Event Addis Media
9.62K subscribers
6.08K photos
12 videos
4 files
4.71K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ዚሞገሩ ስንክሳር ፕሮግራም መጜሐፍ ሆነ

በጋዜጠኛ መኮንን ወ/አሹጋይ ዹተዘጋጀውና በርካታ ጉዳዮቜ ዚተካተቱበት "እነሆ ስንክሳር" ዹተሰኘ መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

በሾገር 102.1 ኀፍ ኀም ሬድዮ ለዓመታት ሲተላለፈ ዹቆዹው "ስንክሳር" ዚሬድዮ ፕሮግራም አሁን በመጜሐፍ መልክ እንደተዘጋጀም ተነግሯል።

"እነሆ ስንክሳር"መጜሐፍ ዚፊታቜን ግንቊት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለንባብ እንደሚበቃም ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጀ ያመለክታል።

መጜሐፉ በጃፋር እና በዕውቀት በር መጻሕፍት መደብሮቜ በኩል ለአንባቢያን ይኹፋፈላም ተብሏል።

ኹዚህ ቀደም በሾገር ኀፍ ኀም 102.1 ሬድዮ ላይ በሚያቀርባ቞ው ዚስንክሳር፣  ዚማሟሻ፣ ዚሃኪሞ መልዕክት፣ ዚአርብ ምሜት ቆዚት ያሉ ሙዚቃዎቜ እና በኢንቢሲ ቎ሌቪዥን በልዩ ልዩ ዝግጅቶቜ ዹምናውቀው ጋዜጠኛ መኮንን ወ/አሹጋይ "እነሆ ማሟሻ" ዹተሰኘ ዚመጀመሪያ ቅጜ አንድ እና ተኚታዩን ቅጜ ሁለት መጻህፍትን በተኚታታይ ኹዚህ ቀደም ለአንባቢያን ማድሚሱ ይታወሳል።

Telegram: https://t.me/EventAddis1
👏7👍4🔥2
📌ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ወደ አዹር ተመለሰ

ተወዳጁ ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ጣቢያ ለተወሰነ ጊዜ ኹአዹር ወርዶ እንደቆዚ ይታወሳል።

቎ሌቪዥን ጣቢያው ኚትላንት ጀምሮ ወደ አዹር እንደተመለሰም ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን በDstv ቻናል 468 እና በኢትዮሳት 11605 አሁን በስርጭት ይገኛል ተብሏል።

ትኩሚቱን ልጆቜ ላይ አድርጎ ዚሚሰራውና በጥቂት ጥሪት፣ ዹሰው ሀይል እዚህ ዹደሹሰው ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ጣቢያ በልጆቜና በቀተሰብ ዘንድ ተወዳጅ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያ እንደሆነ በርካቶቜ ይመሰክራሉ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍18❀7😱1
📌ቻናል 1 ዹመዝናኛ ቎ሌቪዥን ሊኚፈት ነው

ቻናል 1 (Channel 1) ዹተሰኘ አዲስ ዹመዝናኛ ዚ቎ሌቭዥን ጣቢያ ዚኢትዮጵያ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያዎቜን ዘርፍ ሊቀላቀል እንደሆነ ተሰምቷል።

ሰኔ ወር ላይ ዚሙኚራ ስርጭቱን እንደሚጀምር ዹተሰማዉ  ቻናል 1 ፣ ባሳለፍነዉ ሳምንት ኚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዚሳተላይት ስርጭት ፍቃድን ተሚክቧል።

ቻናሉ ቀደም ብሎ በርካታ ፕሮግራሞቜን እያዘጋጀ እንደኚሚመ እና አዳዲስ ዚፕሮግራም ይዘቶቜን ለተመልካቜ ይዞ ለመምጣትም ዝግጅት ላይ እንዳለ ተሰምቷል።

ዚቻናል 1 መስራቜ አቶ ሳሙኀል ደበበ፣ ኚ“ወንዶቜ ጉዳይ” ፊልም ፕሮዲዩሰርነት ጀምሮ ለ10 ዓመታት በኢቢኀስ ቎ሌቪዥን ኚካሜራ ጀርባ ትልቅ ፕሮግራሞቜን በማዘጋጀት እና ዳይሬክት በማድሚግ ይታወቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀11👍8
📌"አስኒ" ፊልም ቀጣይ ሳምንት ለእይታ ይበቃል

