Event Addis Media
9.63K subscribers
6.07K photos
12 videos
4 files
4.69K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌አንጀሊና ጆሊ ዚቅዱስ ጎጥሮስ ሆስፒታልን ጎበኙ

ዝነኛዋ አሜሪካዊት ተዋናይት ፣ ዹፊልም ባለሙያ እና ዚሰብአዊ ድጋፍ አቅራቢ ዚሆኑት አንጀሊና ጆሊ በዛሬው ዕለት ዚቅዱስ ጎጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

ተዋናይቷ ያደሚጉት ጉብኝት በዋነኝነት ሆስፒታሉ እዚሰጠ በሚገኘው መድሃኒቱን ዹተላመደ ቲቢ (ኀም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና ዙሪያ እዚተኚናወኑ ያሉ እንቅስቃሎዎቜን ፣ ዚሚታዩ ለውጊቜን እንዲሁም ድጋፍ ዚሚያስፈልጋ቞ውን ቊታዎቜ መለዚት ላይ ትኩሚት ያደሚገ ነበር።

በጉብኝቱ ላይ አንጀሊና ዚሆስፒታሉን ዚቲቢና መድሃኒቱን ዹተላመደ ቲቢ (ኀም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና አገልግሎት መስጫ ዋርድ ፣ ላብራቶሪ እንዲሁም ታካሚዎቜን ተዘዋውሹው ተመልክተዋል።

አንጀሊና ወደ ሆስፒታሉ ኹሹጅም ጊዜያት በፊት መጥተው እንደነበር ያስታወሱ ሲሆን በአሁኑ ጉብኝታ቞ው ላይ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ለውጊቜ አምጥቶ በመመልኚታ቞ው እጅግ ደስተኛ መሆናቾውን ተናግሚዋል።

አክለውም ሆስፒታሉ ድጋፍ ቢደሚግለት በቀጣይ ዚተሻለ
አገልግሎት ለታካሚዎቜ መስጠት በሚያስቜለው አስተማማኝ ደሹጃ ላይ እንዳለ በጉብኝቱ ላይ መገንዘባ቞ውን ገልፀዋል።

በተጚማሪም በሆስፒታሉ በቲቢ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ዹተገኘው እድገት በእጅጉ ዹሚደነቅ እና ዚሚያስተማምን ስለሆነ በቀጣይ በጂ.ኀቜ.ሲ (Global Health Committee (GHC)) በኩል ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል።

ዚሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም እሞቱ በበኩላ቞ው ቲቢን ለማጥፋት በሚደሹገው ጥሚት ውስጥ ተዋናይቱ ላሳዩት ዘላቂ ቁርጠኝነት ፣ ልግስና እና በቀጣይ ለሚያደርጉት ድጋፍ ኹፍተኛ ምስጋና቞ውን አቅርበዋል።

Via ቅዱስ ጎጥሮስ ሆስፒታል

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀19🀣8🥰1
📌‘ኢመርጅ’ ዚሥነጥበብ አውደርዕይ ተኹፈተ

አስር ሁለት ሠዓሊያ እና ዹፊልም ባለሞያዎቜ ስራዎቻ቞ውን ያቀሚቡበት "ኢመርጅ" ዘመናዊ ዚሥነጥበብ አውደርዕይ ነሐሮ 7 2017 ዓ.ም በገብሚክርስቶስ  ደስታ ዘመናዊ ዚሥነጥበብ ሙዚዹም ውስጥ በይፋ ተኚፍቷል።

ይህ ‘ኢመርጅ’ ዘመናዊ ዚሥነጥበብ አውደርዕይ ለሁለት ዓመት በድህሚ ምሹቃ መርሀግብር፥ ኹአለ ዚሥነጥበብና ዲዛይን ት/ቀት በሥነጥበብ እና በፊልም ጥበብ ዘርፍ ትምህርታ቞ውን ተኚታትለው በሰኔ 2017 ዓ.ም ያጠናቀቁ ተማሪዎቜ መካኚል ዚተመሚጡ ስድስት ሠዓሊያንን እና ስድስት ዹፊልም ባለሙያዎቜን ዚመመሚቂያ ጥናታዊ ዚሥራ ውጀት ለሰፊው ህዝብ ለማሳዚት በዘመናዊ ዚሥነጥበብ ሙዚዹም - ገብሚክርስቶስ ደስታ ማዕኹል ዹተዘጋጀ ዐውደርዕይ ነው።

