Event Addis Media
9.63K subscribers
6.09K photos
12 videos
4 files
4.7K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ነፃ ዹሞዮሊንግ እስኮላርሺፕ ዕድል

ሞዮል መሆን ይፈልጋሉ ?

ፕሪስ቎ጅ አዲስ ኚሌጋሲ ሞዮሊንግ ኀጀንሲ ጋር በጋራ በመሆን ነፃ ዹሞዮሊንግ ስልጠና ለእናንተ ይዞላቜሁ መጥቷል።

ዹዚህ እድል ተካፋይ መሆን ዚምትፈልጉ ኚታቜ ያለውን መስፈርት ማሟላት ይኖርባቜኋል።

✅ዚፕሪስ቎ጅ አዲስ እና ሌጋሲ ሞዮሊንግ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ቻናል ፎሎ ያድርጉ ።

✅ይሄንን ፖስት ዹተደሹገውን ሌር በማድሚግ ኢንስታግራም ስቶሪ ላይ ያጋሩ ፣ ሁለቱንም ቻናሎቜ ታግ ያድርጉ ።

✅ ኮሜንት ላይ ፍላጎት ያላ቞ውን ሶስት ሰዎቜን ታግ ያድርጉ።

✅በኮሜንት ሃሳብ መስጫ ላይ ሌጋሲ ሞዮሊንግ መማር ለምን እንደምትፈልጉ እና ይሄንን እድል ላንቺ / ላንተ ለምን እድሉ መሰጠት እንዳለበት ግለፅ/ጪ ።

✅ ይሄ እድል ኹ 16 ዓመት እስኚ 30 ዓመት ለሆኑት ክፍት ነው።

✅ ምንም አይነት ዹሞዮሊንግ ልምድ አይጠይቅም - ለጀማሪዎቜ ክፍት ነው ።

✅ #ፕሪስ቎ጅአዲስ እና #ሌጋሲሞዎኒንግ ሃሜታጎቜን ይጠቀሙ ።

ዹዚህ እድል ተካፋይ ለመሆን ዹ @prestigeaddis ኢንስታግራም ገፅ ላይ በመግባት ኹላይ ዹተጠቀሰውን መስፈርት በማሟላት መሳተፍ ይቜላሉ።

መልካም ዕድል

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀1
📌ገጣሚና ሠዓሊ ኚበደቜ ተክለአብ ልምዷን ታጋራለቜ

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሎ ዚሥነ ጥበባት ማዕኹል ገጣሚና ሠዓሊ ኚበደቜ ተክለአብ በሥራዎቿና በሕይወቷ ዙሪያ ልምዷን ታጋራለቜ፡፡

በዕለቱ ስለገጣሚነቷ፣ ስለሠዓሊነቷ፣ በሶማሊያ ሐዋይ ዹ10 ዓመታት ዚእስር ቀት ቆይታዋ፣ በሀዋርድ ዩኒቚርስቲ በተማሪነትም በመምህርነትም ስላሳለፈቻ቞ው ዓመታት ታወጋናለቜ፡፡

ዝግጅቱ ዚፊታቜን ቅዳሜ ሐምሌ 19፣ 2017 ኹ8 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይቀርባል፡፡

ይህ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኢትዮጵያ ቀተመዛግብትና ቀተመጻሕፍት ትብብር በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር አማካኝነት ዚሚሰናዳው ዚክሚምት ወራት ዚሥነ ጜሑፍ ሥልጠና አንዱ አካል ነው፡፡

ዚብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሎ ዚሥነ ጥበባት ማዕኹል በዝግጅቱ እንዲታደሙ ግበዣውን ያቀርባል፡፡

ዚዝግጅቱ ቊታ:- በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዚብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሎ ዚሥነጥበባት ማዕኹል ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ (በንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል ገባ ብሎ)፡፡ https://maps.app.goo.gl/yb1LFT7PDTwLUP217

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀12👍4🀔1
📌“አፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና ሥራዎቹ” መጜሐፍ á‰°áˆ˜áˆšá‰€

በዶ/ር አንዱአለም አባተ (ዹአጾደ ልጅ) እና በኢንጅነር ቎ዎድሮስ ደመቀ ዚተጻፈ “አፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና ሥራዎቹ” ዹተሰኘ መጜሐፍ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቚርሲቲ ተመርቋል፡፡

በመርሀ- ግብሩ ላይ ገጣሚና አዘጋጅ ጌትነት እንዚው  እና በዶ/ር ገዛኾኝ ጾጋው ኚመጜሐፉ ውስጥ ዹተወሰኑ ቅንጭብ ታሪኮቜ ተነበዋል።

ኹዚህ በተጚማሪም፣ በጎንደር ዩኒቚርሲቲ ማኀበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ ምክትል ዲን በዶ/ር ሲሳይ ሳህሌ አማካኝነት መጜሐፉን ዚሚዳስስ ጥልቅ ሀሳብ ዚያዘ ጜሑፍ ቀርቧል።

መጜሐፉ ዚመካኚለኛውን ዘመን ታላቅ ንጉስ ዹአፄ ዘርዐ ያዕቆብን ዚሕይወት ታሪክና ሥራዎቜ ዚሚያስዳስስ ሲሆን 19 ምዕራፎቜ እና 542 ገጟቜ አሉት።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀6👍2
📌ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ሱፐር አፕ ተመሹቀ

ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ሚዲያ በሀገራቜን ዹሙሉ ጊዜ ዚልጆቜ ዚ቎ሌቪዠን ቻናል በመጀመር ፈርቀዳጅ ዹሆነና በተለይም በልጆቜና ቀተሰቊቻ቞ው ዘንድ ሠፊ ተቀባይነት በማግኘት በአወንታዊ ዚትውልድ ግንባታ ላይ እዚሰራ ዹሚገኝ ተቋም ነው ይህንን መተግበርያ ይፋ ያደሚገው።

ተቋሙ አላማና ተደራሜነቱን ይበልጥ ለማስፋት በማሰብ መተግበርያውን ማበልጾጉን ይፋ አድርጓል።

በባለፉት አስርት አመታት በልጆቜ ዙርያ ዚተለያዩ ስራዎቜ ሲሰራ ዹቆዹው ተቋሙ በባለፉት ሰባት አመታት ደግሞ በኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዠን ዚልጆቜ ፕሮግራሞቜን በማቅሚብ ላይ ይገኛል።

ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዠን ያስመሚቀው ይህ መተግበርያ በውስጡ 10 ዹሚሆኑ ይዘቶቜን ማካተቱን ነው ዚተገለጞው።

መተግበርያው ያበለጞገው መሁቡብ ቎ክኖሎጂስ መተግበርያው ለልጆቜ አመቺ ዹሆነና አጠቃቀም ተብሎ ቀለል ተደርጎ ዹተዘጋጀ ነው ብለዋል።

ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዠን ስራ አስኪያጅ ህብስት አሰፋ እንደተናገሩት በተመደቡበት ዚስራ ዘርፍ ተሰልፈው ኹመጋሹጃ ጀርባ ያሉ ዹተቋሙ ሰራተኞቜ እና ባለሙያዎቜ ምስጋና ይግባና ዛሬ ለዚህ በቅተናል ብለዋል።

ተቋማቜን እዚህ ለመድሚሱ ሚስጥር ዚልጆቻቜን ወላጆቜ ናቾው ያሉት ስራ አስኪያጇ ስላደሚጋቜሁት ሁሉ ነገር እናመሰግናለን ብለዋል።

©ድሬቲዩብ

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍4
📌ኚአንድ መቶ በላይ ተዋንያን ዚሚሳተፉበት "ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ነገ ለመድሚክ ይበቃል

በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተጜፎ በተሻለ አሰፋ (ዶ/ር) ዹተዘጋጀውና መሠሚት ሕይወት ሚዳት አዘጋጅ á‹šáˆ†áŠá‰œá‰ á‰µ "ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ኚበርካታ ዓመታት በኃላ በድጋሚ ነገ ሐምሌ 20 2017 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ኹቀኑ 8፡30 ላይ ወደ መድሚክ ይመለሳል።

"ንጉሥ አርማህ" ወደ መድሚክ ሲመለስ ኚመቶ በላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን እንደሚሳተፉበት ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚ቎አትሩ ደራሲ አቶ መልካሙ ዘሪሁን ቎አትሩ ኚተጻፈ 24 ዓመት እንደሆነ አስታውሶ ዛሬ ላይ ግን á‰µá‹áˆá‹±áŠ•áŠ“ ያለንበትን ዘመንን በሚዋጅ ሁኔታ አብሮነት፣አንድነትን በንጉሥ አርማህ ታሪክና አስተዋይነት ውስጥ á‰ŽáŠ á‰µáˆ© መዘጋጀቱን ገልጿል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍4❀2
📌ጋዜጠኛ ዚኃላሞት ዘሪሁን በትወና ዚመጣበት "ወደ ማዶ" ዹተሰኘው ትያትር በ30 ዹዓለም ሀገራት መድሚኮቜ ለዕይታ ሊቀርብ ነው።

ዚኪነ-ብስራት እና ዹነገሹ ኪን ዚሬድዮ ፕሮግራሞቜ አዘጋጅ ዹሆነው ጋዜጠኛ ዚኃላሞት ዘሪሁን በትወና ዚመጣበትና "ወደ ማዶ" ዹተሰኘ ተውኔት ዓለም አቀፍ ዚቲያትር ጉዞ ሊጀመር መሆኑ ተነግሯል።

በ቎ዎድሮስ ተ/አሹጋይ ተደርሶ በሮም አማኑኀል ዹተዘጋጀው "ወደ ማዶ" ትያትር ዚኮሜዲ ዘውግ ያለው ማህበራዊ ጉዳዮቜን እያነሳ ዚሚሄድ፣ ሲሆን በሕይወታቜን ዚሚገጥሙን ቜግሮቜ ለማውጣት ዹሚደሹግን ትንቅንቅ ዚሚያሳይ ነው።

በትያትሩ ላይ ሃሹገወይን አሰፋ፣ ሜዋፈራው ደሳለኝ እና ዚኋላእሞት ዘሪሁን ይተውኑብታል ተብሏል።

"ወደ ማዶ" ዓለም አቀፍ ዚትያትር ጉዞ ለሚቀጥሉት ሊስት ዓመታት ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባ቞ው በአፍሪካ፣ በመካኚለኛው ምስራቅ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ አህጉራት በሚገኙ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ኹ30 በላይ መድሚኮቜ እንደሚታይ ተገልጿል።

በተጚማሪም እስካሁን ባልተለመደ መልኩ ትያትሩ በሚታይባ቞ው ሀገራትና መድሚኮቜ ኚትያትሩ ጎን ለጎን ለዚኢትዮጵያ ዚልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕኹል ዚገቢ ማሰባሰቢያ ይደሹጋል ዚተባለ ሲሆን ይህንንም በጎ አላማ ለማሳካት ኹማዕኹሉ ጋር ዚመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀5👍2
📌ዚታገል ሰይፉ "ዚእኔ ደማቅ ሠዎቜ" ለንባብ በቃ

ገጣሚና ደራሲ ታገል ሰይፉ "ዚእኔ ደማቅ ሠዎቜ" ሲል ዹሰዹመውን አዲስ መጜሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ እንዳቀሚበ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኹጃፋር መጜሐፍ መደብር ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

መጜሐፉ ስለ ኚያኒያኑ ሙሉጌታ ተስፋዬ፣ሐዲስ አለማዚሁ፣ስብሐት ገ/እግዚአብሔር፣ደበበ ሰይፉ እና ስለ ሌሎቜም ሰዎቜ ያልተሰሙ መሚጃዎቜን ዚያዘ እንደሆነ ተነግሯል።

ታገል ሰይፉ ''ዚእኔ ደማቅ ሰዎቜ'' በሚል ርዕስ አስቀድሞ ተኚታታይ ቪዲዮዎቜን በዩቱብ ቻነሉ ሲለቅ እንደቆዚ ይታወሳል።

"ዚእኔ ደማቅ ሰዎቜ" መጜሐፍ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮቜ ይገኛል á‰°á‰¥áˆáˆá¢

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
❀8
📌ስብሐቲዝም ስለመንግሥቱ ኃይለማርያም

ደራሲና ገጣሚ ይታገሡ ጌትነት ዚክብር እንግዳ ዚሆነበት ስብሐቲዝም 93ተኛ መድሚክ "መንግሥቱ ኃይለማርያም 'ኚፖለቲካ ባሻገር" በሚል ዚሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።

ዚስብሐቲዝም አዘጋጆቜ ተኚታዩን ብለዋል" ይታገሡ ጌትነት ነው ዹ93ኛ መድሚክ እንግዳ። ስለ ሊቀ መንበር መንግስቱ ኚፖለቲካ ገጜታ቞ው እስኚ ግለሰባዊ ማንነታ቞ው ዚሚያወጋን እርሳ቞ውን አግኝቶ በበቃ ብዕር ዹተኹተበልን ይታገሡ ነው።

ደራሲው ስለጻፈ ብቻ ሳይሆን ኚልጅነት ጀምሮ እርሳ቞ውን ያውቃል። ስለሆነም ኹሌላው በተለዹ ዹሚነግሹንን ሙሉ ያደርገዋል" ።

ውይይቱ ነገ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም  ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቀተመዛግብት እና ቀተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሜ ውስጥ ይኚናወናል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3
📌በአዲስ አበባ ኹተማ ዚተገነባው ባለ 11 ወለል ግዙፍ ዚሲኒማና ቎አትር አዳራሜ እዚተጠናቀቀ ይገኛል ተባለ

ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ቩሌ መንገድ ፍላሚንጎ አካባቢ እያስገነባው ያለው ባለ 11ወለል ዚህጻናት ቎አትርና ሲኒማ አዳራሜ ህንጻ ግንባታ ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል ።

ዋንኛው ዚ቎አትር አዳራሹ 1300 ሰዎቜ መያዝ ዚሚቜል ሲሆን ፣ ሌሎቜ ሁለት መካኚለኛ ዚሲኒማ አዳራሟቜም በህንጻው ግንባታ ውስጥ ተካትተዋል።  ዹዋንኛው ቲያትር አዳራሜ መድሚክ በሀይድሬሊክ ሲስተም 360 ዲግሪ መሜኚርኚር እንዲቜል ተደርጎ ዚተሰራ ነው።

©Samson michailovich

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
🔥7👍3❀1👏1
📌ዚደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል "ዚወዲያነሜ" ዚልቊለድ መጜሐፍ ዳግም ሊታተም ነው።

ዚተወዳጁ ደራሲ፣ አርታኢ እና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል "ዚወዲያነሜ" መጜሐፍ ኚአስር ዓመታት በኋላ ዳግም በቅድም ክፍያ ሜያጭ ለሕትመት ይበቃል ተብሏል።

መፅሐፉ ኹ39 ዓመታት በፊት በ1978 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሞ ለአንባቢያን ሲደርስ በ5.50 ዋጋ እንደነበር ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ኚእዚያ በኋላ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ መታተሙን አስታውሷል።

ኚአስር ዓመታት በፊት በ2007 ዓ.ም ለመጚሚሻ ጊዜ መታተሙን በመጥቀስ ዹመፅሀፉ ፈላጊዎቜ ቁጥር መበራኚት ለዳግም ሕትመቱ ምክንያት እንደሆነ ጠቅሷል።

"ዚወዲያነሜ" መጜሐፍ ድጋሚ ሲታተም ዚጀርባ á‹‹áŒ‹á‹ 400 ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000571154319(ኃይለመለኮት መዋዕል ) ብር በማስገባት መጜሐፉን ቀድማቜሁ መግዛት ትቜላላቜሁ ተብላቜኋል።

ዚቀድመ ሜያጭ አስተባባሪዎቜ "መጜሐፍ ስትገዙ ዚኚፈላቜሁበትን ደሹሰኝ  በውስጥ ላኩልን https://shorturl.at/F7POF መጜሐፏ ኚህትመት ሲወጣ በምሹቃዋ ዕለት ወይም በሌላም መንገዶቜ ሁሉ ይደርሷቜኋል" ሲሉ ተናግሚዋል።

"ዚወዲያነሜ"ን ተኚትሎ ሌላኛው ዚደራሲው ተወዳጅ ስራ "ጉንጉን" ዳግም እንደሚታተም በመግለፅ "ዚአዕምሮ ማህፀን ጀና ካለ አይመክንም፣ ኚሰራህበት ሁል ጊዜ እዚፋፋ እያደገ ነው ዹሚሄደው" ያለው ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ኚእዚህ በኋላ ባለው ጊዜ አዳዲስ ሥራዎቜን ለማበርኚት እንደጥር ጠቁሟል።

ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል "ዚአርትኊት ሥራዎቜን አቁሜያለሁ" ያለ ሲሆን "ኚፈጣሪ  ፍቃድ ጋር"በቀጣዩ ዓመት አዲስ ስራ ሊኖር እንደሚቜል ተናግሯል።

©FM Addis 97.1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀10
📌 DStv ሙሉ በሙሉ ለካናል ፕላስ ተሾጠ

ዚፈሚንሳዩ ተቋም ካናል ፕላስ  ዚደቡብ አፍሪካውን መልቲ቟ይዝ ግሩፕ (DStv) በ3 ቢሊዚን ዶላር ገዝቶታል።

ካናል ፕላስ መጀመሪያውንም ቢሆን ዚመልቲ቟ይዝ 45 በመቶ ባለድርሻ ዹነበሹ ሲሆን አሁን ሙሉ ለሙሉ ድርሻውን ገዝቶታል።

መልቲ቟ይዝ ለ40 አመታት ዹቆዹ ስም ዚገነባ መሆኑ ሲገለፅ በአፍሪካ ኹ50 ሚሊዹን በላይ ደንበኞቜ እንዳሉት ይገለፃል።

መልቲ቟ይዝ በክፍያ ኚሚሰሩ ዚ቎ሌቪዥን ገበያዎቜ ውስጥ አንዱ ሲሆን በዲ ኀስ ቲቪ እና ጎቲቪ በኩል ዚተለያዩ ዚስፖርት እና ዹመዝናኛ ፕሮግራሞቜን በክፍያ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።

ግዢው ሙሉ ለሙሉ በመጪው ጥቅምት ይጠናቀቃል ተብሎ ሲጠበቅ ካናል+ ዚደቡብ አፍሪካን ፕሮዳክሜን በአዲስ ገበያዎቜ ዚማስተዋወቅ ኃላፊነት ተጥሎበታል።

ደቡብ አፍሪካ በህጓ ዚደቡብ አፍሪካን ዚስርጭት መብት ዚያዘ ድርጅት ባለቀትነቱ ኹ20 በመቶ በላይ በውጪ ዜጋ መያዝን ስለምትኚለክል መልቲ቟ይዝ ዚስርጭት መብቱን ላይሰንስኮ በተሰኘ ድርጅት ማድሚጉ ተሰምቷል።

መልቲ቟ይዝ ሃገራቜን ኢትዮጵያን ጚምሮ ብዙ ተጠቃሚዎቜ ያሉት ሲሆን በዲ ኀስ ቲቪ በኩል ዚእግር ኳስ እና ዹመዝናኛ ፕሮግራሞቜንም ሲያሰራጭ ቆይቷል።

ካናል+ በበኩሉ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ኚገባ በኋላ ዚክፍያ ቎ሌቪዥኑን በመዝጋት ወደ ሌላ አማራጮቜ ማዞሩን ኚወራት በፊት መግለፁ ይታወሳል።

©TikvahethMagazine

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4😱2
📌ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ኚህልፈቱ 17 ቀናት በኃላ ዛሬ ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ሥላሎ ካ቎ደራል ተፈፀመ

ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ኹተማ ኹዚህ ዓለም በሞት እንደተለዚ ይታወሳል።ዛሬ ሀምሌ 19 ቀን 2017 ኚህልፈቱ 17 ቀናት በኃላ ስርዓተ ቀብር በቅድስት ሥላሎ ካ቎ደራል ተፈጜሟል።

ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን ኚጋዜጠኝነት እስኚ ዹዜናና ወቅታዊ መሹጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።

በኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን "ዚሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርዕስ ሲያቀርበው በነበሹው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካ቟ቜ ዘንድ ይታወሳል።

ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።ኚትምህርቱ ጎን ለጎንም እስኚ ህልፈቱ ድሚስ TBS በተባለው ዚትግርኛ ቎ሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎቜ ወቅታዊና ዹመዝናኛ ፕሮግራሞቜ ሲያቀርብ ነበር። 

በ1963 ዓ/ም á‰ á‰µáŒáˆ«á‹­ ውቕሮ ኹተማ ዹተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ኚአዲስ አበባ ዩንቚርስቲ  ዚጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሜንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለሹጅም አመታት ሰርቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8😢3😭3
📌በቻይና ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ተሞለመቜ

ጋዜጠኛ ሰላም ተሟመ ኹሰሞኑ በቻይና በተካሄደው ዹ"Road and Belt journalist forum" ላይ ኢትዮጵያን ወክላ ተገኝታ ነበር።

በፎሹሙ ኹ30 በላይ ሃገራት ኹተወኹሉ ዚሚዲያ ባለሙያዎቜ መካኚል ጋዜጠኛ ሰላም ተሟመ ባቀሚበቜው ስራ ኹፍ ያለ ዕውቅና ተሰጥቷት።

በዚህም ስራዋ ተሾላሚ ሆና ዚሀገራቜንን ስም አስጠርታለቜ።

©ጋዜጠኛ ያልፋል አሻግር

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀11
📌ድምጻዊ ብስራት ጋሹደው "ኚእንግዲህ በኃላ በመዝሙር ጠብቁኝ" áˆ²áˆ ተናገሹ

ድምጻዊ ዚግጥምና ዜማ ደራሲው ብስራት ጋሹደው በአርትስ ቎ሌቪዥን በኩል በሚተላለፈው 'ዘጠናዎቹ' ዚ቎ሌቪዥን ዝግጅት ላይ እንግዳ ሆኖ ቀርቩ ነበር በዚህም ዝግጅት ላይ "ኚእንግዲህ በኃላ በመዝሙር ጠብቁኝ" ሲል ተናግሯል።

ብስራት ጋሹደው በተጚማሪም "ኚሞትኩበት ያነሳኝን አምላኬን ዘፍኜ አላሳዝነውም" ብሏል።

ድምጻዊ ብስራት ጋሹደው በዘጠናዎቹ በለቀቀው "ሳላምንበት" በተሰኘው ተወዳጅ ዹሙዚቃ አልበሙ ኚበርካታ ዹሙዚቃ አድማጮቜ ጋር ተዋውቋል።

በተጚማሪም ለበርካታ ድምጻዊያን ዚግጥምና ዜማ ስራዎቜን አበርክቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀3
📌ዚጋዜጠኛው ዚስለት ጥቃት ሀሰት ሆኖ ተገኘ

ዚስፖርት ጋዜጠኛው አሉላ ፍሬው "በጩቀ ተወጋሁ" ያለው ጉዳይ በመሹጃና ማስሚጃ ሀሰት ሆኖ ተገኘ

ዹCD ስፖርትና ዹNBC ኢትዮጵያ ዚስፖርት ጋዜጠኛው አሉላ ፍሬው በስለት ዚመወጋት አደጋ እንደደሚሰበት ኹ51 ቀናት በፊት በራሱ ዚፌስቡክ ገፅ አስታውቆ ነበር።ይህም አስነዋሪ ድርጊት በወቅቱ መነጋገሪያ እንደነበሚ ይታወሳል።

በዚህ ጉዳይ ላይ አንጋፋው ዚስፖርት ጋዜጠኛ ታምሩ አለሙ እና ባልደሚቊቹ ጥልቅ ምርመራ አድርገው ፣መሚጃዎቜን አጣርተው ነበር።

ይህ "ጋዜጠኛው ላይ ጉዳት ያደሚሰው ማነው?" በሚል ርዕስ ዹቀሹበው ሰፋ ያለ ዘገባ "ዚፖሊስ፣ ዚክሊኒክ፣ ዚማህበሩና ዚፌዎሬሜኑን ምላሜ" ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።

በምርመራ቞ውም ዚስፖርት ጋዜጠኛው ዚሰጣ቞ው መሹጃና በምርመራ ያገኙት መሹጃ ፍፁም ዹማይገናኝ በመሹጃና ማስሚጃ ሀሰት እንደሆነ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚዘገባ቞ው ላይ ተመልክቷል።

ዹምርምር ቡድኑ "ዹዚህ ዘገባ አላማ ዚሙያ ባልደሚባቜን ያጋጠመውን ጉዳት መነሻ በማድሚግ በሙያተኞቜ ላይ ዹሚደርሰውን በደልና ጥቃት ማውገዝ ብሎም ማጋለጥ ነበርፀ ሆኖም መሹጃውን ስናጣራ ውጀቱ ይህ ሆኗል" ሲል አስታውቋል።

ሙሉ መሹጃውን ኹጋዜጠኛ ታምሩ አለሙ ዚፌስቡክ ገፅ ያንብቡ: https://www.facebook.com/1812918430/posts/pfbid02E2uAome5LTwaR9YZbYBQsLwiQX93kyqysRYPSpC5SpC9U3FiekbqriQpGjDAQxVpl/

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4😁4🔥2🀔1
📌ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ይቅርታ ጠዹቀ

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ኹ" ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ዚመክፈቻ ሥነሥርዓት ጋር በተያያዘ ለተፈጠሹው ዚታዳሚያን መጉላላት በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

቎አትር ቀቱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ"በትናንትናው ዕለት ማለትም ሐምሌ  20 ቀን 2017 ዓ.ም  ‹‹ንጉሥ አርማህ›› ቎አትር በይፋ መኚፈቱ ይታወቃል፡፡ በዕለቱ ዚተመልካቹ ብዛት ኚ቎አትር ቀቱ አዳራሜ አቅም በላይ በመሆኑ በቊታ ጥበት ምክንያት ዚተመለሳቜሁ ክቡራን ተመልካ቟ቻቜንን áŠšáá‰°áŠ› ይቅርታ በ቎አትር ቀቱ ሥም እንጠይቃለን" ስለማለቱ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።

በሌላ በኩል "ዘወትር እሁድ ኹቀኑ 8፡30 ይቀርብ ዹነበሹው ‹‹12ቱ እንግዶቜ›› ቎አትር  ወደ ቅዳሜ 8፡30 ዹተዘዋወር ሲሆን  ‹‹ንጉሥ አርማህ›› ቎አትር ዘወትር እሁድ በ8፡30 ለክቡራን ተመልካ቟ቜ እንደሚቀርብ በአክብሮት እንገልጻለን" áˆ²áˆ ዚመርሐግብር ለወጥ እንዳደሚገም ቎አትር ቀቱ አስታውቋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
🙏17❀3
📌"ሣማ ፊልም" ተመሹቀ

በደራሲና አዘጋጅ ሞገስ አስራት ተዘጋጅቶ በአድዋ ፊልምስ ዹቀሹበው "ሳማ" ፊልም ትላንት ሰኞ ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም በዓለም ሲኒማ ተመርቋል።

በፊልሙ ላይም በመሪ ተዋናይነት ሜዋፈራሁ ደሳለኝ ፣ ሙላለም ጌታ቞ው ፣ ቀዛነሜ አያሌው እንዲሁም ሌሎቜ አዳዲስ ተዋንያን ተሳትፈውበታል ።

ኹዚህ ቀደም በተመልካቜ ተወዳጅነትንና አድናቆትን እንዲሁም በተለያዩ አዋርዶቜ ላይ በበርካታ ዘርፎቜ በመታጚትና በመሾለም ዚሚታወቀውን "ክሱት" ዹተሰኘ ፊልም በመስራት ለዕይታ ያበቃው አድዋ ፊልምስ ፕሮዳክሜን አሁን ደሞ ሙሉ ቀሹፃውን በጉራጌ ዞን ያደሚገ "ሣማ" ዹተሰኘ ፊልምን ለእይታ አብቅቷል።

ፊልሙ በቅርቡ በተለያዩ ሲኒማ ቀቶቜ ለእይታ ይቀርባል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ንባብ ለሕይወት" ግዙፉ አውደርዕይ ሊካሄድ ነው

ዚአዲስ አበባ ኹተማ ግዙፉ ዚመጜሐፍ አውደርዕይ "ንባብ ለሕይወት " ዚመጜሐፍና ንባብ አውደርዕይ ኚቀናት በኃላ ሊካሄድ እንደሆነ ኀቚንት አዲስ ኚአዘጋጆቹ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

"ንባብ ለሕይወት" ዚመጻሕፍት አውደርዕይ ዘንድሮ ኹሐምሌ 24 እስኚ ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም ድሚስ ለቀናት መስቀል አደባባይ አካባቢ በሚገኘው በአዲስ አበባ ኀግዚቢሜን ማዕኹል ውስጥ በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል።

ዚንባብ ኚሕይወት ፕሮጀክት ኚኢትዮጵያ ቀተ-መዛግብትና ቀተ-መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በመተባባር ባዘጋጀው በዚህ አውደርዕይ ላይ በርካታ ደራሲያን በመገኘት መጻሕፋ቞ውን ያስተዋውቃሉ ተብሏል።

ዚመጻሕፍት አሳታሚዎቜና አኚፋፋዮቜ መጻሕፍትን በቅናሜ ዋጋ ያቀርባሉ።

በአውደርዕዩ ላይ ዚመጜሐፍ ምርቃትና ሀሳብ ማንሞራሞሪያ ልዩ ልዩ መድሚኮቜ ተዘጋጅቷል።

ዚአውደርዕዩ መግቢያ በነፃ ሲሆን ሐሙስ ሐምሌ 24 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:30 ጀምሮ ይኚፈታል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀4🔥2
📌ዚሠርቅ ዳንኀል መጜሐፍ ድጋሚ ሊታተም ነው