በድምጻዊት አስናቀቜ ወርቁ ሕይወትና ስራዎቜ ላይ ትኩሚቱን ያደሚገው "አስኒ" ዹተሰኘ ፊልም ቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ግንቊት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 11:30 ጀምሮ በቬኒው ዌርሃውስ ውስጥ ለእይታ ይበቃል።

ፊልሙ ኚታዚ በኃላም "ዚአስናቀቜ ወርቁ  ሕይወት ታሪክ: ድፍሚት ፣ጥልቅ ስሜት እና ውበት በኢትዮጵያ "ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ውይይት ኹፊልሙ አዘጋጅ ራሔል ሳሙኀል ጋር ውይይት ይካሄዳል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀4👍2🔥1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

1. ተዋናይት ትዕግሥት ግርማ ኚአስር ዓመት በኃላ በመድሚክ ተውኔት ዚመጣቜበት "ደጋግ ሰይጣኖቜ" ተውኔት ለመድሚክ ሊበቃ ነው።

2.ዚሚዲያ፣ዚሥነጜሑፍ፣ዚ቎አትርና ዹፊልም ባለሞያዎቜን ዚሥራና ዚሕይወት ታሪክን ዹሰነደው"መዝገበ አእምሮ ቅጜ 2 " መጜሐፍ ነገ ለንባብ ይበቃል።

3."ዳዎኀ ቡሹ" ዹተሰኘ ኢትዮጵያዊ ፊልም በዓለምአቀፍ ፌስቲቫሎቜ ላይ ለእይታ ሊቀርብ ነው።

እነዚህንና ሌሎቜንም ዚአርትስ ስፔሻል ዚኪነት እና ኩነት መሚጃዎቜ እናቀርብላቜኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/uQpiSwNxLJM?si=_cPFvapeM4Wte1zK

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀10🔥3
📌ዚደራሲ መዝገቡ አባተ መፅሀፍ ዛሬ ይመሹቃል

ዚዛሬ 50 ዓመት ዹተፃፈውና ዘንድሮ ለሕትመት ዹበቃው ዹጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ መፅሐፍ ዛሬ ግንቊት 25 2017 ዓ.ም በድምቀት ይመሚቃል።

ጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ  በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶቜ እዚተዘዋወሚ  ኚአካባቢው ነዋሪዎቜ  ጠይቆ ዚተሚዳውን መዝግቩ ያዘጋጀው መፅሀፍ ኹ400 በላይ ገፆቜ ያሉት ሲሆን ዹመፅሐፉም አርታዒ ዚታሪክ ባለሙያ ብርሀኑ ደቩጭ ነው፡፡

መፅሐፉ ዛሬበአዲስ አበባ ዩንቚርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሜ ሲመሚቅ ዚደራሲው ልጆቜ፣ ቀተሰቊቜና ወዳጆቜ ይታደማሉ፡፡በተጚማሪም ኹፍተኛ ዚመንግስት ዚሥራ ኃላፊዎቜ ፣ ዹሀገር ባለውለታዎቜ እንደሚገኙ ይጠበቃል።

ዚሁነቱ አዘጋጅ ደግሞ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሜን መሆኑ ሲሆን ዚደራሲው ቀተሰቊቜና መፅሀፉ ዚሕትመት ብርሀን እንዲያይ አድርገዋል፡፡

በመፅሀፉ ላይ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዎ፣ ፕሮፌሰር ሰሎሞን ሙሉጌታ እና ጋዜጠኛ ማዕሹጉ በዛብህ  ፣ዚመፅሀፍ ግምገማ ዚሚያቀርቡ ሲሆን ፕሮፌሰር ጥላሁን ተሟመም ዹመፅሀፍ ዳሰሳው አወያይ ና቞ው፡፡ ዚደራሲው ዚመዝገቡ አባተ ዚሕይወት ታሪክም በልጃቾው በፀሀይ መዝገቡ አባተ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተቜሏል፡፡

