Event Addis Media
9.63K subscribers
6.08K photos
12 videos
4 files
4.7K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ዓለም ሲኒማ ሁለተኛ ሲኒማ ቤት ሊከፈት ነው

ለዓመታት የፊልምና ቴአትር ስራዎችን ለታዳሚያን እያቀረበ የቆየው ዓለም ሲኒማ ሁለተኛ ቅርንጫፉን ወደ አገልግሎት ሊያስገባ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ቦሌው ከሚገኘው ሲኒማ ቤቱ ባሻገር  “ዓለም ሲኒማ በመገናኛ " ተብሎ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው ማራቶን ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ ላይ አገልግሎት እንደሚሰጥም ሰምተናል።

የመገናኛው ሲኒማ ቤቱም የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 26 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ በድምቀት ይመረቃል ተብሏል።

ዓለም ሲኒማ ሁለተኛ ቅርጫፉን ሲከፈት በአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎት ላይ ካሉ ሲኒማ ቤቶች ሁለት ቅርንጫፎች ያለሁት ብቸኛው ሲኒማ ቤት ያደርገዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍4
📌የዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በሦስት ቋንቋዎች ዛሬ ይመረቃሉ፡፡

📖  ኒዩሮ ሳይንስ ለሥራ ፈጠራ (ቅጽ ፩)
Neuro Entrepreneur (Vo.1)

📖  የኒዩሮ አመራር ሳይንስ (ቅጽ ፪)
Neuro Leadership Science (Vo.2)

📖  SAAYINSIFII NIWUROO FII HOJII UUMUU

በአማርኛ፣ በኦሮምኛና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅተዋል፡፡

እነዚህ መጻሕፍት በተለይም በወጣቶች ዘንድ የሥራ ፈጠራ መንፈስን በማነሳሳትና የአመራር ብቃትን በማጎልበት ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ።

📆  አርብ፣ ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም.
⌚️ ከቀኑ 10:00 ሰዓት (በኢትዮጵያ ሰዓት)
📍በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ራስ መኮንን አዳራሽ (ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት)፣ 6ኪሎ ይመረቃል።

በእለቱ
የመጽሐፉ ገምጋሚዎች

👉 ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል
👉 ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ
👉 ዶ/ር እንዳለጌታ ከበደ
👉 ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ
👉 ጋዜጠኛ ሡልጣን መሐመድ ኑር

ወግ አቅራቢ
👉 በኃይሉ ገብረመድህን

የነጻ ሐሳብ ቅምሻ
📌 ደራሲ ዓለማየሁ ገላጋይ
📌 ዶ/ር ኤርሲዶ ሌንዶቦ
📌 ኢንጂነር ጌታሁን ሄራሞ
📌 ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጃዋሬ

በስራ አመራር እና በስራ ፈጠራ
📌 ኢ/ር ቤጃይ ናይርሽ ናይከር
📌 ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብ

ቅምሻ

👉 አበበ ባልቻ
👉 ሀረገወይን አሰፋ
👉 ተፈሪ አለሙ
👉 ሙሉዓለም ታደሰ
👉 አንዱዓለም ተስፋዬ

መድረክ አጋፋሪ

📌 ደራሲና ጋዜጠኛ  አዜብ ወርቁ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
8
📌የገጣሚ ጋሻው የኋላሸት /ዘቢደር/ ''ሕይወት እንደ መንገድ'' የተሰኘው አዲስ የግጥም መድብል ተመረቀ

መጽሐፉ በ120 ገፅ የቀረበ ሲሆን  60 ያህል ግጥሞችን ያካተተ ነው።

ግጥሞቹ ለውበት ያደሉ :በቅርጽ እና በቃላት አጠቃቀማቸውም መንፈስን የሚያረኩ ናቸው።

ገጣሚ ጋሻው የኋላሸት ከዚህ ቀደም በአለላ መጽሔት በምክትል አዘጋጅነትና በአምደኝነት ሰርቷል። እንዲሁም በዓባይ ቴሌቪዥንም በፕሮዲዩሰርነት አገልግሏል።

ጋሻው/ዘቢደር/ ከልጅነት ዕድሜው ጀምሮ በስነ-ጹሑፍ ዘርፍ ሰፊ ጊዜውን ያሳለፈ ነው።

በራያ አለማጣ አርብ ምሽት የስነ-ጹሑፍ ክበብ እንዲሁም በራያ ዋጃ-ጥሙጋ ሀይስኩል የኪነ-ጥበብ ተሳትፎው የጎላ ነበር።

ከዚህ ቀደም "የነፍስ እኩያሞች" በተሰኘ የ11 ደራሲያን ስብስብ ልብ-ወለድ መጽሐፍ ላይ ሁለት አጫጭር የልብ ወለድ ስራዎቹ የተካተቱለት ደራሲ ነው።

ወደ ፊትም የህትመት ጊዚያቸውን የሚጠብቁ የረዥም እና የአጫጭር ልብ ወለድ መጽሐፍትም አጠናቋል።

''ሕይወት እንደ መንገድ'' የተሰኘው  የግጥም መድብል ዛሬ ሐምሌ 25 በዋልያ መፅሐፍ ገጣሚያን : ደራሲያንና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች በተገኙበት ተመርቋል።

መጽሐፉን ለገሀር አካባቢ በሚገኙ በጃዕፋርና በሌሎች የመፃሕፍቶ መደብሮች እንዲሁም 6ኪሎ በሚገኘው ኦሮማይ የመጽሐፍ መደብር ያገኙታል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
5🥰4
📌ድምጻዊ ይሁኔ በላይ እውቅና ሊሰጠው ነው

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ለታዋቂው የባሕል ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ይሁኔ በላይ "ለኢትዮጵያ የባሕል ሙዚቃ ጥበብ እድገት ላበረከተው አስተዋጽኦ" የእውቅና ሽልማት (Recognition Certification Award ) ይሰጣል።

ይሁኔ በላይ በነገው ዕለት በግለታሪኩ ዙሪያ ጽፎ ለንባብ ያበቃውን መጽሐፍ ለማስመረቅና የእውቅና ሽልማቱን ለመቀበል ዛሬ ረፋድ ውቢቷ ባሕር ዳር ገብቷል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
9👏3👍1
📌መዓዛ ወርቁ እንግዳ የሆነችበት ልዩ ዝግጅት የፊታችን ሰኞ በአሜሪካ ኤምባሲ ሊካሄድ ነው

(መግቢያው በነፃ ነው)

የCreator lab ዝግጅት አዘጋጆች የቴያትር  እና የፊልም ደራሲ እና አዘጋጅ  የሆነችው  መዓዛ ወርቁን በእንግድነት ጋብዘዋል።

በዚህ ዝግጅት ላይ ስለድርሰት እና ዝግጅት እንዲሁም የራሷን የሕይወት ተሞክሮ ለእናንተ ታካፍላለች። ስለሆነም በዚህ መድረክ ላይ እንዲታደሙ በአክብሮት ተጋብዘዋል።

ደራሲ እና አዘጋጅ  የመሆን ፍላጎት ያላችሁ፤ እንዲሁም በሙያው ላይ ልምድ ያላችሁ ባለሙያዎች በሙሉ ይህ የመገናኛና ዕድል ለእናንተ ነው።


📍አድራሻ ፡ አሜሪካን ኤምባሲ ቅጥር ግቢ (ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ )

📅 ቀን: ሰኞ ሀምሌ 28 ፣ 2017 ዓ.ም

🕗 ሰዓት: ከቀኑ - 8:00 

🎟 መግቢያ: በነፃ

አቅራቢ፦ፕሪስቴጅ አዲስ ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር በመተባበር

በፕሮግራሙ ላይ ለመሳተፍ ኢንስታግራም ገፃችንን ፎሎ ማድረግ እንዳይረሱ

📎 በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://jazzio.land/register
የፕሪስቴጅ ዐባል ለመሆን ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://forms.gle/ekHY5ez8AWm3uwvUA


ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
5
📌"ኪሳራም ሥራ ነው" የተሰኘ መጽሐፍ ተመረቀ

የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ባለሙያው ከፈለኝ ሐይሉ ያሳተሙት "የቢዝነስ ሀሁ በኢትዮጵያ "ኪሳራም ሥራ ነው" የተሰኘ መጽሐፍ በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት አገልግሎት (ወመዘክር) በይፋ ተመርቋል።

በኢትዮጵያ ያለው የንግድ ስርዓት በዘርፉ ለተሰማሩ የንግድ አካላት በአሳሪ ቢሮክራሲና በሌሎች ምክንያቶች መታሰሩ፤ ንግድ በኢትዮጵያ እድገቱ በታሰበው ልክ እንዳይሆን አድርጎታል።

የኢትዮጵያ የንግድ ስርዓት ንግድ በማያውቁ የመንግስት ሃላፊዎች መመራቱ ዘርፉ በሚገባው ልክ እንዳያድግ ስለማድረጉ በመጽሐፉ ዙሪያ ውይይት በተደረገበት በዚሁ መድረክ ላይ ተነግሯል።

በውይይቱ የተለያዩ የፋይናንስ እና ቢዝነስ ባለሙያዎች፣ ኢንተርፕርነሮች እና በርካታ ታዳሚዎች የተገኙ ሲሆን፤ መፀሐፉ ውስጥ በተመረጡ ሃሳቦች ዙሪያ ሙያዊ እይታቸውን አጋርተዋል።

የንግድ ስርዓት፣ የፋይናንስ ፍሰት እና የግብር ስርዓት በኢትዮጵያ ያለው መልክ ከሳይንሱ እና አጠቃላይ የዘፈቀደ  አካሄዶች ያላቸው መልክ ምን ይመስላል የሚለው ተዳሶበታል።

@አሐዱ ሬድዮ

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
8👍1🥰1
📌የአራዳ ፖስታ ቤት ህንጻ የፈጠራ ማዕከል ሆነ

ፒያሳ አካባቢ የሚገኘው እና “አራዳ ፖስታ ቤት” እየተባለ የሚጠራው ታሪካዊው የኢትዮ ፖስታ ህንጻ፣ ወጣቶችን ለማሳተፍ እና ፈጠራን ለማነቃቃት ወደሚያስችል የፈጠራ ማዕከልነት መቀየሩ ተሰምቷል።

ይህ ታሪካዊ ህንጻ፣ ወደ 1900ዎቹ የሚጠጋ ታሪክ ያለው ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዘመናዊ ፖስታ ቤት ነበር። አሁን ደግሞ የከተማ ልማት ፍላጎት እና አዲስ ቦታን ለመጠቀም በሚደረገው ጥረት፣ "Creative Hub Ethiopia" የተሰኘው ድርጅት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የቦታውን አስተዳደር በመረከብ የፈጠራ ኢንዱስትሪዎችን እና ተግባራትን እያስተዋወቀ መሆኑ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

የዚህ ማዕከል ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በወጣቶች በሚመራው የፈጠራ ዘርፍ ማሳደግ እንደሆነ ተገልጿል።

©️ Capital

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
9😢6👎1
📌በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት በዚህ ሳምንት እነዚህ ተውኔቶች ለተውኔት አፍቃሪን ይቀርባሉ።

    መልካም መዝናኛ ይሁንላችሁ !!

https://t.me/EventAddis1/6236
👍84
📌 "እንዳለሁ አበራለሁ" መጽሐፍ ሐሙስ ይመረቃል

በደራሲ ማክዳ አርሺ ተጽፎ፣ በታዋቂው ደራሲና ገጣሚ በውብ አማርኛ በግጥም የተቀናበረው፣ ስለ ኦቲዝም ግንዛቤን የሚያስጨብጠው "እንዳለሁ አበራለሁ" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ሐሙስ ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ግቢ ውስጥ ይመረቃል።

ስለ ኦቲዝም ያለንን ግንዛቤ በጋራ በምናሳድግበት በዚህ ልዩ መድረክ ላይ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
3
📌መቅረዝ ሥነኪን ሐሙስ ይካሄዳል

መቅረዝ ሥነኪን ወርሀዊ የኪነጥበብ ዝግጅት ሐሙስ ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር )አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

በዚህ ዝግጅት ላይ አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ የክብር እንግዳ በመሆን የምትገኝ ሲሆን በተጨማሪም ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎች የግጥም ፣የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።የዚህ ዝግጅት መግቢያ በነፃ ነው።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
1🥰1
📌"የወዲያነሽ" መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል

በአንጋፋው ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል የተዘጋጀውና በቅርቡ በድጋሚ የታተመው "የወዲያነሽ"መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 3 ቀን 2017 ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) ይመረቃል።

ወዳጆቹና አክባሪዎቹ በሚገኙበት በልዩ መርሐግብር ላይ እንድትገኙ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍127
📌ደራሲ ደመወዝ ጎሽሜ እንግዳ የሆነበት መሰናዶ!

በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አዲስቱ እየሩሳሌም" የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት የመጽሐፉ ጸሐፊ ደመወዝ ጎሽሜ ይገኛል ተብሏል። የዝግጅቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍9👏4🙏21
📌አርቲስት ዘሪቱ ከበደ መጽሐፍ ጻፈች

በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ውስጥ በድምጻዊነቷ እንዲሁም በግጥምና ዜማ፣ በትወና ችሎታዋ ከፍተኛ ስምን ያተረፈችውና በኋላም ሙሉ ጊዜዋን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ወደ ዝማሬ ዓለም የገባችው አርቲስት ዘሪቱ ከበደ "ከልጅነት እስከ ልጁነት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው መጽሐፍ ጽፋለች።

በግል ታሪኳ ላይ የሚያጠነጥነው ይህ መጽሐፏ በቅርቡ ለአንባቢያን እንደሚቀርብ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከአርቲስቷ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
37👏7🔥4👎2
📌ጋዜጠኞቹ ደመወዝ እየተከፈላቸው አይደለም ተባለ

የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሠራተኞች ደመወዝ እየተከፈላቸው አለመሆኑንና መቸገራቸውን ተናገሩ።

በቀድሞው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ይተዳደር የነበረው ‹‹የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት››፣ ክልሉ ለአራት ከተከፋፈለ በኋላ፣ እያንዳንዳቸው ክልሎች የሚጠበቅባቸውን በጀት ባለመስጠታቸው፣ ቀናቶች ካለፉ በኋላ ይከፈላቸው የነበረው ደመወዝ ሙሉ በሙሉ መቆሙንና እየተቸገሩ መሆናቸውን የድርጅቱ ሠራተኞች ተናገሩ፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ያነጋገራቸውና ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የጣቢያው ሠራተኞች፣ ላለፉት ስድስት ወራት ደመወዛቸው በጊዜው እንደማይከፈላቸውና ወሩ ባለፈ በ15ኛው ቀን ይከፈላቸው የነበረ ቢሆንም፣ የሰኔ ወር ደመወዝም ግን ሙሉ በሙሉ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል፡፡

ከ400 በላይ ሠራተኞች ያሉት ድርጅቱ፣ አብዛኞቹ ሠራተኞች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ በመሆናቸው፣ በተለይም ከቤተሰቦቻቸው ርቀው የሚኖሩ በደመወዝ መዘግየት ምክንያት ከፍተኛ ጫና ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

‹‹የድርጅቱ ህልውና አደጋ ላይ ወድቋል›› የሚሉት ሠራተኞቹ፣ ለዚህም ወደ ሌሎች የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያዎች እየሄዱ መሆኑን በማሳያነት ይጠቅሳሉ፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የተቋሙ ተወካይ አቶ ዘለዓለም ገነሞ፣‹‹ድርጅቱ ችግር ውስጥም ሆኖ ቢዘገይም ሳይከፍል የቀረበት ጊዜ የለም››ሲሉ ተናግረዋል።

©️ሪፖርተር ጋዜጣ

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
7😢2
📌በርካቶች የተቀባበሉት ነጠላ ሙዚቃ

በድምጻዊት ሳምራት አዘነ የተቀነቀነው "አያ ጥራኝማ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው ነጠላ ሙዚቃ ዛሬ ነሐሴ 2 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ለአድማጮች ከተለቀቀ በኃላ ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በርካቶች እየተቀባበሉ ስለ ሙዚቃው እየጻፉ ይገኛሉ።

"አያ ጥራኝማ" ሙዚቃ ላይ በዜማ ይልቃል አስፋው፣ በግጥም እስጢፋኖስ መስፍን እንዲሁም በቅንብር ታምሩ አማረ ተሳትፈውበታል።

የሙዚቃ ቪዲዮውን ዮናስ ይታየው ዳይሬክት ያደረገው ሲሆን በዋሽንት ጣሰው ወንድም ተሳትፏል።

ድምጻዊት ሳምራዊት አዘነ የሙዚቃ ባለሞያ ስትሆን የኢትዮጵያን አይዶል ዳኛ እና የመረዋ ኳየር የሙዚቃ ቡድን አባል ነች።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
9👍3
📌አንጀሊና ጆሊ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታልን ጎበኙ

ዝነኛዋ አሜሪካዊት ተዋናይት ፣ የፊልም ባለሙያ እና የሰብአዊ ድጋፍ አቅራቢ የሆኑት አንጀሊና ጆሊ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

ተዋናይቷ ያደረጉት ጉብኝት በዋነኝነት ሆስፒታሉ እየሰጠ በሚገኘው መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና ዙሪያ እየተከናወኑ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ፣ የሚታዩ ለውጦችን እንዲሁም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ቦታዎች መለየት ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።

በጉብኝቱ ላይ አንጀሊና የሆስፒታሉን የቲቢና መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና አገልግሎት መስጫ ዋርድ ፣ ላብራቶሪ እንዲሁም ታካሚዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

አንጀሊና ወደ ሆስፒታሉ ከረጅም ጊዜያት በፊት መጥተው እንደነበር ያስታወሱ ሲሆን በአሁኑ ጉብኝታቸው ላይ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ለውጦች አምጥቶ በመመልከታቸው እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አክለውም ሆስፒታሉ ድጋፍ ቢደረግለት በቀጣይ የተሻለ
አገልግሎት ለታካሚዎች መስጠት በሚያስችለው አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንዳለ በጉብኝቱ ላይ መገንዘባቸውን ገልፀዋል።

በተጨማሪም በሆስፒታሉ በቲቢ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተገኘው እድገት በእጅጉ የሚደነቅ እና የሚያስተማምን ስለሆነ በቀጣይ በጂ.ኤች.ሲ (Global Health Committee (GHC)) በኩል ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም እሸቱ በበኩላቸው ቲቢን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ተዋናይቱ ላሳዩት ዘላቂ ቁርጠኝነት ፣ ልግስና እና በቀጣይ ለሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Via ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
19🤣8🥰1
📌‘ኢመርጅ’ የሥነጥበብ አውደርዕይ ተከፈተ

አስር ሁለት ሠዓሊያ እና የፊልም ባለሞያዎች ስራዎቻቸውን ያቀረቡበት "ኢመርጅ" ዘመናዊ የሥነጥበብ አውደርዕይ ነሐሴ 7 2017 ዓ.ም በገብረክርስቶስ  ደስታ ዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ በይፋ ተከፍቷል።

ይህ ‘ኢመርጅ’ ዘመናዊ የሥነጥበብ አውደርዕይ ለሁለት ዓመት በድህረ ምረቃ መርሀግብር፥ ከአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ት/ቤት በሥነጥበብ እና በፊልም ጥበብ ዘርፍ ትምህርታቸውን ተከታትለው በሰኔ 2017 ዓ.ም ያጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል የተመረጡ ስድስት ሠዓሊያንን እና ስድስት የፊልም ባለሙያዎችን የመመረቂያ ጥናታዊ የሥራ ውጤት ለሰፊው ህዝብ ለማሳየት በዘመናዊ የሥነጥበብ ሙዚየም - ገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል የተዘጋጀ ዐውደርዕይ ነው።

በዚህ ዐውደርእይ ላይ የቀረቡት ስራዎች ስለ: ማህበራዊ፣ ልማታዊ ለውጥና ተጽእኖው፣ ሥነጥበባዊ የአእምሮ ህክምና፣ ሶሻል ሚዲያና ተጽእኖው እንዲሁም ከሀገር እስከ ዓለም አቀፍ እየደረሰ ስላለው የተሳሰረ ኢፍትሀዊ ብዝሀ ችግሮች ዙሪያ የሚዳስሱ ርዕሰ ጉዳዮች በዘመናዊ የሥነጥበብ አውድ ቀርበዋል።

ተሳታፊ ሠዓሊዎች፦
አለማየሁ ዳርሰማ፣ ማስተዋል ጌታ፣ ሙሉአዳም አዳነ፣ ሰሎሜ ጌታቸው፣ ቴዎድሮስ ክፍሌ፣ ዮናስ ፍቃዱ

ተሳታፊ የፊልም ባለሙያዎች፦
አቢይ ጌታሁን፣ አብርሐም ባህሩ፣ ኤልሻዳይ ይልማ፣ ጌታሁን ግርማ፣ ሊዲያ ምትኩ፣ ታደሰ በቀለ

የማዕከሉ የእይታ ሰዓት፡ ከማክሰኞ - እሁድ ከጠዋት 4:00 ሰዓት - አመሻሽ 11:00 ሰዓት
ቦታ፡ 6 ኪሎ ምስካየ ሓዙናን መድሃኒያለም ገዳም ከፍተኛ ትምህርት ቤት ጎን በሚገኘው የንግድና ኢኮኖሚ ኮሌጅ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
4
📌ግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው

ግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት የፊታችን ነሐሴ 17 2017 ዓ.ም በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል እንደሚካሄድ የፕሮግራሙ አዘጋጅ Nethor events አስታውቋል።

በግራንድ ጮሮርሳ ኮንሰርት ታዋቂዎቹ ድምጻዊያን ሄለን በርሄ ፣ዮሳን ጌታሁን፣ሌንጮ ገመቹ፣ጌታቸው ኃይለማርያም፣አኒስ ጋቢ - ጆርጂ አቡ እና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎቻቸው ያቀርባሉ ተብሏል።

በዝግጅቱ ላይ በአፍሪካ ረጅሙ የጮርሮሳ ምግብ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ይመዘገባል ተብሏል።

የመግቢያ ክፍያ ቪአይፒ: 10,000 ቪቪአይፒ: 15,000 ብር ነው ተብሏል።

የኮንሰርቱ አዘጋጆች Nethor events እና Kenakon events ሲሆኑ "ይምጡ ባህሎቻችንን ይደግፉ እና ይደሰቱ" ብለዋል።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
5
📌የልጆች መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል የልጆች መጻሕፍት በኢትዮጵያ በተሰኘ ርዕስ የልምምድ ልውውጥና ሙያዊ ውይይት ይካሄዳል፡፡

ሙያዊ ውይይቱ የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 10 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ይካሄዳል።

የዕለቱ ተጋባዥ ከ120 በላይ መጻሕፍትን ለሕትመት ያበቃው የልጆች መጽሐፍ ደራሲ፣ ተርጓሚና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቀድሞ መምህር ዓለም እሸቱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ኑሮውን በሀገረ አሜሪካ አድርጓል፡፡

በዕለቱ የሥነ ጥበባት ማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ይታገሱ ጌትነት በኢትዮጵያ የልጆች መጻሕፍት ታሪክና ተግዳሮት ዙሪያ የመነሻ ጽሑፍ ያቀርባሉ፡፡

ይህ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ትብብር በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር አማካኝነት የሚሰናዳው የክረምት ወራት የሥነ ጽሑፍ ሥልጠና አንዱ አካል ሲሆን በዕለቱ በዘርፉ የተሰማሩ የልጆች መጽሐፍ ደራሲያንና ባለሙያዎችና ይሳተፋሉ፡፡

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
4
📌 የአንጋፋው ደራሲ ሳህለ ሥላሴ ብርሃነማርያም ልደት በልዩ ዝግጅት ዛሬ ይከበራል

ጥበበ መድሎት የጋዜጠኝነትና የኪነ ጥበብ ሰልጣኞች አንጋፋ የኢትዮጵያ የስነ ጽሁፍ ባለውለታዎችን ለመዘከር ቀጠሮ ይዟል።

የ''መከረኞቹ'' ፣ ''ያገር ልጅ'' እና ''ባሻ ቅጣውን የመሰሉ ዘመን ተሻጋሪ የስነ ጽሑፍ ስራዎችን ያጋሩንን ጋሽ ሳሕለሥላሴን እናከብራቸው ዘንድ እንድታጅቡን በክብር ጋበዝናችሁ።

📖 ደራሲና አርታኢ ሀይለመለኮት መዋዕል

📖 ጋዜጠኛ ግርማ ፍሰሃን

📖 ደራሲና ተርጓሚ ሳህለስላሴ ብርሃነማርያም

📖 ገጣሚት ባንቻየሁ አሰፋ


ሰዓት :አርብ ነሐሴ 9 ከቀኑ - 10:30 ጀምሮ

📍 አድራሻ ካሳንችስ ኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል

          መግቢያ በነፃ

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
11🥰3👎1
📌የአርብ ምሽቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ

1.የአንጋፋው ሙዚቀኛ መላቱ አስታጥቄ  አዲስ የሙዚቃ አልበም የሚለቀቅበት ቀን ይፋ ሆነ።

2."ቴአትር በየቤታችሁ ሊገባ ነው" ተብሏል።የአፍሪካን ሬነሳንስ ቴሌቪዥን  "Arts Pluse" የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ ሊያደረግ ነው ።አዲሱ መተግበሪያ ምን ምን ጉዳዮች ይዟል እንነግራችኋለን።

3.መስከረም አበራ እና ቸርነት ፍቃዱ የተጣምሩበት አዲስ ሀገርኛ ፊልም ለእይታ ሊበቃ ነው።

እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:

https://youtu.be/9hJNQhiM_ow?si=Bt_BmTaEvpCymvlY

📌መልካም ምሽት

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍53