የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ህልውና አሳሳቢ ሆነ
ደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አጠቃላይ እንቅስቃሴ በመዳከሙና ህልውናው አሳሳቢ በመሆኑ ቀጣይ ዕጣ ፈንታቸው እንዳስጨነቃቸው የድርጅቱ ጋዜጠኞች ገልጸዋል፡፡
ማንነታቸው እንዳይገለፅ የጠየቁ የድርጅቱ ጋዜጠኞች ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ በተቋሙ ውስጥ በርካታ ችግሮች እንዳሉ ገልፀው፣ ለአብነትም ደመወዝ በሰዓቱ እንደማይከፈላቸው፣ ይህም ተደጋግሞ የሚስተዋል እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ላለፉት ሦስት አመታት የተቋሙ ፊዚካልና ፋይናንሻል የስራ አፈጻጻም፣ እንዲሁም የሰራተኛውም ሆነ የአመራሩ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዶ እንደማያውቅ የገለፁት ጋዜጠኞቹ "በይፋ ፈርሷል ለመባል ጫፍ ላይ ነው ያለው" በማለት ድርጅቱ ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቀዋል፡፡
የድርጅቱ ባለቤት የነበረው የቀድሞው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ከፈረሰና አራት የተለያዩ ክልሎች ከተዋቀሩ በኋላ ክልሎቹ እንደየ ድርሻቸው ለተቋሙ በጀት የሚመድቡበት አሰራር የተዘረጋ ቢሆንም ተግባራዊ ባለመሆኑ ችግሮቹ መፈጠራቸውን ተናግረዋል፡፡
የሲዳማ ክልል የራሱን ብዙሃን መገናኛ በመመስረቱ በጀት ለመመደብ ፍቃደኛ አለመሆኑን፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሚጠበቅበትን እያዋጣ እንዳለሆነ የሚናገሩት ጋዜጠኞቹ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግን ከሚጠበቅበት በላይ በማዋጣት ለማገዝ እየሞከረ ነው ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትየጵያ ክልል በበኩሉ ከተመደበለት ኮታ በታች ቢሆንም በጀት እያዋጣ እንደሆነ ጋዜጠኞቹ ተናግረዋል፡፡
በእነዚህና በሌሎችም ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ምክንያት ድርጅቱ ህልውናው እንደሚያሰጋና ቀጣይ ዕጣ ፈንታቸው አሳሳቢ መሆኑን ነው ጋዜጠኞቹ የገለፁት፡፡
Via ኢትዮ ኤፍኤም
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አጠቃላይ እንቅስቃሴ በመዳከሙና ህልውናው አሳሳቢ በመሆኑ ቀጣይ ዕጣ ፈንታቸው እንዳስጨነቃቸው የድርጅቱ ጋዜጠኞች ገልጸዋል፡፡
ማንነታቸው እንዳይገለፅ የጠየቁ የድርጅቱ ጋዜጠኞች ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ በተቋሙ ውስጥ በርካታ ችግሮች እንዳሉ ገልፀው፣ ለአብነትም ደመወዝ በሰዓቱ እንደማይከፈላቸው፣ ይህም ተደጋግሞ የሚስተዋል እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ላለፉት ሦስት አመታት የተቋሙ ፊዚካልና ፋይናንሻል የስራ አፈጻጻም፣ እንዲሁም የሰራተኛውም ሆነ የአመራሩ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዶ እንደማያውቅ የገለፁት ጋዜጠኞቹ "በይፋ ፈርሷል ለመባል ጫፍ ላይ ነው ያለው" በማለት ድርጅቱ ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቀዋል፡፡
የድርጅቱ ባለቤት የነበረው የቀድሞው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ከፈረሰና አራት የተለያዩ ክልሎች ከተዋቀሩ በኋላ ክልሎቹ እንደየ ድርሻቸው ለተቋሙ በጀት የሚመድቡበት አሰራር የተዘረጋ ቢሆንም ተግባራዊ ባለመሆኑ ችግሮቹ መፈጠራቸውን ተናግረዋል፡፡
የሲዳማ ክልል የራሱን ብዙሃን መገናኛ በመመስረቱ በጀት ለመመደብ ፍቃደኛ አለመሆኑን፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሚጠበቅበትን እያዋጣ እንዳለሆነ የሚናገሩት ጋዜጠኞቹ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግን ከሚጠበቅበት በላይ በማዋጣት ለማገዝ እየሞከረ ነው ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትየጵያ ክልል በበኩሉ ከተመደበለት ኮታ በታች ቢሆንም በጀት እያዋጣ እንደሆነ ጋዜጠኞቹ ተናግረዋል፡፡
በእነዚህና በሌሎችም ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ምክንያት ድርጅቱ ህልውናው እንደሚያሰጋና ቀጣይ ዕጣ ፈንታቸው አሳሳቢ መሆኑን ነው ጋዜጠኞቹ የገለፁት፡፡
Via ኢትዮ ኤፍኤም
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5
📌በአለልኝ አዘነ ገዳዮች ላይ ተፈረደ
የእግር ኳስ ተጫዋች በነበረው አለልኝ አዘነ ግድያ የተከሰሱት ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው።
በአለልኝ አዘነ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ለመስጠት ዛሬ የተሰየመዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት አደይ ጌታቸዉና በእህቷ ባል ላይ የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ ይህንን ዉሳኔ ያስተላለፈው መጋቢት 17/2016 ዓ/ም በተጋቡ በ15ኛ ቀን አለልኝ አዘነን ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል መግደላቸውን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች ካረጋገጠ በኋላ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የእግር ኳስ ተጫዋች በነበረው አለልኝ አዘነ ግድያ የተከሰሱት ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው።
በአለልኝ አዘነ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ለመስጠት ዛሬ የተሰየመዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት አደይ ጌታቸዉና በእህቷ ባል ላይ የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ ይህንን ዉሳኔ ያስተላለፈው መጋቢት 17/2016 ዓ/ም በተጋቡ በ15ኛ ቀን አለልኝ አዘነን ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል መግደላቸውን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች ካረጋገጠ በኋላ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤2
📌የወጣቷ ድምፃዊ ማህሌት ወንድሙ “እድለኛ” አልበም በሰዋሰው በኩል የሚለቀቅበት ቀን ይፋ ሆነ
‘’እሺ አትለኝም ወይ’’ እና ‘’ዝም’’ በሚሉት ሁለት ነጠላ ዜማዎች በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እና ተቀባይነትን ያገኘችዉ የወጣቷ ድምፃዊ ማህሌት ወንድሙ (ማሂ) የመጀመሪያ አልበም ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም ይለቀቃል።
