Event Addis Media
9.59K subscribers
6.04K photos
12 videos
4 files
4.67K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌በዳሞ መንግሥቱ ዚተጻፈው “ያልተሻገርነው ድልድይ” ዹተሰኘ መጜሐፍ ለህትመት በቃ

ደራሲው በዚህ መጜሐፉ ኚጥልቅ ዚህይወት ልምዱ በመነሳት ስለ ሀገራቜን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ህይወት ዚሚመለኚቱ ጉዳዮቜ ኹአዝናኝ እና አስተማሪ ኹሆኑ ዓለም አቀፍ ገጠመኞቹ ጋር በማዋሀድ ትዝብቱን እና ያልተሻገርና቞ውን ድልድዮቜ ለመሻገር ምን ብናደርግ እንደሚሻል ዹግል ምልኚታውን ኚመፍትሔ ሃሳቊቜ ጋር ያጋራል።

በእርግጠኝነት ዚምንነግሮ መፅሀፉን አንብበው ይወዱታል ኪስን በማይጎዳ ዋጋ አትርፋቜሁ ትዝናኑበት ዘንድ እዚጋበዘ ዚመጜሐፉን በጃፋር መደብር፣ በሀሁ ዚመጜሐፍ መደብር እና በኀዞፕ ዚመጜሐፍ መደብር እንደሚገኝ ስንጠቁም በደስታ ነው፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏6❀1👍1
📌ዚነፃነት ላቀው "ደጋ አምባ" ድራማ ዛሬ ይጀምራል

በጋዜጠኛ ነፃነት ላቀው ተደርሶ በአንተነህ ኃይሌ ዹተዘጋጀው "ደጋ አምባ" ተኚታታይ ድራማ ዛሬ ሐሙስ ህዳር 4 ኚምሜቱ 2፡00 ጀምሮ በአቊልቲቪ ፣ ዲኀስቲቪ ቻናል 465 ይጀምራል።

በድራማው ላይ ዚሥነልቊና ባለሞያና ዚቡና ፖድካስት አዘጋጅ  ዚሆነቜው ሰላም አታላይ በመሪ ተዋናይነት ትሳተፋለቜ ተብሏል።

ደጋ አምባ ድራማ በህይወትዎ እጅግ አጥብቀው ለዓመታት ሲፈልጉት ዹነበሹን ነገር ለማግኘት ኚጫፍ ደርሰው ነገር ግን ዚመጚሚሻ ውሳኔዎ ዚአንድ መንደር ሰዎቜን ህይወት አደጋ ላይ ጥሎ እልቂት ቢያመጣ  ምን ያደርጋሉ? በማለት ይጠይቃል።

በደጋ አምባ ድራማ ጥበብ ኚተፈጥሮ፣ራስ ወዳድነት ኚፅናት፣ፍቅር ኚታማኝነት አፈታሪክ ኚእውነታ ጋር ተፋጠው ይቀርቡበታል።

ደጋ አምባ አዲስ ልብ አንጠልጣይ ድራማ በአቩል ቲቪ ዛሬ መቅሚብ ይጀምራል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀19🔥2
📌ያንጎ ኢትዮጵያ ኹቀይ መስቀል ጋር በመተባበር ዹደም ልገሳ ዘመቻ አካሄደ

ዹዓለም አቀፍ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያ ያንጎ ግሩፕ አካል ዹሆነው ያንጎ ኢትዮጵያ (በፍራንቻይዝ ጂ2ጂ አይቲ ሶሉሜንስ አ.ማ. እና ኀሌጋንስ አስመጪና ላኪ ኃ.ዹተ.ዹግ.ማ. ዚሚተዳደር) ኚኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ጋር በመተባበር ዹደም ልገሳ ዘመቻ ጀምሯል። ዘመቻው ያንጎ ዚአካባቢውን ማህበሚሰብ ለመደገፍ ያለውን ተነሳሜነትን ያማኚለ ነው።
 
ዚያንጎ ኢትዮጵያ ዚፍራንቻይዝ አጋሮቜ እና አጋር አሜኚርካሪዎቜ በበጎ ፍቃደኝነት ደም በመለገስ ላይ ሲሆኑ ይህም ዹደም ተፈላጊነት ኹፍተኛ ኹመሆኑ አንጻር ኩባንያው ህብሚተሰቡን ለማገልገል ያለው ቁርጠኝነትን አጉልቶ ያሳያል፡፡
 
"ያንጎ እውነተኛ እድገት ኚማህበሚሰቡ ደህንነት ጋር አብሮ ዚተሳሰሚ ነው ብሎ ያምናል። ይህ ዘመቻ ዚመተሳሰብ፣ዚኃላፊነት እና ዚትብብር እሎቶቻቜንን ያሳያል። ኚኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ጎን በመቆማቜን ኩራት ይሰማናልፀ ተጚባጭ ለውጥ ለማምጣት ለሌሎቜም ጥሪ ለማቅሚብ እወዳለሁ፡፡" በማለት በኢትዮጵያ ዚያንጎ ተወካይ ዶ/ር ይቅናለም አበበ ተናግሚዋል።
 
ዹደም ልገሳ ዘመቻው ዹበጎ ፈቃደኝነትን እና ዚማኅበሚሰብ መንፈስን አስፈላጊነት ዚሚያጎላ ሲሆን፣ ትናንሜ ዚግለሰብ ተግባራት ተባብሚው ትርጉም ያለው ማኅበራዊ ተፅእኖ መፍጠር እንደሚቜሉ ዚያንጎን እምነት ዚሚያጠናክር ነው።
 
ያንጎ ግሩፕ ዋና መሥሪያ ቀቱን በዱባይ ያደሚገ ዓለም አቀፍ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዹተገኙ ቎ክኖሎጂዎቜን ለአካባቢው ማኅበሚሰቊቜ ተስማሚ በሆነ መልኩ ዚዕለት ተዕለት አገልግሎቶቜ ዚሚያቀርብ ኩባንያ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀1👍1
📌በፎሊክ አሲድ በቀላሉ መኹላኹል ዚሚቻል በሜታ ሕጻናትን ለእድሜ ልክ ዚአካል ጉዳትና ለሞት ተጋላጭ እዚዳሚጋ቞ው ነው ተባለ

ሆፕ ኀስ ቢ ኀቜ በዓለም አቀፍ ደሹጃ "ዹነርቭ ዘንግ ክፍተትና ዚጭንቅላት ውስጥ ኹመጠን በላይ ዚፈሳሜ ክምቜት ሕመም ጋር ለሚወለዱ ሕፃናት ዹሚደሹገውን ጥሚት ማፋጠን" በሚል መሪ ቃል እዚተኚበሚ ዹሚገኘውን አለም አቀፍ ክብሚበዓል በማስመልኚት ግንዛቀ መፍጠሪያ መድሚክ አካሄደ።

በዚህ መድሚክ ላይ ስለ ነርቭ ዘንግ አፈጣጠር ቜግር እና ዚጭንቅላት ውስጥ ፈሳሜ ኹመጠን በላይ ክምቜት ወይም "ዚስፖይና ቢፊዳ እና ሀይድሮሎፋለስ" በሜታ ምንነት እንዲሁም ዚበሜታውን መንስዔ እና መፍትሔ በባለሙያዎቜ ዚታገዘ ግንዛቀን ዹመፍጠር ስራን ጚምሮ ኚባለድርሻ አካላት ጋር ዚተለያዩ ስራዎቜ እንደተሰራም ዹሆፕ ኀስ ቢ ኀቜ መስራቜ እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ቀዛ በሻህ ገልጞዋል።

በዓለማቜን በዓመት ውስጥ ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ህፃናት ዹዚህ በሜታ ተጠቂ ይሆናሉ፡፡

በአፍሪካ ይህ በሜታ በብዛት ኚሚኚሰትባ቞ው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ ነቜ።

ስፓይና ቢፊዳ ማለት ደግሞ ዹነርቭ ዘንግ ክፍተት ወይም ዚህብለሰሚሰር በትክክል አለማደግ ሲሆን ዹሚኹሰተውም ዚመጀመሪያዎቹ አራት ዚእርግዝና ሳምንታት ውስጥ ነው፡፡

ምልክቶቹም ዹውጭኛው ዚጀርባ ክፍል ላይ ዚሚታይ እብጠት ወይንም ክፍት ቁስል መታዚት ነው፡፡

ይህ ዚጀና ቜግር ያለባ቞ው ህፃናት ዚቀዶ ጥገና ህክምና ዹሚደሹግላቾው ሲሆን ይህም ዹነርቭ ህዋሳቶቜን ዹበለጠ ጉዳት እንዳይደርስባ቞ው ለማድሚግ ዚሚሚዳ ይሆናል፡፡

በዚህም ምክንያት እነዚህ ሕጻናት ለእድሜ ልክ ዚአካል ጉዳት ብሎም ለሞት ተጋላጭ እንደሆኑም ተገልጿል።

ሆፕ ኀስ ቢ ኀቜ áˆ€áŒˆáˆ­ በቀል ግብሚሰናይ ድርጅት በአሁን ሰዓት ኹ5,700 በላይ ቀተሰቊቜን በተለያዩ መንገዶቜ እያገለገለ ይገኛል።
❀2
📌ዚሕይወት እምሻው አዲስ መጜሐፍ ነገ ይመሹቃል

47 ታሪኮቜን ዚያዘውና "ዥዋዥዌ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዚደራሲ ሕይወት እምሻው ስድስተኛ መጜሐፍ ቅዳሜ ሕዳር 6 2018 ዓ.ም ተመርቆ ለንባብ ይበቃል ተብሏል።

ደራሲዋ ስለ አዲሱ መጜሐፏ<< ዥዋዥዌ አርባ ሰባት ዹዘመን ማስታወሻ ታሪኮቜን ዚያዘ ሲሆን ዚተስተካኚለና ዚተመሰቃቀለውፀ ዚተሳካና ዚተሰናኚለውፀ ዚሚያምርና ዚሚያስቀይመውፀ ዚሚያስደስትና ዚሚያማርሚውፀ ዚሚያኮራና ዚሚያሳፍሚው ዘመነኛ ኢትዮጵያዊ ሕይወታቜንን እንደ ወሹደ ዚሰነድኩበት ነው››  ስትል ተናግራለቜ።

ዹ "ዥዋዥዌ" áˆ˜áŒœáˆá  ምርቃት ቅዳሜ ህዳር 6 ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ ለገሃር በሚገኘው አዲሱ ዹጃፋር መጜሐፍት መደብር ውስጥ ይኚናወናል።

ሕይወት እምሻው ኹዚህ በፊት አምስት መፅሐፍትን ማለትም ባር቟፣ ፍቅፋቂ፣ ማታ ማታ፣ ለእርቃን ሩብ ጉዳይ እና ዚቡና ቁርስ ለአንባቢያን ያደሚሰቜ ደራሲ ነቜ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀17🔥1
📌ዚሀገራቜን ቎ሌቪዥን ጣቢያዎቜ ሁሉ ተቋርጠዋል

ዚሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES ዹቮሌ ፖርት ላይ እስራኀል አካባቢ ባጋጠመው ኹፍተኛ ዹአዹር ፀባይ ለውጥ ምክንያት ዹኃይል መቋሚጥ ተፈጥሯል፡፡

በዚሁ ምክንያ ዚሀገራቜን ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያዎቜ ስርጭት እንደተቋሚጠ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁8👍6❀2
📌ዚክብር ዶክትሬት ዚተሠጣ቞ውን ግለሰቊቜ "በመጠሪያነት መጠቀም" እንደማይቻል ተገለፀ

ዚክብር ዶክትሬት ዚተሠጣ቞ውን ግለሰቊቜ "በመጠሪያነት መጠቀም" ዚማይቻል መሆኑን ዚትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።

ሚኒስትሩ ይህን ዚገለፁት ዚህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዹሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቮክኖሎጂ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ዚትምህርት ዘርፉን ዹ1ኛ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም በትናንትው ዕለት በገመገመበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዚክብር ዶክትሬት አሰጣጥን በተመለኹተ ቜግር ዚነበሚበት መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ ወጥ አሰራር መኹተል በማስፈለጉ ዚክብር ዶክትሬት አሰጣጥን ሀገራዊ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለትግበራ ዝግጁ መደሹጉን ገልፀዋል።

ሁሉም ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋም በመመሪያው መሰሚት ተፈፃሚ ማድሚግ ያለበት መሆኑን ጠቅሰው ዚክብር ዶክትሬት ማዕሹግ ዚሚያገኙ ሰዎቜ ዶክተር ወይንም ዚክብር ዶክተር በሚል መጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አሳስበዋል።

ሚኒስትሩ በሙያው ዹተለዹ ስራ ያበሚኚተ ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላ ዜጋ በመመሪያው ዹተዘሹዘሹውን መስፈርት ዚሚያሟላ ኹሆነ ዚክብር ዶክትሬት ማዓሹግ ማግኘት እንደሚቜል ገልፀው ሆኖም ግን ዹተሠጠውን ዚክብር ዶክትሬት ለመጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አመልክተዋል።

በተጚማሪም ዹኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት ዚክብር ዶክትሬት ማዕሹግ ለመስጠት ሀገራዊ እና አለም አቀፍ መስፈርቶቜን ማሟላት እንዳለባ቞ው መግለጻ቞ውን ኚሚኒስ቎ሩ ዹተገኘው መሹጃ ያመለክታል።

Via አዲስ ስታንዳርድ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
2🀣17❀7👎1
📌ቀቶቜ ድራማ 13ኛ ዓመቱን ሊያኚብር ነው

በ቎ሊቪዥን መስኮት ዚመጀመሪያው ሀገሹኛ ሲትኮም ዚቀተሰብ ድራማ ዹሆነው ቀቶቜ 13ኛ ዓመት ክበሹ በዓሉን እንደሚያኚብር ይፋ አድርጓል።

ቀቶቜ ድራማ ሳይቆራሚጥ ለተኚታታይ 13 ዓመታት በ525 ክፍሎቜ ወደ ተመልካቜመድሚሱን ተዋናይ ጥላሁን ጉግሳ ተናግሯል።

ለተመልካቜ በደሚሱት 525 ክፍሎቜ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮቜንማንሳት መቻሉ ነው ዚተገለፀው።