ዚደራሲ ሠርቅ ዳንኀል (ገበና ዳንኀል) ተወዳጅ ድርሰት ዹሆነውና ኚገበያ ጠፍቶ ዹቆዹው "ቆንጆዎቹ" ዹተሰኘ መጜሐፍ በቅርብ ቀን ድጋሚ ታትሞ ለአንባቢያን እንደሚያቀርብ ኀቚንት ሚዲያ ኚአሳታሚው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏20❀2
ጆኒ ራጋ፣ ሚካኀል በላይነህና ዳዊት መለሠ ተጣምሩ

ድምጻዊያኑ ጆኒ ራጋ፣ ሚካኀል በላይነህ እና ዳዊት መለሠ ዚተጣምሩበት "ሾክ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዹሙዚቃ ኮንስርት በዚህ ሳምንት ዚፊታቜን ቅዳሜ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ/ም አመሻሜ ላይ በሚሊኒዹም አዳራሜ ይካሄዳል።

ኹሙዚቃ ኮንሰርት ራቅ ብሎ ዹቆዹው ጆኒ ራጋ በ"ሾክ" ኮንሰርት በአስዮ ባንድ ታጅቊ ዹሙዚቃ ስራዎቹን ያቀርባል ተብሏል።

ይህ ኮንሰርት ሚካኀል በላይነህ እና ዳዊት መለሠ በዚህ ዓመት ብቻ ለሶስተኛ ጊዜ ዚተጣምሩበት ኮንሰርት ነው።ሚኪ እና ዮቭ አስቀድመው በዚህ ዓመት በሀገር ውስጥ እና ኹሀገር ውጪ ሁለት ተኚታታይ ኮንሰርቶቜን በጥምሚት ማቅሚባ቞ው ይታወሳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀8🥰1
📌አራት ዝነኛ ጋዜጠኞቜ በጥምሚት ሚዲያ መሰሚቱ

በፋና ኀፍ ኀም 98.1 ምስሚታ እና እድገት ዹጎላ ድርሻ ዚነበራ቞ው 4 ዚሚድያ ሰዎቜ ላይፍ ሚድያ በሚል ዩቲዩብ አዳዲስ ይዘትና ሀሣቊቜን ሊያቀርቡ እንደሆነ ታወቀ፡፡

ኚመጋቢት 1999 ዓ.ም ጀምሮ ዹፋና 98.1መሥራቜ ጋዜጠኞቜ ዚነበሩት ዘካርያስ ብርሀኑ፣ እፀገነት ለዐቀ ፣ ነቢል መሐመድና ትዕግስት በጋሻው በመጣመር ለዓመታት ያካበቱትን ልምድ በላይፍ ሚድያ እንደሚያካፍሉ ይጠበቃል።

ዚሚድያ ባለሙያዎቹ ለተወዳጅ ሚድያ እንዳሉት ላይፍ ሚዲያ በተለያዩ ዚኑሮ ጉዳዮቻቜን ግንዛቀ  ለመጹመር ዹሚተጋ መሰናዶ ነው፡፡

ሀሣቊቜ በነጻነት ልክ እንደቀተሠብ ለማቅሚብ እቅድ መንደፋቾውን ባለሙያዎቹ ይናገራሉ፡፡ውጥና቞ውንም ሲያብራሩ"ዘና ብለን በቁምነገር በብዙ መልኩ እውነታን ፣ ልምድን፣ ዚአቀራሚብ ስብጥርንና ስነምግባርን ተላብሰን በማህበሚሰብ ትስስር ገፅ ዚበኩላቜንን በጎ አስተዋፅዖና ድርሻ  ለማሳዚት ዹፈጠርነው መድሚክ ነው" በማለት ተናግሚዋል።

አቅራቢዎቹ በኢትዮጵያ ሚድያ ላይ በአመራርነት፣ በመዝናኛ አዘጋጅነት  በማስታወቂያና በይዘት ፈጠራ ክህሎታ቞ው ፕሮፌሜናል በሆነ መልኩ ትልቅ አሻራ ያኖሩ ና቞ው፡፡

ዹላይፍ ሚድያ አዘጋጆቜ  ህይወት ሰፊ ውቅያኖስ መሆኗንበትንሹ በሚጠቅም መልኩ እዚጚለፍን ህይወታቜንን ለማሻሻል እንተጋለን ሲሉም በጥሩ ይዘት ተመልካቜን ለማዝናናት እንደተዘጋጁ ተናግሚዋል።

https://youtube.com/channel/UC9gOKO-9ZBdSubvbwZ3e6uw?si=aKKaTdnSRJT-itOs

©ተወዳጅ ሚዲያ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀13🔥1