከ ታህሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከጠዋት 4:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 2፡00 ሰዓት ድረስ ዐውደ ርዕዩ ለምዕመናን በአጠቃላይ ክፍት ይሆናል፡፡
ሃይማኖታዊ ትምህርቶች ይሰጣሉ፣መጽሐፍት ይመረቃሉ፣ጥናታዊ ፅሁፎችም ይቀርባሉ፡፡
በኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ መንፈሳዊ ማህበር የሚዘጋጀው ይሄ ዝግጅት በግዮን ሆቴል ግራውንድስ ይደረጋል።
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በአዲስ አበባና በድሬደዋ ከተማ የሚያዘጋጀው የ2018 የ3ኛው የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር ታህሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይና በድሬ ለገሀር አደባባይከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ማህበሩ አስታውሷል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የመጀመሪያው የአእላፋት ሳምንት አውደርዕይ እና ፎረም ዛሬ አርብ ታህሥሣ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 በጊዮን ሆቴል ግራውንድስ በይፋ ይጀምራል።
ከታህሣሥ 18 እስከ ታህሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከጠዋት 4:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 2፡00 ሰዓት ድረስ ዐውደ ርዕዩ ለምዕመናን በአጠቃላይ ክፍት ይሆናል፡፡
ሃይማኖታዊ ትምህርቶች ይሰጣሉ፣መጽሐፍት ይመረቃሉ፣ጥናታዊ ፅሁፎችም ይቀርባሉ፡፡
በኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ መንፈሳዊ ማህበር የሚዘጋጀው ይሄ ዝግጅት በግዮን ሆቴል ግራውንድስ ይደረጋል።
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በአዲስ አበባና በድሬደዋ ከተማ የሚያዘጋጀው የ2018 የ3ኛው የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር ታህሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይና በድሬ ለገሀር አደባባይከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ማህበሩ አስታውሷል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏11❤8👍2
"ዳንቴል" የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ ስራ ጀመረ
በዳንቴል ሶፍትዌር ኃ.የተ.የግ.ማኀበር የተዘጋጀው "ዳንቴል" የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ ስራ ጀምሯል።
"ዳንቴል" መተግበሪያ ተጠቃሚዎች በመተግበሪያው ላይ የሚገኙ ምርቶችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክና ቲክቶክ በማጋራትና ሽያጭ እንዲከናወን በማድረግ የኮሚሽን ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል ይፈጥራል ተብሏል።
ይህ አሰራር በተለይ የስራ ልምድ ያላቸው ነገር ግን ወደ ስራው ዓለም ለመግባት በካፒታል እጥረት ለተቸገሩ ወጣቶች እንደ ትልቅ ድልድይ ያገለግላል ተብሏል።
መተግበሪያው ተጠቃሚዎች የትኛውን ምርት፣ በምን አይነት የገበያ ሁኔታ እና በምን ያህል ካፒታል መጀመር እንዳለባቸው የሚያማክር የራሱ የሆነ የAI ስርዓት እንዳለውም ተገልጿል።
ይህም አምራቾችና ነጋዴዎች የገበያ ፍላጎትን ተረድተው ምርታቸውን በብቃት እንዲያቀርቡ ይረዳቸዋል።
ዳንቴል ከአምራቾች እስከ ሸማቾች ያለውን ሰንሰለት ለማሳለጥ ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።
ይህም ተጠቃሚዎች የሚያዝዟቸው ምርቶች ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲደርሷቸውና የት ደረጃ ላይ እንዳሉ እንዲከታተሉ ያስችላቸዋል።
በተጨማሪም ድርጅቱ የደንበኞችን እምነት ለመጠበቅ "ምርቱ ካልተመቸ የመመለስ መብት" (Return Policy) ከአቅራቢዎች ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዳንቴል ሶፍትዌር ኃ.የተ.የግ.ማኀበር የተዘጋጀው "ዳንቴል" የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ ስራ ጀምሯል።
"ዳንቴል" መተግበሪያ ተጠቃሚዎች በመተግበሪያው ላይ የሚገኙ ምርቶችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክና ቲክቶክ በማጋራትና ሽያጭ እንዲከናወን በማድረግ የኮሚሽን ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል ይፈጥራል ተብሏል።
ይህ አሰራር በተለይ የስራ ልምድ ያላቸው ነገር ግን ወደ ስራው ዓለም ለመግባት በካፒታል እጥረት ለተቸገሩ ወጣቶች እንደ ትልቅ ድልድይ ያገለግላል ተብሏል።
መተግበሪያው ተጠቃሚዎች የትኛውን ምርት፣ በምን አይነት የገበያ ሁኔታ እና በምን ያህል ካፒታል መጀመር እንዳለባቸው የሚያማክር የራሱ የሆነ የAI ስርዓት እንዳለውም ተገልጿል።
ይህም አምራቾችና ነጋዴዎች የገበያ ፍላጎትን ተረድተው ምርታቸውን በብቃት እንዲያቀርቡ ይረዳቸዋል።
ዳንቴል ከአምራቾች እስከ ሸማቾች ያለውን ሰንሰለት ለማሳለጥ ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።
ይህም ተጠቃሚዎች የሚያዝዟቸው ምርቶች ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲደርሷቸውና የት ደረጃ ላይ እንዳሉ እንዲከታተሉ ያስችላቸዋል።
በተጨማሪም ድርጅቱ የደንበኞችን እምነት ለመጠበቅ "ምርቱ ካልተመቸ የመመለስ መብት" (Return Policy) ከአቅራቢዎች ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤4👍1
📌"ቀለም" ዲጂታል መጽሔት ንባብ በቃ
ቀለም ዲጂታል መጽሔት ቅፅ 1/ ዕትም 6 ለአንባቢያን ቀርቧል።ለተከታታይ 6 ወራት በቴሌግራም ቻናል የተለያዩ ዓምዶችን አካቶ ለንባብ የበቃው ቀለም መጽሔት ስድስተኛ ዕትም ከሰሞኑ ንባብ በቅቷል።
ቀለም ዲጂታል መጽሔት በዚህ ዕትሙ ስለ ሠዓሊ እና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ ታሪክ አንስቶ፣ በግጥም ተውቦ ከወጉ አካቶ በስነ-ጽሑፍ ቀለሞች አሸብርቋል።
በነፃ ያንብቡ:-
https://t.me/kelemofficial
ቀለም ዲጂታል መጽሔት ቅፅ 1/ ዕትም 6 ለአንባቢያን ቀርቧል።ለተከታታይ 6 ወራት በቴሌግራም ቻናል የተለያዩ ዓምዶችን አካቶ ለንባብ የበቃው ቀለም መጽሔት ስድስተኛ ዕትም ከሰሞኑ ንባብ በቅቷል።
ቀለም ዲጂታል መጽሔት በዚህ ዕትሙ ስለ ሠዓሊ እና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ ታሪክ አንስቶ፣ በግጥም ተውቦ ከወጉ አካቶ በስነ-ጽሑፍ ቀለሞች አሸብርቋል።
በነፃ ያንብቡ:-
https://t.me/kelemofficial
👍7❤2🙏2
📌የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 75ኛ ዓመት ክብረበዓል
75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፥ የቀድሞ ምሩቃንና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የቤተሰብ ቀንን ከነገ ታህሳስ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ ያከብራል፡፡
ዩኒቨርሲቲው 75ኛ የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን ከባለፈው ወር ጀምሮ በተለያዩ ፕሮግራሞች በማክበር ላይ ይገኛል።
የቀድሞ ተማሪዎች ሳምንት ከታህሳስ 18-24/2018 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
የቀድሞ ተማሪዎች እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቤተሰቦች በበዓሉ ማክበሪያ ሳምንት ታህሳስ 18-19/2018 ዓ.ም በ6 ኪሎ ዋናው ግቢ እና ከታህሳስ 20-24/2018 ዓ.ም በሁሉም ካምፓሶች በመገኘት እንዲያከብሩ ጥሪ አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፥ የቀድሞ ምሩቃንና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የቤተሰብ ቀንን ከነገ ታህሳስ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ ያከብራል፡፡
ዩኒቨርሲቲው 75ኛ የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን ከባለፈው ወር ጀምሮ በተለያዩ ፕሮግራሞች በማክበር ላይ ይገኛል።
የቀድሞ ተማሪዎች ሳምንት ከታህሳስ 18-24/2018 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
የቀድሞ ተማሪዎች እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቤተሰቦች በበዓሉ ማክበሪያ ሳምንት ታህሳስ 18-19/2018 ዓ.ም በ6 ኪሎ ዋናው ግቢ እና ከታህሳስ 20-24/2018 ዓ.ም በሁሉም ካምፓሶች በመገኘት እንዲያከብሩ ጥሪ አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1