Event Addis Media
9.6K subscribers
6.05K photos
12 videos
4 files
4.67K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌የሀገራችን ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ሁሉ ተቋርጠዋል

የሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው ከፍተኛ የአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት የኃይል መቋረጥ ተፈጥሯል፡፡

በዚሁ ምክንያ የሀገራችን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት እንደተቋረጠ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁8👍62
📌የክብር ዶክትሬት የተሠጣቸውን ግለሰቦች "በመጠሪያነት መጠቀም" እንደማይቻል ተገለፀ

የክብር ዶክትሬት የተሠጣቸውን ግለሰቦች "በመጠሪያነት መጠቀም" የማይቻል መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።

ሚኒስትሩ ይህን የገለፁት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ዘርፉን የ1ኛ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም በትናንትው ዕለት በገመገመበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን በተመለከተ ችግር የነበረበት መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ ወጥ አሰራር መከተል በማስፈለጉ የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን ሀገራዊ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለትግበራ ዝግጁ መደረጉን ገልፀዋል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ማድረግ ያለበት መሆኑን ጠቅሰው የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የሚያገኙ ሰዎች ዶክተር ወይንም የክብር ዶክተር በሚል መጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አሳስበዋል።

ሚኒስትሩ በሙያው የተለየ ስራ ያበረከተ ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላ ዜጋ በመመሪያው የተዘረዘረውን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ የክብር ዶክትሬት ማዓረግ ማግኘት እንደሚችል ገልፀው ሆኖም ግን የተሠጠውን የክብር ዶክትሬት ለመጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አመልክተዋል።

በተጨማሪም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ለመስጠት ሀገራዊ እና አለም አቀፍ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለባቸው መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Via አዲስ ስታንዳርድ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
2🤣177👎1
📌ቤቶች ድራማ 13ኛ ዓመቱን ሊያከብር ነው

በቴሊቪዥን መስኮት የመጀመሪያው ሀገረኛ ሲትኮም የቤተሰብ ድራማ የሆነው ቤቶች 13ኛ ዓመት ክበረ በዓሉን እንደሚያከብር ይፋ አድርጓል።

ቤቶች ድራማ ሳይቆራረጥ ለተከታታይ 13 ዓመታት በ525 ክፍሎች ወደ ተመልካችመድረሱን ተዋናይ ጥላሁን ጉግሳ ተናግሯል።

ለተመልካች በደረሱት 525 ክፍሎች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችንማንሳት መቻሉ ነው የተገለፀው።

ሲትኮም ተከታታይ ድራማው አዲስና አቅም ያላቸውን ተዋንያን ማፍራትን አላማድረጉን የገለፀው ተዋናይ ጥላሁን ጉግሳ በዚህ ረገድ ቤቶች ድራማ አዲስ ፊቶችን ለተመልካች ማስተዋወቅ መቻሉ ሌላው ስኬቱ ነውብሏል።

የፊታችን ኅዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ድራማው የተጀመረበት 13ኛ ዓመትበዓል በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ እንደሚከበር አራዳ ኤፍ ኤም ሰምቷል።

በክብረ በዓሉ ላይ የመድረክ ቴአትር፣ ጭውውቶችና ሌሎች ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ይቀርባሉ።

በክብረ በዓሉ ላይ የቤቶች ድራማ አባል የነበረችው በድንገተኛ የመኪና አደጋህይወቷ ያለፈው ተዋናይ ሰብለ ተፈራ እንደምትዘከር ተገልጿል።

Via አራዳ Fm

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🤮109🤷‍♂1👍1
የ11ኛው ጉማ አዋርድ አሸናፊዎች ዝርዝር

1.ምርጥ ተዋናይት፦ ቃልኪዳን ጥበብ (ትዝታ)
2. ምርጥ ተዋናይ:- ናታይ ጌታቸው ( ጥቁር አደይ)
3.ምርጥ ረ/ተዋናይ፦ አማኑኤል ሀብታሙ (አፊኒ)
4. የተመልካች ምርጫ፦( ባለ ክራር)
5.ምርጥ ዳይሬክተር፦  ፍፁም ካሳሁን (ጥቁር አደይ)
6.ምርጥ ፊልም፦ (ጥቁር አደይ)
7. ምርጥ ድምፅ፦ ሐብታም አዲስ (አፊኒ )
8. ምርጥ ኤዲተር፦ ዳንኤል አንማው (ትዝታ)
9.ምርጥ ስኮር፦  ስምአገኘኹ ሳሙኤል (አፊኒ)
10. ምርጥ ማጀቢያ ሙዚቃ፦ ኤደን አይሸሹ፣ ፍፁም ካሳሁን እና አብነት አጎናፍር (ጥቁር አደይ)
11. ምርጥ ሲኒማቶግራፈር፦ ኤልያስ ተስፋዬ 6 ሰዓት ከለሊቱ
12. ምርጥ ሜካአፕ፦ ዝናዊት ዘርጋባቸው (አፊኒ )
13.ምርጥ የፊልም ፅሁፍ፦ ፍፁም ካሳሁን (ጥቁር አደይ)
14.ተስፋ የተጣለባት ተዋናይት፦ ክላራ ሙሉጌት (ሁለት ቅጣት)
15. ተስፋ የተጣለበት ተዋናይ፦ ሳሊም አብዱራህማን (ለፍትህ )
16.ምርጥ ረ/ተዋናይት፦  ማርታ ጎይቶም( 6 ሰዓት ከለሊቱ )

☑️. የሕይወት ዘመን ተሸላሚ፦ ፍቅርተ ጌታሁን እና ወለላ አሰፋ
☑️ የሐርሜላ ተሸላሚ፦ ወይዘሮ ወሰኔ ሀይሉ

☑️ ምርጥ አጭር ፊልም፦ በማን ዓይን አሸናፊ መስፍን

ከ16ቱ 5ቱን አዋርድ በመውሰድ ጥቁር አደይ ፊልም ከፊት ይገኛል፣ አፊኒ 4ት በመውሰድ ይከተላል፤ ትዝታ እና 6 ሰዓት ከለሊት ደሞ ሁለት ሁለት አዋርድ በማሸነፍ 3ተኛን ይዘዋል።

ስለ ተከታታይ ድራማ ከወራት በኃላ ጉማ "ሉሲ አዋርድ" ብሎ ተከታታይ ድራማዎችን ብቻ እንደሚሸልም ገልጿል።

ይህ መረጃ በፅዮን ታምራት የተዘጋጀ ነው!

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍146🔥1
📌ተፈራረሙ !

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል በጋራ ለመስራት ተፈራረሙ::

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ በጎ አድራጎት ድርጅት እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል በጎ አድራጎት ድርጅት በኢትዮጵያ ህገወጥ የሰውን ዝውውር ለመከላከል ፣ አስተማማኝ ፍልሰትን ለማስተዋወቅ እና ለተመላሾች ዳግም የመዋሃድ ድጋፍን ለማጠናከር የተቀናጀ ጥምረት ለመጀመር የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በይፋ ተፈራርመዋል።

"ዲጂታል ድምጾች፣ እውነተኛ ተጽዕኖ፡ የፍልሰት አስተዳደር የሚዲያ ንቅናቄ በኢትዮጵያ"  ይህ ዘላቂ የሶስት ወራት ዘመቻ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ቀን ( Dec18) በፊት የሚዲያ ቅስቀሳን እና የማኅበረሰብ ግንዛቤን ያጠናክራል የተባለውን ዘመቻ ያድጀምራሉ።

ዘመቻው በተጎጂዎች ላይ ያተኮሩ ምስክርነቶችን፣ አስተማማኝ እና ህጋዊ ፍልሰት ላይ የባለሙያ መመሪያዎችን እና በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተጋላጭነት ላላቸው ማህበረሰቦች የታለሙ የግንዛቤ መልዕክቶችን ያስተላልፋል።