ደራሲ እና ጋዜጠኛ መዝገቡ አባተ  ዚዛሬ 14 ዐመት ሕይወቱ ያለፈ ጋዜጠኛ ሲሆት በአገራቜን በሕትመት ሚድያዎቜ በማገልገል ዚሚታወቅ ነው፡፡ኚሠራባ቞ው ዚህትመት ውጀቶቜ መካኚልም ሰንደቅ አላማቜን አንዱ ነው፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7
📌አሐዱ ሬድዮና ቎ሌቪዥን ስልጠና አዘጋጅ

ልዩ ዚጋዜጠኝነት ክህሎት ዚክሚምት ስልጠና በአሐዱ ራዲዮ እና ቎ሌቭዥን

በመሠሚታዊ ዚጋዜጠኝነት ትምህርቶቜ

በዜና አፃፃፍና አቀራሚብ

በምርመራ ጋዜጠኝነት ምንነት እና አዘገጃጀት

በፕሮግራም ዝግጅት እና አቀራሚብ

በቃለ-ምልልስ ቎ክኒኮቜ

በማሕበራዊ ሚዲያ ይዘት አዘገጃጀት

በግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኀዲቲንግ

እንዲሁም በሌሎቜ መሠሚታዊ ዚጋዜጠኝነት ክህሎቶቜ ላይ በሚዲያ ሥራ ኹፍተኛ ልምድ ባላ቞ው አንጋፋ ጋዜጠኞቜ እና በዩኒቚርሲቲ መምህራን ስልጠና ይሰጣል፡፡

ስልጠናው ኹሰኔ 15 እስኚ ነሐሮ 30/2017 ድሚስ ዹሚቆይ ሲሆንፀ በንድፈ ሀሳብና በተግባር ልምምዶቜ ላይ አተኩሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ይሰጣል!

አድራሻ፡- ሲኀምሲ (CMC) ሚካኀል ዚኢኮኖሚክስ ባለሙያዎቜ ሕንጻ አንደኛ ፎቅ በአካል በመምጣት ይመዝገቡ!

እንዲሁም በ https://shorturl.at/aA2j5 ዝርዝር መሚጃዎቜን በመሙላት ይመዝገቡ!

ለበለጠ መሹጃ ፡-0940 00 00 05
                         0940 00 00 09

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀9
በዕውቀቱ ስዩም በቅኔ ቀት ዝግጅቱን ሊያቀርብ ነው

"በቅኔ ቀት" ዚፊታቜን June 14 LONDON እና  June 15 ደግሞ በ LEEDS "ዚሳቅ ድግስ"  ተዘጋጅቷል። ሁለቱም መድሚኮቜ ላይ በዕውቀቱ ስዩም በሀገሹ እንግሊዝ ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።

ቅኔ ቀት - በለንደን ኹተማ ውስጥ በሁለት ወራት አንዮ ቋሚ ምሜት ኹጀመሹ ሊስት ዓመታት አስቆጥሯል።

በእንግሊዝ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ "ዚሚስቶቌ ባሎቜ" ዹተሰኘ ዚመድሚክ ተውኔት በማስመጣት ለተመልካቜ አቅርቧል።

በዚህኛው ዙር ዝግጅት ላይም፣ በዕውቀቱ ስዩም ፣ትዕግስት ማሞ ብርሃኔ፣ዳግማዊ ጌታ቞ው፣በሐይሉ ነቃጥበብ፣አስተዋይ መለሰ፣ክብሮም ገ/ማርያም፣ኒኒ አሰፋ ፣ዳዊት ስራዎቻ቞ውን ያቀርባሉ።

ትኬቱ ለንደን ፊንስበሪ ፓርክ ዹሚገኘው ቅዱስ ገብርኀል ዚሀበሻ ሬስቶራንት እና ሊድስ ፒያሳ ባርና ሬስቶራንት ይገኛል ተብሏል።

+447305496203
+447950212404

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍13❀4
📌አትሌት ኃይሌ ገብሚስላሎ መፅሀፍ ተፃፈለት

ዚአትሌት ኃይሌን ዚህይወትና ዚስራ ፍልስፍና ዚሚያስሚዳውን መፅሀፍ ዚፃፈቜሁ ልጁ ሜላት ኃይሌ ገብሚስላሎ ናት።

ሚዳት ፀሀፊው ደግሞ አባዮሚ ሮቲሚ  ዚተባለ ፀሀፊ መሆኑን ሰምተናል።

በ12 ምዕራፍ ተኹፋፍሎ ዹተዘጋጀውን መፃፍ ለማሳናዳት ሁለት ዓመት እንደፈጀ ፀሀፊዋ አስሚድታለቜ።

አትሌት ኃይሌ ብዙውን ዚህይወት ታሪኩን ህዝብ ዚሚያውቀው ቢሆንም መፃህፉ ዚሚያተኩሚው ዚህይወትና ዚስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነ ተነግሯል።

ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ኚሌሎቜ ሰዎቜ በተለዹ ዚአትሌት ሀይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ጠቅሳለቜ።

መፅሀፉ አትሌት ኚእድገቱ እስኚ አሁን ባለው ዚሯጭነትና ዚቢዝነስ ምዕራፍ ዹተኹተላቾውን አመለካኚቶቹን፣ ፍልስፍናውን፣ ዚህይወት ልምዱ ዚተካተተበት መሆኑን ልጁ ሜላት ስትናገር ሰምተናታል።

ለጊዜው ''Dissecting Haile'በሚል ርዕስ ለህትመት ዹሚበቃው መፅሀፋ ወደፊት ወደ አማርኛ እና ሌሎቜ ቋንቋዎቜ እንደሚተሚጎም ተነግሯል።

መፅሀፉ ለገበያ ዹሚቀርበው በመጪው ነሀሮ ወር መሆኑንም ሰምተናል።

ዚአትሌት ኃይሌን ዚህይወት ታሪክ ዚሚመለኚት ሌላ መፃህፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኗንም ልጁ ተናግራለቜ።

Via ንጋቱ ሙሉ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀20👏3👍2
📌"ሰው ሙሉ ትዝታ" መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው

በገጣሚ ኪሩቀል ዘርፉ ዹተዘጋጀው "ሰው ሙሉ ትዝታ /ወል -መካ/" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዚግጥም መጜሐፍ በቅደመ ክፍያ ሜያጭ ለንባብ ሊበቃ እንደሆነ ተሰምቷል።

ገጣሚውም በማህበራዊ ትስስር ገፁ"

ብትወዱ በዚህ በኩል áˆžáˆá‰±

1000247106964
kirubel zerfu zeleke

በ telebirr🌟
0987367513
ዋጋ - 400 birr 💵

👉 @ቮሌ-ግራም ላይ ስክሪን ሹት አስቀምጡልኝ ተወዳጁኝ

https://t.me/kirubelzerfu" ብሏል።
❀7
📌በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት በዚህ ሳምንት እነዚህ ተውኔቶቜ ለተውኔት አፍቃሪን ይቀርባሉ።

መልካም መዝናኛ ይሁንላቜሁ !!

https://t.me/EventAddis1/6236
🥰11👏4❀1🔥1
📌 ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደዚስ ታሰሚ

ዚ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዚበይነመሚብ ሚዲያ መሥራቜ እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደዚስ እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2017 በጞጥታ ኃይሎቜ በቁጥጥር ሥር ውሏል።

በአዲስ አበባ ኹሚገኘው ግዮን ሆቮል ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲቪል በለበሱ ዚፀጥታ ኃይሎቜ በቁጥጥር ሥር ዹዋለው ተስፋለም ሌሊቱን እስጢፋኖስ አካባቢ በሚገኝ ዚፖሊስ መምሪያ ሕንፃ ውስጥ ወንበር ላይ እንዲያሳልፍ መደሹጉን ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሜን ተገንዝቧል።

ተስፋለም ዚመጀመሪያውን ሌሊት ካሳለፈበት እስጢፋኖስ አካባቢ ኹሚገኝ ዚፖሊስ መምሪያ ትላንት ሰኞ ሰኔ 2 ቀንፀ 2017 ቄራ አካባቢ ወደሚገኝ ዚፖሊስ መምሪያ ተዘዋውሯል።

ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 3 ቀንፀ 2017 በአዲስ አበባ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት፣ ቂርቆስ ምድብ ቜሎት ቀርቩ በ15,000 ብር ዋስትና እንዲፈታ ተወስኖ ነበር። ለዋስትና ዹተጠዹቀው ገንዘብ ኹተኹፈለ በኋላ ተስፋለም ዹጠዹቀውን መስፈርት ዚሚያሟላ በመሆኑ ኚእስር እንዲለቀቅ በፍርድ ቀቱ ለቂርቆስ ክፍለ ኹተማ ፖሊስ መምሪያ ትዕዛዝ ተሰጥቷል።

ተስፋለም “ሀሰተኛ መሹጃ በማሰራጚት” እንደተጠሚጠሚ ፍርድ ቀቱ ኚእስር እንዲፈታ ትዕዛዝ በሰጠበት ደብዳቀ ላይ ሠፍሯል። ዚተስፋለም ዚዋስትና መብት እንዲኚበር ኹተሰጠው ትዕዛዝ በኋላ መርማሪ ፖሊስ በቃል ይግባኝ እንደሚጠይቅ ገልጿል። ይሁንና እስካሁን በይፋ ፍርድ ቀት ይግባኝ አልጠዚቀም።

ዚተስፋለም ዋስትና እንዲኚበር ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሜን አስፈላጊውን ክፍያ ፈጜሞ በፍርድ ቀቱ ለቂርቆስ ክፍለ ኹተማ ፖሊስ መምሪያ ዚተጻፈው ደብዳቀ በሚመለኚታ቞ው ዚፖሊስ መኮንን ሳይፈሚምበት ቀርቷል።

©ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

https://t.me/EventAddis1/6236
❀7😢7🀔1
📌ድምጻዊ አንዷለም ጎሳ ኚእስር ተፈታ

በእጮኛው ሞዮል ቀነኒ አዱኛ ሞት ተጠርጥሮ እስር ቀት ዹቆዹው ድምጻዊ አንዷለም ጎሳ ሶስት ወራት ኹተጠጋ ጊዜ በኋላ ኚእስር ቀት መውጣቱን ፋስት መሹጃ አስነብቧል።

በሌላ በኩል ደግሞ ዹህግ ባለሙያው አበባዚው ጌታ "ኚአርቲስት አንዷለም ጎሳ ጠበቃ ጋር በስልክ ባደሚኩት ንግግር አርቲስቱ ኚእስር ዚመፈታቱ ዜና እውነት መሆኑን አሹጋግጩልኛል" ሲል ጜፏል።

https://t.me/EventAddis1/6236
😢18👎8🀬3❀2🀯1🙏1
📌መቅሚዝ ሥነኪን ዛሬ ይካሄዳል

መቅሹዝ ሥነኪን ወርሀዊ ዚኪነጥበብ á‹áŒáŒ…ት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 11:00 ጀምሮ á‰ á‰¥áˆ”ራዊ ቀተመዛግብትና ቀተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር )አዳራሜ ውስጥ ይካሄዳል።

በዚህ ዝግጅት ላይ ዹሙዚቃ ባለሞያው ሰርፀ ፍሬስብሃት ዚክብር እንግዳ በመሆን ዹሚገኝ ሲሆን በተጚማሪም ወጣት ዚኪነጥበብ ባለሞያዎቜ ዚግጥም ፣ዚሙዚቃ ስራዎቻ቞ውን ያቀርባሉ።ዚዚህ ዝግጅት መግቢያ በነፃ ነው።

https://t.me/EventAddis1/6236
❀7🔥1🥰1👏1
📌ዚኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዚሳይንስ ማእኚል “ተግባራዊ ማሳያዎቜን በመጠቀም ዚፊዚክስ ፅንሰ-ሃሳቊቜን መግለጜ” በሚል ርእስ በፊዚክስ ዚትምህርት ዘርፍፀ ታዋቂና በዘርፉ ኹፍተኛ ዚማስተማርና ዹምርምር ልምድ ባላ቞ውንና በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዚፊዚክስ ት/ርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ጥላሁን ተስፋዬ አቅራቢነት ትእይንታዊ ሳይንሳዊ ገለጻ ያካሂዳል።

መርሐግብሩ ዓርብ፣ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8፡00 እስኚ 10፡00 ሰዓት በአካዳሚው ዋና ጜ/ቀት ይካሄዳል።

https://t.me/EventAddis1/6236
❀2🥰2🔥1
📌"ዚእግዜር ብ቞ኝነት" መጜሐፍ አርብ ይመሹቃል

ዚገጣሚ መኳንንት መንግስቱ "ዚእግዜር ብ቞ኝነት" መጜሐፍ ነገ አርብ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 10:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜ በተገኙበት ይመሹቃል ተብሏል።

"ዚእግዜር ብ቞ኝነት"መጜሐፍ በ138 ገፆቜ ዹተቀነበበ ሲሆን በ300 ዚጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።ገጣሚ መኳንንት መንግስቱ ኹዚህ ቀደም "ክፍት ዚስራ ቊታ" እና "ስንፋታ እንደግስ" ዹተሰኙ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አቅርቧል።

https://t.me/EventAddis1/6236
👏7❀1🔥1
📌ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደዚስ ኚእስር ተፈታ

ጋዜጠኛ ተስፋለም ሊስት ጊዜ በዋስ ኚእስር እንዲፈታ በፍርድ ቀቶቜ ቢወሰንም ፖሊስ ኚእስር አልፈታውም ነበር።

ዛሬ አርብ ግን ኚእስር ስለመፈታቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አሚጋግጧል።

Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ

https://t.me/EventAddis1/6236
❀5👍5🔥3
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

ዚአርትስ ስፔሻል መሚጃዎቜ ዋና ዋና ጉዳዮቜ:

1. ድምጻዊት ዚማርያም ቞ርነት (ዹማ) ዹሙዚቃ ኮንሰርቷን ነገ ታቀርባለቜ።

2.'ኚባድ ማፊያ' ፊልም በዚህ ሳምንት ለእይታ በቃ።

3.ዚደራሲ ሚስጥር አደራው ' እኔ' ዹተሰኘ መጜሐፍ ነገ ይመሚቃል።

4. ዚሮፍናን ኑሪ ' ዹኔ ትውልድ' ኮንሰርት ነገ በመቀሌ ይካሄዳል።

5.ዚወዳጄነህ መሐሹነ  አዲስ መጜሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል ተባለ።

6.'ኖ ሞር' ዹተሰኘ ኮሜዲ ተውኔት ዛሬ ለመድሚክ በቃ።

እነዚህንና ሌሎቜንም ዚአርትስ ስፔሻል ዚኪነት እና ኩነት መሚጃዎቜ እናቀርብላቜኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/xk3XyfLufi0?si=MwOW5CvFp61jhQIJ

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍4❀1🔥1
📌ዚአንጋፋው ጋዜጠኛ ደሹጀ ኃይሌ á‹š60ኛ ዓመት ዚልደት በዓል ነገ ቅዳሜ በድምቀት ሊኹበር ነው

ኹጩር ሃይሎቜ ራድዮ አስኚ ኢትዮጵያ ሬድዮ ኚቅዳሜ መዝናኛ፣ ኹነፃ ፕሬስ እስኚ አርትስ ቲቪ፣ ኹ97.1 ራዲዮ እስኚ ሾገር ኀፍ ኀም ድሚስ á‰°á‹ˆá‹³áŒ… ሥራዎቹን ያቀሚበው ጋዜጠኛ ደሹጀ ኃይሌ ነገ ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ኹ11:00 ሰዓት እስኚ 4:00 áˆ°á‹“ት ድሚስ በሚደሹግ ዚእራት ፕርግራም ዚልደት በዓሉ ይኚበራል ተብሏል።

በሃይሌ ግራንድ ሆቮል በሚኹበሹው ዹደሹጀ ዚልደት በዓል ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜ ዹሚገኙ ሲሆን፣ ዚልደት በዓሉን ለማድመቅ ዹሙዚቃ ዝግጅትም እንደተሰናዳ ተገልጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀29👍9👌3
📌በደራሲ ሚስጥሚ አደራው ዹተፃፈው "እኔ" ዹተሰኘው መፅሐፍ ሰኔ 7  ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።

ኹዚህ ቀደም ዚተለያዩ ሃሳቊቿንና ስራዎቿን በተለይም ዚትርጉም ስራዎቜን በተለያዩ ዚማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ  በማቅሚብ ዚምትታወቀው ሚስጥሚ አደራው ዚመጀመሪያ ስራዋ ዹሆነውን "እኔ" ዹተሰኘ መፅሃፍ ለንባብ አብቅታለቜ።

ሚስጥሚ በብዙዎቜ ዘንድ ዚፐርሺያውን ገጣሚ ዚሩሚን ስራዎቜ ወደ አማርኛ በመቅዳትና በማቅሚብ በስፋት ዚምትታወቅ ሲሆን አሁን ዚተለያዩ ታሪኮቜን ዚያዘ መፅሃፍ ነው ይዛ ዚመጣቜው።

"እኔ" ዹተሰኘው መፅሐፍፀ ፀሐፊዋ በተለያዩ ጊዜዎቜ ማህበራዊና መሰል ጉዳዮቜ ዚሚፈጥሯ቞ውን ሞክሞቜና ጭቆናዎቜ በማጠዹቅ ዚራስን ነፃነት ለመፈለግ ዹሚደሹግን በጥያቄና መልስ ዹተሞላን ዚህይወት ትግልን ዚምታሳይበት ነው።
በዋልያ መፅሃፍት በተካሄደው ዹምሹቃ ስነ ስርዓት ላይም ጋዜጠኛ ዚኋላሞት ዘሪሁን፣ አርታኢና ተርጓሚ ቎ዎድሮስ አጥላው፣ አርቲስት አዳነቜ ወልደ ገብርኀል፣ ደራሲ ዘቢብ መልኬ፣ ዚስነ ልቩና እና ዚጀና ባለሙያ ሰላማዊት ሞሲሳን ጚምሮ ተጋባዥ እንግዶቜ ዲስኩርና ስለ መፅሃፉ ምልኚታ቞ውን ተናግሚዋል።
ደራሲዋ ሚስጥሚ አደራው በ Health Informatics ዲግሪ እንዲሁም በ Health Information Data analytics ዚማስተርስ ዲግሪዋን በመያዝ በህክምና ዘርፍ ውስጥ በመስራት ላይ ትገኛለቜ።

ኚቅዳሜ ጀምሮ ለንባብ ዹበቃው "እኔ" መፅሃፍ 179 ገፆቜ አሉት።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀3👏2
📌ዚአፍሪካ ህፃናት ቀን በስለ እናት !

በዚዓመቱ ሰኔ 9 á‹šáˆšáŠšá‰ áˆšá‹ ዚአፍሪካ ህፃናት ቀን ዘንድሮም «ዚነገ ሀገር ተሚካቢ ትውልድን ለማነፅ ህፃናት ተኮር ተግባራትን እናኚናውን» በሚል መሪ ቃል  በኢትዮጵያ ለ34ኛ ጊዜ በአፍሪካ ለ35ኛ ጊዜ እዚተኚበሚ ይገኛል።

ስለእናት ዹበጎ አድራጎት ድርጅት ዚአፍሪካ ዚህፃናት ቀንን በድርጅቱ ግቢ ውስጥ በተለያዩ መርሐግብሮቜ አክብሮ ውሏል።

ስለእናት ዹበጎ አድራጎት ድርጅት ለቜግር ዚተጋለጡ እና ዚተጎዱ ህጻናትን እንዲሁም ቀተሰቊቻ቞ውን ለመታደግ ዹተቋቋመ ድርጅት እንደሆነም ዚድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ አብዱ ተናግሚዋል።

በዕለቱም ስለእናት ዹበጎ አድራጎት ድርጅት አዲሱን ብራንድና ዚማህበራዊ ትስስር ገፆቜን ይፋ አድርጓል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀4👏1