📌"ውብ አዲስ ፩" የሥዕል ትርዒት ሊከፈት ነው
"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩረቱን በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያደረገ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተከታታይ (ከህዳር-2018 እስከ ህዳር-2019) የግል የሥዕል ትርዒት (Solo Art Exhibition) ለማቅረብ ሠዓሊ ሀሮን ዝግጅቱን ጨርሷል።
የመጀመሪያውን "ውብ አዲስ ፩" የሥዕል ትርዒትም ከአርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ጎላ ሚካኤል አካባቢ በሚገኘው ጎላ ሥነ ጥበብ ማዕከልለህዝብ ዕይታ ክፍት ይሆናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩረቱን በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያደረገ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተከታታይ (ከህዳር-2018 እስከ ህዳር-2019) የግል የሥዕል ትርዒት (Solo Art Exhibition) ለማቅረብ ሠዓሊ ሀሮን ዝግጅቱን ጨርሷል።
የመጀመሪያውን "ውብ አዲስ ፩" የሥዕል ትርዒትም ከአርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ጎላ ሚካኤል አካባቢ በሚገኘው ጎላ ሥነ ጥበብ ማዕከልለህዝብ ዕይታ ክፍት ይሆናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤6
📌የ"ቁንጅና" ሙዚቃ ግጥም የዓለምፀሐይ ወዳጆ አይደለም ሲል ዳዊት መለሰ ተናገረ
ከሁለት አስርት ዓመታት በኃላ 'ምስጢር" የተሰኘ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው ዳዊት መለሠ ሰይፉ ሾው ላይ ቀርቦ ነበር።
በዚህ ቃለመጠየቁ ዳዊት መለሠ በርካታ የእሱ ሙዚቃ ወዳጆች ስለሚወዱለት "ቁንጅና" ሙዚቃው ተከታዩን ብሏል"ቁንጅና የተሰኘው ዘፈኔን ዓለምፀሐይ ወዳጆ የፃፈችው የሚመስላቸው ብዙ ሰዎች አሉ።ዘፈኑን የፃፈው ዮናስ ሙላቱ የተባለ ኪቦርድ ተጫዋች አለ።ቁንጅና እና ብቻሽን የተሰኘ ሁለት ዘፈን ሰጠኝ።ዓለምፀሐይ የፃፈችው ፍረጂኝ የተሰኘውን ዘፈን ነው"
በሌላ በኩል ከራሱ ሕይወት ጋር የሚገኘው ሙዚቃው "እህል ውሃ" የተሰኘው እንደሆነም ተናግሯል"ከራሴ ሕይወት ጋር የሚገናኝ ዘፈን የዘፈንኩት እህል ውሃ የተሰኘውን ዘፈን ነው።ቴዲ አፍሮ የቀድሞ ፍቅረኛዬን ያውቃት ነበር። አሜሪካ ሀገር ሲመጣ ደህና ነች ወይ? ሲለኝ አዎ ደህና ነች ሞክረን ነበር አልሆነም አልሰራም አልኩት።እህል ውሃ የሚለውን ዘፈን ሰርቶ ሰጠኝ። ቴዲን የማደንቀው ትልቅ ጭንቅላት ያለው ልጅ ነው።በዜማም በግጥምም የበሰለ ልጅ ነው"
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ከሁለት አስርት ዓመታት በኃላ 'ምስጢር" የተሰኘ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው ዳዊት መለሠ ሰይፉ ሾው ላይ ቀርቦ ነበር።
በዚህ ቃለመጠየቁ ዳዊት መለሠ በርካታ የእሱ ሙዚቃ ወዳጆች ስለሚወዱለት "ቁንጅና" ሙዚቃው ተከታዩን ብሏል"ቁንጅና የተሰኘው ዘፈኔን ዓለምፀሐይ ወዳጆ የፃፈችው የሚመስላቸው ብዙ ሰዎች አሉ።ዘፈኑን የፃፈው ዮናስ ሙላቱ የተባለ ኪቦርድ ተጫዋች አለ።ቁንጅና እና ብቻሽን የተሰኘ ሁለት ዘፈን ሰጠኝ።ዓለምፀሐይ የፃፈችው ፍረጂኝ የተሰኘውን ዘፈን ነው"
በሌላ በኩል ከራሱ ሕይወት ጋር የሚገኘው ሙዚቃው "እህል ውሃ" የተሰኘው እንደሆነም ተናግሯል"ከራሴ ሕይወት ጋር የሚገናኝ ዘፈን የዘፈንኩት እህል ውሃ የተሰኘውን ዘፈን ነው።ቴዲ አፍሮ የቀድሞ ፍቅረኛዬን ያውቃት ነበር። አሜሪካ ሀገር ሲመጣ ደህና ነች ወይ? ሲለኝ አዎ ደህና ነች ሞክረን ነበር አልሆነም አልሰራም አልኩት።እህል ውሃ የሚለውን ዘፈን ሰርቶ ሰጠኝ። ቴዲን የማደንቀው ትልቅ ጭንቅላት ያለው ልጅ ነው።በዜማም በግጥምም የበሰለ ልጅ ነው"
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍6❤5
📌የአበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ አባት አረፉ
የታዋቂው የሙዚቃ ሰው አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ወላጅ አባት ማረፋቸው ተሰምቷል።
አበጋዝ ከወላጅ አባቱ አቶ ክብረወርቅ ጋር ከወራት በፊት በታዋቂዋ ሞዴልና ፋሽን ዲዛይነር አና ጌታነህ ፕሮውዲስ በሚደረገው ፕሮግራም ( በአቦል ቲቪ ) ላይ ቀርቦ እንደነበር ይታወቃል።
ምናልባትም ከቅርብ ሰዎቹ ውጭ ብዙ አድናቂዎቹ አባቱን በመልክ ያዩዋቸው በዚያ ፕሮግራም ነው። የሙዚቀኛ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ አባት አቶ ክብረወርቅ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የታዋቂው የሙዚቃ ሰው አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ወላጅ አባት ማረፋቸው ተሰምቷል።
አበጋዝ ከወላጅ አባቱ አቶ ክብረወርቅ ጋር ከወራት በፊት በታዋቂዋ ሞዴልና ፋሽን ዲዛይነር አና ጌታነህ ፕሮውዲስ በሚደረገው ፕሮግራም ( በአቦል ቲቪ ) ላይ ቀርቦ እንደነበር ይታወቃል።
ምናልባትም ከቅርብ ሰዎቹ ውጭ ብዙ አድናቂዎቹ አባቱን በመልክ ያዩዋቸው በዚያ ፕሮግራም ነው። የሙዚቀኛ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ አባት አቶ ክብረወርቅ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢6💔3
📌ለሚዲያ በሰጡት መረጃ ከኃላፊነታቸው ተነሱ
የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር በአካባቢው ስለተከሰተው “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው ተላላፊ በሽታ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው ለመገናኛ ብዙሀን መረጃ መስጠታቸውን ተከትሎ ከሀላፊነታቸው ተነሱ።
የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢንያም አስራት ለአንድ ዓለማቀፍ ሚዲያ “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው በሽታ ሳቢያ ሀኪሞችን ጨምሮ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው መረጃ በመስጠታቸው ከሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ምስጢሩ ሐምደኪ በተጻፈ ደብዳቤ ከሕዳር 5 ቀን 2028 ዓ.ም ከሀላፊነታቸው መነሳታቸው ተነግሯቸዋል።
ዳይሬክተሩ ከሃላፊነት ከመነሳታቸው በፊት ወደ ሆስፒታሉ መጥተው ከታከሙት አራት በሽተኞች አንዱ በህይወት እንዳለ እና የተሻለ የሚባል የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ሁለት የሆስፒታላቸው የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ እስካሁን ስድስት ሰዎች ተመሳሳይ ምልክቶችን በማሳየት ህይወታቸው ማለፉን ለዶቸ ቨለ ራዲዮ በይፋ ገልፀው ነበር።
የበሽታው ክስተትና ምንነት ዓለማቀፍ ትኩረት የሳበ ሲሆን የዓለም የጤና ድርጅትም ከመንግስት ጋር በመቀናጀት አስቸኳይ የመስክ ቡድን ወደ ስፍራው ልኳል።
የጤና ሚኒስቴር እስከአሁን ድረስ ስምንት ሰዎች በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑን ባወጣው መግለጫ ይፋ ያደረገ ሲሆን ስለ ሞቱ ሰዎች ያለው ነገር የለም።
ዶክተር ቢንያም አስራት በበሽታው ሞት መመዝገቡን ይፋ ካደረጉ በኋላ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነ የቅርብ የስራ ባልደረቦቻቸው ነግረውናል ሲል ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር በአካባቢው ስለተከሰተው “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው ተላላፊ በሽታ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው ለመገናኛ ብዙሀን መረጃ መስጠታቸውን ተከትሎ ከሀላፊነታቸው ተነሱ።
የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢንያም አስራት ለአንድ ዓለማቀፍ ሚዲያ “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው በሽታ ሳቢያ ሀኪሞችን ጨምሮ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው መረጃ በመስጠታቸው ከሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ምስጢሩ ሐምደኪ በተጻፈ ደብዳቤ ከሕዳር 5 ቀን 2028 ዓ.ም ከሀላፊነታቸው መነሳታቸው ተነግሯቸዋል።
ዳይሬክተሩ ከሃላፊነት ከመነሳታቸው በፊት ወደ ሆስፒታሉ መጥተው ከታከሙት አራት በሽተኞች አንዱ በህይወት እንዳለ እና የተሻለ የሚባል የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ሁለት የሆስፒታላቸው የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ እስካሁን ስድስት ሰዎች ተመሳሳይ ምልክቶችን በማሳየት ህይወታቸው ማለፉን ለዶቸ ቨለ ራዲዮ በይፋ ገልፀው ነበር።
የበሽታው ክስተትና ምንነት ዓለማቀፍ ትኩረት የሳበ ሲሆን የዓለም የጤና ድርጅትም ከመንግስት ጋር በመቀናጀት አስቸኳይ የመስክ ቡድን ወደ ስፍራው ልኳል።
የጤና ሚኒስቴር እስከአሁን ድረስ ስምንት ሰዎች በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑን ባወጣው መግለጫ ይፋ ያደረገ ሲሆን ስለ ሞቱ ሰዎች ያለው ነገር የለም።
ዶክተር ቢንያም አስራት በበሽታው ሞት መመዝገቡን ይፋ ካደረጉ በኋላ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነ የቅርብ የስራ ባልደረቦቻቸው ነግረውናል ሲል ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😡31❤5😁2🤯2🤬2🤨2🤔1
📌እንጀራ በሸቀጣ ሸቀጦች ሱቅ መሸጥ መከልከሉ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣንን የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ የተለያዩ መርዛማ ነገሮች ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦን መሸጥ ልክ ባለመሆኑ ለመከልከል መገደዳቸውን ተናግረዋል ሲል ነው ዘገባው የጠቀሰው።
እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው በምግብ ቤቶች፣ በዳቦ ቤተች እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ መሆኑንም በማንሳትም ያልተፈቀደላቸው ነጋዴዎችም ሲሸጡ ከተገኙ አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስገንዝበዋል ሲል ገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣንን የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ የተለያዩ መርዛማ ነገሮች ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦን መሸጥ ልክ ባለመሆኑ ለመከልከል መገደዳቸውን ተናግረዋል ሲል ነው ዘገባው የጠቀሰው።
እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው በምግብ ቤቶች፣ በዳቦ ቤተች እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ መሆኑንም በማንሳትም ያልተፈቀደላቸው ነጋዴዎችም ሲሸጡ ከተገኙ አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስገንዝበዋል ሲል ገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😱9😁8❤4👍3
📌የሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ አልበም ሊለቀቅ ነው
የሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ "ብርሃን" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው በመሳሪያ የተቀነባበረ የሙዚቃ አልበም የፊታችን አርብ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሙዚቃ አፍቃሪያን ይደርሳል ተብሏል።
ለማዘጋጀት አንድ ዓመት እንደወሰደ የተነገረው "ብርሃን" የሙዚቃ አልበም አስር አንድ የሙዚቃ ስብስቦችን ይዟል።
"ብርሀን" በተሰኘው ሁለተኛ አልበሙ በኪቦርድ፣ ቤዝ፣አኮስቲክ ጊታር፣ክራር፣ የሙዚቃ መሳሪያዎች የተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች ተካተዋል።
አልበሙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በትሪፕል ሆቴልና ስፓ የሚመረቅ ይሆናልም ተብሏል።
የፊታችን ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በDeamat records ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃልም ተብሏል።https://youtube.com/@deamatrecords?si=91IxewcK1ZdGshgL
ሙዚቀኛ መሐመድ ከዚህ ቀደሞ "ሰላምታ " የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙን በ2010 ዓ.ም ለአድማጭ አድርሷል።
ሙዚቀኛ መሐመድ የሙዚቃ ኪቦርድ መጫወት የጀመረው 1998 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዓመት አፍሪካ ጃዝ ስኩል ( ጃዝ አምባ ) ተምሯል።
ሙዚቀኛው ከትግርኛ ዘፋኞች መሐል ለረጅም ጊዜ የአብርሃም ገብረመድህን ፣ የማህሌት ገብረጊዮርጊስ ፣ የሸዊት መዝገቦ ኪቦርዲስት በመሆን በብዙ አገራት ቱር አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ "ብርሃን" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው በመሳሪያ የተቀነባበረ የሙዚቃ አልበም የፊታችን አርብ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሙዚቃ አፍቃሪያን ይደርሳል ተብሏል።
ለማዘጋጀት አንድ ዓመት እንደወሰደ የተነገረው "ብርሃን" የሙዚቃ አልበም አስር አንድ የሙዚቃ ስብስቦችን ይዟል።
"ብርሀን" በተሰኘው ሁለተኛ አልበሙ በኪቦርድ፣ ቤዝ፣አኮስቲክ ጊታር፣ክራር፣ የሙዚቃ መሳሪያዎች የተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች ተካተዋል።
አልበሙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በትሪፕል ሆቴልና ስፓ የሚመረቅ ይሆናልም ተብሏል።
የፊታችን ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በDeamat records ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃልም ተብሏል።https://youtube.com/@deamatrecords?si=91IxewcK1ZdGshgL
ሙዚቀኛ መሐመድ ከዚህ ቀደሞ "ሰላምታ " የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙን በ2010 ዓ.ም ለአድማጭ አድርሷል።
ሙዚቀኛ መሐመድ የሙዚቃ ኪቦርድ መጫወት የጀመረው 1998 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዓመት አፍሪካ ጃዝ ስኩል ( ጃዝ አምባ ) ተምሯል።
ሙዚቀኛው ከትግርኛ ዘፋኞች መሐል ለረጅም ጊዜ የአብርሃም ገብረመድህን ፣ የማህሌት ገብረጊዮርጊስ ፣ የሸዊት መዝገቦ ኪቦርዲስት በመሆን በብዙ አገራት ቱር አድርጓል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤8👍7🔥1
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ቀን ነው
የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ቀን በየዓመቱ በጎርጎሮሳዊያኑ የጊዜ ቀመር November 19 ይከበራል።
ጋዜጠኝነት ዜና እና መረጃን የመሰብሰብ፣ የማጣራት፣ የመተንተን እና ለህዝብ የማቅረብ ተግባር ወይም ሙያ ነው።
ጋዜጠኞች በሥልጣን ላይ ያሉትን ተጠያቂ በማድረግ እና ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመስጠት በህብረተሰቡ ውስጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ በሃሳብ ደረጃ ይታመናል።
ጋዜጠኝነት እውነትን የማወቅ ፍላጎትና ጉጉት ነው። ጋዜጠኝነት ታማኝነትን የተላበሰ ሙያ ነው። በስራው ታማኝ እና ስነ ምግባር ያለው፥ ሁል ጊዜም እውነትን ለመናገር የሚጥር ነው ጋዜጠኛ የሚባል ጋዜጠኛ።
ጋዜጠኝነት ፅናት ነው። ጽኑ መሆንንና ቆራጥነትን ያዘለ፥ ከፍራቻ የፀዳ፤ ገለልተኛነትን የተላበሰ ነው ጋዜጠኝነት።
ከአድሎ መንፃት፤ የርህራሄ ተምሳሌት መሆን፤ ተጨባጭነት፤ አሳማኝና ምክንያታዊ መሆን ነው ጋዜጠኝነት።
ጋዜጠኝነት ነፃነት ነው። ራሱን የቻለ እና በውጫዊ ጫናዎች እና ፍላጎቶች ተጽእኖ ስር አለመውደቅ ነው ጋዜጠኝነት።
የመረጃ ምንጮችን ሚስጥራዊነት ማክበር፤ ለተጠያቂነት ራስን ማዘጋጀት፤ ለተሰራው ስራ ተጠያቂ መሆን፤ ስህተትን ለማረም እና ለስህተት ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ መሆን ነው ትክክለኛ ጋዜጠኝነት።
እናም ከላይ የተነሱ ሀሳቦችን በጥቂቱ የምታሟሉ ጋዜጠኞች፥ እንኳን ለቀናችሁ አደረሳችሁ።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ቀን በየዓመቱ በጎርጎሮሳዊያኑ የጊዜ ቀመር November 19 ይከበራል።
ጋዜጠኝነት ዜና እና መረጃን የመሰብሰብ፣ የማጣራት፣ የመተንተን እና ለህዝብ የማቅረብ ተግባር ወይም ሙያ ነው።
ጋዜጠኞች በሥልጣን ላይ ያሉትን ተጠያቂ በማድረግ እና ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመስጠት በህብረተሰቡ ውስጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ በሃሳብ ደረጃ ይታመናል።
ጋዜጠኝነት እውነትን የማወቅ ፍላጎትና ጉጉት ነው። ጋዜጠኝነት ታማኝነትን የተላበሰ ሙያ ነው። በስራው ታማኝ እና ስነ ምግባር ያለው፥ ሁል ጊዜም እውነትን ለመናገር የሚጥር ነው ጋዜጠኛ የሚባል ጋዜጠኛ።
ጋዜጠኝነት ፅናት ነው። ጽኑ መሆንንና ቆራጥነትን ያዘለ፥ ከፍራቻ የፀዳ፤ ገለልተኛነትን የተላበሰ ነው ጋዜጠኝነት።
ከአድሎ መንፃት፤ የርህራሄ ተምሳሌት መሆን፤ ተጨባጭነት፤ አሳማኝና ምክንያታዊ መሆን ነው ጋዜጠኝነት።
ጋዜጠኝነት ነፃነት ነው። ራሱን የቻለ እና በውጫዊ ጫናዎች እና ፍላጎቶች ተጽእኖ ስር አለመውደቅ ነው ጋዜጠኝነት።
የመረጃ ምንጮችን ሚስጥራዊነት ማክበር፤ ለተጠያቂነት ራስን ማዘጋጀት፤ ለተሰራው ስራ ተጠያቂ መሆን፤ ስህተትን ለማረም እና ለስህተት ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ መሆን ነው ትክክለኛ ጋዜጠኝነት።
እናም ከላይ የተነሱ ሀሳቦችን በጥቂቱ የምታሟሉ ጋዜጠኞች፥ እንኳን ለቀናችሁ አደረሳችሁ።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤26👍8🥰1
📌አሻም ቲቪ 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ ተከሰሰ
አሻም ቴሌቪዥን ብዛታቸው 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ አማካይነት ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ በዚሁም ሂደት የድርጅቱ ንብረቶች ሙሉ በሙሉ እንዳይንቀሳቀሱ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ዕግድ እንደተላለፈበት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል። ምንጮቹ አክለውም፣ ለጣቢያው ጋዜጠኞች የሶስት ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈለ አመልክተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁኑ ሰዓት ድረስ፣ አሻም ቲቪ የሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ የለም።
ከዚህ ቀደም የጣቢያው ቢሮ መታሸጉ የሚታወስ ሲሆን፣ ጣቢያውን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው አሻም ትሬዲንግ የእሸጋ ተግባሩ "ጣቢያውን ወደ መደበኛ ስራው ለመመለስ ከሚደረጉ ጥረቶች" ጋር አስተሳስሮ ምላሽ ሰጥቶ ነበር።
©️ሚኪያስ ጥላሁን
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አሻም ቴሌቪዥን ብዛታቸው 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ አማካይነት ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ በዚሁም ሂደት የድርጅቱ ንብረቶች ሙሉ በሙሉ እንዳይንቀሳቀሱ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ዕግድ እንደተላለፈበት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል። ምንጮቹ አክለውም፣ ለጣቢያው ጋዜጠኞች የሶስት ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈለ አመልክተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁኑ ሰዓት ድረስ፣ አሻም ቲቪ የሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ የለም።
ከዚህ ቀደም የጣቢያው ቢሮ መታሸጉ የሚታወስ ሲሆን፣ ጣቢያውን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው አሻም ትሬዲንግ የእሸጋ ተግባሩ "ጣቢያውን ወደ መደበኛ ስራው ለመመለስ ከሚደረጉ ጥረቶች" ጋር አስተሳስሮ ምላሽ ሰጥቶ ነበር።
©️ሚኪያስ ጥላሁን
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤4👍3😱3🤔1🕊1
📌‘Crazy Day’፣ ‘Valentine Day’ እና ሌሎች ‘መጤ ባህሎች’ በትምህርት ቤቶች የሚከለክል አዲስ ደንብ መዘጋጀቱ ተገለፀ
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማትና አካባቢያቸው የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ አዲስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ማውጣቱን አስታውቋል።
ይህ ደንብ ከኢትዮጵያውያን ወግና ልማድ ጋር ይቃረናሉ ተብለው የተለዩ የውጭ ባህላዊ ልማዶችን ጨምሮ፣ እየጨመረ የመጣውን አዋኪ ጉዳዮች ለመግታት ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
የደንቡ ዋና ዓላማ በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን በመከላከል፣ ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ፣ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀና ግብረ-ገብነትን የተላበሰ ብቁ ትውልድ እንዲፈጠር ማስቻል ነው።
ደንቡ የኢትዮጵያውያንን ባህልና ወግ የሚቃረኑ ተብለው በግልጽ የተዘረዘሩ አሉታዊ መጤ ድርጊቶችንና ክብረ በዓላትን በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መፈጸም ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
የሀገሪቷን ባህልና ወግ ይቃረናል ከተባሉት ድርጊቶች ዉስጥ Crazy Day፣ Gentle Day ፣ Olds Day፣ Valentine Day፣ Color Day፣ Pyjama Day የሚሉት ይገኙበታል።
የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር ቅጣት በአዲሱ ደንብ ይጠብቃቸዋል ተብሏል።
©️ ዘገባው የካፒታል ጋዜጣ ነው
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማትና አካባቢያቸው የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ አዲስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ማውጣቱን አስታውቋል።
ይህ ደንብ ከኢትዮጵያውያን ወግና ልማድ ጋር ይቃረናሉ ተብለው የተለዩ የውጭ ባህላዊ ልማዶችን ጨምሮ፣ እየጨመረ የመጣውን አዋኪ ጉዳዮች ለመግታት ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
የደንቡ ዋና ዓላማ በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን በመከላከል፣ ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ፣ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀና ግብረ-ገብነትን የተላበሰ ብቁ ትውልድ እንዲፈጠር ማስቻል ነው።
ደንቡ የኢትዮጵያውያንን ባህልና ወግ የሚቃረኑ ተብለው በግልጽ የተዘረዘሩ አሉታዊ መጤ ድርጊቶችንና ክብረ በዓላትን በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መፈጸም ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
የሀገሪቷን ባህልና ወግ ይቃረናል ከተባሉት ድርጊቶች ዉስጥ Crazy Day፣ Gentle Day ፣ Olds Day፣ Valentine Day፣ Color Day፣ Pyjama Day የሚሉት ይገኙበታል።
የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር ቅጣት በአዲሱ ደንብ ይጠብቃቸዋል ተብሏል።
©️ ዘገባው የካፒታል ጋዜጣ ነው
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍36❤9👎5🤣5👏4🤡1
የልጆች ፕሮግራም አዘጋጅ ሰሎሞን ገብረስላሴ አረፉ
ከብስራተ ወንጌል ጀምሮ እስከ ኢትዮጵያ ሬድዮ በልጆች ፕሮግራም አዘጋጅነታቸው የሚታወቁት ጋሽ ሰሎሞን ገብሥላሴ ዛሬ ህዳር 12 2018 በ83 ዓመታቸው ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ለተወዳጅ ሚድያ ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል።
አቶ ሰለሞን ከልጆች ፕሮግራም በተጨማሪ ሰዎችና ስራዎቻቸው ፤ ህብረተሰባችን እንዲሁም ባህላዊ ሙዚቃዎቻችን የተባሉ ፕሮግራሞችን በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ፡፡
በኢትዮጵያ ሬዲዮ ከፕሮግራም አዘጋጅነት እስከ ዋና አዘጋጅነት በተጨማሪም የብሄራዊ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ተጠባባቂ ሃላፊ እንዲሁም የምስራች ድምጽ አለም አቀፍ አገልግሎት ሃላፊ ሆነው በ1986 በጡረታ እስከተሰናበቱበት ድረስ ለ40 ዓመታት ለሙያቸው ታማኝ ሆነው አገልግለዋል፡፡
በጡረታ ከተገለሉ በኃላም እንደገና ወደ ሙያው ተመልሰው በምስራች ድምፅ ተዘጋጅቶ ከደቡብ አፍሪካ በሚተላለፈው ተመሳሳይ ይዘት ባለው ፕሮግራም በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ።
የምስራች ድምፅን ደርግ ሲወርሰውና አንዳንድ ጋዜጠኞች ከስራ ሲሰናበቱ አቶ ሰለሞን በስራቸው እንዲቀጥሉ ተደርጎ ነበር ፡፡
በጋዜጠኝነት ሙያቸውም በአድማጮች ዘንድ ተወዳጅ ከመሆናቸውም በላይ ታዋቂ ጋዜጠኞችንና በሚድያ እና በኪነ-ጥበቡ መስክ ተሰማርተው እናት ሀገራቸውን በማገልገል ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችንም ያፈሩ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነበሩ።እመቤት ወ/ገብርኤል፣ ብርሃኑ ገ/ማርያም፣ አስካለ ተስፋዬ፣ ዓለም አታፋረደው፣ አማረች ሙሉ ይገኙበታል።
አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ለሀገርና ለህዝብ ላከናወኑት ተግባር በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፍ የ10ኛውን የበጎ ሰው ሽልማት ተቀብለዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ከብስራተ ወንጌል ጀምሮ እስከ ኢትዮጵያ ሬድዮ በልጆች ፕሮግራም አዘጋጅነታቸው የሚታወቁት ጋሽ ሰሎሞን ገብሥላሴ ዛሬ ህዳር 12 2018 በ83 ዓመታቸው ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ለተወዳጅ ሚድያ ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል።
አቶ ሰለሞን ከልጆች ፕሮግራም በተጨማሪ ሰዎችና ስራዎቻቸው ፤ ህብረተሰባችን እንዲሁም ባህላዊ ሙዚቃዎቻችን የተባሉ ፕሮግራሞችን በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ፡፡
በኢትዮጵያ ሬዲዮ ከፕሮግራም አዘጋጅነት እስከ ዋና አዘጋጅነት በተጨማሪም የብሄራዊ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ተጠባባቂ ሃላፊ እንዲሁም የምስራች ድምጽ አለም አቀፍ አገልግሎት ሃላፊ ሆነው በ1986 በጡረታ እስከተሰናበቱበት ድረስ ለ40 ዓመታት ለሙያቸው ታማኝ ሆነው አገልግለዋል፡፡
በጡረታ ከተገለሉ በኃላም እንደገና ወደ ሙያው ተመልሰው በምስራች ድምፅ ተዘጋጅቶ ከደቡብ አፍሪካ በሚተላለፈው ተመሳሳይ ይዘት ባለው ፕሮግራም በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ።
የምስራች ድምፅን ደርግ ሲወርሰውና አንዳንድ ጋዜጠኞች ከስራ ሲሰናበቱ አቶ ሰለሞን በስራቸው እንዲቀጥሉ ተደርጎ ነበር ፡፡
በጋዜጠኝነት ሙያቸውም በአድማጮች ዘንድ ተወዳጅ ከመሆናቸውም በላይ ታዋቂ ጋዜጠኞችንና በሚድያ እና በኪነ-ጥበቡ መስክ ተሰማርተው እናት ሀገራቸውን በማገልገል ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችንም ያፈሩ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነበሩ።እመቤት ወ/ገብርኤል፣ ብርሃኑ ገ/ማርያም፣ አስካለ ተስፋዬ፣ ዓለም አታፋረደው፣ አማረች ሙሉ ይገኙበታል።
አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ለሀገርና ለህዝብ ላከናወኑት ተግባር በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፍ የ10ኛውን የበጎ ሰው ሽልማት ተቀብለዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5😢5🙏2🫡2🤔1💔1
📌የውበት ሠሌዳ መጽሐፍ ነገ ይመረቃል
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የውበት ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ቅዳሜ ህዳር 13 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 10:00 ጀምሮ በጣይቱ የባህልና የትምህርት ማዕከል ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮተ መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ መራሔ ተውኔት ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ፣ የዝና ወርቁ አርቲስት ስዩም ተፈራ በክብር እንግድነት ይገኛሉ ተብሏል።
ገጣሚያኑ ሰለሞን ሳህለ፣ዋሲሁን በላይ፣ ፌቤን ፋንጮ ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
"የውበት "በ115 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን
43 ግጥሞችን በውስጡ ይዟል በ350 የጀርባ ዋጋም ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" እና "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የውበት ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ቅዳሜ ህዳር 13 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 10:00 ጀምሮ በጣይቱ የባህልና የትምህርት ማዕከል ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮተ መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ መራሔ ተውኔት ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ፣ የዝና ወርቁ አርቲስት ስዩም ተፈራ በክብር እንግድነት ይገኛሉ ተብሏል።
ገጣሚያኑ ሰለሞን ሳህለ፣ዋሲሁን በላይ፣ ፌቤን ፋንጮ ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
"የውበት "በ115 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን
43 ግጥሞችን በውስጡ ይዟል በ350 የጀርባ ዋጋም ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" እና "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3👍2🔥2🥰1
📌አጫጭር ፊልሞች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል አጫጭር ፊልሞች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት አሰናድቷል፡፡
ውይይቱ ቅዳሜ ህዳር 13/2018 ዓ.ም ከ8 ሰዓት ጀምሮ በአካዳሚው ቅጥር ግቢ ይካሄዳል፡፡
አንጋፋው የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ በቀረቡት ፊልሞች ላይ ሙያዊ ዳሰሳውን ያቀርባል፡፡
ዝግጅቱ የአለ ስነጥበብና ዲዛይን ትምሕርት ቤት እና የልቀት ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች በሰሯቸው አጫጭር ፊልሞች ያተኩራል፡፡
በተጨማሪም ህዳር 11 እና 12 ከ8፡00– 11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ ከ3፡00 – 8፡00 በአካዳሚው አዳራሽ ለዕይታ ይቀርባሉም ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል አጫጭር ፊልሞች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት አሰናድቷል፡፡
ውይይቱ ቅዳሜ ህዳር 13/2018 ዓ.ም ከ8 ሰዓት ጀምሮ በአካዳሚው ቅጥር ግቢ ይካሄዳል፡፡
አንጋፋው የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ በቀረቡት ፊልሞች ላይ ሙያዊ ዳሰሳውን ያቀርባል፡፡
ዝግጅቱ የአለ ስነጥበብና ዲዛይን ትምሕርት ቤት እና የልቀት ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች በሰሯቸው አጫጭር ፊልሞች ያተኩራል፡፡
በተጨማሪም ህዳር 11 እና 12 ከ8፡00– 11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ ከ3፡00 – 8፡00 በአካዳሚው አዳራሽ ለዕይታ ይቀርባሉም ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5🔥1
📌የያንጎ ኢትዮጵያ የመንገድ ደኅንነት ሥልጠና
ያንጎ ኢትዮጵያ የመንገድ ደኅንነት ሥልጠና እና የአሽከርካሪዎች ብቃት ማረጋገጫ ዕውቅና መስጠት ጀመረ
የዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ፣ ያንጎ ግሩፕ አካል የሆነውና በጂቱጂ አይቲ ሶሊውሽን አ.ማ. እና በኤለጋንስ ኢምፖርት ኤንድ ኤክስፖርት ፒኤልሲ ሥር የሚተዳደረው ያንጎ ኢትዮጵያ፣ ለደኅንነት፣ ለአገልግሎት ልህቀት እና ቅልጥፍና እንዲሁም ለማኅበረሰብ ተሳትፎ ያለውንቁርጠኝነት በማጠናከር የመንገድ ደኅንነት ፕሮግራም እና የመጀመሪያ እርዳታ እና የአገልግሎት ልህቀት ሥልጠና መርሐግብር ለአጋር አሽከርካሪዎች መስጠት ጀምሯል፡፡
“ያንጎ ኬርስ”በተሰኘው የማኅበራዊ ድጋፍ አገልግሎት ስር የተጀመረው ይህተነሣሽነት፣ የኩባንያው ትኩረት ይበልጥ ደኅንነታቸው በተጠበቁ መንገዶች፣ በጠንካራ ማኅበረሰቦች እና ለተሳፋሪዎች ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡
የሥልጠናው ክፍለ ጊዜ፣ አጋር አሽከርካሪዎች የመንገድደኅንነት ግንዛቤ እና ተግባራዊ የመጀመሪያ ህክምናክህሎቶችን እንዲታጠቁ በማድረግና የተሳፋሪዎችን ልምድበማጎልበት- በመላ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰፊው ሕዝባዊደኅንነት አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ታምኖበታል።
ተጨማሪውን ያንብቡ:https://sl1nk.com/m4IWs
ያንጎ ኢትዮጵያ የመንገድ ደኅንነት ሥልጠና እና የአሽከርካሪዎች ብቃት ማረጋገጫ ዕውቅና መስጠት ጀመረ
የዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ፣ ያንጎ ግሩፕ አካል የሆነውና በጂቱጂ አይቲ ሶሊውሽን አ.ማ. እና በኤለጋንስ ኢምፖርት ኤንድ ኤክስፖርት ፒኤልሲ ሥር የሚተዳደረው ያንጎ ኢትዮጵያ፣ ለደኅንነት፣ ለአገልግሎት ልህቀት እና ቅልጥፍና እንዲሁም ለማኅበረሰብ ተሳትፎ ያለውንቁርጠኝነት በማጠናከር የመንገድ ደኅንነት ፕሮግራም እና የመጀመሪያ እርዳታ እና የአገልግሎት ልህቀት ሥልጠና መርሐግብር ለአጋር አሽከርካሪዎች መስጠት ጀምሯል፡፡
“ያንጎ ኬርስ”በተሰኘው የማኅበራዊ ድጋፍ አገልግሎት ስር የተጀመረው ይህተነሣሽነት፣ የኩባንያው ትኩረት ይበልጥ ደኅንነታቸው በተጠበቁ መንገዶች፣ በጠንካራ ማኅበረሰቦች እና ለተሳፋሪዎች ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡
የሥልጠናው ክፍለ ጊዜ፣ አጋር አሽከርካሪዎች የመንገድደኅንነት ግንዛቤ እና ተግባራዊ የመጀመሪያ ህክምናክህሎቶችን እንዲታጠቁ በማድረግና የተሳፋሪዎችን ልምድበማጎልበት- በመላ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰፊው ሕዝባዊደኅንነት አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ታምኖበታል።
ተጨማሪውን ያንብቡ:https://sl1nk.com/m4IWs
❤2
📌 "ማስተዋል" ኮንሰርት ዛሬ ይካሄዳል
የድምጻዊ ማስተዋል እያዩ "ማስተዋል" የሙዚቃ ኮንሰርት ዛሬ ህዳር 13 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
በዚህ ኮንሰርት ላይ ከማስተዋል እያዩ ባሻገር ድምጻዊት ሔዋን ገብረወልድ የሙዚቃ ስራዋን ታቀርባለች ተብሏል።
የራሱን ነጠላ ዜማዎች ጨምሮ የተለያዩ ድምፃዊያን ሙዚቃዎችን ማለፊያ በሚባል ሁኔታ ሲጫወተው የቆየው ድምጻዊ ማስተዋል በ2016 ዓ.ም የካቲት 1 ነበር "እንዚራ" ሲል የሰየወመውን የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው። ይህም አልበሙም በበርካቶች ዘንድ ተወዶለታል።
አልበሙ ለአድማጮች ከቀረበ 1 ዓመት ከስምንት ወር የቆየው ሲሆን የሙዚቃ ኮንሰርትም ሳይዘጋጅለት ቆይቷል።
የድምጻዊው አድናቂዎቹም የማስተዋል እያዩ ኮንሰርት መቼ ነው የሚል ጥያቄዎች ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የድምጻዊ ማስተዋል እያዩ "ማስተዋል" የሙዚቃ ኮንሰርት ዛሬ ህዳር 13 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
በዚህ ኮንሰርት ላይ ከማስተዋል እያዩ ባሻገር ድምጻዊት ሔዋን ገብረወልድ የሙዚቃ ስራዋን ታቀርባለች ተብሏል።
የራሱን ነጠላ ዜማዎች ጨምሮ የተለያዩ ድምፃዊያን ሙዚቃዎችን ማለፊያ በሚባል ሁኔታ ሲጫወተው የቆየው ድምጻዊ ማስተዋል በ2016 ዓ.ም የካቲት 1 ነበር "እንዚራ" ሲል የሰየወመውን የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው። ይህም አልበሙም በበርካቶች ዘንድ ተወዶለታል።
አልበሙ ለአድማጮች ከቀረበ 1 ዓመት ከስምንት ወር የቆየው ሲሆን የሙዚቃ ኮንሰርትም ሳይዘጋጅለት ቆይቷል።
የድምጻዊው አድናቂዎቹም የማስተዋል እያዩ ኮንሰርት መቼ ነው የሚል ጥያቄዎች ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3👍1🥰1
📌የግመል ስጋ በአዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ከተማ ሕገ-ወጥ የግመል እርድ መበራከቱንና ድርጊቱ ከወትሮው የተለየና አዲስ ፈተና እንደሆነበት የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታውቋል።
የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ግመሎች ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ታርደው ለሽያጭ እየቀረቡ መሆኑን ገልጸው፣ "በተለይም ወደ ቦሌ ሚካኤል ባሉ አካባቢዎች የግመል ስጋ በድብቅ አስገብተው የሚሸጡ መኖራቸውን" አስረድተዋል።
ሕገ-ወጥ እርድ የሚፈጸመው አስፈላጊው ምርመራ ባልተካሄደበትና ባልተፈቀደ ቦታ ላይ ሲሆን እንደሆነ፣ ይህ የህብረተሰቡን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ድርጅቱ ለማስተካከል እየሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
"ሕብረተሰቡ ጥራቱን የጠበቀ ስጋ መውሰድ እንደሚፈልግ እናውቃለን" ያሉት ሥራ አስኪያጁ፣ ለዚህም ሲባል ማኅበረሰቡ ሕገ-ወጥ የግመል እርድን ሲመለከት ወዲያውኑ ጥቆማ መስጠት እንደሚገባው አሳስበዋል።
ሕጋዊው የግመል እርድ በቄራዎች ድርጅት በተለይም በአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ በስፋት እንደሚከናወንና፣ ስጋውን በስፋት ለሚጠቀሙት የሶማሌና የአፋር ህዝብ ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
የቄራዎች ድርጅት በአማካኝ በቀን ከ7 እስከ 10 የሚደርሱ ግመሎችን እርድ እንደሚያከናውን ጭምር ተዘግቧል።
©️አሐዱ ሬድዮ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በአዲስ አበባ ከተማ ሕገ-ወጥ የግመል እርድ መበራከቱንና ድርጊቱ ከወትሮው የተለየና አዲስ ፈተና እንደሆነበት የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታውቋል።
የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ግመሎች ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ታርደው ለሽያጭ እየቀረቡ መሆኑን ገልጸው፣ "በተለይም ወደ ቦሌ ሚካኤል ባሉ አካባቢዎች የግመል ስጋ በድብቅ አስገብተው የሚሸጡ መኖራቸውን" አስረድተዋል።
ሕገ-ወጥ እርድ የሚፈጸመው አስፈላጊው ምርመራ ባልተካሄደበትና ባልተፈቀደ ቦታ ላይ ሲሆን እንደሆነ፣ ይህ የህብረተሰቡን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ድርጅቱ ለማስተካከል እየሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
"ሕብረተሰቡ ጥራቱን የጠበቀ ስጋ መውሰድ እንደሚፈልግ እናውቃለን" ያሉት ሥራ አስኪያጁ፣ ለዚህም ሲባል ማኅበረሰቡ ሕገ-ወጥ የግመል እርድን ሲመለከት ወዲያውኑ ጥቆማ መስጠት እንደሚገባው አሳስበዋል።
ሕጋዊው የግመል እርድ በቄራዎች ድርጅት በተለይም በአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ በስፋት እንደሚከናወንና፣ ስጋውን በስፋት ለሚጠቀሙት የሶማሌና የአፋር ህዝብ ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
የቄራዎች ድርጅት በአማካኝ በቀን ከ7 እስከ 10 የሚደርሱ ግመሎችን እርድ እንደሚያከናውን ጭምር ተዘግቧል።
©️አሐዱ ሬድዮ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤4🕊1
📌 "ቢራቢሮ "የተሰኘ ተውኔት ለእይታ ሊበቃ ነው
በደራሲ ኤልያስ ቤተማርያም ተጽፎ በዘካርያስ ረታ የተዘጋጀው "ቢራቢሮ" የተሰኘ ተውኔት የፊታችን ረቡዕ ህዳር 17 ከ11:30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይቀርባል።
በተውኔቱ ላይ ሩሐማ ኃ/ሚካኤል ፣ ዮናታን መኮንን፣ እየሩሳሌም ገ/ስላሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል።
የተወኔቱ ሚውዚክ ዳይሬክተር ዮሐንስ አማረ ሲሆን የፕሮዳክሽን ማናጀሮች ሀና ታዬ(እርጎዬ) እና ሔኖክ ተሾመ ናቸው።
ተውኔቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ አመት የቴአትር ጥበባት ተማሪዎች የተዘጋጀ ነው።
"ቢራቢሮ" ተውኔት ባለፈው ዓመት ሰኔ 23 ብሔራዊ ቴአትር ቤት ለተመልካች ቀርቦ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በደራሲ ኤልያስ ቤተማርያም ተጽፎ በዘካርያስ ረታ የተዘጋጀው "ቢራቢሮ" የተሰኘ ተውኔት የፊታችን ረቡዕ ህዳር 17 ከ11:30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይቀርባል።
በተውኔቱ ላይ ሩሐማ ኃ/ሚካኤል ፣ ዮናታን መኮንን፣ እየሩሳሌም ገ/ስላሴና ሌሎችም ተሳትፈውበታል።
የተወኔቱ ሚውዚክ ዳይሬክተር ዮሐንስ አማረ ሲሆን የፕሮዳክሽን ማናጀሮች ሀና ታዬ(እርጎዬ) እና ሔኖክ ተሾመ ናቸው።
ተውኔቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ አመት የቴአትር ጥበባት ተማሪዎች የተዘጋጀ ነው።
"ቢራቢሮ" ተውኔት ባለፈው ዓመት ሰኔ 23 ብሔራዊ ቴአትር ቤት ለተመልካች ቀርቦ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5🥰1
📌"ውብ አዲስ" የሥነጥበብ አውደርዕይ ተከፈተ
"ውብ አዲስ" የተሰኘ የሥነጥበብ አውደርዕይ በዚህ ሳምንት በቅዱስ ጊዮርጊስ ጎላ የሥነጥበብ ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩረቱን በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያደረገው ይህ አውደርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተከታታይ (ከህዳር-2018 እስከ ህዳር-2019) የሚቀረብ የግል የሥዕል ትርዒት ነው።
ይህ በዓመቱ ውስጥ በተከታታይ የሚቀርብ የሥዕል አውደርዕይ በሠዓሊ ሀሮን የተዘጋጀ ነው።
አውደርዕው ከህዳር 11 እስከ ህዳር 22 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ውብ አዲስ" የተሰኘ የሥነጥበብ አውደርዕይ በዚህ ሳምንት በቅዱስ ጊዮርጊስ ጎላ የሥነጥበብ ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩረቱን በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያደረገው ይህ አውደርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተከታታይ (ከህዳር-2018 እስከ ህዳር-2019) የሚቀረብ የግል የሥዕል ትርዒት ነው።
ይህ በዓመቱ ውስጥ በተከታታይ የሚቀርብ የሥዕል አውደርዕይ በሠዓሊ ሀሮን የተዘጋጀ ነው።
አውደርዕው ከህዳር 11 እስከ ህዳር 22 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5👍1
📌የኤፍ.ኤ ካፕ ዋንጫ ወደ ኢትዮጵያ መጣ !
የብሪትሽ ኤንባሲ ከአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና ኤን ዜድ ኮምኒኬሽንስ ጋር በጋራ በመሆን "ሺ ዊንስ" በሚለው ፕሮጀክቱ በቀጣይ ሳምንት ለእግር ኳስ አሰልጣኞች(ሴቶች) ስልጠና ለመስጠት ቀጠሮ ተይዟል።
"ሺ ዊንስ" ወጣት ሴቶችን በስፖርት ለማብቃት የተነደፈ ተነሳሽነት ነው። በዚህ መርሃግብር መሰረት ታዋቂ የቀድሞ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ጨምሮ የበጎ ፍቃደኛ አሰልጣኞች የልዑካን ቡድን አዲስ አበባን በመጎብኘት የአሰልጣኝነት ስልጠናዎችን በማካሄድ፣ ከዓለም አቀፍ አሰልጣኞች ጋር የእግር ኳስ ውድድርን በመምራት፣ ከ17 አመት በታች ያሉ ወጣት ሴት ተሰጥኦዎችን በመለየት እና የስፖርት ትጥቅ ለሚፈልጉ ሴቶች ያስረክባል፣ ስልጠናም ይሰጣል።
ለዚህም ዓላማ ከሀገረ እንግሊዝ በ2013 ከዊጋን አትሌቲክ ጋር የኤፍ.ኤ ካፕ ሻምፒዮን በሆነው ኤመርሰን ቦይሴ የተመራ 3 ኢንተርናሽናል የአሰልጣኞች ቡድን ዛሬ እሁድ ህዳር 14 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ገብቷል።
ከእንግሊዝ ሀገር የሚመጡት ባለሙያዎች ተወዳጁን የኤፍ.ኤ ካፕ ዋንጫን ይዘውም ገብተዋል።
በዚህ መርሐግብር ላይ ለመሳተፍ
👉https://nz-events.vercel.app/rsvp
የብሪትሽ ኤንባሲ ከአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና ኤን ዜድ ኮምኒኬሽንስ ጋር በጋራ በመሆን "ሺ ዊንስ" በሚለው ፕሮጀክቱ በቀጣይ ሳምንት ለእግር ኳስ አሰልጣኞች(ሴቶች) ስልጠና ለመስጠት ቀጠሮ ተይዟል።
"ሺ ዊንስ" ወጣት ሴቶችን በስፖርት ለማብቃት የተነደፈ ተነሳሽነት ነው። በዚህ መርሃግብር መሰረት ታዋቂ የቀድሞ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ጨምሮ የበጎ ፍቃደኛ አሰልጣኞች የልዑካን ቡድን አዲስ አበባን በመጎብኘት የአሰልጣኝነት ስልጠናዎችን በማካሄድ፣ ከዓለም አቀፍ አሰልጣኞች ጋር የእግር ኳስ ውድድርን በመምራት፣ ከ17 አመት በታች ያሉ ወጣት ሴት ተሰጥኦዎችን በመለየት እና የስፖርት ትጥቅ ለሚፈልጉ ሴቶች ያስረክባል፣ ስልጠናም ይሰጣል።
ለዚህም ዓላማ ከሀገረ እንግሊዝ በ2013 ከዊጋን አትሌቲክ ጋር የኤፍ.ኤ ካፕ ሻምፒዮን በሆነው ኤመርሰን ቦይሴ የተመራ 3 ኢንተርናሽናል የአሰልጣኞች ቡድን ዛሬ እሁድ ህዳር 14 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ገብቷል።
ከእንግሊዝ ሀገር የሚመጡት ባለሙያዎች ተወዳጁን የኤፍ.ኤ ካፕ ዋንጫን ይዘውም ገብተዋል።
በዚህ መርሐግብር ላይ ለመሳተፍ
👉https://nz-events.vercel.app/rsvp
❤7😁6
በኮሪደር ልማቱ ወንበሮች ላይ ልብስ ያሰጡ ተቀጡ
በኮሪደር ልማት ለህዝብ ማረፊያ በተሰሩ ወንበሮች ላይ የታጠቡ ልብሶችን ያሰጡ ግለሰቦችና ተቋም ላይ እርምጃ ተወሰደ
ህዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በኮሪደር ልማት በተሰሩ የህዝብ ማረፊያ ወንበሮች ላይ የታጠቡ ልብሶችን ያሰጡ ግለሰቦችና ተቋም እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ።
ድርጊቱን ፈጽመው የተገኙ የኮሪደር ልማቱ የመዝናኛ ካፌ እና ሰራተኞቹን ወደ ህግ በማቅረብ ተጠያቂ በማድረግ ካፌው ተገቢው ቅጣት አስኪቀጣ መታሸጉ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በከተማዋ ውስጥ በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ የኮሪደር ልማቶችና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶችን እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅ ለታለመላቸው ዓላማ ብቻ መገልገልና መጠቀም እንደሚገባም አስታውቋል፡፡
ደንብ ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይ በህጉ መሠረት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ባለስልጣኑ አስታውቋል ሲል ኤኤምኤን ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በኮሪደር ልማት ለህዝብ ማረፊያ በተሰሩ ወንበሮች ላይ የታጠቡ ልብሶችን ያሰጡ ግለሰቦችና ተቋም ላይ እርምጃ ተወሰደ
ህዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በኮሪደር ልማት በተሰሩ የህዝብ ማረፊያ ወንበሮች ላይ የታጠቡ ልብሶችን ያሰጡ ግለሰቦችና ተቋም እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ።
ድርጊቱን ፈጽመው የተገኙ የኮሪደር ልማቱ የመዝናኛ ካፌ እና ሰራተኞቹን ወደ ህግ በማቅረብ ተጠያቂ በማድረግ ካፌው ተገቢው ቅጣት አስኪቀጣ መታሸጉ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በከተማዋ ውስጥ በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ የኮሪደር ልማቶችና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶችን እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅ ለታለመላቸው ዓላማ ብቻ መገልገልና መጠቀም እንደሚገባም አስታውቋል፡፡
ደንብ ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይ በህጉ መሠረት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ባለስልጣኑ አስታውቋል ሲል ኤኤምኤን ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🤣46❤5👏4
📌ኦዳ አዋርድ ሕዳር 30 ይካሄዳል
የዘንድሮው ኦዳ አዋርድ የሽልማት እና የእውቅና የመስጠት ሥነሥርዓት የፊታችን ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በድምቀት ይከናወናል፡፡
ኦዳ አዋርድ ዘንድሮ ለዘጠነኛ ጊዜ በሚያዘጋጀው የሽልማት መርሃግብር ከቀደምት ዓመት ውድድሮች ለየት ባለ መልኩ በመቅረብ ትኩረቱን ሙሉ በሙሉ በሙዚቃው ዘርፍ ላይ ብቻ በማተኮር የሽልማት ስነስርዓቱን እንደሚያከናውን ተነግሯል።
በመሆኑም በሙዚቃው ዘርፍ ብቻ ከሀገር ውስጥ 30 እጩዎችን በ6 የሽልማት ዘርፎች ለምርጫ ያቀረበ ሲሆን ከሀገር ውስጥ እጩዎች በተጨማሪ ከ12 አፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ እጩዎችን ለህዝቡ ይፋ ያደርጋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም እጩዎች ለሽልማት የሚበቁት ሙሉ በሙሉ በህዝብ ምርጫ መሆኑ ተገልጿል።
ከአፍሪካ ሃገራት በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ በ"AFRICAN SUPER STAR” ዘርፍ ላይ ተሸላሚ ለመሆን የሚሳተፉት 12 የአፍሪካ ሃገራት፦ ሩዋንዳ፣ ማሊ፣ ሞሮኮ፣ አንጎላ፣ ማዳጋስካር፣ ኬንያ፣ ጅቡቲ፣ ሲሼልስ፣ ጋና፣ ቶጎ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳ ናቸው።
በተጨማሪም 9ኛው ኦዳ አዋርድ ከሃገር ውስጥ የሙዚቃ ስራዎች ለሽልማት እጩዎችን የሚያቀርብበት ስድስት ዘርፎች ሲኖሩት እነሱም፡- የህይወት ዘመን ተሸላሚ፣የአመቱ ምርጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ አርቲስት፣የአመቱ ምርጥ ቪዲዮ ክሊፕ፣የአመቱ ምርጥ ሴት ድምፃዊት፣የአመቱ ምርጥ ወንድ ድምፃዊ፣የአመቱ ምርጥ ምርጥ ሀገርኛ ዘፋኝ ናቸው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የዘንድሮው ኦዳ አዋርድ የሽልማት እና የእውቅና የመስጠት ሥነሥርዓት የፊታችን ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በድምቀት ይከናወናል፡፡
ኦዳ አዋርድ ዘንድሮ ለዘጠነኛ ጊዜ በሚያዘጋጀው የሽልማት መርሃግብር ከቀደምት ዓመት ውድድሮች ለየት ባለ መልኩ በመቅረብ ትኩረቱን ሙሉ በሙሉ በሙዚቃው ዘርፍ ላይ ብቻ በማተኮር የሽልማት ስነስርዓቱን እንደሚያከናውን ተነግሯል።
በመሆኑም በሙዚቃው ዘርፍ ብቻ ከሀገር ውስጥ 30 እጩዎችን በ6 የሽልማት ዘርፎች ለምርጫ ያቀረበ ሲሆን ከሀገር ውስጥ እጩዎች በተጨማሪ ከ12 አፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ እጩዎችን ለህዝቡ ይፋ ያደርጋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም እጩዎች ለሽልማት የሚበቁት ሙሉ በሙሉ በህዝብ ምርጫ መሆኑ ተገልጿል።
ከአፍሪካ ሃገራት በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ በ"AFRICAN SUPER STAR” ዘርፍ ላይ ተሸላሚ ለመሆን የሚሳተፉት 12 የአፍሪካ ሃገራት፦ ሩዋንዳ፣ ማሊ፣ ሞሮኮ፣ አንጎላ፣ ማዳጋስካር፣ ኬንያ፣ ጅቡቲ፣ ሲሼልስ፣ ጋና፣ ቶጎ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳ ናቸው።
በተጨማሪም 9ኛው ኦዳ አዋርድ ከሃገር ውስጥ የሙዚቃ ስራዎች ለሽልማት እጩዎችን የሚያቀርብበት ስድስት ዘርፎች ሲኖሩት እነሱም፡- የህይወት ዘመን ተሸላሚ፣የአመቱ ምርጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ አርቲስት፣የአመቱ ምርጥ ቪዲዮ ክሊፕ፣የአመቱ ምርጥ ሴት ድምፃዊት፣የአመቱ ምርጥ ወንድ ድምፃዊ፣የአመቱ ምርጥ ምርጥ ሀገርኛ ዘፋኝ ናቸው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3👍3
📌የደጃፍ ፖድካስት ምዕራፍ 4 በቅርቡ ይጀመራል
በዳዊት ተስፋዬ የሚዘጋጀውና በበርካቶች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው "ደጃፍ ከዳዊት ተስፋዬ ጋር" የፖድካስት ዝግጅት ምዕራፍ 4 በቅርቡ እንደሚጀምር የፖድካስቱ አዘጋጅ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዳዊት ተስፋዬ የሚዘጋጀውና በበርካቶች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው "ደጃፍ ከዳዊት ተስፋዬ ጋር" የፖድካስት ዝግጅት ምዕራፍ 4 በቅርቡ እንደሚጀምር የፖድካስቱ አዘጋጅ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤30👍10🔥5