"ጣፋጭ ህይወት" የሬዲዮ ፕሮግራምን ጨምሮ በተለያዩ የሚድያ አማራጮች ተከታታይነት ያለው ፕሮግራም በማድረግ አቅጣጫዎችን ከአላማው ለማሳካት  መሰረት ያደርጋል።

ሁለቱ ተቋማት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታሰበውን የፍልሰተኞች ቀን Dec18/ 2025 በተለያዩ ተግባራት ይከውናሉ።

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል ለጋሾች እና ባለድርሻ አካላት በብሔራዊ የመከላከያ ዘመቻዎች ላይ ኢንቨስትመንትን እንዲያሰፉ እና ለተጎጂዎች የስነልቦና፣ የትምህርት ስልጠና እና የኑሮ ድጋፍንም አቅደዋል።

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ ትኩረቱን በስደት ላይ በማድረግ የሚሰራ ሲሆን በተመሳሳይ ስዊት ላይፍ ፎር ኦል ወጣቶችን  ሁለገብ አቅም ለማሳደግ ትኩረት በማድረግም ይሰራል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
6
📌 ሁለት የሥዕል አውደርዕዮች በዕይታ ላይ ይገኛሉ

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነጥበብ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ተማሪዎች ያዘጋጁት የሥነጥበብ ዓውደርዕይ በዚህ ሳምንት በይፋ ተከፍቷል።

የሥዕል አውደርዕይውም ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ እስከ ታኅሣሥ 2 2018 ዓ.ም ድረስ በኮሌጁ የሥዕል ማሳያ ውስጥ በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።

በሌላ በኩል "አብሮነት" የተሰኘው በብሩ ወርቁ ፣ያሬድ ወንደሰን እና ዘውዱ ገ/ሚካኤል የተዘጋጁ የሥዕል ሥራዎች የቀረቡበት አውደርዕይ ባሳለፍነው ረቡዕ ህዳር 3 2018 ዓ.ም በፈንድቃ የባህል ማዕከል ለእይታ ክፍት ሆኗል። እስከ ህዳር 29 2018 ዓ.ም እንደሚቀይም ተነግሯል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
6
📌 "መልቲ" ተውኔት በይፋ ተመረቀ

በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር በትናንትናው ዕለት በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።

በአዶት ሲኒማ በተመረቀው ትያትር ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ትያትር አፍቃሪያን፣ እና በርካታ ተመልካቾች ተገኝተዋል።

በከፍተኛ የተመልካች ሳቅ የታጀበው  የ"መልቲ" ትያትር የመጀመሪያ የምርቃት መድረክ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ማግኘት ችሏል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌድሪ የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ትያትሩ እንዲሳካ ላደረጉ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።

ትያትሩ ዘወትር አርብ በ11:30 በአዶት ሲኒማ በቋሚነት መታየት ይጀምራል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
2
📌"ውብ አዲስ ፩" የሥዕል ትርዒት ሊከፈት ነው

"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩረቱን በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያደረገ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተከታታይ (ከህዳር-2018 እስከ ህዳር-2019) የግል የሥዕል ትርዒት (Solo Art Exhibition) ለማቅረብ ሠዓሊ ሀሮን ዝግጅቱን ጨርሷል።

የመጀመሪያውን "ውብ አዲስ ፩" የሥዕል ትርዒትም ከአርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ጎላ ሚካኤል አካባቢ በሚገኘው ጎላ ሥነ ጥበብ ማዕከልለህዝብ ዕይታ ክፍት ይሆናል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
6
📌የ"ቁንጅና" ሙዚቃ ግጥም የዓለምፀሐይ ወዳጆ አይደለም ሲል ዳዊት መለሰ ተናገረ

ከሁለት አስርት ዓመታት በኃላ 'ምስጢር" የተሰኘ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው ዳዊት መለሠ ሰይፉ ሾው ላይ ቀርቦ ነበር።

በዚህ ቃለመጠየቁ ዳዊት መለሠ በርካታ የእሱ ሙዚቃ ወዳጆች ስለሚወዱለት "ቁንጅና" ሙዚቃው ተከታዩን ብሏል"ቁንጅና የተሰኘው ዘፈኔን ዓለምፀሐይ ወዳጆ የፃፈችው የሚመስላቸው ብዙ ሰዎች አሉ።ዘፈኑን የፃፈው ዮናስ ሙላቱ የተባለ ኪቦርድ ተጫዋች አለ።ቁንጅና እና ብቻሽን የተሰኘ ሁለት ዘፈን ሰጠኝ።ዓለምፀሐይ የፃፈችው ፍረጂኝ የተሰኘውን ዘፈን ነው"

በሌላ በኩል ከራሱ ሕይወት ጋር የሚገኘው ሙዚቃው "እህል ውሃ" የተሰኘው እንደሆነም ተናግሯል"ከራሴ ሕይወት ጋር የሚገናኝ ዘፈን የዘፈንኩት እህል ውሃ የተሰኘውን ዘፈን ነው።ቴዲ አፍሮ የቀድሞ ፍቅረኛዬን ያውቃት ነበር። አሜሪካ ሀገር ሲመጣ ደህና ነች ወይ? ሲለኝ አዎ ደህና ነች ሞክረን ነበር አልሆነም አልሰራም አልኩት።እህል ውሃ የሚለውን ዘፈን ሰርቶ ሰጠኝ። ቴዲን የማደንቀው ትልቅ ጭንቅላት ያለው ልጅ ነው።በዜማም በግጥምም የበሰለ ልጅ ነው"

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍65
📌የአበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ አባት አረፉ

የታዋቂው የሙዚቃ ሰው አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ወላጅ አባት ማረፋቸው ተሰምቷል።

አበጋዝ ከወላጅ አባቱ አቶ ክብረወርቅ ጋር ከወራት በፊት በታዋቂዋ ሞዴልና ፋሽን ዲዛይነር አና ጌታነህ ፕሮውዲስ በሚደረገው ፕሮግራም ( በአቦል ቲቪ ) ላይ ቀርቦ እንደነበር ይታወቃል።

ምናልባትም ከቅርብ ሰዎቹ ውጭ ብዙ አድናቂዎቹ አባቱን በመልክ ያዩዋቸው በዚያ ፕሮግራም ነው። የሙዚቀኛ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ አባት አቶ ክብረወርቅ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢6💔3
📌ለሚዲያ በሰጡት መረጃ ከኃላፊነታቸው ተነሱ

የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር በአካባቢው ስለተከሰተው “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው ተላላፊ በሽታ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው ለመገናኛ ብዙሀን መረጃ መስጠታቸውን ተከትሎ ከሀላፊነታቸው ተነሱ።

የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢንያም አስራት ለአንድ ዓለማቀፍ ሚዲያ “የሔሞሬጂክ ፊቨር” እንደሆነ በተገመተው በሽታ ሳቢያ ሀኪሞችን ጨምሮ ሰዎች መሞታቸውን ገልፀው መረጃ በመስጠታቸው ከሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ምስጢሩ ሐምደኪ በተጻፈ ደብዳቤ ከሕዳር 5 ቀን 2028 ዓ.ም ከሀላፊነታቸው መነሳታቸው ተነግሯቸዋል። 

ዳይሬክተሩ ከሃላፊነት ከመነሳታቸው በፊት ወደ ሆስፒታሉ መጥተው ከታከሙት አራት በሽተኞች አንዱ በህይወት እንዳለ እና የተሻለ የሚባል የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ሁለት የሆስፒታላቸው የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ እስካሁን ስድስት ሰዎች ተመሳሳይ ምልክቶችን በማሳየት ህይወታቸው ማለፉን ለዶቸ ቨለ ራዲዮ በይፋ ገልፀው ነበር።

የበሽታው ክስተትና ምንነት ዓለማቀፍ ትኩረት የሳበ ሲሆን የዓለም የጤና ድርጅትም ከመንግስት ጋር በመቀናጀት አስቸኳይ የመስክ ቡድን ወደ ስፍራው ልኳል። 

የጤና ሚኒስቴር እስከአሁን ድረስ ስምንት ሰዎች  በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑን ባወጣው መግለጫ ይፋ ያደረገ ሲሆን ስለ ሞቱ ሰዎች  ያለው ነገር የለም።
ዶክተር ቢንያም አስራት በበሽታው ሞት መመዝገቡን ይፋ ካደረጉ በኋላ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነ የቅርብ የስራ ባልደረቦቻቸው ነግረውናል ሲል ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😡315😁2🤯2🤬2🤨2🤔1
📌እንጀራ በሸቀጣ ሸቀጦች ሱቅ መሸጥ መከልከሉ ተገለጸ

የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣንን የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።

የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ የተለያዩ መርዛማ ነገሮች ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦን መሸጥ ልክ ባለመሆኑ ለመከልከል መገደዳቸውን ተናግረዋል ሲል ነው ዘገባው የጠቀሰው።

እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው በምግብ ቤቶች፣ በዳቦ ቤተች እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ መሆኑንም በማንሳትም ያልተፈቀደላቸው ነጋዴዎችም ሲሸጡ ከተገኙ አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስገንዝበዋል ሲል ገልጿል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😱9😁84👍3
📌የሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ አልበም ሊለቀቅ ነው

የሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ "ብርሃን" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው በመሳሪያ የተቀነባበረ የሙዚቃ አልበም የፊታችን አርብ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሙዚቃ አፍቃሪያን ይደርሳል ተብሏል። 

ለማዘጋጀት አንድ ዓመት እንደወሰደ የተነገረው "ብርሃን" የሙዚቃ አልበም አስር አንድ የሙዚቃ ስብስቦችን ይዟል።

"ብርሀን" በተሰኘው ሁለተኛ አልበሙ በኪቦርድ፣ ቤዝ፣አኮስቲክ ጊታር፣ክራር፣ የሙዚቃ መሳሪያዎች የተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች ተካተዋል።

አልበሙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በትሪፕል ሆቴልና ስፓ የሚመረቅ ይሆናልም ተብሏል።

የፊታችን ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በDeamat records ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃልም ተብሏል።https://youtube.com/@deamatrecords?si=91IxewcK1ZdGshgL

ሙዚቀኛ መሐመድ ከዚህ ቀደሞ "ሰላምታ " የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙን በ2010 ዓ.ም ለአድማጭ አድርሷል።

ሙዚቀኛ መሐመድ የሙዚቃ ኪቦርድ መጫወት የጀመረው 1998 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዓመት አፍሪካ ጃዝ ስኩል ( ጃዝ አምባ ) ተምሯል።

ሙዚቀኛው ከትግርኛ ዘፋኞች መሐል ለረጅም ጊዜ  የአብርሃም ገብረመድህን ፣ የማህሌት ገብረጊዮርጊስ ፣ የሸዊት መዝገቦ ኪቦርዲስት በመሆን በብዙ አገራት ቱር አድርጓል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
8👍7🔥1
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ቀን ነው

የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ቀን በየዓመቱ በጎርጎሮሳዊያኑ የጊዜ ቀመር November 19 ይከበራል።

ጋዜጠኝነት ዜና እና መረጃን የመሰብሰብ፣ የማጣራት፣ የመተንተን እና ለህዝብ የማቅረብ ተግባር ወይም ሙያ ነው።

ጋዜጠኞች በሥልጣን ላይ ያሉትን ተጠያቂ በማድረግ እና ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመስጠት በህብረተሰቡ ውስጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ በሃሳብ ደረጃ ይታመናል።

ጋዜጠኝነት እውነትን የማወቅ ፍላጎትና ጉጉት ነው። ጋዜጠኝነት ታማኝነትን የተላበሰ ሙያ ነው። በስራው ታማኝ እና ስነ ምግባር ያለው፥ ሁል ጊዜም እውነትን ለመናገር የሚጥር ነው ጋዜጠኛ የሚባል ጋዜጠኛ።

ጋዜጠኝነት ፅናት ነው። ጽኑ መሆንንና ቆራጥነትን ያዘለ፥ ከፍራቻ የፀዳ፤ ገለልተኛነትን የተላበሰ ነው ጋዜጠኝነት።

ከአድሎ መንፃት፤ የርህራሄ ተምሳሌት መሆን፤ ተጨባጭነት፤ አሳማኝና ምክንያታዊ መሆን ነው ጋዜጠኝነት።

ጋዜጠኝነት ነፃነት ነው። ራሱን የቻለ እና በውጫዊ ጫናዎች እና ፍላጎቶች ተጽእኖ ስር አለመውደቅ ነው ጋዜጠኝነት።

የመረጃ ምንጮችን ሚስጥራዊነት ማክበር፤ ለተጠያቂነት ራስን ማዘጋጀት፤ ለተሰራው ስራ ተጠያቂ መሆን፤ ስህተትን ለማረም እና ለስህተት ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ መሆን ነው ትክክለኛ ጋዜጠኝነት።

እናም ከላይ የተነሱ ሀሳቦችን በጥቂቱ የምታሟሉ ጋዜጠኞች፥ እንኳን ለቀናችሁ አደረሳችሁ።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
26👍8🥰1
📌አሻም ቲቪ 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ ተከሰሰ

አሻም ቴሌቪዥን ብዛታቸው 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ አማካይነት ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ በዚሁም ሂደት የድርጅቱ ንብረቶች ሙሉ በሙሉ እንዳይንቀሳቀሱ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ዕግድ እንደተላለፈበት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል። ምንጮቹ አክለውም፣ ለጣቢያው ጋዜጠኞች የሶስት ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈለ አመልክተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁኑ ሰዓት ድረስ፣ አሻም ቲቪ የሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ የለም።

ከዚህ ቀደም የጣቢያው ቢሮ መታሸጉ የሚታወስ ሲሆን፣ ጣቢያውን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው አሻም ትሬዲንግ የእሸጋ ተግባሩ "ጣቢያውን ወደ መደበኛ ስራው ለመመለስ ከሚደረጉ ጥረቶች" ጋር አስተሳስሮ ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

©️ሚኪያስ ጥላሁን

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
4👍3😱3🤔1🕊1
📌‘Crazy Day’፣ ‘Valentine Day’ እና ሌሎች ‘መጤ ባህሎች’ በትምህርት ቤቶች የሚከለክል አዲስ ደንብ መዘጋጀቱ ተገለፀ

ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማትና አካባቢያቸው የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ አዲስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ማውጣቱን አስታውቋል።

ይህ ደንብ ከኢትዮጵያውያን ወግና ልማድ ጋር ይቃረናሉ ተብለው የተለዩ የውጭ ባህላዊ ልማዶችን ጨምሮ፣ እየጨመረ የመጣውን አዋኪ ጉዳዮች ለመግታት ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

የደንቡ ዋና ዓላማ በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን በመከላከል፣ ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ፣ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀና ግብረ-ገብነትን የተላበሰ ብቁ ትውልድ እንዲፈጠር ማስቻል ነው።

ደንቡ የኢትዮጵያውያንን ባህልና ወግ የሚቃረኑ ተብለው በግልጽ የተዘረዘሩ አሉታዊ መጤ ድርጊቶችንና ክብረ በዓላትን በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መፈጸም ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።

የሀገሪቷን ባህልና ወግ ይቃረናል ከተባሉት ድርጊቶች ዉስጥ Crazy Day፣ Gentle Day ፣ Olds Day፣  Valentine Day፣ Color Day፣ Pyjama Day የሚሉት ይገኙበታል።

የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር ቅጣት በአዲሱ ደንብ ይጠብቃቸዋል ተብሏል።

©️ ዘገባው የካፒታል ጋዜጣ ነው

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍369👎5🤣5👏4🤡1
የልጆች ፕሮግራም አዘጋጅ ሰሎሞን ገብረስላሴ  አረፉ

ከብስራተ ወንጌል ጀምሮ እስከ ኢትዮጵያ ሬድዮ በልጆች ፕሮግራም  አዘጋጅነታቸው የሚታወቁት ጋሽ ሰሎሞን ገብሥላሴ ዛሬ ህዳር 12 2018 በ83 ዓመታቸው  ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ለተወዳጅ ሚድያ ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል።

አቶ ሰለሞን ከልጆች ፕሮግራም በተጨማሪ ሰዎችና ስራዎቻቸው ፤ ህብረተሰባችን እንዲሁም ባህላዊ ሙዚቃዎቻችን የተባሉ ፕሮግራሞችን በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ፡፡

በኢትዮጵያ ሬዲዮ ከፕሮግራም አዘጋጅነት እስከ ዋና አዘጋጅነት በተጨማሪም የብሄራዊ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ተጠባባቂ ሃላፊ እንዲሁም የምስራች ድምጽ አለም አቀፍ አገልግሎት ሃላፊ ሆነው በ1986 በጡረታ እስከተሰናበቱበት ድረስ ለ40 ዓመታት ለሙያቸው ታማኝ ሆነው አገልግለዋል፡፡

በጡረታ ከተገለሉ  በኃላም እንደገና ወደ ሙያው ተመልሰው በምስራች ድምፅ ተዘጋጅቶ ከደቡብ አፍሪካ በሚተላለፈው ተመሳሳይ ይዘት ባለው ፕሮግራም በዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል ።

የምስራች ድምፅን ደርግ ሲወርሰውና አንዳንድ ጋዜጠኞች ከስራ ሲሰናበቱ አቶ ሰለሞን በስራቸው እንዲቀጥሉ ተደርጎ ነበር ፡፡

በጋዜጠኝነት ሙያቸውም በአድማጮች ዘንድ ተወዳጅ ከመሆናቸውም በላይ ታዋቂ ጋዜጠኞችንና በሚድያ እና በኪነ-ጥበቡ መስክ ተሰማርተው እናት ሀገራቸውን በማገልገል ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችንም ያፈሩ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነበሩ።እመቤት ወ/ገብርኤል፣ ብርሃኑ ገ/ማርያም፣ አስካለ ተስፋዬ፣ ዓለም አታፋረደው፣ አማረች ሙሉ ይገኙበታል።

አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ለሀገርና ለህዝብ ላከናወኑት ተግባር በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፍ የ10ኛውን የበጎ ሰው ሽልማት ተቀብለዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
5😢5🙏2🫡2🤔1💔1
📌የውበት ሠሌዳ መጽሐፍ ነገ ይመረቃል

የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የውበት ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ቅዳሜ ህዳር 13 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 10:00 ጀምሮ በጣይቱ የባህልና የትምህርት ማዕከል ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።

በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮተ መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ መራሔ ተውኔት ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ፣ የዝና ወርቁ አርቲስት ስዩም ተፈራ በክብር እንግድነት ይገኛሉ ተብሏል።

ገጣሚያኑ ሰለሞን ሳህለ፣ዋሲሁን በላይ፣ ፌቤን ፋንጮ ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።

"የውበት "በ115 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን
43 ግጥሞችን በውስጡ ይዟል በ350 የጀርባ ዋጋም ለአንባቢያን ቀርቧል።

ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" እና "የጊዜ ሰሌዳ"  የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
3👍2🔥2🥰1
📌አጫጭር ፊልሞች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል አጫጭር ፊልሞች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት አሰናድቷል፡፡

ውይይቱ ቅዳሜ ህዳር 13/2018 ዓ.ም ከ8 ሰዓት ጀምሮ በአካዳሚው ቅጥር ግቢ ይካሄዳል፡፡

አንጋፋው የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ በቀረቡት ፊልሞች ላይ ሙያዊ ዳሰሳውን ያቀርባል፡፡

ዝግጅቱ የአለ ስነጥበብና ዲዛይን ትምሕርት ቤት እና የልቀት ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች በሰሯቸው አጫጭር ፊልሞች ያተኩራል፡፡

በተጨማሪም ህዳር 11 እና 12 ከ8፡00– 11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ ከ3፡00 – 8፡00 በአካዳሚው አዳራሽ ለዕይታ ይቀርባሉም ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
5🔥1
📌የያንጎ ኢትዮጵያ የመንገድ ደኅንነት ሥልጠና

ያንጎ ኢትዮጵያ የመንገድ ደኅንነት ሥልጠና እና የአሽከርካሪዎች ብቃት ማረጋገጫ ዕውቅና መስጠት ጀመረ

የዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ፣ ያንጎ ግሩፕ አካል የሆነውና በጂቱጂ አይቲ ሶሊውሽን አ.ማ. እና በኤለጋንስ ኢምፖርት ኤንድ ኤክስፖርት ፒኤልሲ ሥር የሚተዳደረው ያንጎ ኢትዮጵያ፣ ለደኅንነት፣ ለአገልግሎት ልህቀት እና ቅልጥፍና እንዲሁም ለማኅበረሰብ ተሳትፎ ያለውንቁርጠኝነት በማጠናከር የመንገድ ደኅንነት ፕሮግራም እና የመጀመሪያ እርዳታ እና የአገልግሎት ልህቀት ሥልጠና መርሐግብር ለአጋር አሽከርካሪዎች መስጠት ጀምሯል፡፡

“ያንጎ ኬርስ”በተሰኘው የማኅበራዊ ድጋፍ አገልግሎት ስር የተጀመረው ይህተነሣሽነት፣ የኩባንያው ትኩረት ይበልጥ ደኅንነታቸው በተጠበቁ መንገዶች፣ በጠንካራ ማኅበረሰቦች እና ለተሳፋሪዎች ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡

የሥልጠናው ክፍለ ጊዜ፣ አጋር አሽከርካሪዎች የመንገድደኅንነት ግንዛቤ እና ተግባራዊ የመጀመሪያ ህክምናክህሎቶችን እንዲታጠቁ በማድረግና የተሳፋሪዎችን ልምድበማጎልበት- በመላ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰፊው ሕዝባዊደኅንነት አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ታምኖበታል።

ተጨማሪውን ያንብቡ:https://sl1nk.com/m4IWs
2
📌 "ማስተዋል"  ኮንሰርት ዛሬ ይካሄዳል

የድምጻዊ ማስተዋል እያዩ "ማስተዋል" የሙዚቃ ኮንሰርት ዛሬ ህዳር 13 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።

በዚህ ኮንሰርት ላይ ከማስተዋል እያዩ ባሻገር ድምጻዊት ሔዋን ገብረወልድ የሙዚቃ ስራዋን ታቀርባለች ተብሏል።

የራሱን ነጠላ ዜማዎች ጨምሮ የተለያዩ ድምፃዊያን ሙዚቃዎችን ማለፊያ በሚባል ሁኔታ ሲጫወተው የቆየው ድምጻዊ ማስተዋል በ2016 ዓ.ም የካቲት 1 ነበር "እንዚራ" ሲል የሰየወመውን የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ያቀረበው። ይህም አልበሙም በበርካቶች ዘንድ ተወዶለታል።

አልበሙ ለአድማጮች ከቀረበ 1 ዓመት ከስምንት ወር የቆየው ሲሆን የሙዚቃ ኮንሰርትም ሳይዘጋጅለት ቆይቷል።

የድምጻዊው አድናቂዎቹም የማስተዋል እያዩ ኮንሰርት መቼ ነው የሚል ጥያቄዎች ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
3👍1🥰1