ሲትኮም ተኚታታይ ድራማው አዲስና አቅም ያላ቞ውን ተዋንያን ማፍራትን አላማድሚጉን ዹገለፀው ተዋናይ ጥላሁን ጉግሳ በዚህ ሚገድ ቀቶቜ ድራማ አዲስ ፊቶቜን ለተመልካቜ ማስተዋወቅ መቻሉ ሌላው ስኬቱ ነውብሏል።

ዚፊታቜን ኅዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ድራማው ዚተጀመሚበት 13ኛ ዓመትበዓል በአድዋ ሙዚዹም አዳራሜ እንደሚኚበር አራዳ ኀፍ ኀም ሰምቷል።

በክብሚ በዓሉ ላይ ዚመድሚክ ቎አትር፣ ጭውውቶቜና ሌሎቜ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶቜ ይቀርባሉ።

በክብሚ በዓሉ ላይ ዚቀቶቜ ድራማ አባል ዚነበሚቜው በድንገተኛ ዚመኪና አደጋህይወቷ ያለፈው ተዋናይ ሰብለ ተፈራ እንደምትዘኚር ተገልጿል።

Via አራዳ Fm

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
🀮10❀9🀷‍♂1👍1
ዹ11ኛው ጉማ አዋርድ አሞናፊዎቜ ዝርዝር

1.ምርጥ ተዋናይትፊ ቃልኪዳን ጥበብ (ትዝታ)
2. ምርጥ ተዋናይ:- ናታይ ጌታ቞ው ( ጥቁር አደይ)
3.ምርጥ ሚ/ተዋናይ፩ አማኑኀል ሀብታሙ (አፊኒ)
4. ዚተመልካቜ ምርጫፊ( ባለ ክራር)
5.ምርጥ ዳይሬክተርፊ  ፍፁም ካሳሁን (ጥቁር አደይ)
6.ምርጥ ፊልም፩ (ጥቁር አደይ)
7. ምርጥ ድምፅፊ ሐብታም አዲስ (አፊኒ )
8. ምርጥ ኀዲተርፊ ዳንኀል አንማው (ትዝታ)
9.ምርጥ ስኮርፊ  ስምአገኘኹ ሳሙኀል (አፊኒ)
10. ምርጥ ማጀቢያ ሙዚቃ፩ ኀደን አይሞሹ፣ ፍፁም ካሳሁን እና አብነት አጎናፍር (ጥቁር አደይ)
11. ምርጥ ሲኒማቶግራፈርፊ ኀልያስ ተስፋዬ 6 ሰዓት ኚለሊቱ
12. ምርጥ ሜካአፕፊ ዝናዊት ዘርጋባ቞ው (አፊኒ )
13.ምርጥ ዹፊልም ፅሁፍ፩ ፍፁም ካሳሁን (ጥቁር አደይ)
14.ተስፋ ዚተጣለባት ተዋናይትፊ ክላራ ሙሉጌት (ሁለት ቅጣት)
15. ተስፋ ዚተጣለበት ተዋናይ፩ ሳሊም አብዱራህማን (ለፍትህ )
16.ምርጥ ሚ/ተዋናይትፊ  ማርታ ጎይቶም( 6 ሰዓት ኚለሊቱ )

☑. ዚሕይወት ዘመን ተሾላሚ፩ ፍቅርተ ጌታሁን እና ወለላ አሰፋ
☑ ዹሐርሜላ ተሾላሚ፩ ወይዘሮ ወሰኔ ሀይሉ

☑ ምርጥ አጭር ፊልም፩ በማን ዓይን አሾናፊ መስፍን

ኹ16ቱ 5ቱን አዋርድ በመውሰድ ጥቁር አደይ ፊልም ኚፊት ይገኛል፣ አፊኒ 4ት በመውሰድ ይኚተላልፀ ትዝታ እና 6 ሰዓት ኚለሊት ደሞ ሁለት ሁለት አዋርድ በማሾነፍ 3ተኛን ይዘዋል።

ስለ ተኚታታይ ድራማ ኚወራት በኃላ ጉማ "ሉሲ አዋርድ" ብሎ ተኚታታይ ድራማዎቜን ብቻ እንደሚሞልም ገልጿል።

ይህ መሹጃ በፅዮን ታምራት ዹተዘጋጀ ነው!

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍14❀6🔥1
📌ተፈራሚሙ !

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኩል á‰ áŒ‹áˆ« ለመስራት ተፈራሚሙ::

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ በጎ አድራጎት ድርጅት እና ስዊት ላይፍ ፎር ኩል በጎ አድራጎት ድርጅት በኢትዮጵያ ህገወጥ ዹሰውን ዝውውር ለመኹላኹል ፣ አስተማማኝ ፍልሰትን ለማስተዋወቅ እና ለተመላሟቜ ዳግም ዚመዋሃድ ድጋፍን ለማጠናኹር ዹተቀናጀ ጥምሚት ለመጀመር ዚመግባቢያ ሰነድ (MoU) በይፋ ተፈራርመዋል።

"ዲጂታል ድምጟቜ፣ እውነተኛ ተጜዕኖ፡ ዚፍልሰት አስተዳደር ዚሚዲያ ንቅናቄ በኢትዮጵያ"  á‹­áˆ… ዘላቂ ዚሶስት ወራት ዘመቻ ኹዓለም አቀፍ ዚፍልሰተኞቜ ቀን ( Dec18) በፊት ዚሚዲያ ቅስቀሳን እና ዚማኅበሚሰብ ግንዛቀን ያጠናክራል ዚተባለውን ዘመቻ ያድጀምራሉ።

ዘመቻው በተጎጂዎቜ ላይ ያተኮሩ ምስክርነቶቜን፣ አስተማማኝ እና ህጋዊ ፍልሰት ላይ ዚባለሙያ መመሪያዎቜን እና በአገር አቀፍ ደሹጃ ኹፍተኛ ተጋላጭነት ላላቾው ማህበሚሰቊቜ ዚታለሙ ዚግንዛቀ መልዕክቶቜን ያስተላልፋል።

"ጣፋጭ ህይወት" ዚሬዲዮ ፕሮግራምን ጚምሮ በተለያዩ ዚሚድያ አማራጮቜ ተኚታታይነት ያለው ፕሮግራም በማድሚግ አቅጣጫዎቜን ኹአላማው ለማሳካት  መሰሚት ያደርጋል።

ሁለቱ ተቋማት በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዚሚታሰበውን ዚፍልሰተኞቜ ቀን Dec18/ 2025 በተለያዩ ተግባራት ይኚውናሉ።

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኩል ለጋሟቜ እና ባለድርሻ አካላት በብሔራዊ ዚመኚላኚያ ዘመቻዎቜ ላይ ኢንቚስትመንትን እንዲያሰፉ እና ለተጎጂዎቜ ዚስነልቊና፣ ዚትምህርት ስልጠና እና ዚኑሮ ድጋፍንም አቅደዋል።

ሲግማ ምስራቅ አፍሪካ ትኩሚቱን በስደት ላይ በማድሚግ ዚሚሰራ ሲሆን በተመሳሳይ ስዊት ላይፍ ፎር ኩል ወጣቶቜን  ሁለገብ አቅም ለማሳደግ ትኩሚት በማድሚግም ይሰራል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6
📌 ሁለት ዚሥዕል አውደርዕዮቜ በዕይታ ላይ ይገኛሉ

ዚተፈሪ መኮንን ፖሊ ቮክኒክ ኮሌጅ ዚሥነጥበብ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ተማሪዎቜ ያዘጋጁት ዚሥነጥበብ ዓውደርዕይ በዚህ ሳምንት በይፋ ተኚፍቷል።

ዚሥዕል አውደርዕይውም ቅዳሜ እና እሁድን ጚምሮ እስኚ ታኅሣሥ 2 2018 ዓ.ም ድሚስ በኮሌጁ ዚሥዕል ማሳያ ውስጥ በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።

በሌላ በኩል "አብሮነት" ዹተሰኘው በብሩ ወርቁ ፣ያሬድ ወንደሰን እና ዘውዱ ገ/ሚካኀል ዹተዘጋጁ ዚሥዕል ሥራዎቜ ዚቀሚቡበት አውደርዕይ ባሳለፍነው ሚቡዕ ህዳር 3 2018 ዓ.ም በፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል ለእይታ ክፍት ሆኗል። እስኚ ህዳር 29 2018 ዓ.ም እንደሚቀይም ተነግሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6
📌 "መልቲ" ተውኔት በይፋ ተመሹቀ

በስንታዚሁ ታዬ (ፋቡላ) ዹተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቎አትር በትናንትናው ዕለት በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።

በአዶት ሲኒማ በተመሹቀው ትያትር ታላላቅ ዚኪነ ጥበብ ባለሙያዎቜ፣ ትያትር አፍቃሪያን፣ እና በርካታ ተመልካ቟ቜ ተገኝተዋል።

በኹፍተኛ ዚተመልካቜ ሳቅ ዚታጀበው  ዹ"መልቲ" ትያትር ዚመጀመሪያ ዚምርቃት መድሚክ በብዙዎቜ ዘንድ አድናቆትን ማግኘት ቜሏል።

ዚዕለቱ ዚክብር እንግዳ ዚኢፌድሪ ዹቮክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ኚድር (ዶ/ር) ትያትሩ እንዲሳካ ላደሹጉ ዚምስክር ወሚቀት ሰጥተዋል።

ትያትሩ ዘወትር አርብ በ11:30 በአዶት ሲኒማ በቋሚነት መታዚት ይጀምራል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀2
📌"ውብ አዲስ ፩" ዚሥዕል ትርዒት ሊኚፈት ነው

"ውብ አዲስ" በሚል ርዕስ ፣ትኩሚቱን በአዲስ አበባ ኹተማ ላይ ያደሚገ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓመት ውስጥ ሶስት ተኚታታይ (ኚህዳር-2018 እስኚ ህዳር-2019) ዹግል ዚሥዕል ትርዒት (Solo Art Exhibition) ለማቅሚብ ሠዓሊ ሀሮን ዝግጅቱን ጚርሷል።

ዚመጀመሪያውን "ውብ አዲስ ፩" ዚሥዕል ትርዒትም ኚአርብ ህዳር 12 ቀን 2018 á‹“.ም ኹቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ጎላ ሚካኀል አካባቢ በሚገኘው ጎላ ሥነ ጥበብ ማዕኚልለህዝብ ዕይታ ክፍት ይሆናል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6
📌ዚ"ቁንጅና" ሙዚቃ ግጥም ዹዓለምፀሐይ ወዳጆ አይደለም ሲል ዳዊት መለሰ ተናገሹ

ኚሁለት አስርት ዓመታት በኃላ 'ምስጢር" ዹተሰኘ አልበሙን ለአድማጮቜ ያቀሚበው ዳዊት መለሠ ሰይፉ ሟው ላይ ቀርቩ ነበር።

በዚህ ቃለመጠዹቁ ዳዊት መለሠ በርካታ ዚእሱ ሙዚቃ ወዳጆቜ ስለሚወዱለት "ቁንጅና" ሙዚቃው ተኚታዩን ብሏል"ቁንጅና ዹተሰኘው ዘፈኔን ዓለምፀሐይ ወዳጆ ዚፃፈቜው ዚሚመስላ቞ው ብዙ ሰዎቜ አሉ።ዘፈኑን ዹፃፈው ዮናስ ሙላቱ ዚተባለ ኪቊርድ ተጫዋቜ አለ።ቁንጅና እና ብቻሜን ዹተሰኘ ሁለት ዘፈን ሰጠኝ።ዓለምፀሐይ ዚፃፈቜው ፍሹጂኝ ዹተሰኘውን ዘፈን ነው"

በሌላ በኩል ኚራሱ ሕይወት ጋር ዹሚገኘው ሙዚቃው "እህል ውሃ" ዹተሰኘው እንደሆነም ተናግሯል"ኚራሎ ሕይወት ጋር ዹሚገናኝ ዘፈን ዚዘፈንኩት እህል ውሃ ዹተሰኘውን ዘፈን ነው።቎ዲ አፍሮ ዚቀድሞ ፍቅሚኛዬን ያውቃት ነበር። አሜሪካ ሀገር ሲመጣ ደህና ነቜ ወይ? ሲለኝ አዎ ደህና ነቜ ሞክሹን ነበር አልሆነም አልሰራም አልኩት።እህል ውሃ ዹሚለውን ዘፈን ሰርቶ ሰጠኝ። ቎ዲን ዹማደንቀው ትልቅ ጭንቅላት ያለው ልጅ ነው።በዜማም በግጥምም ዹበሰለ ልጅ ነው"

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍6❀5
📌ዚአበጋዝ ክብሚወርቅ ሺዎታ አባት አሹፉ

ዚታዋቂው ዹሙዚቃ ሰው አበጋዝ ክብሚወርቅ ሺዎታ ወላጅ አባት ማሹፋቾው ተሰምቷል።

አበጋዝ ኹወላጅ አባቱ አቶ ክብሚወርቅ ጋር ኚወራት በፊት በታዋቂዋ ሞዮልና ፋሜን ዲዛይነር አና ጌታነህ ፕሮውዲስ በሚደሹገው ፕሮግራም ( በአቩል ቲቪ ) ላይ ቀርቩ እንደነበር ይታወቃል።

ምናልባትም ኚቅርብ ሰዎቹ ውጭ ብዙ አድናቂዎቹ አባቱን በመልክ ያዩዋ቞ው በዚያ ፕሮግራም ነው። ዹሙዚቀኛ አበጋዝ ክብሚወርቅ ሺዎታ አባት አቶ ክብሚወርቅ ኹዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢6💔3
📌ለሚዲያ በሰጡት መሹጃ ኚኃላፊነታ቞ው ተነሱ

ዚጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር በአካባቢው ስለተኚሰተው “ዚሔሞሬጂክ ፊቹር” እንደሆነ በተገመተው ተላላፊ በሜታ ሰዎቜ መሞታ቞ውን ገልፀው ለመገናኛ ብዙሀን መሹጃ መስጠታ቞ውን ተኚትሎ ኚሀላፊነታ቞ው ተነሱ።

ዚጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢንያም አስራት ለአንድ ዓለማቀፍ ሚዲያ “ዚሔሞሬጂክ ፊቹር” እንደሆነ በተገመተው በሜታ ሳቢያ ሀኪሞቜን ጚምሮ ሰዎቜ መሞታ቞ውን ገልፀው መሹጃ በመስጠታ቞ው ኚሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ምስጢሩ ሐምደኪ በተጻፈ ደብዳቀ ኚሕዳር 5 ቀን 2028 ዓ.ም ኚሀላፊነታ቞ው መነሳታ቞ው ተነግሯ቞ዋል። 

ዳይሬክተሩ ኚሃላፊነት ኚመነሳታ቞ው በፊት ወደ ሆስፒታሉ መጥተው ኚታኚሙት አራት በሜተኞቜ አንዱ በህይወት እንዳለ እና ዚተሻለ ዚሚባል ዚጀና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ሁለት ዚሆስፒታላ቞ው ዚጀና ባለሙያዎቜን ጚምሮ እስካሁን ስድስት ሰዎቜ ተመሳሳይ ምልክቶቜን በማሳዚት ህይወታ቞ው ማለፉን ለዶ቞ ቹለ ራዲዮ በይፋ ገልፀው ነበር።

ዚበሜታው ክስተትና ምንነት ዓለማቀፍ ትኩሚት ዚሳበ ሲሆን ዹዓለም ዚጀና ድርጅትም ኚመንግስት ጋር በመቀናጀት አስ቞ኳይ ዚመስክ ቡድን ወደ ስፍራው ልኳል። 

ዚጀና ሚኒስ቎ር እስኚአሁን ድሚስ ስምንት ሰዎቜ  በበሜታው ዚተጠሚጠሩ መሆኑን ባወጣው መግለጫ ይፋ ያደሚገ ሲሆን ስለ ሞቱ ሰዎቜ  ያለው ነገር ዚለም።
ዶክተር ቢንያም አስራት በበሜታው ሞት መመዝገቡን ይፋ ካደሚጉ በኋላ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እዚደሚሰባ቞ው እንደሆነ ዚቅርብ ዚስራ ባልደሚቊቻ቞ው ነግሹውናል ሲል ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😡31❀5😁2🀯2🀬2🀚2🀔1
📌እንጀራ በሞቀጣ ሞቀጊቜ ሱቅ መሞጥ መኹልኹሉ ተገለጾ

ዚአዲስ አበባ áˆáŒá‰¥áŠ“ መድሃኒት ባለስልጣንን ዚተለያዩ ሞቀጣሞቀጊቜ በሚሞጡባ቞ው ሱቆቜ ውስጥ እንጀራ መሞጥ መኹልኹሉን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።

ዚባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ ዚተለያዩ መርዛማ ነገሮቜ ሳሙና እና ለጀና ጠንቅ ዹሆኑ ሞቀጊቜ በሚሞጡባ቞ው ሱቆቜ በቀጥታ ለምግብነት ዚሚውሉትን እንጀራ እና ዳቊን መሞጥ ልክ ባለመሆኑ ለመኹልኹል መገደዳ቞ውን ተናግሹዋል ሲል ነው ዘገባው ዚጠቀሰው።

እንጀራ እና ዳቊ መሞጥ ያለባ቞ው በምግብ ቀቶቜ፣ በዳቊ ቀተቜ እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቊታ ብቻ መሆኑንም በማንሳትም ያልተፈቀደላ቞ው ነጋዎዎቜም ሲሞጡ ኹተገኙ አስፈላጊው ዚእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባ቞ው አስገንዝበዋል ሲል ገልጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😱9😁8❀4👍3
📌ዚሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ አልበም ሊለቀቅ ነው

ዹሙዚቀኛ መሐመድ ራጅኡ "ብርሃን" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው በመሳሪያ ዚተቀነባበሚ ዹሙዚቃ አልበም ዚፊታቜን አርብ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሙዚቃ አፍቃሪያን ይደርሳል ተብሏል። 

ለማዘጋጀት አንድ ዓመት እንደወሰደ ዹተነገሹው "ብርሃን" ዹሙዚቃ አልበም አስር አንድ ዹሙዚቃ ስብስቊቜን ይዟል።

"ብርሀን" በተሰኘው ሁለተኛ አልበሙ በኪቊርድ፣ ቀዝ፣አኮስቲክ ጊታር፣ክራር፣ ዹሙዚቃ መሳሪያዎቜ ዚተሰሩ ዹሙዚቃ ስራዎቜ ተካተዋል።

አልበሙ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜ በተገኙበት በትሪፕል ሆቮልና ስፓ ዹሚመሹቅ ይሆናልም ተብሏል።

ዚፊታቜን ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በDeamat records ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃልም ተብሏል።https://youtube.com/@deamatrecords?si=91IxewcK1ZdGshgL

ሙዚቀኛ መሐመድ ኹዚህ ቀደሞ "ሰላምታ " ዹተሰኘው ዚመጀመሪያ አልበሙን በ2010 ዓ.ም ለአድማጭ አድርሷል።

ሙዚቀኛ መሐመድ ዹሙዚቃ ኪቊርድ መጫወት ዹጀመሹው 1998 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዓመት አፍሪካ ጃዝ ስኩል ( ጃዝ አምባ ) ተምሯል።

ሙዚቀኛው ኚትግርኛ ዘፋኞቜ መሐል ለሹጅም ጊዜ  ዚአብርሃም ገብሚመድህን ፣ ዚማህሌት ገብሚጊዮርጊስ ፣ ዚሞዊት መዝገቩ ኪቊርዲስት በመሆን በብዙ አገራት ቱር አድርጓል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8👍7🔥1
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ ዚጋዜጠኞቜ ቀን ነው

ዹዓለም አቀፉ ዚጋዜጠኞቜ ቀን በዚዓመቱ በጎርጎሮሳዊያኑ ዹጊዜ ቀመር November 19 ይኚበራል።

ጋዜጠኝነት ዜና እና መሹጃን ዚመሰብሰብ፣ ዚማጣራት፣ ዹመተንተን እና ለህዝብ ዚማቅሚብ ተግባር ወይም ሙያ ነው።

ጋዜጠኞቜ በሥልጣን ላይ ያሉትን ተጠያቂ በማድሚግ እና ድምጜ ለሌላቾው ድምጜ በመስጠት በህብሚተሰቡ ውስጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ በሃሳብ ደሹጃ ይታመናል።

ጋዜጠኝነት እውነትን ዹማወቅ ፍላጎትና ጉጉት ነው። ጋዜጠኝነት ታማኝነትን ዹተላበሰ ሙያ ነው። በስራው ታማኝ እና ስነ ምግባር ያለው፥ ሁል ጊዜም እውነትን ለመናገር ዚሚጥር ነው ጋዜጠኛ ዚሚባል ጋዜጠኛ።

ጋዜጠኝነት ፅናት ነው። ጜኑ መሆንንና ቆራጥነትን ያዘለ፥ ኚፍራቻ ዚፀዳፀ ገለልተኛነትን ዹተላበሰ ነው ጋዜጠኝነት።

ኚአድሎ መንፃትፀ ዚርህራሄ ተምሳሌት መሆንፀ ተጚባጭነትፀ አሳማኝና ምክንያታዊ መሆን ነው ጋዜጠኝነት።

ጋዜጠኝነት ነፃነት ነው። ራሱን ዚቻለ እና በውጫዊ ጫናዎቜ እና ፍላጎቶቜ ተጜእኖ ስር አለመውደቅ ነው ጋዜጠኝነት።

ዹመሹጃ ምንጮቜን ሚስጥራዊነት ማክበርፀ ለተጠያቂነት ራስን ማዘጋጀትፀ ለተሰራው ስራ ተጠያቂ መሆንፀ ስህተትን ለማሹም እና ለስህተት ይቅርታ ለመጠዹቅ ፈቃደኛ መሆን ነው ትክክለኛ ጋዜጠኝነት።

እናም ኹላይ ዚተነሱ ሀሳቊቜን በጥቂቱ ዚምታሟሉ ጋዜጠኞቜ፥ እንኳን ለቀናቜሁ አደሚሳቜሁ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀26👍8🥰1
📌አሻም ቲቪ 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ ተኹሰሰ

አሻም ቎ሌቪዥን ብዛታ቞ው 22 በሚሆኑ ሰራተኞቹ አማካይነት ክስ ዚተመሰሚተበት ሲሆን፣ በዚሁም ሂደት ዚድርጅቱ ንብሚቶቜ ሙሉ በሙሉ እንዳይንቀሳቀሱ በዛሬው ዕለት በዋለው ቜሎት ዕግድ እንደተላለፈበት ለጉዳዩ ቅርበት ያላ቞ው ምንጮቜ ገልጞዋል። ምንጮቹ አክለውም፣ ለጣቢያው ጋዜጠኞቜ ዚሶስት ወራት ደመወዝ እንዳልተኚፈለ አመልክተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁኑ ሰዓት ድሚስ፣ አሻም ቲቪ ዹሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ ዚለም።

ኹዚህ ቀደም ዚጣቢያው ቢሮ መታሞጉ ዚሚታወስ ሲሆን፣ ጣቢያውን በባለቀትነት ዚሚያስተዳድሚው አሻም ትሬዲንግ ዚእሞጋ ተግባሩ "ጣቢያውን ወደ መደበኛ ስራው ለመመለስ ኹሚደሹጉ ጥሚቶቜ" ጋር አስተሳስሮ ምላሜ ሰጥቶ ነበር።

©ሚኪያስ ጥላሁን

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4👍3😱3🀔1🕊1