‘’እድለኛ’’ የተሰኘዉ የወጣቷ ድምፃዊ አልበም በሰዋሰዉ መልቲሚዲያ ፕሮዲዩስ የተደረገ ሲሆን የሬከርዲንግ ፕሮዲዩሰሩ ደግሞ ወንዶሰን ይሁብ እንደሆነ ተነግሯል።
በጥቂት ወራት ልዩነት በተከታታይ ሁለት ነጠላ ዜማዎችን በመልቀቅ ከ13 ሚሊየን በላይ ተመልካች በዩቲዩብ ማግኘት የቻለችዉ ድምፃዊ ማህሌት ወንድሙ(ማሂ) በአልበሟም ልዩ ነገር ይዛ ብቅ ስለማለቷ ሰምተናል።
10 ያህል ሙዚቃዎችን የያዘዉ ‘’እድለኛ’’ አልበም የፊታችን አርብ በሰዋሰዉ መተግበሪያ እና የዩቲዩብ ገጽ ይለቀቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
‘’እሺ አትለኝም ወይ’’ እና ‘’ዝም’’ በሚሉት ሁለት ነጠላ ዜማዎች በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እና ተቀባይነትን ያገኘችዉ የወጣቷ ድምፃዊ ማህሌት ወንድሙ (ማሂ) የመጀመሪያ አልበም ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም ይለቀቃል።
‘’እድለኛ’’ የተሰኘዉ የወጣቷ ድምፃዊ አልበም በሰዋሰዉ መልቲሚዲያ ፕሮዲዩስ የተደረገ ሲሆን የሬከርዲንግ ፕሮዲዩሰሩ ደግሞ ወንዶሰን ይሁብ እንደሆነ ተነግሯል።
በጥቂት ወራት ልዩነት በተከታታይ ሁለት ነጠላ ዜማዎችን በመልቀቅ ከ13 ሚሊየን በላይ ተመልካች በዩቲዩብ ማግኘት የቻለችዉ ድምፃዊ ማህሌት ወንድሙ(ማሂ) በአልበሟም ልዩ ነገር ይዛ ብቅ ስለማለቷ ሰምተናል።
10 ያህል ሙዚቃዎችን የያዘዉ ‘’እድለኛ’’ አልበም የፊታችን አርብ በሰዋሰዉ መተግበሪያ እና የዩቲዩብ ገጽ ይለቀቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤10👍3🥰1
📌የሙዚቃ አቀናባሪው የራሱን የሙዚቃ አልበም ሰራ
በድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ "አስቻለ" አልበም ላይ የተለያዩ ሙዚቃዎችን ያቀናበረው ቢንአንዴ የራሱን "ነጭ ጤፍ" የተሰኘ አልበም ለአድማጮች ሊያቀርብ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"ነጭ ጤፍ" የተለያዩ አንጋፋ እና ጀማሪ ድምፃዊያንን፣ ደራሲዎችን እንዲሁም ሙዚቀኞች እንደተሳተፉበት ተገልጿል።
የሙዚቃ ስራው ብዙ የተደከመበትና እንዲሁም ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ሙዚቃ ላይ ያልተለመዱ ፕሮፌሽናል የሙዚቃ ድምፆችን፣ የሙዚቃ ቅንብሮችን እንዲሁም ዜማዎችንና አዛዜሞችን ይዞ እንደቀረበ ተነግሯል።
ይህ የሙዚቃ አልበም በቅርቡ በተለያዩ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ለአድማጮች ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ "አስቻለ" አልበም ላይ የተለያዩ ሙዚቃዎችን ያቀናበረው ቢንአንዴ የራሱን "ነጭ ጤፍ" የተሰኘ አልበም ለአድማጮች ሊያቀርብ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"ነጭ ጤፍ" የተለያዩ አንጋፋ እና ጀማሪ ድምፃዊያንን፣ ደራሲዎችን እንዲሁም ሙዚቀኞች እንደተሳተፉበት ተገልጿል።
የሙዚቃ ስራው ብዙ የተደከመበትና እንዲሁም ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ሙዚቃ ላይ ያልተለመዱ ፕሮፌሽናል የሙዚቃ ድምፆችን፣ የሙዚቃ ቅንብሮችን እንዲሁም ዜማዎችንና አዛዜሞችን ይዞ እንደቀረበ ተነግሯል።
ይህ የሙዚቃ አልበም በቅርቡ በተለያዩ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ለአድማጮች ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤11👍1
📌"ሰተቴ" ተከታታይ ድራማ ለእይታ ሊበቃ ነው
በመንገደኛው ባለቅኔ ከድር ሰተቴ ላይ መሠረቱን ያደረገ "ሰተቴ" የተሰኘ አዲስ ተከታታይ አስቂኝ ድራማ በአርትስ ቴሌቪዥን ከሐምሌ 20 ጀምሮ ለተመልካቾች መቅረብ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ሰምቷል።
"ሰተቴ" ተከታታይ አስቂኝ ድራማ ከፍተኛ በጀት ወጥቶበት በከፍተኛ ጥራት የተዘጋጀ ሥራ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በተስፋዬ አየለ (ዶ/ር) ‘መንገደኛው ባለ ቅኔ ከድር ሰተቴ’ በተሰኘ መፅሐፍና በጦቢያ ግጥምን በጃዝ ሲቀርብ በነበረው የአንድ ሰው ቴአትር ላይ ተመርኩዞ በአንተነህ ኃይሌ ዳይሬክተርነት ተመርቶ የሀገራችንን ወጣትና አንጋፋ ተዋናዮችን በማሳተፍ የተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በመንገደኛው ባለቅኔ ከድር ሰተቴ ላይ መሠረቱን ያደረገ "ሰተቴ" የተሰኘ አዲስ ተከታታይ አስቂኝ ድራማ በአርትስ ቴሌቪዥን ከሐምሌ 20 ጀምሮ ለተመልካቾች መቅረብ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ሰምቷል።
"ሰተቴ" ተከታታይ አስቂኝ ድራማ ከፍተኛ በጀት ወጥቶበት በከፍተኛ ጥራት የተዘጋጀ ሥራ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በተስፋዬ አየለ (ዶ/ር) ‘መንገደኛው ባለ ቅኔ ከድር ሰተቴ’ በተሰኘ መፅሐፍና በጦቢያ ግጥምን በጃዝ ሲቀርብ በነበረው የአንድ ሰው ቴአትር ላይ ተመርኩዞ በአንተነህ ኃይሌ ዳይሬክተርነት ተመርቶ የሀገራችንን ወጣትና አንጋፋ ተዋናዮችን በማሳተፍ የተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤11🔥2👍1😁1
📌“የከተማው መናኝ” መጽሐፍ በድጋሚ ለንባብ በቃ
የኤልያስ መልካ ሕይወትና ሥራዎችን የሚተርከው “የከተማው መናኝ” መጽሐፍ በአንባቢያን ጥያቄ መሰረት በድጋሚ ታትሞ ለአንባቢያን ቀረበ።
“የከተማው መናኝ” መጽሐፍ ጃፋርን መጻሕፍት ቤትን ጨምሮ በሁሉም የመጻሕፍት መደብሮች ለአንባብያን ቀርቧል::
በደራሲና ጋዜጠኛ ይነገር ጌታቸው (ማዕረግ) የተዘጋጀው መጽሐፉ ለንባብ ከበቃበት ጊዜ አንስቶ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
“የከተማው መናኝ” መጽሐፍ የተናፋቂውን ኤልያስ መልካ አነጋጋሪ የግል ፍልስፍና እና የሕይወት ውጣ ውረድ የሚተርክ ሲሆን መጽሐፉ በወጣበት ዓመትም በኢ-ልብወለድ ዘርፍ ከዓመቱ አምስት ምርጥ መጽሐፍት አንዱ ለመሆን በቅቷል፡፡
ይነገር ጌታቸው (ማዕረግ) በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ላይ ምርምርን በማድረግ የሚታወቅ ሲሆን በ2015 ዓ.ም ሙዚቃ፣ታሪክና ፖለቲካ ላይ ያተኮረውን “ጠመንጃና ሙዚቃ” የተሰኘ መጽሐፍ ለአንባብያን አድርሷል፡፡
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የኤልያስ መልካ ሕይወትና ሥራዎችን የሚተርከው “የከተማው መናኝ” መጽሐፍ በአንባቢያን ጥያቄ መሰረት በድጋሚ ታትሞ ለአንባቢያን ቀረበ።
“የከተማው መናኝ” መጽሐፍ ጃፋርን መጻሕፍት ቤትን ጨምሮ በሁሉም የመጻሕፍት መደብሮች ለአንባብያን ቀርቧል::
በደራሲና ጋዜጠኛ ይነገር ጌታቸው (ማዕረግ) የተዘጋጀው መጽሐፉ ለንባብ ከበቃበት ጊዜ አንስቶ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
“የከተማው መናኝ” መጽሐፍ የተናፋቂውን ኤልያስ መልካ አነጋጋሪ የግል ፍልስፍና እና የሕይወት ውጣ ውረድ የሚተርክ ሲሆን መጽሐፉ በወጣበት ዓመትም በኢ-ልብወለድ ዘርፍ ከዓመቱ አምስት ምርጥ መጽሐፍት አንዱ ለመሆን በቅቷል፡፡
ይነገር ጌታቸው (ማዕረግ) በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ላይ ምርምርን በማድረግ የሚታወቅ ሲሆን በ2015 ዓ.ም ሙዚቃ፣ታሪክና ፖለቲካ ላይ ያተኮረውን “ጠመንጃና ሙዚቃ” የተሰኘ መጽሐፍ ለአንባብያን አድርሷል፡፡
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤9🔥3👍1
📌ሚሊኒየም አዳራሽ ፈርሶ በድጋሚ ሊገነባ ነው
በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው እና በተለምዶ ሚሊኒየም አዳራሽ በመባል የሚታወቀው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት ከታህሳስ 2018 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ እንደሚገነባ ተገለጸ።
በ2000 ዓ.ም. አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ግዙፍ አዳራሽ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ታላላቅ አዳራሾች ግንባር ቀደሙ ነው።
አዲሱ ግንባታ የአዳራሹን አቅም እና ዘመናዊነት ይበልጥ እንደሚያሳድግ ሲጠበቅ፣ ለግንባታው የሚወጣው ኢንቨስትመንት መጠን እና የስራ ተቋራጩ ማንነት በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል።
ሚሊኒየም አዳራሽ በ20 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ በአንድ ጊዜ እስከ 25,000 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም አለው።
ይህ አዳራሽ ከትልልቅ ብሔራዊ ፕሮግራሞች፣ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ኃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የምርቃት ስነስርዓቶች በተጨማሪ፣ ታላላቅ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ለሽኝት ስነስርዓቶች ጭምር ሚናውን ሲጫወት መቆየቱ ከካፒታል መግለጫው ተመልክቷል።
በሰኔ ወር 2017 ምሽት ላይ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ የተለመደውን አገልግሎት እየሰጠ በነበረበት ወቅት ድንገተኛ የእሳት አደጋ እንደገጠመው ታውቋል። የዚህ ችግር ምንጭ ለጊዜው በሚመለከተው አካል እየተጣራ በመሆኑ፣ ጊዜው ሲደርስ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከ 17 ዓመታት በኃላ አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ መገንባት ለወደፊቱ ለተለያዩ ዝግጅቶች የተሻለ እና ዘመናዊ የመስተንግዶ አማራጭ እንደሚሰጥ ይጠበቃል ተብሏል።
Via ካፒታል ጋዜጣ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው እና በተለምዶ ሚሊኒየም አዳራሽ በመባል የሚታወቀው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት ከታህሳስ 2018 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ እንደሚገነባ ተገለጸ።
በ2000 ዓ.ም. አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ግዙፍ አዳራሽ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ታላላቅ አዳራሾች ግንባር ቀደሙ ነው።
አዲሱ ግንባታ የአዳራሹን አቅም እና ዘመናዊነት ይበልጥ እንደሚያሳድግ ሲጠበቅ፣ ለግንባታው የሚወጣው ኢንቨስትመንት መጠን እና የስራ ተቋራጩ ማንነት በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል።
ሚሊኒየም አዳራሽ በ20 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ በአንድ ጊዜ እስከ 25,000 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም አለው።
ይህ አዳራሽ ከትልልቅ ብሔራዊ ፕሮግራሞች፣ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ኃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የምርቃት ስነስርዓቶች በተጨማሪ፣ ታላላቅ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ለሽኝት ስነስርዓቶች ጭምር ሚናውን ሲጫወት መቆየቱ ከካፒታል መግለጫው ተመልክቷል።
በሰኔ ወር 2017 ምሽት ላይ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ የተለመደውን አገልግሎት እየሰጠ በነበረበት ወቅት ድንገተኛ የእሳት አደጋ እንደገጠመው ታውቋል። የዚህ ችግር ምንጭ ለጊዜው በሚመለከተው አካል እየተጣራ በመሆኑ፣ ጊዜው ሲደርስ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከ 17 ዓመታት በኃላ አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ መገንባት ለወደፊቱ ለተለያዩ ዝግጅቶች የተሻለ እና ዘመናዊ የመስተንግዶ አማራጭ እንደሚሰጥ ይጠበቃል ተብሏል።
Via ካፒታል ጋዜጣ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤14👍1👏1
📌የዘሪቱ ከበደ የመዝሙር ዝግጅት ሊካሄድ ነው
በዘመናዊ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በድምጻዊነቷና በግጥም ችሎታዋ ከፍተኛ ስምን ያተረፈችውና በኋላም ሙሉ ጊዜዋን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ወደ ዝማሬ ዓለም የገባችው ዘሪቱ ከበደ፣ “ማጽናናትህ” በሚል ርዕስ አዲስ የመዝሙርና የምስክርነት ዝግጅት ማዘጋጀቷን አስታውቃለች።
ይህ ዝግጅት፣ አርቲስቷ በህይወቷ ካሳለፈቻቸው ከባድ ውጣ ውረዶች እና ከደረሰባት ጥልቅ ሐዘን በመነሳት፣ እግዚአብሔር እንዴት እንዳጽናናት የምትመሰክርበት ልዩ መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዘሪቱ ከበደ በሙዚቃው ዓለም በከፍተኛ ዝና ላይ በነበረችበት ወቅት ከገጠማት የህይወት ለውጥ አንስቶ፣ በተለይም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ህጻን ልጇን በሞት በማጣቷ ምክንያት የደረሰባትን ከባድ ሐዘን በይፋ መናገሯ ይታወሳል። የ"ማጽናናትህ" ዝግጅት ርዕስም በቀጥታ ከዚሁ የግል የህይወት ምዕራፍ ጋር የተያያዘ ነው።
ይህ የምስክርነት ምሽት ዘሪቱ ከደረሰባት ከባድ የሐዘን ስሜትና የህይወት ፈተና ውስጥ ያለፈችበትን መንገድ እና ያገኘችውን መንፈሳዊ መጽናናት ለሌሎች የምታካፍልበት መድረክ ይሆናል። ዝግጅቱ፣ የግል ስቃይን ወደ ህዝባዊ የተስፋ መልዕክት የመቀየር ጥልቅ መንፈሳዊ አንድምታ ያለው ሲሆን፣ በህይወታቸው ተመሳሳይ ፈተና ላለፈባቸው ብዙዎች መጽናናትንና መነቃቃትን ይሰጣል ተብሎ ይታመናል።
የዝግጅቱ ዝርዝር:
የዝግጅቱ ስም፦ ማጽናናትህ (የመዝሙርና የምስክርነት ምሽት)
ቀን፦ ነሐሴ 10, 2017 ዓ.ም. | August 16, 2025
ቦታ፦Beza International Church
©️ዘ-ሐበሻ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በዘመናዊ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በድምጻዊነቷና በግጥም ችሎታዋ ከፍተኛ ስምን ያተረፈችውና በኋላም ሙሉ ጊዜዋን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ወደ ዝማሬ ዓለም የገባችው ዘሪቱ ከበደ፣ “ማጽናናትህ” በሚል ርዕስ አዲስ የመዝሙርና የምስክርነት ዝግጅት ማዘጋጀቷን አስታውቃለች።
ይህ ዝግጅት፣ አርቲስቷ በህይወቷ ካሳለፈቻቸው ከባድ ውጣ ውረዶች እና ከደረሰባት ጥልቅ ሐዘን በመነሳት፣ እግዚአብሔር እንዴት እንዳጽናናት የምትመሰክርበት ልዩ መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዘሪቱ ከበደ በሙዚቃው ዓለም በከፍተኛ ዝና ላይ በነበረችበት ወቅት ከገጠማት የህይወት ለውጥ አንስቶ፣ በተለይም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ህጻን ልጇን በሞት በማጣቷ ምክንያት የደረሰባትን ከባድ ሐዘን በይፋ መናገሯ ይታወሳል። የ"ማጽናናትህ" ዝግጅት ርዕስም በቀጥታ ከዚሁ የግል የህይወት ምዕራፍ ጋር የተያያዘ ነው።
ይህ የምስክርነት ምሽት ዘሪቱ ከደረሰባት ከባድ የሐዘን ስሜትና የህይወት ፈተና ውስጥ ያለፈችበትን መንገድ እና ያገኘችውን መንፈሳዊ መጽናናት ለሌሎች የምታካፍልበት መድረክ ይሆናል። ዝግጅቱ፣ የግል ስቃይን ወደ ህዝባዊ የተስፋ መልዕክት የመቀየር ጥልቅ መንፈሳዊ አንድምታ ያለው ሲሆን፣ በህይወታቸው ተመሳሳይ ፈተና ላለፈባቸው ብዙዎች መጽናናትንና መነቃቃትን ይሰጣል ተብሎ ይታመናል።
የዝግጅቱ ዝርዝር:
የዝግጅቱ ስም፦ ማጽናናትህ (የመዝሙርና የምስክርነት ምሽት)
ቀን፦ ነሐሴ 10, 2017 ዓ.ም. | August 16, 2025
ቦታ፦Beza International Church
©️ዘ-ሐበሻ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤9👎5👍2🙏1
📌ነፃ የሞዴሊንግ እስኮላርሺፕ ዕድል
ሞዴል መሆን ይፈልጋሉ ?
ፕሪስቴጅ አዲስ ከሌጋሲ ሞዴሊንግ ኤጀንሲ ጋር በጋራ በመሆን ነፃ የሞዴሊንግ ስልጠና ለእናንተ ይዞላችሁ መጥቷል።
የዚህ እድል ተካፋይ መሆን የምትፈልጉ ከታች ያለውን መስፈርት ማሟላት ይኖርባችኋል።
✅የፕሪስቴጅ አዲስ እና ሌጋሲ ሞዴሊንግ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ቻናል ፎሎ ያድርጉ ።
✅ይሄንን ፖስት የተደረገውን ሼር በማድረግ ኢንስታግራም ስቶሪ ላይ ያጋሩ ፣ ሁለቱንም ቻናሎች ታግ ያድርጉ ።
✅ ኮሜንት ላይ ፍላጎት ያላቸውን ሶስት ሰዎችን ታግ ያድርጉ።
✅በኮሜንት ሃሳብ መስጫ ላይ ሌጋሲ ሞዴሊንግ መማር ለምን እንደምትፈልጉ እና ይሄንን እድል ላንቺ / ላንተ ለምን እድሉ መሰጠት እንዳለበት ግለፅ/ጪ ።
✅ ይሄ እድል ከ 16 ዓመት እስከ 30 ዓመት ለሆኑት ክፍት ነው።
✅ ምንም አይነት የሞዴሊንግ ልምድ አይጠይቅም - ለጀማሪዎች ክፍት ነው ።
✅ #ፕሪስቴጅአዲስ እና #ሌጋሲሞዴኒንግ ሃሽታጎችን ይጠቀሙ ።
የዚህ እድል ተካፋይ ለመሆን የ @prestigeaddis ኢንስታግራም ገፅ ላይ በመግባት ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት በማሟላት መሳተፍ ይችላሉ።
መልካም ዕድል
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
ሞዴል መሆን ይፈልጋሉ ?
ፕሪስቴጅ አዲስ ከሌጋሲ ሞዴሊንግ ኤጀንሲ ጋር በጋራ በመሆን ነፃ የሞዴሊንግ ስልጠና ለእናንተ ይዞላችሁ መጥቷል።
የዚህ እድል ተካፋይ መሆን የምትፈልጉ ከታች ያለውን መስፈርት ማሟላት ይኖርባችኋል።
✅የፕሪስቴጅ አዲስ እና ሌጋሲ ሞዴሊንግ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ቻናል ፎሎ ያድርጉ ።
✅ይሄንን ፖስት የተደረገውን ሼር በማድረግ ኢንስታግራም ስቶሪ ላይ ያጋሩ ፣ ሁለቱንም ቻናሎች ታግ ያድርጉ ።
✅ ኮሜንት ላይ ፍላጎት ያላቸውን ሶስት ሰዎችን ታግ ያድርጉ።
✅በኮሜንት ሃሳብ መስጫ ላይ ሌጋሲ ሞዴሊንግ መማር ለምን እንደምትፈልጉ እና ይሄንን እድል ላንቺ / ላንተ ለምን እድሉ መሰጠት እንዳለበት ግለፅ/ጪ ።
✅ ይሄ እድል ከ 16 ዓመት እስከ 30 ዓመት ለሆኑት ክፍት ነው።
✅ ምንም አይነት የሞዴሊንግ ልምድ አይጠይቅም - ለጀማሪዎች ክፍት ነው ።
✅ #ፕሪስቴጅአዲስ እና #ሌጋሲሞዴኒንግ ሃሽታጎችን ይጠቀሙ ።
የዚህ እድል ተካፋይ ለመሆን የ @prestigeaddis ኢንስታግራም ገፅ ላይ በመግባት ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት በማሟላት መሳተፍ ይችላሉ።
መልካም ዕድል
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤1
📌ገጣሚና ሠዓሊ ከበደች ተክለአብ ልምዷን ታጋራለች
በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል ገጣሚና ሠዓሊ ከበደች ተክለአብ በሥራዎቿና በሕይወቷ ዙሪያ ልምዷን ታጋራለች፡፡
በዕለቱ ስለገጣሚነቷ፣ ስለሠዓሊነቷ፣ በሶማሊያ ሐዋይ የ10 ዓመታት የእስር ቤት ቆይታዋ፣ በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በተማሪነትም በመምህርነትም ስላሳለፈቻቸው ዓመታት ታወጋናለች፡፡
ዝግጅቱ የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 19፣ 2017 ከ8 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይቀርባል፡፡
ይህ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ትብብር በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር አማካኝነት የሚሰናዳው የክረምት ወራት የሥነ ጽሑፍ ሥልጠና አንዱ አካል ነው፡፡
የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል በዝግጅቱ እንዲታደሙ ግበዣውን ያቀርባል፡፡
የዝግጅቱ ቦታ:- በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ (በንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል ገባ ብሎ)፡፡ https://maps.app.goo.gl/yb1LFT7PDTwLUP217
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል ገጣሚና ሠዓሊ ከበደች ተክለአብ በሥራዎቿና በሕይወቷ ዙሪያ ልምዷን ታጋራለች፡፡
በዕለቱ ስለገጣሚነቷ፣ ስለሠዓሊነቷ፣ በሶማሊያ ሐዋይ የ10 ዓመታት የእስር ቤት ቆይታዋ፣ በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በተማሪነትም በመምህርነትም ስላሳለፈቻቸው ዓመታት ታወጋናለች፡፡
ዝግጅቱ የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 19፣ 2017 ከ8 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይቀርባል፡፡
ይህ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ትብብር በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር አማካኝነት የሚሰናዳው የክረምት ወራት የሥነ ጽሑፍ ሥልጠና አንዱ አካል ነው፡፡
የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል በዝግጅቱ እንዲታደሙ ግበዣውን ያቀርባል፡፡
የዝግጅቱ ቦታ:- በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ (በንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል ገባ ብሎ)፡፡ https://maps.app.goo.gl/yb1LFT7PDTwLUP217
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤12👍4🤔1
📌“አፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና ሥራዎቹ” መጽሐፍ ተመረቀ
በዶ/ር አንዱአለም አባተ (የአጸደ ልጅ) እና በኢንጅነር ቴዎድሮስ ደመቀ የተጻፈ “አፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና ሥራዎቹ” የተሰኘ መጽሐፍ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተመርቋል፡፡
በመርሀ- ግብሩ ላይ ገጣሚና አዘጋጅ ጌትነት እንየው እና በዶ/ር ገዛኸኝ ጸጋው ከመጽሐፉ ውስጥ የተወሰኑ ቅንጭብ ታሪኮች ተነበዋል።
ከዚህ በተጨማሪም፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኀበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ ምክትል ዲን በዶ/ር ሲሳይ ሳህሌ አማካኝነት መጽሐፉን የሚዳስስ ጥልቅ ሀሳብ የያዘ ጽሑፍ ቀርቧል።
መጽሐፉ የመካከለኛውን ዘመን ታላቅ ንጉስ የአፄ ዘርዐ ያዕቆብን የሕይወት ታሪክና ሥራዎች የሚያስዳስስ ሲሆን 19 ምዕራፎች እና 542 ገጾች አሉት።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በዶ/ር አንዱአለም አባተ (የአጸደ ልጅ) እና በኢንጅነር ቴዎድሮስ ደመቀ የተጻፈ “አፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና ሥራዎቹ” የተሰኘ መጽሐፍ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተመርቋል፡፡
በመርሀ- ግብሩ ላይ ገጣሚና አዘጋጅ ጌትነት እንየው እና በዶ/ር ገዛኸኝ ጸጋው ከመጽሐፉ ውስጥ የተወሰኑ ቅንጭብ ታሪኮች ተነበዋል።
ከዚህ በተጨማሪም፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኀበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ ምክትል ዲን በዶ/ር ሲሳይ ሳህሌ አማካኝነት መጽሐፉን የሚዳስስ ጥልቅ ሀሳብ የያዘ ጽሑፍ ቀርቧል።
መጽሐፉ የመካከለኛውን ዘመን ታላቅ ንጉስ የአፄ ዘርዐ ያዕቆብን የሕይወት ታሪክና ሥራዎች የሚያስዳስስ ሲሆን 19 ምዕራፎች እና 542 ገጾች አሉት።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤6👍2
📌የኢትዮጵያ ልጆች ሱፐር አፕ ተመረቀ
የኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ በሀገራችን የሙሉ ጊዜ የልጆች የቴሌቪዠን ቻናል በመጀመር ፈርቀዳጅ የሆነና በተለይም በልጆችና ቤተሰቦቻቸው ዘንድ ሠፊ ተቀባይነት በማግኘት በአወንታዊ የትውልድ ግንባታ ላይ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው ይህንን መተግበርያ ይፋ ያደረገው።
ተቋሙ አላማና ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት በማሰብ መተግበርያውን ማበልጸጉን ይፋ አድርጓል።
በባለፉት አስርት አመታት በልጆች ዙርያ የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ የቆየው ተቋሙ በባለፉት ሰባት አመታት ደግሞ በኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን የልጆች ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን ያስመረቀው ይህ መተግበርያ በውስጡ 10 የሚሆኑ ይዘቶችን ማካተቱን ነው የተገለጸው።
መተግበርያው ያበለጸገው መሁቡብ ቴክኖሎጂስ መተግበርያው ለልጆች አመቺ የሆነና አጠቃቀም ተብሎ ቀለል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን ስራ አስኪያጅ ህብስት አሰፋ እንደተናገሩት በተመደቡበት የስራ ዘርፍ ተሰልፈው ከመጋረጃ ጀርባ ያሉ የተቋሙ ሰራተኞች እና ባለሙያዎች ምስጋና ይግባና ዛሬ ለዚህ በቅተናል ብለዋል።
ተቋማችን እዚህ ለመድረሱ ሚስጥር የልጆቻችን ወላጆች ናቸው ያሉት ስራ አስኪያጇ ስላደረጋችሁት ሁሉ ነገር እናመሰግናለን ብለዋል።
©️ድሬቲዩብ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ በሀገራችን የሙሉ ጊዜ የልጆች የቴሌቪዠን ቻናል በመጀመር ፈርቀዳጅ የሆነና በተለይም በልጆችና ቤተሰቦቻቸው ዘንድ ሠፊ ተቀባይነት በማግኘት በአወንታዊ የትውልድ ግንባታ ላይ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው ይህንን መተግበርያ ይፋ ያደረገው።
ተቋሙ አላማና ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት በማሰብ መተግበርያውን ማበልጸጉን ይፋ አድርጓል።
በባለፉት አስርት አመታት በልጆች ዙርያ የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ የቆየው ተቋሙ በባለፉት ሰባት አመታት ደግሞ በኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን የልጆች ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን ያስመረቀው ይህ መተግበርያ በውስጡ 10 የሚሆኑ ይዘቶችን ማካተቱን ነው የተገለጸው።
መተግበርያው ያበለጸገው መሁቡብ ቴክኖሎጂስ መተግበርያው ለልጆች አመቺ የሆነና አጠቃቀም ተብሎ ቀለል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዠን ስራ አስኪያጅ ህብስት አሰፋ እንደተናገሩት በተመደቡበት የስራ ዘርፍ ተሰልፈው ከመጋረጃ ጀርባ ያሉ የተቋሙ ሰራተኞች እና ባለሙያዎች ምስጋና ይግባና ዛሬ ለዚህ በቅተናል ብለዋል።
ተቋማችን እዚህ ለመድረሱ ሚስጥር የልጆቻችን ወላጆች ናቸው ያሉት ስራ አስኪያጇ ስላደረጋችሁት ሁሉ ነገር እናመሰግናለን ብለዋል።
©️ድሬቲዩብ
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍4
📌ከአንድ መቶ በላይ ተዋንያን የሚሳተፉበት "ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ነገ ለመድረክ ይበቃል
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተጽፎ በተሻለ አሰፋ (ዶ/ር) የተዘጋጀውና መሠረት ሕይወት ረዳት አዘጋጅ የሆነችበት "ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ከበርካታ ዓመታት በኃላ በድጋሚ ነገ ሐምሌ 20 2017 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ከቀኑ 8፡30 ላይ ወደ መድረክ ይመለሳል።
"ንጉሥ አርማህ" ወደ መድረክ ሲመለስ ከመቶ በላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን እንደሚሳተፉበት ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቴአትሩ ደራሲ አቶ መልካሙ ዘሪሁን ቴአትሩ ከተጻፈ 24 ዓመት እንደሆነ አስታውሶ ዛሬ ላይ ግን ትውልዱንና ያለንበትን ዘመንን በሚዋጅ ሁኔታ አብሮነት፣አንድነትን በንጉሥ አርማህ ታሪክና አስተዋይነት ውስጥ ቴአትሩ መዘጋጀቱን ገልጿል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተጽፎ በተሻለ አሰፋ (ዶ/ር) የተዘጋጀውና መሠረት ሕይወት ረዳት አዘጋጅ የሆነችበት "ንጉሥ አርማህ" ተውኔት ከበርካታ ዓመታት በኃላ በድጋሚ ነገ ሐምሌ 20 2017 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ከቀኑ 8፡30 ላይ ወደ መድረክ ይመለሳል።
"ንጉሥ አርማህ" ወደ መድረክ ሲመለስ ከመቶ በላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን እንደሚሳተፉበት ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቴአትሩ ደራሲ አቶ መልካሙ ዘሪሁን ቴአትሩ ከተጻፈ 24 ዓመት እንደሆነ አስታውሶ ዛሬ ላይ ግን ትውልዱንና ያለንበትን ዘመንን በሚዋጅ ሁኔታ አብሮነት፣አንድነትን በንጉሥ አርማህ ታሪክና አስተዋይነት ውስጥ ቴአትሩ መዘጋጀቱን ገልጿል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍4❤2
📌ጋዜጠኛ የኃላሸት ዘሪሁን በትወና የመጣበት "ወደ ማዶ" የተሰኘው ትያትር በ30 የዓለም ሀገራት መድረኮች ለዕይታ ሊቀርብ ነው።
የኪነ-ብስራት እና የነገረ ኪን የሬድዮ ፕሮግራሞች አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ የኃላሸት ዘሪሁን በትወና የመጣበትና "ወደ ማዶ" የተሰኘ ተውኔት ዓለም አቀፍ የቲያትር ጉዞ ሊጀመር መሆኑ ተነግሯል።
በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተደርሶ በሴም አማኑኤል የተዘጋጀው "ወደ ማዶ" ትያትር የኮሜዲ ዘውግ ያለው ማህበራዊ ጉዳዮችን እያነሳ የሚሄድ፣ ሲሆን በሕይወታችን የሚገጥሙን ችግሮች ለማውጣት የሚደረግን ትንቅንቅ የሚያሳይ ነው።
በትያትሩ ላይ ሃረገወይን አሰፋ፣ ሽዋፈራው ደሳለኝ እና የኋላእሸት ዘሪሁን ይተውኑብታል ተብሏል።
"ወደ ማዶ" ዓለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ አህጉራት በሚገኙ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ30 በላይ መድረኮች እንደሚታይ ተገልጿል።
በተጨማሪም እስካሁን ባልተለመደ መልኩ ትያትሩ በሚታይባቸው ሀገራትና መድረኮች ከትያትሩ ጎን ለጎን ለየኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ይህንንም በጎ አላማ ለማሳካት ከማዕከሉ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የኪነ-ብስራት እና የነገረ ኪን የሬድዮ ፕሮግራሞች አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ የኃላሸት ዘሪሁን በትወና የመጣበትና "ወደ ማዶ" የተሰኘ ተውኔት ዓለም አቀፍ የቲያትር ጉዞ ሊጀመር መሆኑ ተነግሯል።
በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተደርሶ በሴም አማኑኤል የተዘጋጀው "ወደ ማዶ" ትያትር የኮሜዲ ዘውግ ያለው ማህበራዊ ጉዳዮችን እያነሳ የሚሄድ፣ ሲሆን በሕይወታችን የሚገጥሙን ችግሮች ለማውጣት የሚደረግን ትንቅንቅ የሚያሳይ ነው።
በትያትሩ ላይ ሃረገወይን አሰፋ፣ ሽዋፈራው ደሳለኝ እና የኋላእሸት ዘሪሁን ይተውኑብታል ተብሏል።
"ወደ ማዶ" ዓለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ አህጉራት በሚገኙ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ30 በላይ መድረኮች እንደሚታይ ተገልጿል።
በተጨማሪም እስካሁን ባልተለመደ መልኩ ትያትሩ በሚታይባቸው ሀገራትና መድረኮች ከትያትሩ ጎን ለጎን ለየኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ይህንንም በጎ አላማ ለማሳካት ከማዕከሉ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤5👍2
📌የታገል ሰይፉ "የእኔ ደማቅ ሠዎች" ለንባብ በቃ
ገጣሚና ደራሲ ታገል ሰይፉ "የእኔ ደማቅ ሠዎች" ሲል የሰየመውን አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ እንዳቀረበ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከጃፋር መጽሐፍ መደብር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
መጽሐፉ ስለ ከያኒያኑ ሙሉጌታ ተስፋዬ፣ሐዲስ አለማየሁ፣ስብሐት ገ/እግዚአብሔር፣ደበበ ሰይፉ እና ስለ ሌሎችም ሰዎች ያልተሰሙ መረጃዎችን የያዘ እንደሆነ ተነግሯል።
ታገል ሰይፉ ''የእኔ ደማቅ ሰዎች'' በሚል ርዕስ አስቀድሞ ተከታታይ ቪዲዮዎችን በዩቱብ ቻነሉ ሲለቅ እንደቆየ ይታወሳል።
"የእኔ ደማቅ ሰዎች" መጽሐፍ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
ገጣሚና ደራሲ ታገል ሰይፉ "የእኔ ደማቅ ሠዎች" ሲል የሰየመውን አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ እንዳቀረበ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከጃፋር መጽሐፍ መደብር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
መጽሐፉ ስለ ከያኒያኑ ሙሉጌታ ተስፋዬ፣ሐዲስ አለማየሁ፣ስብሐት ገ/እግዚአብሔር፣ደበበ ሰይፉ እና ስለ ሌሎችም ሰዎች ያልተሰሙ መረጃዎችን የያዘ እንደሆነ ተነግሯል።
ታገል ሰይፉ ''የእኔ ደማቅ ሰዎች'' በሚል ርዕስ አስቀድሞ ተከታታይ ቪዲዮዎችን በዩቱብ ቻነሉ ሲለቅ እንደቆየ ይታወሳል።
"የእኔ ደማቅ ሰዎች" መጽሐፍ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤8
📌ስብሐቲዝም ስለመንግሥቱ ኃይለማርያም
ደራሲና ገጣሚ ይታገሡ ጌትነት የክብር እንግዳ የሆነበት ስብሐቲዝም 93ተኛ መድረክ "መንግሥቱ ኃይለማርያም 'ከፖለቲካ ባሻገር" በሚል የሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።
የስብሐቲዝም አዘጋጆች ተከታዩን ብለዋል" ይታገሡ ጌትነት ነው የ93ኛ መድረክ እንግዳ። ስለ ሊቀ መንበር መንግስቱ ከፖለቲካ ገጽታቸው እስከ ግለሰባዊ ማንነታቸው የሚያወጋን እርሳቸውን አግኝቶ በበቃ ብዕር የተከተበልን ይታገሡ ነው።
ደራሲው ስለጻፈ ብቻ ሳይሆን ከልጅነት ጀምሮ እርሳቸውን ያውቃል። ስለሆነም ከሌላው በተለየ የሚነግረንን ሙሉ ያደርገዋል" ።
ውይይቱ ነገ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይከናወናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ደራሲና ገጣሚ ይታገሡ ጌትነት የክብር እንግዳ የሆነበት ስብሐቲዝም 93ተኛ መድረክ "መንግሥቱ ኃይለማርያም 'ከፖለቲካ ባሻገር" በሚል የሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።
የስብሐቲዝም አዘጋጆች ተከታዩን ብለዋል" ይታገሡ ጌትነት ነው የ93ኛ መድረክ እንግዳ። ስለ ሊቀ መንበር መንግስቱ ከፖለቲካ ገጽታቸው እስከ ግለሰባዊ ማንነታቸው የሚያወጋን እርሳቸውን አግኝቶ በበቃ ብዕር የተከተበልን ይታገሡ ነው።
ደራሲው ስለጻፈ ብቻ ሳይሆን ከልጅነት ጀምሮ እርሳቸውን ያውቃል። ስለሆነም ከሌላው በተለየ የሚነግረንን ሙሉ ያደርገዋል" ።
ውይይቱ ነገ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይከናወናል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3
📌በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው ባለ 11 ወለል ግዙፍ የሲኒማና ቴአትር አዳራሽ እየተጠናቀቀ ይገኛል ተባለ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ መንገድ ፍላሚንጎ አካባቢ እያስገነባው ያለው ባለ 11ወለል የህጻናት ቴአትርና ሲኒማ አዳራሽ ህንጻ ግንባታ ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል ።
ዋንኛው የቴአትር አዳራሹ 1300 ሰዎች መያዝ የሚችል ሲሆን ፣ ሌሎች ሁለት መካከለኛ የሲኒማ አዳራሾችም በህንጻው ግንባታ ውስጥ ተካትተዋል። የዋንኛው ቲያትር አዳራሽ መድረክ በሀይድሬሊክ ሲስተም 360 ዲግሪ መሽከርከር እንዲችል ተደርጎ የተሰራ ነው።
©️Samson michailovich
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ መንገድ ፍላሚንጎ አካባቢ እያስገነባው ያለው ባለ 11ወለል የህጻናት ቴአትርና ሲኒማ አዳራሽ ህንጻ ግንባታ ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል ።
ዋንኛው የቴአትር አዳራሹ 1300 ሰዎች መያዝ የሚችል ሲሆን ፣ ሌሎች ሁለት መካከለኛ የሲኒማ አዳራሾችም በህንጻው ግንባታ ውስጥ ተካትተዋል። የዋንኛው ቲያትር አዳራሽ መድረክ በሀይድሬሊክ ሲስተም 360 ዲግሪ መሽከርከር እንዲችል ተደርጎ የተሰራ ነው።
©️Samson michailovich
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🔥7👍3❤1👏1
📌የደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል "የወዲያነሽ" የልቦለድ መጽሐፍ ዳግም ሊታተም ነው።
የተወዳጁ ደራሲ፣ አርታኢ እና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል "የወዲያነሽ" መጽሐፍ ከአስር ዓመታት በኋላ ዳግም በቅድም ክፍያ ሽያጭ ለሕትመት ይበቃል ተብሏል።
መፅሐፉ ከ39 ዓመታት በፊት በ1978 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሞ ለአንባቢያን ሲደርስ በ5.50 ዋጋ እንደነበር ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ከእዚያ በኋላ በተለያዩ አጋጣሚዎች መታተሙን አስታውሷል።
ከአስር ዓመታት በፊት በ2007 ዓ.ም ለመጨረሻ ጊዜ መታተሙን በመጥቀስ የመፅሀፉ ፈላጊዎች ቁጥር መበራከት ለዳግም ሕትመቱ ምክንያት እንደሆነ ጠቅሷል።
"የወዲያነሽ" መጽሐፍ ድጋሚ ሲታተም የጀርባ ዋጋው 400 ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000571154319(ኃይለመለኮት መዋዕል ) ብር በማስገባት መጽሐፉን ቀድማችሁ መግዛት ትችላላችሁ ተብላችኋል።
የቀድመ ሽያጭ አስተባባሪዎች "መጽሐፍ ስትገዙ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በውስጥ ላኩልን https://shorturl.at/F7POF መጽሐፏ ከህትመት ሲወጣ በምረቃዋ ዕለት ወይም በሌላም መንገዶች ሁሉ ይደርሷችኋል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የወዲያነሽ"ን ተከትሎ ሌላኛው የደራሲው ተወዳጅ ስራ "ጉንጉን" ዳግም እንደሚታተም በመግለፅ "የአዕምሮ ማህፀን ጤና ካለ አይመክንም፣ ከሰራህበት ሁል ጊዜ እየፋፋ እያደገ ነው የሚሄደው" ያለው ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ከእዚህ በኋላ ባለው ጊዜ አዳዲስ ሥራዎችን ለማበርከት እንደጥር ጠቁሟል።
ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል "የአርትኦት ሥራዎችን አቁሜያለሁ" ያለ ሲሆን "ከፈጣሪ ፍቃድ ጋር"በቀጣዩ ዓመት አዲስ ስራ ሊኖር እንደሚችል ተናግሯል።
©️FM Addis 97.1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የተወዳጁ ደራሲ፣ አርታኢ እና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል "የወዲያነሽ" መጽሐፍ ከአስር ዓመታት በኋላ ዳግም በቅድም ክፍያ ሽያጭ ለሕትመት ይበቃል ተብሏል።
መፅሐፉ ከ39 ዓመታት በፊት በ1978 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሞ ለአንባቢያን ሲደርስ በ5.50 ዋጋ እንደነበር ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ከእዚያ በኋላ በተለያዩ አጋጣሚዎች መታተሙን አስታውሷል።
ከአስር ዓመታት በፊት በ2007 ዓ.ም ለመጨረሻ ጊዜ መታተሙን በመጥቀስ የመፅሀፉ ፈላጊዎች ቁጥር መበራከት ለዳግም ሕትመቱ ምክንያት እንደሆነ ጠቅሷል።
"የወዲያነሽ" መጽሐፍ ድጋሚ ሲታተም የጀርባ ዋጋው 400 ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000571154319(ኃይለመለኮት መዋዕል ) ብር በማስገባት መጽሐፉን ቀድማችሁ መግዛት ትችላላችሁ ተብላችኋል።
የቀድመ ሽያጭ አስተባባሪዎች "መጽሐፍ ስትገዙ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በውስጥ ላኩልን https://shorturl.at/F7POF መጽሐፏ ከህትመት ሲወጣ በምረቃዋ ዕለት ወይም በሌላም መንገዶች ሁሉ ይደርሷችኋል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የወዲያነሽ"ን ተከትሎ ሌላኛው የደራሲው ተወዳጅ ስራ "ጉንጉን" ዳግም እንደሚታተም በመግለፅ "የአዕምሮ ማህፀን ጤና ካለ አይመክንም፣ ከሰራህበት ሁል ጊዜ እየፋፋ እያደገ ነው የሚሄደው" ያለው ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ከእዚህ በኋላ ባለው ጊዜ አዳዲስ ሥራዎችን ለማበርከት እንደጥር ጠቁሟል።
ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል "የአርትኦት ሥራዎችን አቁሜያለሁ" ያለ ሲሆን "ከፈጣሪ ፍቃድ ጋር"በቀጣዩ ዓመት አዲስ ስራ ሊኖር እንደሚችል ተናግሯል።
©️FM Addis 97.1
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤10
📌 DStv ሙሉ በሙሉ ለካናል ፕላስ ተሸጠ
የፈረንሳዩ ተቋም ካናል ፕላስ የደቡብ አፍሪካውን መልቲቾይዝ ግሩፕ (DStv) በ3 ቢሊየን ዶላር ገዝቶታል።
ካናል ፕላስ መጀመሪያውንም ቢሆን የመልቲቾይዝ 45 በመቶ ባለድርሻ የነበረ ሲሆን አሁን ሙሉ ለሙሉ ድርሻውን ገዝቶታል።
መልቲቾይዝ ለ40 አመታት የቆየ ስም የገነባ መሆኑ ሲገለፅ በአፍሪካ ከ50 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት ይገለፃል።
መልቲቾይዝ በክፍያ ከሚሰሩ የቴሌቪዥን ገበያዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን በዲ ኤስ ቲቪ እና ጎቲቪ በኩል የተለያዩ የስፖርት እና የመዝናኛ ፕሮግራሞችን በክፍያ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።
ግዢው ሙሉ ለሙሉ በመጪው ጥቅምት ይጠናቀቃል ተብሎ ሲጠበቅ ካናል+ የደቡብ አፍሪካን ፕሮዳክሽን በአዲስ ገበያዎች የማስተዋወቅ ኃላፊነት ተጥሎበታል።
ደቡብ አፍሪካ በህጓ የደቡብ አፍሪካን የስርጭት መብት የያዘ ድርጅት ባለቤትነቱ ከ20 በመቶ በላይ በውጪ ዜጋ መያዝን ስለምትከለክል መልቲቾይዝ የስርጭት መብቱን ላይሰንስኮ በተሰኘ ድርጅት ማድረጉ ተሰምቷል።
መልቲቾይዝ ሃገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በዲ ኤስ ቲቪ በኩል የእግር ኳስ እና የመዝናኛ ፕሮግራሞችንም ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ካናል+ በበኩሉ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ከገባ በኋላ የክፍያ ቴሌቪዥኑን በመዝጋት ወደ ሌላ አማራጮች ማዞሩን ከወራት በፊት መግለፁ ይታወሳል።
©️TikvahethMagazine
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የፈረንሳዩ ተቋም ካናል ፕላስ የደቡብ አፍሪካውን መልቲቾይዝ ግሩፕ (DStv) በ3 ቢሊየን ዶላር ገዝቶታል።
ካናል ፕላስ መጀመሪያውንም ቢሆን የመልቲቾይዝ 45 በመቶ ባለድርሻ የነበረ ሲሆን አሁን ሙሉ ለሙሉ ድርሻውን ገዝቶታል።
መልቲቾይዝ ለ40 አመታት የቆየ ስም የገነባ መሆኑ ሲገለፅ በአፍሪካ ከ50 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት ይገለፃል።
መልቲቾይዝ በክፍያ ከሚሰሩ የቴሌቪዥን ገበያዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን በዲ ኤስ ቲቪ እና ጎቲቪ በኩል የተለያዩ የስፖርት እና የመዝናኛ ፕሮግራሞችን በክፍያ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።
ግዢው ሙሉ ለሙሉ በመጪው ጥቅምት ይጠናቀቃል ተብሎ ሲጠበቅ ካናል+ የደቡብ አፍሪካን ፕሮዳክሽን በአዲስ ገበያዎች የማስተዋወቅ ኃላፊነት ተጥሎበታል።
ደቡብ አፍሪካ በህጓ የደቡብ አፍሪካን የስርጭት መብት የያዘ ድርጅት ባለቤትነቱ ከ20 በመቶ በላይ በውጪ ዜጋ መያዝን ስለምትከለክል መልቲቾይዝ የስርጭት መብቱን ላይሰንስኮ በተሰኘ ድርጅት ማድረጉ ተሰምቷል።
መልቲቾይዝ ሃገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በዲ ኤስ ቲቪ በኩል የእግር ኳስ እና የመዝናኛ ፕሮግራሞችንም ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ካናል+ በበኩሉ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ከገባ በኋላ የክፍያ ቴሌቪዥኑን በመዝጋት ወደ ሌላ አማራጮች ማዞሩን ከወራት በፊት መግለፁ ይታወሳል።
©️TikvahethMagazine
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤4😱2
📌ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከህልፈቱ 17 ቀናት በኃላ ዛሬ ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈፀመ
ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ይታወሳል።ዛሬ ሀምሌ 19 ቀን 2017 ከህልፈቱ 17 ቀናት በኃላ ስርዓተ ቀብር በቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈጽሟል።
ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከጋዜጠኝነት እስከ የዜናና ወቅታዊ መረጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን "የሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርዕስ ሲያቀርበው በነበረው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካቾች ዘንድ ይታወሳል።
ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።ከትምህርቱ ጎን ለጎንም እስከ ህልፈቱ ድረስ TBS በተባለው የትግርኛ ቴሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ወቅታዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሲያቀርብ ነበር።
በ1963 ዓ/ም በትግራይ ውቕሮ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሽንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም አመታት ሰርቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ይታወሳል።ዛሬ ሀምሌ 19 ቀን 2017 ከህልፈቱ 17 ቀናት በኃላ ስርዓተ ቀብር በቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈጽሟል።
ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከጋዜጠኝነት እስከ የዜናና ወቅታዊ መረጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን "የሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርዕስ ሲያቀርበው በነበረው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካቾች ዘንድ ይታወሳል።
ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።ከትምህርቱ ጎን ለጎንም እስከ ህልፈቱ ድረስ TBS በተባለው የትግርኛ ቴሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ወቅታዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሲያቀርብ ነበር።
በ1963 ዓ/ም በትግራይ ውቕሮ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሽንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም አመታት ሰርቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤8😢3😭3
📌በቻይና ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ተሸለመች
ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ከሰሞኑ በቻይና በተካሄደው የ"Road and Belt journalist forum" ላይ ኢትዮጵያን ወክላ ተገኝታ ነበር።
በፎረሙ ከ30 በላይ ሃገራት ከተወከሉ የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ባቀረበችው ስራ ከፍ ያለ ዕውቅና ተሰጥቷት።
በዚህም ስራዋ ተሸላሚ ሆና የሀገራችንን ስም አስጠርታለች።
©️ጋዜጠኛ ያልፋል አሻግር
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ከሰሞኑ በቻይና በተካሄደው የ"Road and Belt journalist forum" ላይ ኢትዮጵያን ወክላ ተገኝታ ነበር።
በፎረሙ ከ30 በላይ ሃገራት ከተወከሉ የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ባቀረበችው ስራ ከፍ ያለ ዕውቅና ተሰጥቷት።
በዚህም ስራዋ ተሸላሚ ሆና የሀገራችንን ስም አስጠርታለች።
©️ጋዜጠኛ ያልፋል አሻግር
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤11