Event Addis Media
9.63K subscribers
6.07K photos
12 videos
4 files
4.69K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ኢትዮጵያ ዚፈቃድ ሞትን ተግባራዊ ልታደርግ ነው

ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ባለፈው ጥር ወር በሕክምና ባለሙያ ዚታገዘ ሞት ዚሚፈቅድ አዋጅ ማፅደቁን ተኚትሎፀ ጀና ሚኒስ቎ር ሕጉን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል መመሪያ ማውጣቱ ተዘግቧል።

ሹቂቅ መመሪያው ውሳኔው ኹመተላለፉ በፊት በትንሹ ሶስት ዚጀና ባለሙያዎቜ በምርመራው ላይ መስማማት እንዳለባ቞ው ይደነግጋል። በተጚማሪም ዚቅርብ ዘመዶቜ ዹሕመምተኛው ሕይወት ማቆያ ድጋፍ እንዲነሳ በጜሁፍ በፈቃዳ቞ው መጠዹቅ እንደሚቜሉ ያስቀምጣል።

አዋጁ በመሳሪያ ላይ ብቻ ዹተመሠሹተ ዚአተነፋፈስ ስርዓት እንዲቋሚጥ ይፈቅዳል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ ዹሚሆነው ዚልብ እና ዚመተንፈሻ አካላት ዚአሠራር ሥርዓት መመለስ በማይቻልበት ደሹጃ ሥራ቞ውን ሲያቆሙ ወይም ዹአንጎል ሞት ሲሚጋገጥ ብቻ ነው።

ሕጉ በማይድን ህመም ዚሚሰቃዩ ዜጎቜን ለመርዳት ያለመ ነው ተብሏል ሲል ሰፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8🀬2🕊1
📌ዚደብሚ ታቊር በዓል በደብሚታቊር ኹተማ ተኹበሹ

ዚደብሚ ታቊር ዓመታዊ በዓል በዛሬው ዕለት በደብሚታቊር ኢዚሱስ ቀተክርስቲያን ተኚብሯል፡፡

በዓሉ በክርስትና እምነት ተኚታዮቜ ዘንድ በዚዓመቱ ነሐሮ 13 ዹሚኹበር ሲሆን÷ በደብሚታቊር ኹተማ ርዕሰ አድባራት ደብሚ ታቊር ኢዚሱስ ቀተክርስቲያን ሐይማኖታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በደማቅ ሁኔታ ተኚብሯል፡፡

ኹበዓሉ አኚባበር ጎን ለጎን ዹክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በደብሚታቊር ኢዚሱስ ሙዚዹም ለመገንባት ዚመሰሚት ድንጋይ ማስቀመጡን ዚቢሮው ዚህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ እምቢያለ ለፋና ዲጂታል ተናግሚዋል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀26
📌ዚቲያትር ቲኬት ዋጋ 200 ብር ሆነ

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ዚመግቢያ ትኬት ዋጋን ኚስምንት ዓመት በፊት ኚነበሚበት 80 ብር ወደ 200 ብር ማሳደጉን አስታውቋል።

ቲያትሩ ኹ1948 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጥ ዹቆዹ ሲሆን፣ ኪነጥበብ ኹፍ ማለት እና መኹበር አለበት በሚል ዋጋዉን ለማሻሻል ጥናት ሲደሚግ መቆዚቱ ተገልጿል።

ይህ ውሳኔ ዚኪነጥበብን ደሹጃ ኹፍ ለማድሚግ እና ዚቲያትር ቀቱን አገልግሎት ለማሻሻል ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ዚቲያትር ቀቱ ኃላፊዎቜ፣ ዚቲኬት ዋጋው ኹዚህ ቀደም በጣም ዝቅተኛ ስለነበር፣ አሁን ዹተደሹገው ጭማሪ ሳይሆን 'ማሻሻያ' ነው ሲሉ አብራርተዋል። ዹዋጋ ማሻሻያው "ማንንም ዚማይጎዳ መልኩ" መሆኑን በማስሚገጥ፣ ዚቲኬት ዋጋው ለሁሉም ትያትሮቜ በ200 ብር መወሰኑን ገልጞዋል።

ኩንላይን ትኬት ሜያጭ እና ሌሎቜ ለውጊቜ
ኹተመሠሹተ 70 ዓመታትን ያስቆጠሚው ብሔራዊ ቲያትር፣ አዳዲስ ለውጊቜን በማምጣት ተመልካቹን ለማርካት መዘጋጀቱን አስታውቋል።

ኚለውጊቹ መካኚል ተመልካ቟ቜ ኚዚቀታ቞ው ሆነው ትኬት መግዛት ዚሚያስቜላ቞ውን 'ኩንላይን' ዚቲኬት ሜያጭ ሥርዓት ማመቻ቞ቱ ተገልጿል።

በተጚማሪም፣ ዚቲያትር ቀቱ ኃላፊዎቜ በቀጣይ ሁሉም ክልሎቜ ዚሚሳተፉበት ሥልጠና በብሔራዊ ቲያትር እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። ይህ ዹዋጋ ማሻሻያ እና ሌሎቜ ተያያዥ ለውጊቜ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትርን ወደ ተሻለ ደሹጃ ለማምጣት እና ዘመናዊ አገልግሎቶቜን ለመስጠት እንደሚያግዝ ይጠበቃል ሲል ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏22❀13🀯3👍1😱1😭1
📌ዚኢትዮጵያ ቀዳማዊት እመቀት መዝሙር

ቀዳማዊት እመቀት ዝናሜ ታያ቞ው "ያዘኝ" በሚል ርዕስ አዲስ ዹመዝሙር ቪድዮ በቅርቡ ለህዝብ እንደሚያደርሱ ጜህፈት ቀታ቞ው አስታውቋል።

"ያዘኝ" ዹሚለው ዚአዲሱ መዝሙር ርዕስ፣ "በፈተና ጊዜ እግዚአብሔር ደግፎኛል" ዹሚል መንፈሳዊ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ መዝሙሩም ተመሳሳይ ዚምስጋና እና ዚተስፋ መልዕክትን ይዞ እንደሚመጣ ይጠበቃል።

ይህ ስራ቞ው፣ ኹዚህ ቀደም ካወጧ቞ው መዝሙሮቜ እና ካሳተሟ቞ው መጜሐፍት ዹቀጠለ ዚጥበብ ስራ቞ው አካል ነው።

ቀዳማዊት እመቀት ዝናሜ ታያ቞ው፣ ኹመዝሙር ጥበብ ስራዎቻ቞ው በተጚማሪ፣ በጜህፈት ቀታ቞ው በኩል በተለያዩ ማህበራዊ ስራዎቜ ላይ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ሲገለጜ ቆይቷል።

ዚአዲሱ ዹመዝሙር ቪድዮ መቌ እንደሚለቀቅ ዝርዝር መሹጃው ገና ይፋ አልተደሚገም።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁13👎8❀7
📌በአርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ  ምክንያት "ኚትዳር በላይ" ቎አትር ዛሬ ኚመድሚክ ይሰናበታል

በ቎ዎድሮስ ተ/አሹጋይ ተጜፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ ዹተዘጋጀው "ኚትዳር በላይ" ዚኮሜዲ ቎አትር ኚወራት በኃላ በአርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ ምክንያት ዛሬ ኚመድሚክ እንደሚሰናበት ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚተውኔቱ ደራሲ ቎ዎድሮስ ተ/አሹጋይ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ባለፉት 6 ወራት በዓለም ሲኒማ ሲታይ ዹቆዹው "ኚትዳር በላይ" ቎አትሩ ኚመድሚክ ዚሚወርድበት ምክንያት አርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ በተዋናይነት ዚሚሳተፍበት "ወደ ማዶ" ዹተሰኘ ቎አትር በቅርቡ ዓለም አቀፍ ጉዞ ስለሚያደርግ እንደሆነም ተነግሯል።

ኚዚካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ሲቀሚብ ዹቆዹው ቎አትሩ ዛሬ ነሐሮ 14 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 12:00 ጀምሮ ኚመድሚክ ይሰናበታል።

በ቎አትሩ ላይ መስኚሚም አበራ፣ ሞዋፈራው ደሳለኝ፣ ዚማታወርቅ ታደሰና መዓዛ ገብሚሕይወት፣ ዕፀሕይወት አዳንኚኝ፣ ቞ርነት ፍቃዱ በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀13👏3
📌ዚሐናን "ሻደይ" ሙዚቃ ለአድማጮቜ ቀሹበ

ዚወጣቷ ድምጻዊት ሀናን አብዱ "ሻደይ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ ዹሙዚቃ ስራ ኚቀናት በፊት በናሆም ሪኚርድስ ዩቲዩብ ቻኛል ለሙዚቃ አፍቃሪያን ቀርቧል።

"ሻደይ" ሙዚቃ ላይ በዜማ ይግዛው በላይ በአማርኛ ግጥም ተስፋ አብርሃ በኜምጥኛ ግጥም ይግዛው በላይ በቅንብር ኪዱ አድማሱ ተሳትፈዋል።

ዹሙዚቃ ቪዲዮውን ዳይሬክተር ያደሚገው ይግዛው ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7
📌ዚኪያ ካሣሁን "ምልምልወይ" ሙዚቃ ተለቀቀ

ዚድምጻዊት ጠሹፍ ካሣሁን (ኪያ) "ምልምልወይ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ ዹሙዚቃ ስራ በናሆም ሪኚርድስ ዚዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮቜ ቀርቧል።

በ"ምልምልወይ" ሙዚቃ ላይ በግጥምና ዜማ ይግዛው በላይ በሙዚቃ ቅንብር ኪዱ አድማሱ ተሳትፈዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6
📌ሎጆቜና ሬስቶራንቶቜ ደሹጃ ሊሰጣ቞ው ነው

ዚቱሪዝም ሚኒስ቎ር ቀደም ሲል በሆ቎ሎቜና ሪዞርቶቜ ላይ ብቻ ሲካሄድ ዹቆዹውን ዹደሹጃ ምዘና ሥራ፣ ሎጆቜንና ሬስቶራንቶቜን ጭምር እንዲያካትት ዚሚያስቜል አዲስ ሀገራዊ መመዘኛ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

ይህ አዲስ ዹደሹጃ አሰጣጥ ሥርዓት አገሪቱ ለቱሪዝም ዘርፍ ዚምትሰጠውን ትኩሚት ኹፍ ዚሚያደርግ ሲሆን፣ ዹዘርፉን ጥራትና አገልግሎት ለማሻሻል ያለመ ነው ተብሏል።

ዹተዘጋጀው መመዘኛ በሹቂቅ ደሹጃ ተጠናቅቆ፣ በቀጣይነት ለባለድርሻ አካላት ውይይት ቀርቩ ተግባራዊ እንደሚደሚግ ዚሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ ገልጿል።

በሌላ በኩል፣ ኹ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ አዳዲስ ሆ቎ሎቜ በተገቢው ጊዜ ዹደሹጃ ምደባ እንዲያደርጉ ዚታቀደ ቢሆንም፣ ዹደሹጃ ምደባው ሂደት ላይ ቜግሮቜ መፈጠራ቞ው ታውቋል።

ዚተፈጠሩት ቜግሮቜ ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶቜ እንዳሏ቞ው ተጠቁሟል። አንደኛው፣ ባለሀብቶቜ በተያዘው ጊዜ ዚኮኚብ ደሹጃ ለመመደብ ፈቃደኛ አለመሆናቾው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ አብዛኞቹ ተቋማት ዚኮኚብ ደሹጃ ለመመደብ ብቁ ሆነው አለመገኘታ቞ው ነው። ይህ ደግሞ ዚቱሪዝም ዘርፉን ጥራት ለመቆጣጠር በሚደሹገው ጥሚት ላይ ፈተና እንደሚሆን ተገልጿል ሲል ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3
📌ዚአነጋጋሪው ሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ማታ ይለቀቃል

ዚድምጻዊ ናቲ ኬር "ነገር ነገር " ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠውና በቲክቶክ ዚማህበራዊ ትስስር ገፅ መድሚክ በርካቶቜ ዚተቀባበሉት ሙዚቃ ቪዲዮ ነገ አርብ ነሐሮ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በድምጻዊው ዚዩቲዩብ ቻናል ለአድማጮቜ ተመልካቜ ይቀርባል ተብሏል።

"ነገር ነገር ባይልሜ ነገር - ተሾክሜ አኖርሜ ነበሹ"

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8👍2🔥2
📌 ዚኢቢሲ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሹም ሜር

ዚኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሜንን ኚታህሳስ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ ዚቆዩት አቶ ጌትነት ታደሠ ኚኢቢሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኃላፊነታ቞ው ተነስተው ዚኢትዮጵያ ኅብሚት ሥራ ኮሚሜን ኮሚሜነር ሆነው እንደተሟሙ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

አቶ ጌትነት ታደሰ ዚኢትዮጵያ ህብሚት ስራ ኮሚሞን ኮሚሜነር ኃላፊ ሆኖ ዚተመደቡት በአምባሳደር ሜፍራው ሜጉጀ (ዶ/ር) ምትክ መሆኑንም ሰምተናል።

አቶ ጌትነት ታደሠ ኚኢቢሲ ስራ አስፈፃሚነታ቞ው አስቀድሞ ዚኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ እንደነበሩ ይታወሳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍5😁4❀2🀣1
📌በአዲስ አበባ ዚጋሚዱ አሟሟት መነጋገሪያ ሆነ

ኹሰሞኑ በአዲስ አበባ ኹተማ በተለምዶ 22 አካባቢ በሚገኘው "ቪ.አይ.ፒ ላውንጅ" በተሰኘው ጭፍራ ቀት (ክለብ) ውስጥ በጠባቂነት(ጋሚድ) ሆኖ ሲሰራ ዹቆዹው ወጣት ልደቱ አዹነው (አቢ) በድንገተኛ ጥቃት እንደተገደለ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

በወቅቱም ዚሟቜ አስክሬን ለምርመራ ዹተወሰደ ሲሆን ውጀቱም ኹ15 ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚሆን ተነግሯል።

ወጣት ልደቱ አዹነው (አቢ) በሚሰራበት ቪ.አይ.ፒ ላውንጅ ውስጥ ስራ ላይ እያለ በጩቀ ተወግቶ መገደሉንም ዚቅርብ ቀተሰቊቹ በማህበራዊ ገፆቻ቞ው ሲናገሩ ተመልክተናል።

ዚሟቜ ቀተሰቊቜና ወዳጆቜ ዚሚሰራበት ሆቮል ሰራተኛው ተገደሎበት ለአንድ ቀን እንኳ ስራውን ሳያቆም እዚሰራ እንዳለና ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ገዳዮቹን ለህግ በማቅሚብና ለጠፋው ህይወት ተመጣጣኝ ፍትህ ለመስጠት ምንም አይነት እንቅስቃሎ አለማድሚጉንም ጭምር እዚተናገሩ ይገኛሉ።

በዚህም ምክንያት "ፍትህ ለአቢ" እና "ሕጉ ይኚበር፣ ፍትህ ይስፈን" በሚል ዚማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እያካሄዱ ነው።

በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ቞ውም 1ኛ ግልጜና ፍጥነት ያለው ምርመራ እንዲፈጞም 2ኛ ዹተጠሹጠሹው አካል በህግ ፊት ዚሚገባውን ፍርድ እንዲያገኝ 3ኛ ፍትህ ሳይዘገይ በተግባር እንዲፈጞም በአጠቃላይ ለወጣት ልደቱ ፍትህ እንዲሰጠው ጥያቄዎቜን እዚቀሚቡ ይገኛል።

ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚአዲስ አበባ ፖሊስና እና ኚቪ.አይ.ፒ ላውንጅ ስለጉዳዩ መሹጃ ለማግኘት ቢሞክርም አልተሳካም።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀11😭11🀔2
Event Addis Media
📌በአዲስ አበባ ዚጋሚዱ አሟሟት መነጋገሪያ ሆነ ኹሰሞኑ በአዲስ አበባ ኹተማ በተለምዶ 22 አካባቢ በሚገኘው "ቪ.አይ.ፒ ላውንጅ" በተሰኘው ጭፍራ ቀት (ክለብ) ውስጥ በጠባቂነት(ጋሚድ) ሆኖ ሲሰራ ዹቆዹው ወጣት ልደቱ አዹነው (አቢ) በድንገተኛ ጥቃት እንደተገደለ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል። በወቅቱም ዚሟቜ አስክሬን ለምርመራ ዹተወሰደ ሲሆን ውጀቱም ኹ15 ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚሆን 
📌ዚፖሊስ መግለጫ ስለ ጋሚዱ አሟሟት

ቪ አይ ፒ ላውንጅ በሚባል ሆቮል በሁለት ግለሰቊቜ መካኚል በተፈጠሹ አለመግባባት ዹሰው ህይወት ማለፉን ተኚትሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
                          
ድርጊቱ ዹተኹሰተው ነሀሮ 07 ቀን 2017 ዓ/ም በግምት ኹቀኑ 7 ሰዓት ኚሩብ ገደማ በቩሌ ክፍለ ኹተማ ወሚዳ 3 ሃያ ሁለት አካባቢ በሚገኘው" ቪ አይ ፒ ላውንጅ"  በተባለ ሆቮል ውስጥ ነው።

በዕለቱ በድርጅቱ በጋርድነትና በዲጄ ሰራተኝነት ተቀጥሚው በሚሰሩ ልደቱ አያኖ እና ናትናኀል ልዑል በተባሉ ግለሰቊቜ መካኚል ምክንያቱ ባልታወቀ አለመግባባት በተፈጠሹ ጞብ ምክንያት ናትናኀል ልዑል ዚተባለው ግለሰብ ጭንቅላቱ ላይ ኹፍተኛ ጉዳት ዚደሚስበት መሆኑን ፖሊስ በስፍራው ደርሶ ካሰባሰበው መሹጃ ማሚጋገጥ ተቜሏል።

በቅርብ ርቀት ዚነበሩ ሰዎቜ ተጎጂውን ወደ ህክምና በመወሰድ ልደቱ አያኖ ዚተባለው ግለስብ ኚአካባቢው እንዳይሞሜ እዚጠበቁት በነበሚበት አጋጣሚ  ድብደባው በተፈፀመበት አልጋ ክፍል ቁጥሩ 505 አምስተኛ ፎቅ ላይ ባለ ክፍል ውስጥ ገብቶ በሩን ኚውስጥ በመዝጋት ኹክፍሉ ባለ መስኮት ወደ መሬት ወድቆ ጉዳት ደርሶበት ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እርዳታ እዚተደሚገለት ህይወቱ ያለፈ ሲሆን ትክክለኛ ዚአሟሟቱን ሁኔታ ለማወቅ ምርመራው ቀጥሏል።                         

ኚባድ ጉዳት ዚደሚሰበት ናትናኀል ልዑል ዚተባለው ግለሰብ አሁንም በህክምና ተቋም ውስጥ ተኝቶ ክትትል እዚተደሚገለት ይገኛል።

በጉዳዩ ላይ ተጚማሪ ማስሚጃ ዚማሰባሰብ ስራዎቜን በመስራት እና ዚአስክሬን ምርመራ ውጀት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል ዚምርመራ ስራው እንደተጠናቀቀ ሙሉ መሹጃውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

@EventAddis1
❀8😭2
📌 ዚተሰወሩት ጋዜጠኞቜ መፈታታ቞ው ተሰማ

ኹሰሞኑ መነጋገርያ ሆኖ ዹሰነበተው ዚሶስት ጋዜጠኞቜ በሀይል ታፍነው ኚተወሰዱ በኋላ ደብዛ቞ው መጥፋቱ ነበር። ድርጊቱ በሀገር ውስጥ እንዲሁም በውጭ ያሉ ጋዜጠኞቜን እና እንደ ሲፒጄ ያሉ ዚጋዜጠኞቜ መብት ተኚራካሪ ቡድኖቜን ትኩሚት ስቊ ቆይቷል።

መሠሚት ሚድያ እንደዘገበው ኹሆነ ትላንት ማምሻውን (ነሐሮ 16 2017 ዓ.ም) ታፍነው ተወስደው ዚነበሩት ጋዜጠኞቜ አብዱልሰመድ መሐመድ፣ ዮናስ አማሹ እና ሐሰን ሰይድ ኚታፈኑበት ተለቀው በተለያዩ ዚአዲስ አበባ ስፍራዎቜ ተበትነው ተገኝተዋል።

ትላንትና ምሜት ሶስት ሰዓት ገደማ ጋዜጠኞቹ ኚአዲስ አበባ ወጣ ባሉ ስፍራዎቜ ተለቀው መገኘታ቞ው ታውቋል።

©ዘገባው ዚመሠሚት ሚዲያ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏3🀬3✍1😚1
📌ድምፃዊ ኢሳያስ ታምራት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ

ድምፃዊ ኢሳያስ ታምራት በሕገወጥ ዚሰዎቜ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኝ ኢትዮፒካሊንክ ዘግቧል።

ፖሊስ ድምጻዊ ኢሳያስን ኹነሐሮ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በቁጥጥር ስር ያዋለው ሲሆን ፀነሀሎ 07 በፌደራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት አራዳ ምድብ ዚቀጠሮ ቜሎት ቀርቧል ።

ፖሊስ ተጠርጣሪውን በህገወጥ ዚሰዎቜ ዝውውር ወንጀል እንደጠሚጠሚውና ተጚማሪ ዚምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

ፍርድ ቀትም ስምንት ዚምርመራ ቀናት ፈቅዷል። በዚህ መሰሚት ቀጣዩ ቜሎት ሀሙስ ነሀሮ 15 ታይቶ ፖሊስ በድጋሜ ተጚማሪ ዚምርመራ ቀናት እንዲሰጡት ጠይቋል።

ዚኢሳያስ ጠበቃም ድምፃዊው ኚቀናት በኋላ አልበምን እንደሚያወጣ እና ለዚያም ዝግጅት እያደሚግ እንደሆነ እንዲሁም በተመሳሳይ ወንጀል ዹተጠሹጠሹው ጓደኛው በዋስ መለቀቁን በማስሚዳት ዚዋስትና መብቱ እንዲኚበርለት ጠይቋል።

ኢሳያስ በበኩሉ "ዚተያዝኩት ኹፀበል ቊታ ነው ፀ ደካማ እና቎ን እና ዚስድስት ወር ልጄን ጥዬ ነው እዚህ ያለሁት በመሆኑም ዋስትናዬ ተኚብሮ በውጪ ሆኜ ጉዳይን ልኚታተል" ሲል ጠይቋል።

መርማሪ ፖሊስ ደግሞ ተኚሳሹ ያቀሚበውን ዚዋስትና ጥያቄ እንደሚቃወም እና ሌሎቜ አባሪዎቹን ለመያዝ ተጚማሪ ማስሚጃዎቜን ኚተለያዩ ተቋማት ለማምጣት እንዲቜል ተጚማሪ ዚምርመራ ቀን እንዲፈቀድለት ፍርድ ቀቱን ጠይቋል።

ፍርድ ቀቱም ግራ ቀኙን አድምጊ ለፖሊስ ስምንት ተጚማሪ ቀናትን ፈቅዶ ዚቜሎቱ ሂደት መጠናቀቁ ተነግሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😱9❀4
📌በኢትዮጵያ ዹቮምር ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው።

በኢትዮጵያ ዚመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ዹቮምር ፌስቲቫል ኹነሃሮ 20 እስኚ 22 2017 ዓ.ም በአፋር ሰመራ ሆቮል ይካሄዳል ተብሏል።

ፌስቲቫሉ ኹዘጠኝ ሃገራት ዚተውጣጡ ዹቮምር አምራ቟ቜ፣ ዹዘርፉ ተመራማሪዎቜ እና ዚፈጠራ ባለቀቶቜ ዚሚገኙበት ነው።

በፌስቲቫሉም ዚልምድ ለውውጥ ይደሚጋል፣ ዘመናዊ ዹቮምር አመራሚት ዘዮ ይዳሰሳል፣ እንዲሁም ዚተሻሻሉ ዹቮምር ዝርያዎቜ ይተዋወቃሉ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4👏1
ባይራ ዲጂታል መጜሄት ቅጜ 2 ቁጥር 4.pdf
8.9 MB
📌ባይራ ዲጂታል መጜሔት ለንባብ በቅቷል።

ቅጜ 2 ቁጥር 4

በእነዚህ ዚማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮቻቜን ቀተሰብ ይሁኑ!

቎ሌግራም- https://t.me/Bayradigital
ድሚገጜ (Website)- https://bayradigital.com/
ፌስቡክ (Facebook) - ባይራ ዲጂታል መጜሔት

ለማንኛውም አስተያዚት ብሎም ጜሑፍ ለመላክ

ኢ-ሜይል- bayradigital2016@gmail.com
❀8
📌ዚአስቻለው "እመት ሾዋ" ቪዲዮ ዛሬ ይለቀቃል

ዚድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ(አርዲ) "እመት ሾዋ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዹሙዚቃ ቪዲዮው በዛሬው ዕለት በብርቧክስ ሪኚርድስ በኩል ይሰራጫል።

አስቻለው ፈጠነ (አርዲ) ኹዚህ ቀደም በለቀቃቾው "እናትዋ ጎንደር" እና "ካሲናው ጎጃም" "አሞራው ካሞራው" በተሰኙ ሙዚቃዎቜ  ኹፍተኛ ተደማጭነትን አግኝቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀10👍1
📌ንጉሥ ማልት በምርት ጥራት ተሾለመ

በምርቱ ጣዕም እና ጥራት ተወዳጅነትን ያተሚፈው ንጉስ ማልት ለሜልማት በቅቷል።

ሾላሚው á‹µáˆ­áŒ…ት በ1961 በብራስልስ፣ ቀልጂዚም ዹተመሰሹተው Monde Selection ሲሆን ግንባር ቀደም ራሱን ዚቻለ ዚጥራት ግምገማ ተቋም ነው።

በጠንካራ ግምገማዎቹ እና መስፈርቶቹ ዚሚታወቀው ሞንዮ ሰሌክሜን በዚአመቱ ምርቶቜን በምግብ፣ መጠጊቜ፣ መዋቢያዎቜ እና ሌሎቜንም ኹ3,000 በላይ ዹሆኑ ዚተለያዩ  ምርቶቜ ገምግሞ እንደዚ ጥራት ደሹጃቾው ሜልማት ይሰጣል። 

ይህ ተቋም ዚነሐስ፣ ሲልቚር፣ ወርቅ እና ግራንድ ወርቅን ጚምሮ ዚተኚበሩ ዚጥራት መለያዎቜን በመሾለም በአለም አቀፍ ደሹጃ ይታወቃል። 

ኹ60 ዓመታት በላይ ባለው እውቀት፣ Monde Selection በተጠቃሚ ምርቶቜ ጥራት ላይ ዓለም አቀፍ ደሚጃዎቜን ያዘጋጃል።
በእዚህ ትልቅ ተቋም ኚአልኮል ነፃ መጠጥ ዹሆነው ንጉስ ማልት ዹ2025 በምርት ጥራት ዹወርቅ ተሾላሚ ሆኗል።

ንጉስ ማልት ኚሞድን ሰሌክሜ ዚጥራት ሜልማት ሲያገኝ ይህ ዚመጀመሪያው አይደለም።

ባለፈው አመትም ዚብር ተሾላሚ እንደነበር ይታወሳል። በአገራቜን ኢትዮጵያ ኚንጉስ ተጚማሪም ሌሎቜ ምርቶቜም እንደዚ ጥራት ደሹጃቾው እውቅና እና ሜልማት ተበርክቶላ቞ዋል።

ይህ ተደጋጋሚ ሜልማት ለንጉስ ማልት እና ለተጠቃሚዎቹ ብቻ ሳይሆን ለአገር  ዚሚያበሚክተው እውቅና ቀላል አይደለም።
ንጉስ ደሹጃውን አስጠብቆ እንዲቆይ ለሌሎቜ ምርቶቜ ደግሞ áŠ áˆ­áŠ á‹« በመሆን በምርት ጥራታ቞ውን አስጠብቀው ኚአመት አመት ለሜልማት እንዲበቁ መነቃቃትን ይፈጥራል ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6👍2
📌ፈንድቃ አዲስ ዚሚያስገነባውን ህንፃ ይፋ አደሹገ

ፈንድቃ ባህል ማዕኹል በቀጣይ ዚሚያስገነባውን ዘመናዊ ዚባህል ማዕኹል ህንፃ ንድፍ ይፋ አድርጓል።

ፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል ስራ አስኪያጅ መላኩ በላይ በማህበራዊ ትስስር ገጜ "በካርሎ ራቲ አሶሺያቲ - ዚሚመራው  በዓለም አቀፍ ታዋቂ ዹሆነው ዚኢጣሊያ ዚስነ ሕንፃ ተቋም - ለአዲሱ ዚፈንድቃ  ህንፃ ንድፍ ዚመጀመሪያውን  ምዕራፍ እንዳጠናቀቀ በማካፈሌ በጣም ደስተኛ ነኝ" ብሏል።

ፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል በጥቅምት 2017 ዓ.ም ኹፈሹሰ በኋላ በቊታው ዚራሱን ህንጻ እንዲሰራ ቊታው ለፈንድቃ መሰጠቱ ይታወሳል።

ኚታህሳስ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ፈንድቃ ኚሀያት ሬጀንሲ ጋር በመተባበር ኮንሰርቶቜንና እና አዝማሪ ፕሮግራሞቜን እያቀሚ ይገኛል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8👍6👎2👌2
📌ዚአዲስ ለገሠ "ማስታወሻ" አልበም ተለቀቀ

“ማስታወሻ" á‹šá‰°á‰£áˆˆ ስያሜ ዚያዘው ይህ ዚመጀመሪያ አልበሙ 14 ዹሙዚቃ ስራዎቜ ዚተካተተበት ነው።

አልበሙ ፍቅር ዚተቀነቀነበት መዋደድ ዚነገሠበት አዲስ ለገሠ ዚራሱን ቀለም እና አቀራሚብ ያስተዋወቀበት ስራ ነው ተብሏል።

አልበሙ በርካታ ዹሙዚቃ ዘይቀዎቜን እና ዘውጎቜን ያካተተ ሲሆን በሀሳብ፥ በሙዚቃ ቅንብር፥ በድምፅ እና በአዘፋፈን አዲስ ጣዕም ይዞ መቅሚብ ቜሏል።

በማስታወሻ አልበሙ ላይ ይልማ ገ/አብ፣ ናትናኀል ግርማ቞ው፣ እሱባለው ይታዚው (ዚዚሺ ልጅ)፣ ሞገስ ተካ እና ሌሎቜ ዕውቅ ዹዜማና ዚግጥም ደራሲዎቜ፣ እንዲሁም እራሱ አዲስ ለገሠ በግጥም እና ዜማ ዚተሳተፉበት ነው፡፡

በሙዚቃ ቅንብሩም ሚካኀል ሃይሉ፥ ኪሩቀል ተስፋዬ፥ ብሩክ አፈወርቅ እንዲሁም ሌሎቜም ዚተሳተፉብት ሲሆን ማስተሪንጉን ኪሩቀል ተስፋዬ ተጠቊበታል፡፡

ዹ “ማስታወሻ” አልበም ስራን ጀምሮ ለማጠናቀቅ ሶስት ዓመታትን እንደፈጀ ዹተነገሹ ድምጻዊው ለዚህ ዹአልበም ሥራው ሲል በርክት ያለ ክፍያ ኚሚኚፈልበት ኹሙዚቃ ክለብ ስራዎቜ ራሱን ኚሁለት ዓመታት እንዳቀበም ተናግሯል።

ድምጻዊ አዲስ ለገሠ "ኮርቌ ዚሚናገርለት አልበም ነው" ሲሉ ዹገለጾውን ዚመጀመሪያ አልበሙን በአዲስ ለገሰ ይፋዊ ዩትዩብ ቻናልና በሁሉም ዓለም አቀፍ ዹሙዚቃ መተግበሪያዎቜ በኩል ለአድማጮቜ ለቋል።

አዲስ ለገሠ: YouTube:https://youtube.com/@addislegesseofficial?si=k2XXutbiqlcdVMcD

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀20😢1
📌አንዱ መጜሐፍ በ130 ሺህ ብር ተሾጠ

ዚጀና ልማትና ፀሹ-ወባ ማኀበር ዚተቋቋመበትን 27ኛ ዓመት ዚምስሚታ በዓል “ወባን በእኛ ሐብት፣ በእኛ እውቀትና ጉልበት እናጠፋለን!" በሚል መሪ ቃል ነሐሮ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በስዊስ ኢን ኔክሰስ ሆቮል በድምቀት ተኚብሯል።

በዚህ ዚምስሚታ ክብሚ በዓል ላይ ዚማኅበሩን ዚሃያ ሰባት ዓመታት ታሪክ ዚሚያሳይ "ፈጥኖ ደራሹ ማኅበር" ዹተሰኘ መጜሐፍ ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።

በክብሚ በዓሉ ላይ ይህ "ፈጥኖ ደራሹ ማኅበር" ዹተሰኘው መጜሐፍ በ130 ሺህ ብር ተሞጧል። መፅሐፉን ለጚሚታ ያቀሚበው ዚፕሮግራሙ መሪ ማናዬ እውነቱ ነው።  ጚሚታውን ሲሲ አር ዲኀ በ80ሺ ብር ያሞነፈ ሲሆን መፅሐፉን ለመግዛት ኹፍተኛ ፉክክር ሲያደርግ ዹነበሹው ለወገኔ ማይክሮ ፋይናንስ ለጚሚታ ያዘጋጀውን 50ሺ ብር ለማህበሩ ገቢ አድርጏል። 

"ፈጥኖ ደራሹ ማኅበር" መጜሐፍ በአስር ሁለት ምዕራፎቜ ዹተዘጋጀ ሲሆን ዚመጜሐፉ ዓላማ ዚማኅበሩን አመሠራሚት፣ ያኚናወና቞ውን ሥራዎቜ፣ ዹተገኙ ለውጊቜን፣ እዚተካሄዱ ያሉ ሥራዎቜን፣ መልካም ጎኖቜና ያጋጠሙ ተግዳሮቶቜ፣ ዚተወሰዱ ዚመፍትሔ እርምጃዎቜን ዘርዝሮ በማቅሚብ ለቀጣይ ትውልድ ብሎም ለመሰል ድርጅቶቜ ትምህርት ሆኖ እንዲያገለግል እንደሆነም ተገልጿል።

ዚጀና፣ልማትና ፀሹ-ወባ ማኀበር ነሐሮ 17 ቀን 1990 ዓ.ም ተመሥርቶ ባለፉት 27 ዓመታት ሕብሚተሰቡን ዹሚጠቅሙ በርካታ ዹበጎ አድራጎት ስራዎቜን እንዳኚናወነ አስታውቋል።

ፎቶ: Tekle Markon

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍8❀5🀣4👎2