በዚህ ዐውደርእይ ላይ ዚቀሚቡት ስራዎቜ ስለ: ማህበራዊ፣ ልማታዊ ለውጥና ተጜእኖው፣ ሥነጥበባዊ ዚአእምሮ ህክምና፣ ሶሻል ሚዲያና ተጜእኖው እንዲሁም ኹሀገር እስኚ ዓለም አቀፍ እዚደሚሰ ስላለው ዚተሳሰሚ ኢፍትሀዊ ብዝሀ ቜግሮቜ ዙሪያ ዚሚዳስሱ ርዕሰ ጉዳዮቜ በዘመናዊ ዚሥነጥበብ አውድ ቀርበዋል።

ተሳታፊ ሠዓሊዎቜፊ
አለማዹሁ ዳርሰማ፣ ማስተዋል ጌታ፣ ሙሉአዳም አዳነ፣ ሰሎሜ ጌታ቞ው፣ ቎ዎድሮስ ክፍሌ፣ ዮናስ ፍቃዱ

ተሳታፊ ዹፊልም ባለሙያዎቜፊ
አቢይ ጌታሁን፣ አብርሐም ባህሩ፣ ኀልሻዳይ ይልማ፣ ጌታሁን ግርማ፣ ሊዲያ ምትኩ፣ ታደሰ በቀለ

ዹማዕኹሉ ዚእይታ ሰዓት፡ ኹማክሰኞ - እሁድ ኚጠዋት 4:00 ሰዓት - አመሻሜ 11:00 ሰዓት
ቊታ፡ 6 ኪሎ ምስካዚ ሓዙናን መድሃኒያለም ገዳም ኹፍተኛ ትምህርት ቀት ጎን በሚገኘው ዚንግድና ኢኮኖሚ ኮሌጅ አዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀4
📌ግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው

ግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት ዚፊታቜን ነሐሮ 17 2017 ዓ.ም በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቮል እንደሚካሄድ ዚፕሮግራሙ አዘጋጅ Nethor events አስታውቋል።

በግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት ታዋቂዎቹ ድምጻዊያን ሄለን በርሄ ፣ዮሳን ጌታሁን፣ሌንጮ ገመቹ፣ጌታ቞ው ኃይለማርያም፣አኒስ ጋቢ - ጆርጂ አቡ እና ሌሎቜም ዹሙዚቃ ስራዎቻ቞ው ያቀርባሉ ተብሏል።

በዝግጅቱ ላይ በአፍሪካ ሹጅሙ ዚጮርሮሳ ምግብ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ይመዘገባል ተብሏል።

ዚመግቢያ ክፍያ ቪአይፒ: 10,000 ቪቪአይፒ: 15,000 ብር ነው ተብሏል።

ዚኮንሰርቱ አዘጋጆቜ Nethor events እና Kenakon events ሲሆኑ "ይምጡ ባህሎቻቜንን ይደግፉ እና ይደሰቱ" ብለዋል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀5
📌ዚልጆቜ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሎ ዚሥነ ጥበባት ማዕኹል ዚልጆቜ መጻሕፍት በኢትዮጵያ በተሰኘ ርዕስ ዚልምምድ ልውውጥና ሙያዊ ውይይት ይካሄዳል፡፡

ሙያዊ ውይይቱ ዚፊታቜን ቅዳሜ ነሐሮ 10 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዚብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሎ ዚሥነጥበባት ማዕኹል ይካሄዳል።

ዚዕለቱ ተጋባዥ ኹ120 በላይ መጻሕፍትን ለሕትመት ያበቃው ዚልጆቜ መጜሐፍ ደራሲ፣ ተርጓሚና ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ዚቀድሞ መምህር ዓለም እሞቱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ኑሮውን በሀገሹ አሜሪካ አድርጓል፡፡

በዕለቱ ዚሥነ ጥበባት ማዕኹሉ ዳይሬክተር አቶ ይታገሱ ጌትነት በኢትዮጵያ ዚልጆቜ መጻሕፍት ታሪክና ተግዳሮት ዙሪያ ዚመነሻ ጜሑፍ ያቀርባሉ፡፡

ይህ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኢትዮጵያ ቀተመዛግብትና ቀተመጻሕፍት ትብብር በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር አማካኝነት ዚሚሰናዳው ዚክሚምት ወራት ዚሥነ ጜሑፍ ሥልጠና አንዱ አካል ሲሆን በዕለቱ በዘርፉ ዚተሰማሩ ዚልጆቜ መጜሐፍ ደራሲያንና ባለሙያዎቜና ይሳተፋሉ፡፡

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀4
📌 ዹአንጋፋው ደራሲ ሳህለ ሥላሎ ብርሃነማርያም ልደት በልዩ ዝግጅት ዛሬ ይኚበራል

ጥበበ መድሎት ዚጋዜጠኝነትና ዚኪነ ጥበብ ሰልጣኞቜ አንጋፋ ዚኢትዮጵያ ዚስነ ጜሁፍ ባለውለታዎቜን ለመዘኹር ቀጠሮ ይዟል።

ዹ''መኚሚኞቹ'' ፣ ''ያገር ልጅ'' እና ''ባሻ ቅጣውን ዹመሰሉ ዘመን ተሻጋሪ ዚስነ ጜሑፍ ስራዎቜን ያጋሩንን ጋሜ ሳሕለሥላሎን እናኚብራ቞ው ዘንድ እንድታጅቡን በክብር ጋበዝናቜሁ።

📖 ደራሲና አርታኢ ሀይለመለኮት መዋዕል

📖 ጋዜጠኛ ግርማ ፍሰሃን

📖 ደራሲና ተርጓሚ ሳህለስላሎ ብርሃነማርያም

📖 ገጣሚት ባንቻዚሁ አሰፋ


⏰ ሰዓት :አርብ ነሐሮ 9 ኹቀኑ - 10:30 ጀምሮ

📍 አድራሻ ካሳንቜስ ኢሊሊ ኢንተርናሜናል ሆቮል

          መግቢያ በነፃ

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀11🥰3👎1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

1.ዹአንጋፋው ሙዚቀኛ መላቱ አስታጥቄ  አዲስ ዹሙዚቃ አልበም ዚሚለቀቅበት ቀን ይፋ ሆነ።

2."቎አትር በዚቀታቜሁ ሊገባ ነው" ተብሏል።ዚአፍሪካን ሬነሳንስ ቎ሌቪዥን  "Arts Pluse" ዹተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ ሊያደሚግ ነው ።አዲሱ መተግበሪያ ምን ምን ጉዳዮቜ ይዟል እንነግራቜኋለን።

3.መስኚሚም አበራ እና ቞ርነት ፍቃዱ ዚተጣምሩበት አዲስ ሀገርኛ ፊልም ለእይታ ሊበቃ ነው።

እነዚህንና ሌሎቜንም ዚአርትስ ስፔሻል ዚኪነት እና ኩነት መሚጃዎቜ እናቀርብላቜኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/9hJNQhiM_ow?si=Bt_BmTaEvpCymvlY

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍5❀3
"ቀለም" ዲጂታል መጜሔት ዛሬ ለንባብ ይበቃል

ዹቀለም ዲጂታል መጜሔት አዘጋጆቜ "ዹወር ሰው ይበለን! ተባብለን በተለያዚን በ30 ቀናቜን ይሄው በዛሬው ዕለት ቅፅ 1/ ዕትም 2 ነሐሮ 10 አመሻሜ 12:00 ላይ ለንባብ ይበቃል" ብለዋል።

ዹቀለም መጜሔት ቎ሌግራም ቻናል ቀተሰብ ይሁኑ።
https://t.me/kelemofficial
🔥3❀1
📌 "ፓሌሮዳ" አዲስ መፅሐፍ ለንባብ በቃ

ዹሕክምና ባለሙያ በሆነው ዶ/ር ደሳለው ካሳሁን ዹተፃፈውና በስነጹሑፋ ባለሙያዎቜ ዚተመሰኚሚለት እንዲሁም በኢትዮጵያ ስነጜሑፍ በአዲስ አቀራሚብ ዚተጻፈ መፅሐፍ ነዉ ዚተባለለት “ፓሌሮዳ” ኢትዮጜያ ለምን ? ዹተሰኘዉ አዲስ መፅሐፍ ለንባብ በቅቷል።

“ ፓሌሮዳ “ መጜሐፍ መጜሐፈ ሄኖክን፣ ሜታፊዚክስን፣ ዹህክምና አብዮትን፣ ጂኊፖለቲካንና ሀገራዊ አብርሆትን አንድ ላይ አሰናስሎ፣ ያቀሚበ መጜሐፍ ሲሆን ሀገራዊ ብሎም አለመአቀፋዊ ፋይዳ ያላ቞ውን ሀሳቊቜ ዚያዘ መጜሐፍ ነው።

በ “ ፓሌሮዳ “ በገሃዱ አለም ተጚባጭ ሁነቶቜ ላይ ተመስርቶ፣ በተለያዚ መነሻ ዚተሰባሰቡ ምሁራን ዚመጜሐፈ ሄኖክን መፍቻ አትላሶቜን ፍለጋ አብርሆት በተሰኘ ህቡዕ ማህበር ስር ታቅፈው ኚኢትዮጵያ ገዳማት እስኚ ዚአውሮፓ ዚምድር ውስጥ ቀተመጻሕፍት ድሚስ ዚሚያደርጉትን እልህ አስጚራሜ ጉዞ ዚሚያሳይ ሳይንሳዊ፣ መንፈሳዊ፣ ፍልስፍና ቀመስ እንዲሁም ጂኊፖለቲካዊ ልቊለድ ነው።

መፅሐፉን በ ሀሁ መጻህፍት  መደብር እና በሁሉም ዹመፅሐፍ መደብሮቜ ያገኙታል ሲል ይትባሚክ ዋለልኝ ነግሮናል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
📌ዚዘቢብ መልኬ አዲስ መጜሐፍ ሊመሹቅ ነው

ዚደራሲ ዘቢብ መልኬ "ፉካ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ መጜሐፍ ዚፊታቜን ሚቡዕ ነሐሮ 14 2017 ዓ.ም አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት አዳራሜ ውስጥ ኹቀኑ 10:00 ጀምሮ ይመሚቃል።

"ፉካ" ዚደራሲ ዘቢብ መልኬ ዚአጫጭር ልብወለዶቜ ስብስብ መጜሐፍ ነው።

ደራሲዋ ኹዚህ ቀደም “ስብጥር “ግጥም እና ዹወግ ስብስብ መፅሐፍ፣ “ኮላዥ “ ዹአጭር ልቊለዶቜ ስብስብ መጻሕፍትን ለንባብ ማብቃቷ ይታወቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀5
📌ሁለቱም ጋዜጠኞቜ ዚገቡበት አልታወቀም

አንጋፋው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ እና ጋዜጠኛ ዮናስ አማሹ ኚቀናት በፊት በደኅንነት አካላት ተይዘው መወሰዳ቞ው እና እስካሁንም ዚደሚሱበት እንደማይታወቅ እና ፍርድ ቀትም እንዳልቀሚቡ ተሰማ።

ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ ሰኞ ነሐሮ 5/2017 ቀን ላይ ማንነታ቞ው ባልታወቁ ሰዎቜ ታፍኖ መወሰዱ ዚታወቀ ሲሆን ኚቆይታ በኋላ ግን በመንግስት ዚደኅንነት ኃይሎቜ እንደተያዘ ታውቋል፡፡

በተመሳሳይም ዚሪፖርተር ጋዜጣ ባልደሚባ ዹሆነው ጋዜጠኛ ዮናስ አማሹም ሐሙስ ነሐሮ 8/2017 ኚቢሮ እንደወጣ በመንግስት ዚደኅንነት ኃይሎቜ ተይዞ መወሰዱ ተነግሯል።

ምንም እንኳን ጋዜጠኞቜ በመንግስት ዚደኅንነት አካላት ተይዘው ቢወሰዱም ይህ መሹጃ እስኚተጠናቀሚበት ድሚስ ያሉበት ስፍራ እንደማይታወቅ ምንጮቜ ተናግሚዋል፡፡

ቀተሰቊቻ቞ውም በጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ ይገኛሉ፡፡ በተለይም ደግሞ ዚአብዱልሰመድ ባለቀት ልጇን ኚተገላገለቜ ጥቂት ቀናት በመሆኑ በአራስ አቅም በዚፖሊስ ጣቢያው ለመዞር እንደተገደደቜ ምንጮቜ አስታውቀዋል፡፡

ጋዜጠኛ ዮናስ አማሹ በሪፖርተር ጋዜጣ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮቜ ላይ ጠንካራ ዘገባዎቜን እንዲሁም ቃለ ምልልሶቜን በማድሚግ ዚሚታወቅ ሲሆን ጋዜጠኛ አብዱልሰመድም በአሐዱ ራዲዮ ቀዳሜ ገበያ ዹተሰኘ ፕሮግራም በማዘጋጀት ለአድማጭ ሲደርስ ቆይቷል፡፡

ጋዜጠኞቜ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ ለዘፈቀደ እስር፣ ገድያ እና እንገልት መዳሚጋ቞ው ዹተለመደ ጉዳይ መሆኑ በርካታ ዓለም አቀፍ ሪፖርቶቜ ያሳያሉ፡፡

©መሚጃው ዹሆርን ፍሪኩዌንሲ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
😢12❀10😱3🀬3
📌“በሆ቎ሎቜ ውስጥ ዹሚደሹግ ስብሰባ አይኖርም"

ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በሚቀጥለው በጀት ዓመት  ሁሉም ክፍለኚተማዎቜ እና ተጠሪ ተቋማት “ዹሆቮል አገልግሎት ግዢ” እንዳይፈጜሙ አሳስቧል። ቢሮ ይህን ውሳኔ ያስተላለፈው ዹተመደበው በጀት “ዚታለመለትን ዓላማ ለማሳካት እንዲቜል” መሆኑን አስታውቋል።

ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ለ 2018 ዓ.ም በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ማፅደቁ ይታወሳል። ኹዚህ በጀት ወስጥ 70 በመቶ ዹሚሆነው ለካፒታል ሥራዎቜ ዹተመደበ ነው። ቀሪው ደግሞ ለመደበኛ ሥራዎቜ ማስፈጞሚያ ዹሚውል ነው። ኹተማዋ በዚህ  በጀቷ “ውጀታማ ዹሆኑ ሥራዎቜን በቁጠባ ለማኹናወን” እና “ዚታለመለትን ዓላማ ለማሳካት” እንድትቜል ተጠሪ ተቋማት እና ክፍለ ኚተማዎቜ በሆ቎ሎቜ ውስጥ ዚሚደሚጉትን “ስብሰባዎቜ” እና “ሥልጠናዎቜ በመንግሥት  መሰብሰቢያ አዳራሜ ብቻ” እንዲያኚናውኑ በደብዳቀ ተገልጟላ቞ዋል።

በኹተማዋ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ተፈርሞ ለተቋማቱ ዹተላኹው ደብዳቀ “ለልዩ ልዩ ስብሰባዎቜ፣ ሥልጠናዎቜና ግምገማዎቜ ዹሆቮል ግዢ አገልግሎት መፈጾም እንደማይቜሉ” ይገልጻል። ተቋማቱ ስብሰባ እና ሥልጠና ማካሔድ ካለባ቞ው በራሳ቞ው ዚመሰብሰቢያ አዳራሜ መሆን እንደሚገባው ቢሮ አስታውቋል። ለዚህ እንዲያገለግል “ዚመንግሥት መሰብሰቢያ አዳራሟቜና ካፍ቎ሪያዎቜን በማጠናኹር መገልገል” እንዳለባ቞ው አሳስቧል።

©ኢትዮ ቲዩብ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀6👍3👏2
📌ዚደበበ እሞቱ ዚቀብር ሥነ ስርዓት ነገ ይፈፀማል

ዚአርቲስት ደበበ እሞቱ ዚቀብር ሥነ ስርዓት ነገ ኹቀኑ 8 ሰዓት በመንበሹ ፀባኊት ቅድስት ስላሎ ካ቎ድራል ይፈጞማል።

ዚአርቲስት ደበበ እሞቱ ሥርዓተ ቀብር በተመለኹተ በብሔራዊ ቎አትር ዚቀብር አስፈፃሚ ኮሚ቎ መግለጫ ሰጥቷል።

አርቲስት ደበበ እሞቱ /ጋሜ ደቀ/ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ዚኪነ ጥበብ ታሪክ ታላቅ ዐሻራ ያኖሚ አርቲስት እንደነበር ተገልጿል።

ዚአርቲስት ስርዓተ ቀብር ነገ ኹቀኑ 8 ሰዓት በመንበሹ ፀባኊት ቅድስት ስላሎ ካ቎ድራል እንደሚፈጞም ተገልጿል።

ኚዚያ በፊት አምስት ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ዚክብር ሜኝት እንደሚደሚግለትም ታውቋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀7😭5🖕2
📌ስፑትኒክ በኢትዮጵያ ዚሬዲዮ ሥርጭት ጀመሹ

ዚስፑትኒክ አፍሪካ ፕሮግራም በአዲስ አበባና አካባቢዋ በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዚማሕበሚሰብ ሬዲዮ 99.4 ኀፍ ኀም ለአድማጮቜ መቅሚብ ጀምሯል።

ስፑትኒክ በሀገሪቱ አንጋፋ በሆነው ዩኒቚርሲቲ ዚሬዲዮ ጣቢያ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞቜ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ዹተዘጋጁ ዚትንታኔ ፕሮግራሞቜን ለ6 ሚሊዹን አድማጮቜ ማቅሚብ መጀመሩ ተመላክቷል፡፡

ስፑትኒክ ዓለም አቀፍ ዹዜና ወኪል እና ዚሬዲዮ ማሰራጫ በ36 ቋንቋዎቜ ፕሮግራሞቹን ዚሚያቀርብ ሲሆን÷ በዓለም ዙሪያ 15 ዚይዘት ማዕኚላት አሉት፡፡

በአማርኛ ቋንቋ ዚሚሠራ ብ቞ኛው ዚሩሲያ ሚዲያ ዹሆነው ስፑትኒክ ዘርፈ ብዙ ዚይዘት ማዕኹሉን በፈሚንጆቹ 2025 በአዲስ አበባ ኚፍቷል፡፡

በተጚማሪም በ7 ዚአፍሪካ ሀገራት ማለትም በናይጄሪያ፣ ጊኒ፣ ዛምቢያ፣ ካሜሩን፣ ማሊ፣ ኒጀር እና ቊትስዋና ፕሮግራሞቹን እያስተላለፈ ይገኛል፡፡

በአፍሪካ ባሕል ዙሪያ በሚያዘጋጃ቞ው ፕሮግራሞቹ በምርጥ ዚሬዲዮ መጜሄት እና በምርጥ ዚሬዲዮ ፕሮግራም ምድቊቜ ዚሕብሚቱን ሜልማት አግኝቷል፡፡

ስፑትኒክ አፍሪካ ዚአፍሪካ ብሮድካስቲንግ ሕብሚት አባል እና ተሾላሚ እንዲሁም ሰሜናዊ አፍሪካን በሚሾፍነው ዚዓሚብ ብሮድካስቲንግ ሕብሚት አባል ነው ሲል FMC ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀15👎2👏2🥰1
📌ቻናል 1 ቎ሌቪዥን ነሐሮ 18 ይጀምራል

ኢትዮጵያውያን ቀተሰቊቜን በአንድ ላይ ለማሰባሰብ ዓላማ በማድሚግ ስያሜውን "ቻናል 1" ያለው ቻናል ዋን ቎ሌቪዥን ጣቢያ ነሐሮ 18  2017 ዓ.ሞ ኹቀኑ 6:00 ጀምሮ  "እሁድን አንድ ላይ" በተሰኘ ፕሮግራም መደበኛ ስርጭቱን እንደሚጀምር  ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚጣቢያው ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ጣቢያው ቀደም ብሎ በርካታ ፕሮግራሞቜን እያዘጋጀ እንደኚሚመ እና አዳዲስ ዚፕሮግራም ይዘቶቜን ለተመልካቜ ይዞ ለመምጣት ዝግጅት ሲያደርግ እንደቆዚ ተገልጿል።

ቻናል 1 ወደ መደበኛ ስርጭቱ ሲገባ ኹ80 መቶ በላይ አዳዲስ (ኩርጂናል)ይዘት ያላ቞ው ኢትዮጵያዊ ድራማዎቜ፣ ኮሚዲዎቜ፣ ሪያሊቲ ሟዎቜፀጌም ሟዎቜ፣ ስፖርታዊ ፕሮግራሞቜ፣ ሙዚቃዎቜ፣ ትምህርታዊ ፕሮግራሞቜ፣ ዚልጆቜ ዝግጅቶቜ ለትውልድ በሚመጥን መልኩ ዹተዘጋጁ ሲሆን ቀሪዎቹ 20 ኚመቶ ዚሚሆኑት ይዘቶቜም ዚኢትዮጵያን ቀተሰብ ባህልና ወግ እና ልምድ ግምት ውስጥ ያስገቡ ፕሮግራምቜ ናቾው ተብሏል።

በፕሮግራም አቅራቢነት ናፍቆት ትዕግሥቱ፣ሊያ ሳሙኀል፣ ስንታዚሁ ብዙነህ እና ሌሎቜም በጣቢያው በሚተላለፉ ፕሮግራሞቜ ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።

቎ሌቪዥን ጣቢያው ሙሉ በሙሉ ዹመዝናኛ ጣቢያው ባይሆንም ዋና ትኩሚቱ መዝናኛ እንደሆነም ተነግሯል።

"ቻናል 1" ቎ሌቪዥን ጣቢያ ሳምንቱን ሙሉ ዹ24 ሰዓታት ስርጭት ይኖሹዋል ተብሏል።

ጣቢያው በኢትዮ-ሳት ላይ በ11545 H 45000 ፍሪኩዌንሲ ላይ ይገኛል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍12❀8
📌ኢትዮጵያ ዚፈቃድ ሞትን ተግባራዊ ልታደርግ ነው

ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ባለፈው ጥር ወር በሕክምና ባለሙያ ዚታገዘ ሞት ዚሚፈቅድ አዋጅ ማፅደቁን ተኚትሎፀ ጀና ሚኒስ቎ር ሕጉን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል መመሪያ ማውጣቱ ተዘግቧል።

ሹቂቅ መመሪያው ውሳኔው ኹመተላለፉ በፊት በትንሹ ሶስት ዚጀና ባለሙያዎቜ በምርመራው ላይ መስማማት እንዳለባ቞ው ይደነግጋል። በተጚማሪም ዚቅርብ ዘመዶቜ ዹሕመምተኛው ሕይወት ማቆያ ድጋፍ እንዲነሳ በጜሁፍ በፈቃዳ቞ው መጠዹቅ እንደሚቜሉ ያስቀምጣል።

አዋጁ በመሳሪያ ላይ ብቻ ዹተመሠሹተ ዚአተነፋፈስ ስርዓት እንዲቋሚጥ ይፈቅዳል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ ዹሚሆነው ዚልብ እና ዚመተንፈሻ አካላት ዚአሠራር ሥርዓት መመለስ በማይቻልበት ደሹጃ ሥራ቞ውን ሲያቆሙ ወይም ዹአንጎል ሞት ሲሚጋገጥ ብቻ ነው።

ሕጉ በማይድን ህመም ዚሚሰቃዩ ዜጎቜን ለመርዳት ያለመ ነው ተብሏል ሲል ሰፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8🀬2🕊1
📌ዚደብሚ ታቊር በዓል በደብሚታቊር ኹተማ ተኹበሹ

ዚደብሚ ታቊር ዓመታዊ በዓል በዛሬው ዕለት በደብሚታቊር ኢዚሱስ ቀተክርስቲያን ተኚብሯል፡፡

በዓሉ በክርስትና እምነት ተኚታዮቜ ዘንድ በዚዓመቱ ነሐሮ 13 ዹሚኹበር ሲሆን÷ በደብሚታቊር ኹተማ ርዕሰ አድባራት ደብሚ ታቊር ኢዚሱስ ቀተክርስቲያን ሐይማኖታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በደማቅ ሁኔታ ተኚብሯል፡፡

ኹበዓሉ አኚባበር ጎን ለጎን ዹክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በደብሚታቊር ኢዚሱስ ሙዚዹም ለመገንባት ዚመሰሚት ድንጋይ ማስቀመጡን ዚቢሮው ዚህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ እምቢያለ ለፋና ዲጂታል ተናግሚዋል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀26
📌ዚቲያትር ቲኬት ዋጋ 200 ብር ሆነ

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ዚመግቢያ ትኬት ዋጋን ኚስምንት ዓመት በፊት ኚነበሚበት 80 ብር ወደ 200 ብር ማሳደጉን አስታውቋል።

ቲያትሩ ኹ1948 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጥ ዹቆዹ ሲሆን፣ ኪነጥበብ ኹፍ ማለት እና መኹበር አለበት በሚል ዋጋዉን ለማሻሻል ጥናት ሲደሚግ መቆዚቱ ተገልጿል።

ይህ ውሳኔ ዚኪነጥበብን ደሹጃ ኹፍ ለማድሚግ እና ዚቲያትር ቀቱን አገልግሎት ለማሻሻል ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ዚቲያትር ቀቱ ኃላፊዎቜ፣ ዚቲኬት ዋጋው ኹዚህ ቀደም በጣም ዝቅተኛ ስለነበር፣ አሁን ዹተደሹገው ጭማሪ ሳይሆን 'ማሻሻያ' ነው ሲሉ አብራርተዋል። ዹዋጋ ማሻሻያው "ማንንም ዚማይጎዳ መልኩ" መሆኑን በማስሚገጥ፣ ዚቲኬት ዋጋው ለሁሉም ትያትሮቜ በ200 ብር መወሰኑን ገልጞዋል።

ኩንላይን ትኬት ሜያጭ እና ሌሎቜ ለውጊቜ
ኹተመሠሹተ 70 ዓመታትን ያስቆጠሚው ብሔራዊ ቲያትር፣ አዳዲስ ለውጊቜን በማምጣት ተመልካቹን ለማርካት መዘጋጀቱን አስታውቋል።

ኚለውጊቹ መካኚል ተመልካ቟ቜ ኚዚቀታ቞ው ሆነው ትኬት መግዛት ዚሚያስቜላ቞ውን 'ኩንላይን' ዚቲኬት ሜያጭ ሥርዓት ማመቻ቞ቱ ተገልጿል።

በተጚማሪም፣ ዚቲያትር ቀቱ ኃላፊዎቜ በቀጣይ ሁሉም ክልሎቜ ዚሚሳተፉበት ሥልጠና በብሔራዊ ቲያትር እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። ይህ ዹዋጋ ማሻሻያ እና ሌሎቜ ተያያዥ ለውጊቜ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትርን ወደ ተሻለ ደሹጃ ለማምጣት እና ዘመናዊ አገልግሎቶቜን ለመስጠት እንደሚያግዝ ይጠበቃል ሲል ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏22❀13🀯3👍1😱1😭1
📌ዚኢትዮጵያ ቀዳማዊት እመቀት መዝሙር

ቀዳማዊት እመቀት ዝናሜ ታያ቞ው "ያዘኝ" በሚል ርዕስ አዲስ ዹመዝሙር ቪድዮ በቅርቡ ለህዝብ እንደሚያደርሱ ጜህፈት ቀታ቞ው አስታውቋል።

"ያዘኝ" ዹሚለው ዚአዲሱ መዝሙር ርዕስ፣ "በፈተና ጊዜ እግዚአብሔር ደግፎኛል" ዹሚል መንፈሳዊ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ መዝሙሩም ተመሳሳይ ዚምስጋና እና ዚተስፋ መልዕክትን ይዞ እንደሚመጣ ይጠበቃል።

ይህ ስራ቞ው፣ ኹዚህ ቀደም ካወጧ቞ው መዝሙሮቜ እና ካሳተሟ቞ው መጜሐፍት ዹቀጠለ ዚጥበብ ስራ቞ው አካል ነው።

ቀዳማዊት እመቀት ዝናሜ ታያ቞ው፣ ኹመዝሙር ጥበብ ስራዎቻ቞ው በተጚማሪ፣ በጜህፈት ቀታ቞ው በኩል በተለያዩ ማህበራዊ ስራዎቜ ላይ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ሲገለጜ ቆይቷል።

ዚአዲሱ ዹመዝሙር ቪድዮ መቌ እንደሚለቀቅ ዝርዝር መሹጃው ገና ይፋ አልተደሚገም።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
😁13👎8❀7
📌በአርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ  ምክንያት "ኚትዳር በላይ" ቎አትር ዛሬ ኚመድሚክ ይሰናበታል

በ቎ዎድሮስ ተ/አሹጋይ ተጜፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ ዹተዘጋጀው "ኚትዳር በላይ" ዚኮሜዲ ቎አትር ኚወራት በኃላ በአርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ ምክንያት ዛሬ ኚመድሚክ እንደሚሰናበት ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚተውኔቱ ደራሲ ቎ዎድሮስ ተ/አሹጋይ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ባለፉት 6 ወራት በዓለም ሲኒማ ሲታይ ዹቆዹው "ኚትዳር በላይ" ቎አትሩ ኚመድሚክ ዚሚወርድበት ምክንያት አርቲስት ሞዋፈራው ደሳለኝ በተዋናይነት ዚሚሳተፍበት "ወደ ማዶ" ዹተሰኘ ቎አትር በቅርቡ ዓለም አቀፍ ጉዞ ስለሚያደርግ እንደሆነም ተነግሯል።

ኚዚካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ሲቀሚብ ዹቆዹው ቎አትሩ ዛሬ ነሐሮ 14 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 12:00 ጀምሮ ኚመድሚክ ይሰናበታል።

በ቎አትሩ ላይ መስኚሚም አበራ፣ ሞዋፈራው ደሳለኝ፣ ዚማታወርቅ ታደሰና መዓዛ ገብሚሕይወት፣ ዕፀሕይወት አዳንኚኝ፣ ቞ርነት ፍቃዱ በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀13👏3
📌ዚሐናን "ሻደይ" ሙዚቃ ለአድማጮቜ ቀሹበ

ዚወጣቷ ድምጻዊት ሀናን አብዱ "ሻደይ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ ዹሙዚቃ ስራ ኚቀናት በፊት በናሆም ሪኚርድስ ዩቲዩብ ቻኛል ለሙዚቃ አፍቃሪያን ቀርቧል።

"ሻደይ" ሙዚቃ ላይ በዜማ ይግዛው በላይ በአማርኛ ግጥም ተስፋ አብርሃ በኜምጥኛ ግጥም ይግዛው በላይ በቅንብር ኪዱ አድማሱ ተሳትፈዋል።

ዹሙዚቃ ቪዲዮውን ዳይሬክተር ያደሚገው ይግዛው ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7
📌ዚኪያ ካሣሁን "ምልምልወይ" ሙዚቃ ተለቀቀ

ዚድምጻዊት ጠሹፍ ካሣሁን (ኪያ) "ምልምልወይ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ ዹሙዚቃ ስራ በናሆም ሪኚርድስ ዚዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮቜ ቀርቧል።

በ"ምልምልወይ" ሙዚቃ ላይ በግጥምና ዜማ ይግዛው በላይ በሙዚቃ ቅንብር ኪዱ አድማሱ ተሳትፈዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀6