Event Addis Media
9.6K subscribers
6.05K photos
12 videos
4 files
4.67K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌OBN የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግን በነፃ አሳያለሁ አለ

የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ውድድር በነፃ ለተመልካች እንደሚያስመለክት በይፋ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዚህ በፊት በዲኤስቲቪ በክፍያ ሲተላለፍ የቆየ ሲሆን በቀጣይ በነፃ ለተመልካች ይደርሳል።

OBN የውጭ እና ሀገር ውስጥ ሚዲያዎችን ተወዳድሮ በማሸነፍ የሊጉን የስርጭት መብት መግዛቱን በይፋ አሳውቋል።

ዲኤስቲቪ በመጨረሻ የሊጉ አመታት ቆይታው በ OBN የፕሮዳክሽን መሳሪያዎች ተከራይቶ ሊጉን ሲያሳይ እንደነበር ይታወቃል።

በርካታ ተመልካቾች ያሉት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሀገራችን ሚዲያ በነፃ መቅረቡ ለስፖርቱ ተመልካቾች መልካም ዜና ሆኗል።

በስምምነቱ ዙሪያ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁167😍3👎2🤣2👍1👏1💩1
📌 የኃይሉ አመርጋ አልበም የሚለቀቅበት ቀን ታወቀ

ድምጻዊ ኃይሉ አመርጋ ከተራራው ማዶ፣ እንግዳ፣ ይነጋል፣ ማርዬ፣ ይገርማል የተሰኙ ሙዚቃዎችን ጨምሮ አስር ያህል ሥራዎችን በጃኖ ባንድ በኩል መዋጮ አድርጎ።

ከጃኖ ባንድ ባንድ መፈርስ በኃላ ከኃይሉ አመርጋ በቀር 3ቱ የባንዱ ድምጻዊያን በየፊናቸው የራሳቸውን የሙዚቃ  አልበም ለአድማጮች አቅረበዋል።

በሙዚቃ ወዳጆችም ዘንድ የኃይሉ አመርጋ የሙዚቃ አልበም መቼ  ነው የሚለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ለድምጻዊው ሲቀርቡ ቆይተዋል።

ለዚህም ጥያቄ በመጨረሻም አልበሙ ለአድማጮች የሚቀርብበት ቀን ታወቋል።

ድምጻዊው በግሉ የሰራው የመጀመሪያ አልበሙ ጥቅምት 21 2018 ዓ.ም ለአድማጮች እንደሚቀረብ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የአልበሙን ስራ ለመከውን ስድስት ዓመታት እንደፈጀ የተነገረለት አልበሙ "አሁን " የተሰኘ ርዕስ ተሰጥቷል።

ከመለቀቁ በፊትም ጥቅምት 18 2018 ዓ.ም የሙዚቃ ማድመጭ መሰናድ እንደተዘጋጀለትም ሰምተናል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
36🔥6
📌ታላቁ አባት ሐጂ ኡመር ኢድሪስ አረፉ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢45💔76😭3
📌"ጀሚላ" የተሰኘ ፊልም ዛሬ ይመረቃል

በዜማ ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ በካብ ኢንተርቴይመንት አቅራቢነት ለእይታ የሚቀረበው ይህ ፊልም ድርሰትና ዝግጅቱ  የደራሲና ዳይሬክተር ፀጋ ካህሳይ (ጃምቦ ) ነው።

የፊልሙ ጭብጡም እንደ ሃገር እንደ ቤተሰብ  በፍቅር ተዋዶና ተፈላልጎ የመኖር ነባር ቤተሰባዊ ባህላችንን በማጠናከር ዙሪያ የሚያጠነጥን የፍቅር ፊልም ነው።

የ“ጀሚላ” ፊልምን ስራዎችን ለመከወን ከሁለት አመት በላይ እንደፈጀ የተነገረ ሲሆን  1:35 ደቂቃ የሚፈጅ የቆይታ ጊዜ አለው።

በትወና አዳዲስና ነባር ተዋንያን የተሳተፉበት ሲሆን ሄኖክ አለማየሁ፣ነፃነት አንበርብር
ምህረት በለጠ ፣ቁምላቸው አዱኛ(ከድር ሰተቴ)  ሌሎችም ተሳታፈዋል።

ጀሚላ ፊልም ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 10 2018 ዓ.ም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዓለም ሲኒማ  ከ11:00 ጀምሮ ይመረቃል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
5👍4
📌ታሪካዊው አንበሳ መድሐኒት ቤት ፈረሰ

አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ የሚገኘዉ እድሜ ጠገቡ አንበሳ ፋርማሲ መፍረሱን ቅዳሜ ገበያ በስፍራው ተገኝታ አረጋግጣለች።

እየፈረሰ ያለው አንበሳ ፋርማሲ ከተመሰረተ 80ኛ ዓመቱን የያዘና ጥንታዊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በጀርመናዉያን ሁለተኛ እና በሦስተኛ ትዉልድ እየተንቀሳቀሰ የነበረው አንጋፋዉ አንበሳ መድሐኒት ቤት የመድሐኒት ሽያጭና ቅመማ ብቻ ሳይሆን የሕክምና ቁሳቁስ አስመጭና አገር ውስጥ አከፋፋይም ነበር ።

ከዓመታት በፊት አንበሳ ፋርማሲ ይፈርሳል መባሉን ተከትሎ በአዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ኤምባሲ የአንበሳ መድሐኒት ቤትን ድጋፍ መስጠትን ይመለከታል በሚል ለአዲስ አበባ ከተማ የወቅቱ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በፃፈዉ ደብዳቤ አዲስ አበባን ብሎም ኢትዮጵያን የጀርመን የመዋለ ንዋይ ፍሰት መዳረሻ ለማድረግ እንደሚያበረታታ አንድ ኤምባሲ፤ ጉዳዩ ሕጋዊ መንገድን መከተል አለበት ብለን እናምናለን። ምክንያቱም በእድሜ ጠገቡ የአንበሳ መድሐኒት ቤት ላይ አስተዳደሩ ይወስዳል የተባለዉ ርምጃ ሌሎች የጀርመን ባለ ኃብቶችን ሊያሸሽ ይችላል ሲል ደብዳቤ ማግባቱ በወቅቱ ተዘግቧል።

አንበሳ ፋርማሲ የሚገኝበት አነስተኛ ህንጻ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሲሆን ከአመታት በፊት ከአካባቢ ልማት ጋር በተያያዘ ፋርማሲው ይፈርሳል ተብሎ የሚናፈሰው መረጃ ፍጹም ከእውነታው የራቀና መሰረተ ቢስ መረጃ ነው ሲል ኮርፖሬሽኑ ማስተባበሉ የሚታወስ ነው።

Via ቅዳሜ ገበያ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😭63
📌የጋዜጠኝነት ስልጠና ለሰልጣኞች

ጋዜጠኝነትን መማርና ጋዜጠኛ መሆን ህልማችሁ ከሆነ ልጠቁማችሁና ወደሴጅ ጎራ በሉ።

ደግሞ 6 ወር ብቻ በቂ እንደሆነ ሰምቻለሁ።

ስልጠናው ልምድ ባላቸውና የሚዲያውን ዓለም በሚያውቁት መምህራን  ይሰጣል። ተጋባዥ እውቅ ጋዜጠኞችም ከልምዳቸው ያካፍላሉ።

9ኛ ዙር ላይ ደርሰው አሁንም ለ10ኛ ዙር አዳዲስ ሰልጣኞችን እየመዘገቡ ነውና እንዳያመልጣችሁ።

ጋዜጠኝነቱን ለይቼ ጠቆምኳቹ እንጂ ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከ30 በላይ በሆኑ ዘርፎች ስልጠና ይሰጣል።

ሴጅ ላለፉት ዓመታት በማሰልጠን በሙያ ምዘና ብቃት አስመዝኖ በማብቃት ለገበያው ተወዳዳሪ የሆነ ባለሙያዎች በማበርከት ላይ የሚገኝም ተቋም ነው።

ከታች ካሉት አድራሻዎች በተጨማሪ በማስፈንጠሪያዉም ጎብኟቸው።

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute

Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/

Threads: https://www.threads.net/@sage_training_institute
11👍3👎2
📌 አሻም ቴሌቪዥን ታሸገ

በአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የሚተዳደረው "አሻም ቴሌቪዥን" ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደታሸገ ኤቨንት አዲስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው በምን ምክንያት እንደታሸገ ለጊዜው አልታወቀም።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🙊85😱2
📌 "ኑ እንጫወት ልብ እንጠግን" ልዩ መርሐግብር

በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል እየተጫወትን የህጻናትን ልብ ለመጠገን ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ ፈስቲቫል ለሕፃናት እና ለታዳጊዎች ተዘጋጅቷል።

ፌስቲቫሉ ልባቸውን ለመታከም ወረፋ በመጠበቅ ላይ ላሉ ሕፃናት ገቢ ለማሰባሰብ እና ለማህበረሰብ ደሞ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ዓላማ ያደረገ ነው።

ለሕጻናት እና ለታዳጊዎች የተዘጋጀው ፌስቲቫሉ ቅዳሜ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በአምባሳደር ፓርክ ከጠዋት 4፡00 ጀምሮ ይካሄዳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
7👍2
📌ጥበብና የአእምሮ ጤና አውደርዕይ መዝጊያ

በሜታል ሄልዝ አዲስ የተዘጋጀውና የአእምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ የሥዕል ስራዎችየቀረቡበት አውደርዕይ በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ሲካሄድ ቆይቷል።

በዚህ "Art inspired by mental health" በሚል ርዕስ በተካሄደ አውደርዕይ ላይ የሠዓሊ ሶሎሜ ጌታቸው፣ የሠዓሊ አለማየሁ ደረሰማ ሥዕሎች ቀረበዋል።

ይህ የሥዕል አውደርዕይ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች የመዝጊያ ሥነሥርዓቱ ይከናወናል ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
6
📌በጣቢያው ባለቤት የታሸገው አሻም ቴሌቪዥን

አሻም ቴሌቪዥን ከትላንትና ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በጣቢያው ባለቤቶች እንደታሽገ ጣቢያው ከአሰራጨው መግለጫ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።

አሻም በመግለጫው "የቴሌቪዥን ጣቢያው ከረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የጣቢያውን መደበኛ ስርጭት ማከናወን አልተቻለም።ችግሩን ለመቅረፍ የሚዲያው አስተዳደር ጥረቶች እያደረገ ይገኛል:: ያጋጠመው ችግር እስኪስተካከል በሚል አስተዳደሩ በካሜራና መሰል የሚዲያው ንብረቶች እንዳይንቀሳቀሱ ፤ የውስጥ ንብረት ክፍሉን አሽጓል" ሲል አስታውቋል።

ጣቢያው ይህንን ይበል እንጂ አንድ የቴሌቪዥን ጣቢያው ሰራተኛ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጣቢያው ምን እንደተፈጠረ እንዲህ ሲል ያብራራል "ከቅርብ ግዜ ( ከ5 ወይ 6 ወር ) ወዲህ ምን እንደሆነ ባናዉቅም (የሚነገረን ምክንያት ብር የለንም ብቻ ነበር ) ቤቱ የሰራተኛን ደሞዝ በማቆየት እና ከዛም ባለፈ እስከ 2 ወራት ባለመክፈል ቆይቷል።

እኛም የገጠመውን ችግር በመረዳት በተደጋጋሚ ደሞዙን ሳይጠይቅ በገባለት ሰዓት ጠብቀናል። በሚዲያው ዉስጥ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ፣ ተከራይ እና ብዙ ወጪዎች ያሉበት ሰራተኛ እንደመኖሩ ለወራት በችግር አሳልፈናል። የሆነዉ ሆኖ ነገሮች ተስተካከሉ ስንል እየባሱ በመምጣታቸዉ በድጋሜ በመስከረም ወር ጀምሮ የሁለት ወር ደሞዛችን እንዲገባና ጥያቄ ብናቀርብም '' በዚህ ሰዓት መክፈል አንችልም፣ከዚህ በኋላ ለአንድ ወር ጠብቁ '' የሚል ምላሽ ተሰጥቷል።ከዚህ ባለፈ የሰራንበትን የስራ ልምድ ብንጠይቅም ሊሰጡን አልቻሉም" ሲል ተናግሯል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
21🤔5😁2
📌የዶቸ ቬለ ዘጋቢዎች እንዳይዘግቡ ለጊዜዉ ታገዱ

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለዶቸ ቬለ የሚዘግቡ ጋዜጠኞች ዘገባ እንዳይሰሩ ለጊዜዉ አገዱ።

ዶቸ ቬለ ከ1980ዎቹ ጀምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በሚገኙ ዘጋቢዎች አማካኝነት የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሐብታዊና ማሕበራዊ ጉዳዮችን እና የአፍሪቃ ሕብረትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ አካባቢያዊ፣ አሐጉራዊና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ተቋማትና ማሕበራትን እንቅስቃሴና ክንዋኔዎችን ሲዘግብ ቆይቷል።

ዓለምአቀፉ ማሰራጪያ ጣቢያ ከ 2010 ጀምሮ የወኪሎቹን ቁጥር በማሳደግ መቀሌ፣ ባሕርዳር፣ ደሴ፣ አዲስ አበባ፣ ሐዋሳ፣ ድሬዳዋና አሶሳ በሚገኙ 9 ወኪሎቹ አማካይነት መረጃዎችን በማሰባሰብ ገለልተኛ፣ ሚዛናዊና ትክክለኛ ዘገባዎችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያሰራጫል። ይሁንና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዛሬ በፃፈዉ ደብዳቤዉ ዶቼ ቬለና ወኪሎቹን የኢትዮጵያን ሕግና ደንብ ጥሰዋል፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን አያከብሩም በማለት ወቅሷል።

ከዛሬ ጀምሮ ኢትዮጵያ የሚገኙ የዶቸ ቬለ ዘጋቢዎችን የሥራ ፈቃድ ለጊዜዉ ማገዱን አስታዉቋል። ባለሥልጣኑ «ጊዚያዊ» ያለዉ  እግዳ ሥለሚቆይበት ጊዜ  የገለፀዉ ነገር የለም።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
4🤔4👍2
📌አቤ ከቤ ከአሰላ እውቅና ተሰጠው

በተለያዩ የሬድዮ ጣቢያዎች እና የሬዲዮ ፕሮግራሞች ላይ በንቁ ተሳታፊነቱ ዝነኛ የሆነው አቤ ከቤ ከአሰላ በትውልድ ከተማው አሰላ በOptical Art Acadamy አማካኝነት የዕውቅና ሰርተፍኬትና ሜዳሊያ ተበርክቶለታል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
22👏5👍4
📌የአንጋፋው አርቲስት ተክሌ ደስታ የመኖሪያ ቤት በዕዳ ምክንያት የሐራጅ ጨረታ ወጣበት

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአርቲስት ተክሌ መኖሪያ ቤት የሐራጅ ጨረታ ያወጣባቸው ሚድ ትሬዲንግ ለሚባል ድርጅት ለወሰደው ብድር ቤታቸውን መያዣ በማድረጋቸውንና ድርጅቱ ብድሩን በአግባቡ ባለመመለሱ ነው።

አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ጠቢብ ተክሌ ደስታ " ድመቷን ማን ገደላት? " የሚል ተወዳጅ የቴሌቪዥን ድራማ ደራሲ የአንድን መ/ቤት መዝገብ ቤት አይጥ አስቸግሮ ድመት ሊገዛ ተፈልጎ " ድመቷ በየትኛው የመ/ቤቱ ህግ ትተዳደር ? በምን መዝገብ ላይ ትስፈር ? ለቀለቧ በጀት እንዴት ይያዝ ? " አይነት ሀሳቦች የተነሱበት የምን ጊዜም ምርጥ ሥራ ይታወቃሉ።

©️ድሬቲዩብ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢303👍1
📌'ባልቻ አባነፍሶ' ተውኔት ወደ መድረክ ሊመለስ ነው

የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ ተውኔት ማሳየት ሊጀምር እንደሆነ ተሰምቷል።

ከሰሞኑ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ባልተለመደ መልኩ ከተውኔት ደራሲያን እና ከተውኔት አዘጋጆች ጋር ልዩ ልዩ ስምምነቶችን ሲፈፅም የኤቨንት አዲስ ሚዲያ አዘጋጆች ተመልክተናል።

በዚህ የስምምነት ሥነሥርዓት ላይ ከተሰሙ ጉዳዮች በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ያለው የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ ከዓመታት በኃላ ተውኔት ማሳየት ሊጀምር እንደሆነ የተገለጸበት ጉዳይ አንደኛው ነው።

የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ ወደ ወደ መደበኛው ስራ ሲመለስም የ"ባልቻ አባነፍሶ" ቴአትርን ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ አምርቶ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለተመልካች እንደሚያቀርብ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

"ባልቻ አባነብሶ" ታሪካዊ ተውኔት እንዲዘጋጅም ስምምነት ተፈጽሟል።  የዚህ አዲስ ድርሰት መራሔ ተውኔት  በመሆን አዘጋጅ ዶ/ር ተሻለ አሠፋ የስምምነት ፊርማውን አስፍሯል።

ሌላ በኩል የደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ድርሰት የሆነው "ወህኒ አምባ" የተባለውን አዲስ ወጥ ተውኔትን ወደ መድረክ ለማምጣት ስምምነት ተፈጽሟል። 

ለዚህ አዲስ ድርሰት መራሔ ተውኔት  በመሆን አዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ የስምምነት ፊርማውን አስፍሯል። የዚህ ተውኔትም ልምምድ በይፋ ተጀምሯል።'ወህኒ አምባ' ተውኔት በሦስት ወራት ውስጥ ተሠርቶ እንደሚጠናቀቅ ተነግሯል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት የሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት በ2018 ዓ.ም ለተመልካች የሚያቀርበውን የኦሮምኛ "ሰዴተ" የተሰኘ የሙሉ ጊዜ የኦሮምኛ ተውኔት ለመመድረክ ተስማምቷል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
18👏31
📌በኢትዮጵያ የሥነ-ውበት ፕላስቲክ ሰርጀሪ ላይ የሚሰራ ዓለም አቀፍ ክሊኒክ ተከፈተ

ኤስቴቲክ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ በስነውበት ሕክምና ላይ በበርካታ ሀገራት የሚሰራ ዝነኛ ክሊኒክ ሲሆን በዓለም ዙሪያ ካሉት 8 ቅርንጫፎች በተጨማሪ ዘጠነኛውን ቅርንጫፍ በኢትዮጵያ መክፈቱ አስታውቋል።

አቮራ ቢዝነስ ግሩፕ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር በስነውበት ሕክምና በተለይም በፕላስቲክ ሰርጀሪ ዘርፍ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ከሆኑት የሕክምና ተቋማት አንዱ የሆነውን ኤስቴቲክ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ በኢትዮጵያ በፍራንቻይዝ መክፈቱ ተገልጿል።

በዘርፉ 26 አመታትን ያስቆጠረው ክሊኒኩ ከሚሰጣቸው የፕላስቲክ ሰርጀሪ መካከል የብልት፣ የመቀመጫ፣ የደረት፣ የጸጉር፣ የፊት፣ የደረት ሰርጀሪዎች ተጠቃሽ ናቸው።

አቮራ ቢዝነስ ግሩፕ በወጪ ንግድ ላይ የተሰማራ ሀገር በቀል ኩባንያ ሲሆን ድርጅቱ በዘርፉ ለሀገር እያበረከተ ከሚገኘው ቀጥተኛ አስተዋጽዖ በተጓዳኝ ከተመረጡ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ችግር ፈቺ የሆኑ አገልግሎቶችን/ ግኝቶችን ወደ ሀገር ውስጥ በማምጣት የተሻለ ማኅበረሰባዊ ተጠቃሚነት ይፈጠር ዘንድ የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ ባለራዕይ ተቋም እንደሆነ ተነግሯል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👎122👍2🤯1
📌 የሎሬቱ ቤት 'ቪላ አልፋ' ሚያዝያ ላይ ይከፈታል

ለ14 ዓመታት ዝግ የሆኖ የቆየው የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ ቤት ወይም ቪላ አልፋ እስከ ሚያዚያ 2018  ይከፈታል ተባለ።

እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በሚያዚያ 2 ቀን 2004 ዓ.ም ካረፉ በኋላ ዝግ ሆኖ እስካሁን የዘለቀው ቪላ አልፋ፤ የተለያዩ የጥገና ሥራዎች እየተሰሩለት ነው ቢባልም ግን ለሕዝብ እይታ ተከልክሎ 14ኛ ዓመቱን ይዟል፡፡

የአለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ቤት ወይም ቪላ አልፋ እስከ ጥቅምት 2018 ለሕዝብ ክፍት ይሆናል ቢባልም፤ ክፍት ከመደረጉ በፊት መሰራት ያለባቸው ሥራዎች ገና ባለመጠናቀቃቸው እስከ ሚያዚያ ወር ሊቆይ እንደሚችል ነው የተገልጿል፡፡

ቪላ አልፋ የጥገና ሥራው ከመጀመሩ በፊት ውስጡ ያሉት ተንቀሳቃሽ የጥበብ ሥራዎች እና ሌሎችም ንብረቶች ወደ ቅርስ ባለ-ስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዲሄዱ ተደርጎ እንደነበርም የሚታወስ ነው፡፡

ከመሬት በታች በሚወጣ እና ከላይ በሚዘንብ ዝናብ ቪላ አልፋ በጣም ተጎድቶ ነበር፤ አሁን ላይ ግን ከውጭ ሀገራትም ይሁን ከሀገር ውስጥ የአርቲስቱን ሥራዎች እየተመለከቱ ባለሙያዎች ትምህርት ለመውሰድ በሚችሉበት ደረጃ ጥገናው ተደርጓል ነው የተባለው፡፡

እንደ ሙዚየም የሚደራጅ በመሆኑ ጊዜ እንደወሰደም ነው የተገለጸው፡፡

የእድሳቱ ሥራ ተጠናቆ የርክክብ እና ቅርሶችን በቦታቸው የመመለስ ሥራዎች ብቻ ቀርቷል ሲሉም የብሄራዊ ሙዚየም መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ግርማይ  ተናግረዋል፡፡

የእድሳት ሥራው 65 ሚሊየን ብር እንዳስወጣ ከዚህ በፊት የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

©️አሐዱ ሬድዮ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
18🤔1
📌ዲጂዎቹ አልተደበደቡም መረጃው ሀሰት ነው

የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው Mapara A JAZZ የተባሉት ሙዚቀኞች ወደ አዲስ አበባ የመጡት የሙዚቃ ስራቸውን ለማቅረብ እንደሆነ ፖሊስ ባሰባሰበው መረጃ ማወቅ ተችሏል።

እነዚህ ግለሰቦች ስራቸውን ጨርሰው በሠላም ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ አፈናና ድብደባ ተፈፅሞብናል ብለው በፌስ ቡክ ገፃቸው ያሰራጩትን መረጃ መሰረት በማድረግ ፖሊስ ተገቢውን የማጣራት ተግባር አከናውኗል።

ተፈፅሞብናል ስላሉት ወንጀል ለፖሊስ መረጃ ደርሶ እንደሆነ ለማረጋገጥ በክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በፖሊስ ጣቢያዎች ተጠይቆ ምንም ዓይነት የቀረበ አቤቱታ ካለመገኘቱም ባሻገር በፖሊስ ምርመራ የተሰባሰቡ የተንቀሳቃሽ ምስል፣ የፎቶና የድምጽ ማስረጃዎች እንዲሁም ከአዘጋጁ ቅሩንፉድ ኢንተርቴይመንት ጭምር እንደተረጋገጠው ግለሠቦቹ ይህን የሀሠት መረጃ የለቀቁት ብዙ ተከታዮችን ለማግኘት ሆን ብለው መሆኑን ተረጋግጧል።

ግለሰቦቹ አፈናና ድብደባ ተፈጽሞብናል ያሉት አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ/ም ቢሆንም በማግስቱ ጥቅምት 15 በተጋበዙበት መድረክ ላይ ተገኝተው የሙዚቃ ስራቸውን ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገድ አቅርበው ማጠናቀቃቸው እና በሠላም ወደመጡበት ሀገር መመለሳቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እንዲሁም ከአዘጋጆቹ የተረጋገጠና ሲሆን የተሰራጨውም መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል።

ከተማችን አዲስ አበባ በአስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ሲሆን የከተማዋን ብሎም የሀገሪቱን መልካም ገፅታ ለማጉደፍ የሚደረጉ መሠል እንቅስቃሴዎችን ህብረተሰቡ በንቃት ሊከታተልና የመረጃዎቹን ትክክለኛነት ሊያጤን እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
8👎2
📌ጤናማ አፈር ለዘላቂ ምርታማነት !

ግሪን ዌቭ አሊያንስ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል በወልመራ ወረዳ በተመረጡ ቀበሌዎች ከፍተኛ አመራር እና በመሪ ስራ አስፈጻሚዎች፤ የፕሮግራምና ፕሮጀክት ማኔጀሮች እንዲሁም የክልሎች የዘርፍ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች እና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች( ቲክቶከሮች) በተገኙበት የመስክ ጉብኝት መርሃ ግብር  አካሂደዋል።

በኩታ ገጠም እና በክላስተር የታረሱ በኑራ የታከሙ መሬቶች ከዚህ ቀደም ከሚሰጡት የምርት መጠን በእጥፍ እየሰጡ እንደሆነ በመስክ ምልከታው ወቅት ማበራሪያ ተሰጥቷል።

ይህ ተሞክሮ ውጤታማ በመሆኑ በሌሎች አከባቢዎችም  በማስፋት  እና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።

አሁን እየተዘራ የሚገኘው ጥራቱን የጠበቀ የቢራ ገብስ በመሆኑ በአቅራቢያው የሚገኘው ኬኛ ቢራ እየተረከበ ሲሆን በቀጣይ ከድንች ጋር እየተፈራረቀ በኖራ የታከመው መሬት ከፍተኛ ምርት እየሰጠ እንደሚገኘ ተነግሯል።

ግሪን ዌቭ አሊያንስ በአርቲስት ሚኪያስ ነጋሳ የተመሰረተ ሲሆን ባለፉት ዓመታት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመሆን የኪነጥበብ እና የሚድያ ባለሙያዎችን ጨምሮ የተለያዩ የማኀበረሰብ ክፍሎችን በማንቀሳቀስ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ሲካኼድ እና አሻራውን ያሳረፈ አንጋፋ  ድርጅት ነው።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
3
📌ድምፃዊ ወንዲ ማክ አዲስ ገሚስ (EP )አልበም ለአድማጭ ለማድረስ መዘጋጀቱ ገልጿል

'ክምክም' የተሰኘው የወንዲ ማክ ገሚስ EP አልበም 6 ያህል በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የተቀነቀኑ ዘፈኖች እንዳሉትና ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን ለአድማጭ ለማድረስ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አስነብቧል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍2👏1
የፎቶግራፍ እና አጫጭር ፊልሞች ውድድር ይፋ ሆነ

የ5ኛውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና አጫጭር ፊልሞች ውድድር በመሳተፍ ዛሬውኑ ይቀላቀሉ ይሸለሙ!

የፎቶግራፍ ውድድር፦ ትምህርት የማግኘት መብት

‘የትምህርት መብት’፦ ሰፊና በርካታ ተያያዥነት ያላቸውን ጉዳዮች የሚዳስስ ሲሆን ከመሠረታዊ ሰብአዊ መብቶች መካከል የሚመደብ ነው። ማንኛውም ሰው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በነጻ እንዲያገኝ፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በአጠቃላይ ለሁሉም ክፍት፣ ተደራሽ እና በሂደትም በነጻ እንዲቀርብለት፤ እና የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ደግሞ ችሎታን መሠረት አድርጎ ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርግ፣ በሂደትም ያለክፍያ ማስገኘት የሚያስችል መብት ነው። በአጭሩ የትምህርት የተጠበቀላቸውን እና ያልተጠበቀላቸውን ልጆችና ወጣቶችን ሁኔታ የሚያሳዩ ፎቶ ግራፎችን በካሜራዎ በማስቀረት ለውድድር ያቅርቡ!

የአጫጭር ፊልሞች ውድድር፦ (ጀማሪ፣ ባለሙያ) ዘርፍ ውድድር የነጻነት መብት
የነጻነት መብት ማንኛውም ሰው በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጭ ያለመያዝ ወይም ክስ ሳይቀርብበት ወይም ሳይፈረድበት ያለመታሰር መብትን የሚመለከት ነው፡፡ የነጻነት መብት የመጠበቅ እና የማጣት ሁኔታን የሚያስቃኙ አጫጭር ፊልሞችን በሞባይል እና በፕሮፌሽናል ካሜራ በመቅረጽ፣ አርትኦት በመሥራት ይወዳደሩ።  

ተወዳዳሪዎች ለውድድር ያቀረቧቸውን ፎቶግራፎች እና አጫጭር ፊልሞች በመቀበል ላይ ነን።

ውድድሩ እስከ ኅዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ክፍት ሆኖ ይቆያል!

ለተጨማሪ መረጃ፦  https://filmfest.ehrc.org
                        0973149236

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
1
📌ሉሲና ሰላም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ

በቼክ ሪፐብሊክ ለእይታ ቀርበው የነበሩት ሉሲና ሰላም ከሁለት ወር ቆይታ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።

ሁለቱ ቅሪተ አካላት በፕራግ ሙዚየም የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ዛሬ ንጋት ላይ አዲስ አበባ መግባታቸውን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በቆይታቸው ከመላው አውሮፓ በጎረፉ ቱሪስቶች እንደተጎበኙ እና የኢትየጵያን የሰው ዘር መገኛነት በዓለም አደባባይ ማስተዋወቃቸውንም ጨምሮ ገልጿል፡፡

ሁለቱ ቅርሶች ከነሐሴ 19፣ 2017 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 13፣ 2018 ድረስ በፕራግ ሙዚየም ለሕዝብ እይታ ቀርበዋል፡፡

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁102