📌የአእምሮ ጤና ላይ ያተኮረ አውደርዕይ
የአእምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ የሥዕል ስራዎች
የቀረቡበት "Art inspired by mental health " አውደርዕይ ባሳለፍነው ማክሰኞ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ተከፍቷል።
በዚህ አውደርዕይ የሠዓሊ ሶሎሜ ጌታቸው፣ የሠዓሊ አለማየሁ ደረሰማ ሥዕሎች ቀረበዋል። አውደርዕይው እስከ ጥቅምት 8 ድረስ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የአእምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ የሥዕል ስራዎች
የቀረቡበት "Art inspired by mental health " አውደርዕይ ባሳለፍነው ማክሰኞ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ተከፍቷል።
በዚህ አውደርዕይ የሠዓሊ ሶሎሜ ጌታቸው፣ የሠዓሊ አለማየሁ ደረሰማ ሥዕሎች ቀረበዋል። አውደርዕይው እስከ ጥቅምት 8 ድረስ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤13👍2
📌የመንሱር እና ብስራት ሬዲዮ ውዝግብ
የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።
ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ከሬድዮ ጣቢያው ጋር ስለተፈጠረው ውዝግብ ተከታዩን ብሏል"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር ''ብስራት-ስፖርት" የተሰኘውን ፕሮግራም ለ12 ዓመታት ሳቀርብ መቆየቴ ይታወቃል።
ይሁንና በእነዚህ ሁለት ቀናት (ረቡዕ እና ሐሙስ መስከረም 28 እና 29) ከእኔ የስራ ትጋት ጋርባልተያያዘ (በግሌ ልፈታው በማልችለው ምክንያት) ከጣቢያው ጋር ያልተግባባንባቸው ጉዳዮች ተፈጥረዋል።
እነዚህ ልዩነቶች መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ (ዛሬ በማለዳ ያስተዋወቅኳችሁን ፕሮግራም ጨምሮ) "ብስራት-ስፖርት" ከሬድዮ አየር ላይ እንደወረደ ስገልጽላችሁ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው" ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።
ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ከሬድዮ ጣቢያው ጋር ስለተፈጠረው ውዝግብ ተከታዩን ብሏል"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር ''ብስራት-ስፖርት" የተሰኘውን ፕሮግራም ለ12 ዓመታት ሳቀርብ መቆየቴ ይታወቃል።
ይሁንና በእነዚህ ሁለት ቀናት (ረቡዕ እና ሐሙስ መስከረም 28 እና 29) ከእኔ የስራ ትጋት ጋርባልተያያዘ (በግሌ ልፈታው በማልችለው ምክንያት) ከጣቢያው ጋር ያልተግባባንባቸው ጉዳዮች ተፈጥረዋል።
እነዚህ ልዩነቶች መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ (ዛሬ በማለዳ ያስተዋወቅኳችሁን ፕሮግራም ጨምሮ) "ብስራት-ስፖርት" ከሬድዮ አየር ላይ እንደወረደ ስገልጽላችሁ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው" ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤14
📌"አውደ ፋጎስ" የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል
70ኛው ዙር አውደ ፋጎስ የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር አሮን ደጎል ሀብቴ "ዳኝነት እና ፍትህ" በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያቀርባል።ይህም ውይይት እሁድ ጥቅምት 2 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
70ኛው ዙር አውደ ፋጎስ የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር አሮን ደጎል ሀብቴ "ዳኝነት እና ፍትህ" በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያቀርባል።ይህም ውይይት እሁድ ጥቅምት 2 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍2
📌9ኛው የBCAA የፎቶግራፍ አውደርዕይ!
የBored Cellphone Addis Ababa የፎቶግራፍ አውደርዕይ ለዘጠነኛ ጊዜ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 1 2018 ዓ.ም ከረፋዱ ጀምሮ እስከ ምሽት ድረስ ሲ ኤም ሲ አደባባይ ፊትለፊት በሚገኘው አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የፎቶግራፍ አውደርዕይ ላይ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢያዎች በስልክ የተነሱ ፎቶግራፎች ለእይታ ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የBored Cellphone Addis Ababa የፎቶግራፍ አውደርዕይ ለዘጠነኛ ጊዜ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 1 2018 ዓ.ም ከረፋዱ ጀምሮ እስከ ምሽት ድረስ ሲ ኤም ሲ አደባባይ ፊትለፊት በሚገኘው አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የፎቶግራፍ አውደርዕይ ላይ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢያዎች በስልክ የተነሱ ፎቶግራፎች ለእይታ ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5
📌የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዋና አዘጋጅ ከዓለም የፕሬስ ነጻነት ጀግና ሽልማት ተሸላሚዎች አንዱ ሆኖ ተመረጠ
ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” መስራቾች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ ዓለም አቀፉ የፕሬስ ኢንስቲትዩት (IPI) እና ዓለም አቀፍ ሚዲያ ሰፖርት (IMS) የተባሉ ሁለት ተቋማት በትብብር ለሚሰጡት የዓለም ፕሬስ ነጻነት ጀግና ሽልማት ተመረጠ። የእዚህን ዓመት ሽልማት እንዲቀበሉ የተመረጡት ተስፋለምን ጨምሮ ሰባት ጋዜጠኞች እና አርታዒያን ናቸው።
ዓለም አቀፉ ሽልማት ለሚዲያ ነጻነት ወይም ያልተገደበ የዜና እና የመረጃ ፍሰት በተለይ ግለሰባዊ ደህንነታቸው ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ሆኖ ጉልህ አስተዋጽዖ ላበረከቱ ጋዜጠኞች የሚሰጥ ነው።
ተስፋለም ለሽልማቱ የተመረጠው “ለገለልተኛ ጋዜጠኝነት ባለው የማይናወጥ ቁርጠኝነት” እንደሆነ ሸላሚዎቹ ዛሬ ሐሙስ መስከረም 29፤ 2018 ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ጋዜጠኛው “ከባለስልጣናት ለሚሰነዘር ቀጥተኛ የበቀል እርምጃ” ዒላማ ከመሆኑ ባሻገር በሥራው ምክንያት “የግል ሕይወቱን በተደጋጋሚ ለአደጋ እንዳጋለጠ” ሸላሚዎቹ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። ከአንድ ዓመት በላይ የሚረዝመውን ጨምሮ ለተደጋጋሚ የዘፈቀደ እስራት የተዳረገው ተስፋለም፤ “ከጊዜ ወደ ጊዜ ለነጻ ሚዲያ አስቸጋሪ በሆነ ምህዳር ውስጥ ለሕዝብ ለሚጠቅም ጋዜጠኝነት ቦታ ለመፍጠር ባለው ቁርጠኝነት” ተሰድዶ ከነበረበት ሀገር ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን ተቋማቱ በመግለጫቸው አመልክተዋል።
ተስፋለም “ለዚህ ታላቅ ሽልማት በመመረጤ ታላቅ ክብር ይሰማኛል” በማለት ደስታውን ገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” መስራቾች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ ዓለም አቀፉ የፕሬስ ኢንስቲትዩት (IPI) እና ዓለም አቀፍ ሚዲያ ሰፖርት (IMS) የተባሉ ሁለት ተቋማት በትብብር ለሚሰጡት የዓለም ፕሬስ ነጻነት ጀግና ሽልማት ተመረጠ። የእዚህን ዓመት ሽልማት እንዲቀበሉ የተመረጡት ተስፋለምን ጨምሮ ሰባት ጋዜጠኞች እና አርታዒያን ናቸው።
ዓለም አቀፉ ሽልማት ለሚዲያ ነጻነት ወይም ያልተገደበ የዜና እና የመረጃ ፍሰት በተለይ ግለሰባዊ ደህንነታቸው ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ሆኖ ጉልህ አስተዋጽዖ ላበረከቱ ጋዜጠኞች የሚሰጥ ነው።
ተስፋለም ለሽልማቱ የተመረጠው “ለገለልተኛ ጋዜጠኝነት ባለው የማይናወጥ ቁርጠኝነት” እንደሆነ ሸላሚዎቹ ዛሬ ሐሙስ መስከረም 29፤ 2018 ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ጋዜጠኛው “ከባለስልጣናት ለሚሰነዘር ቀጥተኛ የበቀል እርምጃ” ዒላማ ከመሆኑ ባሻገር በሥራው ምክንያት “የግል ሕይወቱን በተደጋጋሚ ለአደጋ እንዳጋለጠ” ሸላሚዎቹ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። ከአንድ ዓመት በላይ የሚረዝመውን ጨምሮ ለተደጋጋሚ የዘፈቀደ እስራት የተዳረገው ተስፋለም፤ “ከጊዜ ወደ ጊዜ ለነጻ ሚዲያ አስቸጋሪ በሆነ ምህዳር ውስጥ ለሕዝብ ለሚጠቅም ጋዜጠኝነት ቦታ ለመፍጠር ባለው ቁርጠኝነት” ተሰድዶ ከነበረበት ሀገር ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን ተቋማቱ በመግለጫቸው አመልክተዋል።
ተስፋለም “ለዚህ ታላቅ ሽልማት በመመረጤ ታላቅ ክብር ይሰማኛል” በማለት ደስታውን ገልጿል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤18👏2
📌የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ
የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በሚል ርእስ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሙያዊ ውይይት ተካሂዷል።
ዝግጅቱ በአካዳሚው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ የእንኳን በደህና መጣችሁ ንግግር የተከፈተ ሲሆን አካዳሚው ይህንን መሰል ለፖሊስ ግብዓትነት የሚጠቅሙ እና ሙያዊ ተዋስዖዎችን ለመፍጠር አበክሮ እንደሚሠራ አስታውሰዋል፡፡
ውይይቱ በፕሮፌሰር ዘላለም ልየው እየተመራ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና አቶ ይኩኖ አምላክ መዝገቡ፥ የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ሊኖረው ስለሚገባው ሚና እና የመማርና ማስተማር ሥርዓት የመነሻ ሐሳቦቻቸውን በማቅረብ ከታዳሚያን ጋር ሰፋ ያለ የውይይት ጊዜን አሳልፈዋል፡፡
በዚህ ዝግጅት ላይ የአካዳሚው ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚው አባላት፣ ተመራማሪዎች፣ ፖሊስ አውጪዎች እና በጉዳዩ ላይ ፍላጎት ያላቸው ታዳሚያን በአካልና በበይነ መረብ ታድመዋል፡፡
የዚህ ውይይት ሙሉ ቪዲዮ ከጥቂት ቀናት በኋላ በአካዳሚው የዩቲዩብ ቻናል እና የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ተጭኖ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በሚል ርእስ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሙያዊ ውይይት ተካሂዷል።
ዝግጅቱ በአካዳሚው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ የእንኳን በደህና መጣችሁ ንግግር የተከፈተ ሲሆን አካዳሚው ይህንን መሰል ለፖሊስ ግብዓትነት የሚጠቅሙ እና ሙያዊ ተዋስዖዎችን ለመፍጠር አበክሮ እንደሚሠራ አስታውሰዋል፡፡
ውይይቱ በፕሮፌሰር ዘላለም ልየው እየተመራ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና አቶ ይኩኖ አምላክ መዝገቡ፥ የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ሊኖረው ስለሚገባው ሚና እና የመማርና ማስተማር ሥርዓት የመነሻ ሐሳቦቻቸውን በማቅረብ ከታዳሚያን ጋር ሰፋ ያለ የውይይት ጊዜን አሳልፈዋል፡፡
በዚህ ዝግጅት ላይ የአካዳሚው ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚው አባላት፣ ተመራማሪዎች፣ ፖሊስ አውጪዎች እና በጉዳዩ ላይ ፍላጎት ያላቸው ታዳሚያን በአካልና በበይነ መረብ ታድመዋል፡፡
የዚህ ውይይት ሙሉ ቪዲዮ ከጥቂት ቀናት በኋላ በአካዳሚው የዩቲዩብ ቻናል እና የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ተጭኖ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍8❤5👏4
📌"ቼኑ" ጥናታዊ ፊልም ጥቅምት 3 ይመረቃል
"ቼኑ" ጥናታዊ ፊልም የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ይመረቃል።
"ቼኑ" ጥናታዊ ፊልም ደጀኑ በቀለ በሚባል እና ቄራ ሰፈር ተወልዶ ስላደገው አንድ ኢትዮጵያዊ የ60 ዓመት ጎልማሳ ግለሰብ እውነተኛ የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን ፊልም ነው።
"ቼኑ" ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አራት ዓመታትና 6 ሚሊየን ብር ገደማ ፈጅቷል። ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ አቀራረብና ዝግጅት ይዞ የቀረበው ፊልሙ ለሀገርም ለወገንም ታሪክን ሰንዶ ማስቀመጥ ያለውን ከፍተኛ ሀገራዊ ሚና የሚያሳይና ውድ የሆነ የህይወት ልምድን ለአሁኑ ትውልድ አስተምሮ የሚያልፍ ጥናታዊ ፊልም ነው ሲሉ የፊልሙ ባለታሪክ አቶ ደጀኑ በቀለ ተናግረዋል።
"ቼኑ" ፊልም በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራ ፊልም ሲሆን፣ የ2 ሰዓት ርዝመት ያለው ዶክመንተሪ ፊልም መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ጥናታዊ ፊልም ለመስራት መነሻው ምክንያት የደጀኑን አስገራሚ ህይወት ለሌሎች ማስቃኘት ነው ያለው የፊልሙ ዳይሬክተር ይድነቃቸው ዓይኔ፥ ታሪኩ የሚያስተምርና ፋይዳው ለማህበረሰቡ ላቅ ያለ ነው ብሏል።
ማስታወሻ: የዚህን ጥናታዊ ፊልም ምረቃ የመግቢያ ትኬት ለ10 ቤተሰቦቻችን በክብር እንሸልማለን።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ቼኑ" ጥናታዊ ፊልም የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ይመረቃል።
"ቼኑ" ጥናታዊ ፊልም ደጀኑ በቀለ በሚባል እና ቄራ ሰፈር ተወልዶ ስላደገው አንድ ኢትዮጵያዊ የ60 ዓመት ጎልማሳ ግለሰብ እውነተኛ የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን ፊልም ነው።
"ቼኑ" ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አራት ዓመታትና 6 ሚሊየን ብር ገደማ ፈጅቷል። ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ አቀራረብና ዝግጅት ይዞ የቀረበው ፊልሙ ለሀገርም ለወገንም ታሪክን ሰንዶ ማስቀመጥ ያለውን ከፍተኛ ሀገራዊ ሚና የሚያሳይና ውድ የሆነ የህይወት ልምድን ለአሁኑ ትውልድ አስተምሮ የሚያልፍ ጥናታዊ ፊልም ነው ሲሉ የፊልሙ ባለታሪክ አቶ ደጀኑ በቀለ ተናግረዋል።
"ቼኑ" ፊልም በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራ ፊልም ሲሆን፣ የ2 ሰዓት ርዝመት ያለው ዶክመንተሪ ፊልም መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ጥናታዊ ፊልም ለመስራት መነሻው ምክንያት የደጀኑን አስገራሚ ህይወት ለሌሎች ማስቃኘት ነው ያለው የፊልሙ ዳይሬክተር ይድነቃቸው ዓይኔ፥ ታሪኩ የሚያስተምርና ፋይዳው ለማህበረሰቡ ላቅ ያለ ነው ብሏል።
ማስታወሻ: የዚህን ጥናታዊ ፊልም ምረቃ የመግቢያ ትኬት ለ10 ቤተሰቦቻችን በክብር እንሸልማለን።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤21👍6🔥2
📌አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ተመረቀ
"አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ" የተሰኘ ባለ 15 ወለል የሲኒማ ኮምፕሌክስ ተመረቀ ።
በ24,000 ካ.ሜ ላይ ያረፈው "አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ" ባለ አራት ወለል የመኪና ማቆሚያ 592 ህፃናትንና 887 አዋቂዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የሲኒማ አዳራሾችን ከሙሉ መገልገያዎች ጋር የያዘ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርብ ጊዜ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስን አስመርቆ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ" የተሰኘ ባለ 15 ወለል የሲኒማ ኮምፕሌክስ ተመረቀ ።
በ24,000 ካ.ሜ ላይ ያረፈው "አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ" ባለ አራት ወለል የመኪና ማቆሚያ 592 ህፃናትንና 887 አዋቂዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የሲኒማ አዳራሾችን ከሙሉ መገልገያዎች ጋር የያዘ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርብ ጊዜ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስን አስመርቆ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤10
📌የደራሲ አዳም ረታ ተወዳጅ መጽሐፍ ተተረጎመ
ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ የተተረጎመው የደራሲ አዳም ረታ መጽሐፍ "እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ" የተሰኘው መጽሐፉ ነው።
ወደ እንግሊዝኛ ስትረጎመም "Couch grass" በሚል ርዕስ እንደሆነም ሰምተናል።
መጽሐፉን በእንግሊዝኛ ቋንቋ በተርጓሚነት የምታቀርበው ቤተልሄም አትፊልድ ትባላለች።
በማህበራዊ ትስስር ገጿም "እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ የተሰኘው የደራሲ አዳም ረታን መጽሐፍን "Couch grass" በሚል ርዕስ ተርጉሜ በዚህ ወር መጨረሻ እንደሚታተም ሳበስራችው ደስ ብሎኛል" ብላለች።
በተጨማሪም ተርጓሚዋ አራት ተረኮችን እንዳካተተችም ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"እቴ ሜቴ ሎሚ ሽታ" መጽሐፍ በውስጡ ከአጭር ልቦለድ ከፍ ከረጅም ልቦለድ ዝቅ ያሉ 7 ታሪኮችን ይዟል።
ከዓመታት በፊትም በአብርሃም ገዛኸኝ አዘጋጅነት "የሎሚ ሽታ" በሚል ርዕስ ወደ ፊልም ተቀይሮ ለተመልካቾች ቀርቧል።
ደራሲ አዳም ረታ ደራሲ "መዝሙረ ሄላዊ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለአንባቢያን አቅርባለው ካለ አንድ ዓመት አልፎታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ የተተረጎመው የደራሲ አዳም ረታ መጽሐፍ "እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ" የተሰኘው መጽሐፉ ነው።
ወደ እንግሊዝኛ ስትረጎመም "Couch grass" በሚል ርዕስ እንደሆነም ሰምተናል።
መጽሐፉን በእንግሊዝኛ ቋንቋ በተርጓሚነት የምታቀርበው ቤተልሄም አትፊልድ ትባላለች።
በማህበራዊ ትስስር ገጿም "እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ የተሰኘው የደራሲ አዳም ረታን መጽሐፍን "Couch grass" በሚል ርዕስ ተርጉሜ በዚህ ወር መጨረሻ እንደሚታተም ሳበስራችው ደስ ብሎኛል" ብላለች።
በተጨማሪም ተርጓሚዋ አራት ተረኮችን እንዳካተተችም ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"እቴ ሜቴ ሎሚ ሽታ" መጽሐፍ በውስጡ ከአጭር ልቦለድ ከፍ ከረጅም ልቦለድ ዝቅ ያሉ 7 ታሪኮችን ይዟል።
ከዓመታት በፊትም በአብርሃም ገዛኸኝ አዘጋጅነት "የሎሚ ሽታ" በሚል ርዕስ ወደ ፊልም ተቀይሮ ለተመልካቾች ቀርቧል።
ደራሲ አዳም ረታ ደራሲ "መዝሙረ ሄላዊ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለአንባቢያን አቅርባለው ካለ አንድ ዓመት አልፎታል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤22🥰2
📌ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) በጠና ታመሙ
ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) በጠና መታመማቸው ተሰምቷል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) የጤና እክል ገጥሟቸዉ ለህክምና ወደ ቱርክ ሀገር መሄዳቸውም ተነግሯል።
ሀጅ ዑመር ኢድሪስ ያጋጠማቸው የጤና እክል ምንነት እስካሁን በይፋ አልተነገረም።
የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) ከገጠማቸው የጤና እክል አላህ አፊያ እንዲያረጋቸው ዱአ እንዲደረግላቸው ጥሪ ቀርቧል።
Via ነጃሺ ቲቪ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) በጠና መታመማቸው ተሰምቷል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) የጤና እክል ገጥሟቸዉ ለህክምና ወደ ቱርክ ሀገር መሄዳቸውም ተነግሯል።
ሀጅ ዑመር ኢድሪስ ያጋጠማቸው የጤና እክል ምንነት እስካሁን በይፋ አልተነገረም።
የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) ከገጠማቸው የጤና እክል አላህ አፊያ እንዲያረጋቸው ዱአ እንዲደረግላቸው ጥሪ ቀርቧል።
Via ነጃሺ ቲቪ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🙏26😭9❤7👍5🥰4👏1
📌የአንጋፋው ሰዓሊ ወርቁ ማሞ ልጅ በሆነቸው በወጣቷ ሰዓሊ ገብርኤልዋ ወርቁ ማሞ የተዘጋጁ የሥዕል ስራዎች ብቻ የሚቀርቡበት "ከልብስ ባሻገር" የሥዕል አውደርዕይ ለእይታ ሊበቃ ነው።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ ጥቅምት 8 2018 ዓ.ም በአርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ ይበቃል።
ሠዓሊዋ በዚህ የሥዕል አውደርዕይዋ ላይ "የሰው ልጅ ከልብሱ በላይ ዋጋ የለውም ወይ?" በማለት ጠይቃለች።
ጥቅምት 8 የሚከፈተው አውደርዕይው እስከ ጥቅምት 29 2018 ዓ.ም በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ይህ የሥዕል አውደርዕይ ጥቅምት 8 2018 ዓ.ም በአርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ ይበቃል።
ሠዓሊዋ በዚህ የሥዕል አውደርዕይዋ ላይ "የሰው ልጅ ከልብሱ በላይ ዋጋ የለውም ወይ?" በማለት ጠይቃለች።
ጥቅምት 8 የሚከፈተው አውደርዕይው እስከ ጥቅምት 29 2018 ዓ.ም በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍13❤10
📌OBN የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግን በነፃ አሳያለሁ አለ
የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ውድድር በነፃ ለተመልካች እንደሚያስመለክት በይፋ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዚህ በፊት በዲኤስቲቪ በክፍያ ሲተላለፍ የቆየ ሲሆን በቀጣይ በነፃ ለተመልካች ይደርሳል።
OBN የውጭ እና ሀገር ውስጥ ሚዲያዎችን ተወዳድሮ በማሸነፍ የሊጉን የስርጭት መብት መግዛቱን በይፋ አሳውቋል።
ዲኤስቲቪ በመጨረሻ የሊጉ አመታት ቆይታው በ OBN የፕሮዳክሽን መሳሪያዎች ተከራይቶ ሊጉን ሲያሳይ እንደነበር ይታወቃል።
በርካታ ተመልካቾች ያሉት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሀገራችን ሚዲያ በነፃ መቅረቡ ለስፖርቱ ተመልካቾች መልካም ዜና ሆኗል።
በስምምነቱ ዙሪያ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ውድድር በነፃ ለተመልካች እንደሚያስመለክት በይፋ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዚህ በፊት በዲኤስቲቪ በክፍያ ሲተላለፍ የቆየ ሲሆን በቀጣይ በነፃ ለተመልካች ይደርሳል።
OBN የውጭ እና ሀገር ውስጥ ሚዲያዎችን ተወዳድሮ በማሸነፍ የሊጉን የስርጭት መብት መግዛቱን በይፋ አሳውቋል።
ዲኤስቲቪ በመጨረሻ የሊጉ አመታት ቆይታው በ OBN የፕሮዳክሽን መሳሪያዎች ተከራይቶ ሊጉን ሲያሳይ እንደነበር ይታወቃል።
በርካታ ተመልካቾች ያሉት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሀገራችን ሚዲያ በነፃ መቅረቡ ለስፖርቱ ተመልካቾች መልካም ዜና ሆኗል።
በስምምነቱ ዙሪያ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁16❤7😍3👎2🤣2👍1👏1💩1
📌 የኃይሉ አመርጋ አልበም የሚለቀቅበት ቀን ታወቀ
ድምጻዊ ኃይሉ አመርጋ ከተራራው ማዶ፣ እንግዳ፣ ይነጋል፣ ማርዬ፣ ይገርማል የተሰኙ ሙዚቃዎችን ጨምሮ አስር ያህል ሥራዎችን በጃኖ ባንድ በኩል መዋጮ አድርጎ።
ከጃኖ ባንድ ባንድ መፈርስ በኃላ ከኃይሉ አመርጋ በቀር 3ቱ የባንዱ ድምጻዊያን በየፊናቸው የራሳቸውን የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች አቅረበዋል።
በሙዚቃ ወዳጆችም ዘንድ የኃይሉ አመርጋ የሙዚቃ አልበም መቼ ነው የሚለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ለድምጻዊው ሲቀርቡ ቆይተዋል።
ለዚህም ጥያቄ በመጨረሻም አልበሙ ለአድማጮች የሚቀርብበት ቀን ታወቋል።
ድምጻዊው በግሉ የሰራው የመጀመሪያ አልበሙ ጥቅምት 21 2018 ዓ.ም ለአድማጮች እንደሚቀረብ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአልበሙን ስራ ለመከውን ስድስት ዓመታት እንደፈጀ የተነገረለት አልበሙ "አሁን " የተሰኘ ርዕስ ተሰጥቷል።
ከመለቀቁ በፊትም ጥቅምት 18 2018 ዓ.ም የሙዚቃ ማድመጭ መሰናድ እንደተዘጋጀለትም ሰምተናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ድምጻዊ ኃይሉ አመርጋ ከተራራው ማዶ፣ እንግዳ፣ ይነጋል፣ ማርዬ፣ ይገርማል የተሰኙ ሙዚቃዎችን ጨምሮ አስር ያህል ሥራዎችን በጃኖ ባንድ በኩል መዋጮ አድርጎ።
ከጃኖ ባንድ ባንድ መፈርስ በኃላ ከኃይሉ አመርጋ በቀር 3ቱ የባንዱ ድምጻዊያን በየፊናቸው የራሳቸውን የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች አቅረበዋል።
በሙዚቃ ወዳጆችም ዘንድ የኃይሉ አመርጋ የሙዚቃ አልበም መቼ ነው የሚለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ለድምጻዊው ሲቀርቡ ቆይተዋል።
ለዚህም ጥያቄ በመጨረሻም አልበሙ ለአድማጮች የሚቀርብበት ቀን ታወቋል።
ድምጻዊው በግሉ የሰራው የመጀመሪያ አልበሙ ጥቅምት 21 2018 ዓ.ም ለአድማጮች እንደሚቀረብ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአልበሙን ስራ ለመከውን ስድስት ዓመታት እንደፈጀ የተነገረለት አልበሙ "አሁን " የተሰኘ ርዕስ ተሰጥቷል።
ከመለቀቁ በፊትም ጥቅምት 18 2018 ዓ.ም የሙዚቃ ማድመጭ መሰናድ እንደተዘጋጀለትም ሰምተናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤36🔥6
📌ታላቁ አባት ሐጂ ኡመር ኢድሪስ አረፉ
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😢45💔7❤6😭3
📌"ጀሚላ" የተሰኘ ፊልም ዛሬ ይመረቃል
በዜማ ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ በካብ ኢንተርቴይመንት አቅራቢነት ለእይታ የሚቀረበው ይህ ፊልም ድርሰትና ዝግጅቱ የደራሲና ዳይሬክተር ፀጋ ካህሳይ (ጃምቦ ) ነው።
የፊልሙ ጭብጡም እንደ ሃገር እንደ ቤተሰብ በፍቅር ተዋዶና ተፈላልጎ የመኖር ነባር ቤተሰባዊ ባህላችንን በማጠናከር ዙሪያ የሚያጠነጥን የፍቅር ፊልም ነው።
የ“ጀሚላ” ፊልምን ስራዎችን ለመከወን ከሁለት አመት በላይ እንደፈጀ የተነገረ ሲሆን 1:35 ደቂቃ የሚፈጅ የቆይታ ጊዜ አለው።
በትወና አዳዲስና ነባር ተዋንያን የተሳተፉበት ሲሆን ሄኖክ አለማየሁ፣ነፃነት አንበርብር
ምህረት በለጠ ፣ቁምላቸው አዱኛ(ከድር ሰተቴ) ሌሎችም ተሳታፈዋል።
ጀሚላ ፊልም ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 10 2018 ዓ.ም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዓለም ሲኒማ ከ11:00 ጀምሮ ይመረቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዜማ ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ በካብ ኢንተርቴይመንት አቅራቢነት ለእይታ የሚቀረበው ይህ ፊልም ድርሰትና ዝግጅቱ የደራሲና ዳይሬክተር ፀጋ ካህሳይ (ጃምቦ ) ነው።
የፊልሙ ጭብጡም እንደ ሃገር እንደ ቤተሰብ በፍቅር ተዋዶና ተፈላልጎ የመኖር ነባር ቤተሰባዊ ባህላችንን በማጠናከር ዙሪያ የሚያጠነጥን የፍቅር ፊልም ነው።
የ“ጀሚላ” ፊልምን ስራዎችን ለመከወን ከሁለት አመት በላይ እንደፈጀ የተነገረ ሲሆን 1:35 ደቂቃ የሚፈጅ የቆይታ ጊዜ አለው።
በትወና አዳዲስና ነባር ተዋንያን የተሳተፉበት ሲሆን ሄኖክ አለማየሁ፣ነፃነት አንበርብር
ምህረት በለጠ ፣ቁምላቸው አዱኛ(ከድር ሰተቴ) ሌሎችም ተሳታፈዋል።
ጀሚላ ፊልም ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 10 2018 ዓ.ም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዓለም ሲኒማ ከ11:00 ጀምሮ ይመረቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5👍4
📌ታሪካዊው አንበሳ መድሐኒት ቤት ፈረሰ
አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ የሚገኘዉ እድሜ ጠገቡ አንበሳ ፋርማሲ መፍረሱን ቅዳሜ ገበያ በስፍራው ተገኝታ አረጋግጣለች።
እየፈረሰ ያለው አንበሳ ፋርማሲ ከተመሰረተ 80ኛ ዓመቱን የያዘና ጥንታዊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
በጀርመናዉያን ሁለተኛ እና በሦስተኛ ትዉልድ እየተንቀሳቀሰ የነበረው አንጋፋዉ አንበሳ መድሐኒት ቤት የመድሐኒት ሽያጭና ቅመማ ብቻ ሳይሆን የሕክምና ቁሳቁስ አስመጭና አገር ውስጥ አከፋፋይም ነበር ።
ከዓመታት በፊት አንበሳ ፋርማሲ ይፈርሳል መባሉን ተከትሎ በአዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ኤምባሲ የአንበሳ መድሐኒት ቤትን ድጋፍ መስጠትን ይመለከታል በሚል ለአዲስ አበባ ከተማ የወቅቱ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በፃፈዉ ደብዳቤ አዲስ አበባን ብሎም ኢትዮጵያን የጀርመን የመዋለ ንዋይ ፍሰት መዳረሻ ለማድረግ እንደሚያበረታታ አንድ ኤምባሲ፤ ጉዳዩ ሕጋዊ መንገድን መከተል አለበት ብለን እናምናለን። ምክንያቱም በእድሜ ጠገቡ የአንበሳ መድሐኒት ቤት ላይ አስተዳደሩ ይወስዳል የተባለዉ ርምጃ ሌሎች የጀርመን ባለ ኃብቶችን ሊያሸሽ ይችላል ሲል ደብዳቤ ማግባቱ በወቅቱ ተዘግቧል።
አንበሳ ፋርማሲ የሚገኝበት አነስተኛ ህንጻ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሲሆን ከአመታት በፊት ከአካባቢ ልማት ጋር በተያያዘ ፋርማሲው ይፈርሳል ተብሎ የሚናፈሰው መረጃ ፍጹም ከእውነታው የራቀና መሰረተ ቢስ መረጃ ነው ሲል ኮርፖሬሽኑ ማስተባበሉ የሚታወስ ነው።
Via ቅዳሜ ገበያ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ የሚገኘዉ እድሜ ጠገቡ አንበሳ ፋርማሲ መፍረሱን ቅዳሜ ገበያ በስፍራው ተገኝታ አረጋግጣለች።
እየፈረሰ ያለው አንበሳ ፋርማሲ ከተመሰረተ 80ኛ ዓመቱን የያዘና ጥንታዊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
በጀርመናዉያን ሁለተኛ እና በሦስተኛ ትዉልድ እየተንቀሳቀሰ የነበረው አንጋፋዉ አንበሳ መድሐኒት ቤት የመድሐኒት ሽያጭና ቅመማ ብቻ ሳይሆን የሕክምና ቁሳቁስ አስመጭና አገር ውስጥ አከፋፋይም ነበር ።
ከዓመታት በፊት አንበሳ ፋርማሲ ይፈርሳል መባሉን ተከትሎ በአዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ኤምባሲ የአንበሳ መድሐኒት ቤትን ድጋፍ መስጠትን ይመለከታል በሚል ለአዲስ አበባ ከተማ የወቅቱ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በፃፈዉ ደብዳቤ አዲስ አበባን ብሎም ኢትዮጵያን የጀርመን የመዋለ ንዋይ ፍሰት መዳረሻ ለማድረግ እንደሚያበረታታ አንድ ኤምባሲ፤ ጉዳዩ ሕጋዊ መንገድን መከተል አለበት ብለን እናምናለን። ምክንያቱም በእድሜ ጠገቡ የአንበሳ መድሐኒት ቤት ላይ አስተዳደሩ ይወስዳል የተባለዉ ርምጃ ሌሎች የጀርመን ባለ ኃብቶችን ሊያሸሽ ይችላል ሲል ደብዳቤ ማግባቱ በወቅቱ ተዘግቧል።
አንበሳ ፋርማሲ የሚገኝበት አነስተኛ ህንጻ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሲሆን ከአመታት በፊት ከአካባቢ ልማት ጋር በተያያዘ ፋርማሲው ይፈርሳል ተብሎ የሚናፈሰው መረጃ ፍጹም ከእውነታው የራቀና መሰረተ ቢስ መረጃ ነው ሲል ኮርፖሬሽኑ ማስተባበሉ የሚታወስ ነው።
Via ቅዳሜ ገበያ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
😭6❤3
📌የጋዜጠኝነት ስልጠና ለሰልጣኞች
ጋዜጠኝነትን መማርና ጋዜጠኛ መሆን ህልማችሁ ከሆነ ልጠቁማችሁና ወደሴጅ ጎራ በሉ።
ደግሞ 6 ወር ብቻ በቂ እንደሆነ ሰምቻለሁ።
ስልጠናው ልምድ ባላቸውና የሚዲያውን ዓለም በሚያውቁት መምህራን ይሰጣል። ተጋባዥ እውቅ ጋዜጠኞችም ከልምዳቸው ያካፍላሉ።
9ኛ ዙር ላይ ደርሰው አሁንም ለ10ኛ ዙር አዳዲስ ሰልጣኞችን እየመዘገቡ ነውና እንዳያመልጣችሁ።
ጋዜጠኝነቱን ለይቼ ጠቆምኳቹ እንጂ ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከ30 በላይ በሆኑ ዘርፎች ስልጠና ይሰጣል።
ሴጅ ላለፉት ዓመታት በማሰልጠን በሙያ ምዘና ብቃት አስመዝኖ በማብቃት ለገበያው ተወዳዳሪ የሆነ ባለሙያዎች በማበርከት ላይ የሚገኝም ተቋም ነው።
ከታች ካሉት አድራሻዎች በተጨማሪ በማስፈንጠሪያዉም ጎብኟቸው።
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute
Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/
Threads: https://www.threads.net/@sage_training_institute
ጋዜጠኝነትን መማርና ጋዜጠኛ መሆን ህልማችሁ ከሆነ ልጠቁማችሁና ወደሴጅ ጎራ በሉ።
ደግሞ 6 ወር ብቻ በቂ እንደሆነ ሰምቻለሁ።
ስልጠናው ልምድ ባላቸውና የሚዲያውን ዓለም በሚያውቁት መምህራን ይሰጣል። ተጋባዥ እውቅ ጋዜጠኞችም ከልምዳቸው ያካፍላሉ።
9ኛ ዙር ላይ ደርሰው አሁንም ለ10ኛ ዙር አዳዲስ ሰልጣኞችን እየመዘገቡ ነውና እንዳያመልጣችሁ።
ጋዜጠኝነቱን ለይቼ ጠቆምኳቹ እንጂ ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከ30 በላይ በሆኑ ዘርፎች ስልጠና ይሰጣል።
ሴጅ ላለፉት ዓመታት በማሰልጠን በሙያ ምዘና ብቃት አስመዝኖ በማብቃት ለገበያው ተወዳዳሪ የሆነ ባለሙያዎች በማበርከት ላይ የሚገኝም ተቋም ነው።
ከታች ካሉት አድራሻዎች በተጨማሪ በማስፈንጠሪያዉም ጎብኟቸው።
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute
Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/
Threads: https://www.threads.net/@sage_training_institute
❤11👍3👎2
📌 አሻም ቴሌቪዥን ታሸገ
በአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የሚተዳደረው "አሻም ቴሌቪዥን" ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደታሸገ ኤቨንት አዲስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው በምን ምክንያት እንደታሸገ ለጊዜው አልታወቀም።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የሚተዳደረው "አሻም ቴሌቪዥን" ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደታሸገ ኤቨንት አዲስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው በምን ምክንያት እንደታሸገ ለጊዜው አልታወቀም።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🙊8❤5😱2
📌 "ኑ እንጫወት ልብ እንጠግን" ልዩ መርሐግብር
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል እየተጫወትን የህጻናትን ልብ ለመጠገን ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ ፈስቲቫል ለሕፃናት እና ለታዳጊዎች ተዘጋጅቷል።
ፌስቲቫሉ ልባቸውን ለመታከም ወረፋ በመጠበቅ ላይ ላሉ ሕፃናት ገቢ ለማሰባሰብ እና ለማህበረሰብ ደሞ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ዓላማ ያደረገ ነው።
ለሕጻናት እና ለታዳጊዎች የተዘጋጀው ፌስቲቫሉ ቅዳሜ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በአምባሳደር ፓርክ ከጠዋት 4፡00 ጀምሮ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል እየተጫወትን የህጻናትን ልብ ለመጠገን ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ ፈስቲቫል ለሕፃናት እና ለታዳጊዎች ተዘጋጅቷል።
ፌስቲቫሉ ልባቸውን ለመታከም ወረፋ በመጠበቅ ላይ ላሉ ሕፃናት ገቢ ለማሰባሰብ እና ለማህበረሰብ ደሞ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ዓላማ ያደረገ ነው።
ለሕጻናት እና ለታዳጊዎች የተዘጋጀው ፌስቲቫሉ ቅዳሜ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በአምባሳደር ፓርክ ከጠዋት 4፡00 ጀምሮ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤7👍2
📌ጥበብና የአእምሮ ጤና አውደርዕይ መዝጊያ
በሜታል ሄልዝ አዲስ የተዘጋጀውና የአእምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ የሥዕል ስራዎችየቀረቡበት አውደርዕይ በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ሲካሄድ ቆይቷል።
በዚህ "Art inspired by mental health" በሚል ርዕስ በተካሄደ አውደርዕይ ላይ የሠዓሊ ሶሎሜ ጌታቸው፣ የሠዓሊ አለማየሁ ደረሰማ ሥዕሎች ቀረበዋል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች የመዝጊያ ሥነሥርዓቱ ይከናወናል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በሜታል ሄልዝ አዲስ የተዘጋጀውና የአእምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ የሥዕል ስራዎችየቀረቡበት አውደርዕይ በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ሲካሄድ ቆይቷል።
በዚህ "Art inspired by mental health" በሚል ርዕስ በተካሄደ አውደርዕይ ላይ የሠዓሊ ሶሎሜ ጌታቸው፣ የሠዓሊ አለማየሁ ደረሰማ ሥዕሎች ቀረበዋል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች የመዝጊያ ሥነሥርዓቱ ይከናወናል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤6
📌በጣቢያው ባለቤት የታሸገው አሻም ቴሌቪዥን
አሻም ቴሌቪዥን ከትላንትና ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በጣቢያው ባለቤቶች እንደታሽገ ጣቢያው ከአሰራጨው መግለጫ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
አሻም በመግለጫው "የቴሌቪዥን ጣቢያው ከረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የጣቢያውን መደበኛ ስርጭት ማከናወን አልተቻለም።ችግሩን ለመቅረፍ የሚዲያው አስተዳደር ጥረቶች እያደረገ ይገኛል:: ያጋጠመው ችግር እስኪስተካከል በሚል አስተዳደሩ በካሜራና መሰል የሚዲያው ንብረቶች እንዳይንቀሳቀሱ ፤ የውስጥ ንብረት ክፍሉን አሽጓል" ሲል አስታውቋል።
ጣቢያው ይህንን ይበል እንጂ አንድ የቴሌቪዥን ጣቢያው ሰራተኛ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጣቢያው ምን እንደተፈጠረ እንዲህ ሲል ያብራራል "ከቅርብ ግዜ ( ከ5 ወይ 6 ወር ) ወዲህ ምን እንደሆነ ባናዉቅም (የሚነገረን ምክንያት ብር የለንም ብቻ ነበር ) ቤቱ የሰራተኛን ደሞዝ በማቆየት እና ከዛም ባለፈ እስከ 2 ወራት ባለመክፈል ቆይቷል።
እኛም የገጠመውን ችግር በመረዳት በተደጋጋሚ ደሞዙን ሳይጠይቅ በገባለት ሰዓት ጠብቀናል። በሚዲያው ዉስጥ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ፣ ተከራይ እና ብዙ ወጪዎች ያሉበት ሰራተኛ እንደመኖሩ ለወራት በችግር አሳልፈናል። የሆነዉ ሆኖ ነገሮች ተስተካከሉ ስንል እየባሱ በመምጣታቸዉ በድጋሜ በመስከረም ወር ጀምሮ የሁለት ወር ደሞዛችን እንዲገባና ጥያቄ ብናቀርብም '' በዚህ ሰዓት መክፈል አንችልም፣ከዚህ በኋላ ለአንድ ወር ጠብቁ '' የሚል ምላሽ ተሰጥቷል።ከዚህ ባለፈ የሰራንበትን የስራ ልምድ ብንጠይቅም ሊሰጡን አልቻሉም" ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አሻም ቴሌቪዥን ከትላንትና ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በጣቢያው ባለቤቶች እንደታሽገ ጣቢያው ከአሰራጨው መግለጫ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
አሻም በመግለጫው "የቴሌቪዥን ጣቢያው ከረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የጣቢያውን መደበኛ ስርጭት ማከናወን አልተቻለም።ችግሩን ለመቅረፍ የሚዲያው አስተዳደር ጥረቶች እያደረገ ይገኛል:: ያጋጠመው ችግር እስኪስተካከል በሚል አስተዳደሩ በካሜራና መሰል የሚዲያው ንብረቶች እንዳይንቀሳቀሱ ፤ የውስጥ ንብረት ክፍሉን አሽጓል" ሲል አስታውቋል።
ጣቢያው ይህንን ይበል እንጂ አንድ የቴሌቪዥን ጣቢያው ሰራተኛ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጣቢያው ምን እንደተፈጠረ እንዲህ ሲል ያብራራል "ከቅርብ ግዜ ( ከ5 ወይ 6 ወር ) ወዲህ ምን እንደሆነ ባናዉቅም (የሚነገረን ምክንያት ብር የለንም ብቻ ነበር ) ቤቱ የሰራተኛን ደሞዝ በማቆየት እና ከዛም ባለፈ እስከ 2 ወራት ባለመክፈል ቆይቷል።
እኛም የገጠመውን ችግር በመረዳት በተደጋጋሚ ደሞዙን ሳይጠይቅ በገባለት ሰዓት ጠብቀናል። በሚዲያው ዉስጥ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ፣ ተከራይ እና ብዙ ወጪዎች ያሉበት ሰራተኛ እንደመኖሩ ለወራት በችግር አሳልፈናል። የሆነዉ ሆኖ ነገሮች ተስተካከሉ ስንል እየባሱ በመምጣታቸዉ በድጋሜ በመስከረም ወር ጀምሮ የሁለት ወር ደሞዛችን እንዲገባና ጥያቄ ብናቀርብም '' በዚህ ሰዓት መክፈል አንችልም፣ከዚህ በኋላ ለአንድ ወር ጠብቁ '' የሚል ምላሽ ተሰጥቷል።ከዚህ ባለፈ የሰራንበትን የስራ ልምድ ብንጠይቅም ሊሰጡን አልቻሉም" ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤21🤔5😁2