Event Addis Media
9.62K subscribers
6.08K photos
12 videos
4 files
4.71K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌"ስካርፍ፣ ቡና ና ጢስ" መጜሐፍ ቅዳሜ ይመሹቃል

ዚገጣሚ አንዱ ጌታ቞ው "ስካርፍ፣ቡና ና ጢስ" ዹተሰኘ መጜሐፍ ዚፊታቜን ቅዳሜ ግንቊት 16 ቀን 2017 ዓ.ሞ ኹቀኑ 8:30 ጀምሮ በመሶብ ዹሙዚቃ ማዕኹል ውስጥ ይመሚቃል።"ስካርፍ፣ቡና ና ጢስ" መጜሐፍ በቅድመ ሜያጭ በ300 ዚጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍1
📌"ሻሞ" መጜሐፍ ዚፊታቜን አርብ ይመሹቃል

በደራሲ ብሩክ በቀለ ዹተዘጋጀው "ሻሞ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው መጜሐፍ ዚፊታቜን አርብ ግንቊት 15 ቀን 2017 ዓ.ም ኹ11:30 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመሚቃል።

በዕለቱም ልዩ ልዩ ዚሥነጜሑፍ ባለሞያዎቜ ሀሳቊቻ቞ውን በመድሚኩ ያጋራሉ ተብሏል።

"ሻሞ" መጜሐፍ 16 ታሪኮቜ ያሉት ሲሆን በ400 ገፆቜ ተቀንብቧል 550 ብር ዚጀርባ ዋጋም ለአንባቢያን ቀርቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍10
📌ዚኢትዮጵያ ስነ-ጜሁፍ እና ኊዲዮ ቡክ ዹተሰኘ ዝግጅት ዛሬ ይካሄዳል

ዚመሰናዶው አዘጋጆቜ" ዚኢትዮጵያ ስነ-ጜሁፍ እና ኊዲዮ ቡክ በሚል ርዕስ ኹ"ኢትዮጵያ ቡክ ፎሹም" አሰናኝ ዳዊት ብርሃኑ፣ ኹ "በተለይ አሥራ አንደኛው" እና "ወድቆ ዹተገኘ ሐገር" መፅሐፍት ደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ፣ ኹ "ለምንን ፍለጋ" መፅሐፍ ተርጓሚ ቎ዎድሮስ አጥላው እንዲሁም ኹ"ተራኪ አፕ" መስራቜ እና ስራ አስኪያጅ ናሆም ጞጋዬ ጋር በመሆን ዚኢትዮጵያን ስነ-ጜሁፍ እና ኊዲዮ ቡክ ዚምንዳስበበት ዝግጅት ይኖሹናል" ብለዋል።

https://forms.gle/LGk4PnfL6uKXSogv6

ቀን፡ ዓርብ ግንቊት 15፣ 2017 ዓ.ም
ሰዓት፡ ኹቀኑ 11፡00 እስኚ ምሜቱ 2፡00 ሰዓት
ቊታ፡ ኚቀት እስኚ ኹተማ ዹኹተማ ማዕኹል

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍2👏1
📌ዝሆኑን በሎራ መጜሐፍ ሊመሹቅ ነው

በኢትዮጵያ ዚቀድሞ ሰራዊት ውስጥ ኹፍተኛ ድርሻ ዚነበራ቞ውና ኹሰሜን እስኚ ምስራቁ ዚኢትዮጵያ ክፍል ድሚስ በነበራ቞ው ወታደራዊ ሃላፊነት እና ሚና ዚሚታወቁት ሌተናንት ኮሎኔል በላይነህ ታዬ ዚጻፉትና እና በኢትዮጵያ ሠራዊት ምስሚታ እና ውድቀት እንዲሁም በደርግ ውስጥ ሰለነበሩ ሎራዎቜ እና ሌሎቜ አዳዲስ መሚጃዎቜንና ያልተሰሙ ታሪኮቜን አካቷል።

ዝሆኑን በሎራ ዹተሰኘ መጜሃፍ ግንቊት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ኚሚፋዱ 3፡00 በኢትዮጵያ ኢኮኖሚስቶቜ ማህበር አዳራሜ ኹፍተኛ ዚመንግስት ዚስራ ሃላፊዎቜ፣ ዚቀድሞው ዚኢትዮጵያ ሠራዊት ኹፍተኛ ዹጩር መሪዎቜና ዚመንግስት ባለስልጣናቜ ተጜእኖ ፈጣሪ ግለሰቊቜ ፣ጥሪ ዹሚደሹግላቾው እንግዶቜ በተገኙበት በደማቅ ስነስርአት ያስመርቃሉ፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀3🔥1
📌ዚግጥም ግጥሚያ ለሁለተኛ ጊዜ ሊካሄድ ነው

ዚኢትዮጜያ á‹šáŒáŒ¥áˆ ግጥሚያ ሁለተኛ ጊዜ ነገ ቅዳሜ ግንቊት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በመሶብ ዹሙዚቃ ማዕኹል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።

በተጚማሪም ዚገጣሚ አንዱ ጌታ቞ው "ስካርፍ፣ቡና ና ጢስ" ዹተሰኘ መጜሐፍ  ይመሹቃል ተብሏል ።

አዘጋጆቹም ስለዚህ መሰናዶ ተኚታዩን ብለዋል"ዚመጀመሪያው ዚግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይፀ ምግባር ሲራጅ ራስ በነበሚበት እሱ ቀጣይ ባለተራ ስለነበር ዝግጅቱን አጋፍሮ በሁለተኛው ዝግጅታቜን ደሞ headliner poet (ራስ) በመሆን በዲበኩሉ ጌታ አጋፋሪነት “ባዶ ሰው በባዶ ቀት” ዚተሰኘቜ መጜሐፉ ተነበበቜ፣ ቀሚበቜ፣ በወዳጆቿ ተዘዚሚቜ።

አሁን እኛም ሁለተኛውን ኢትዮጜያ  ዚግጥም ግጥሚያ ስናዘጋጅ እሱም ሁለተኛ መጜሐፉን “ስካርፍ፣ ቡና’ና ጢስ “ን ያስመርቃል! እልል እንጂ ምን ይባላል!!! ለመጜሐፍ ምርቃቱ ኑ! ዚግጥም ግጥሚያውንም ታደሙ! ግጥም በቡናም በጢስም ታጅባ በሞሰብ ዹሙዚቃ ማዕኹል ትነግሳለቜ። ዹ2017 ዚኢትዮጜያ ዚግጥም ግጥሚያ ቻምፒዮን እንሰይማለን"

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍4❀1🔥1
📌"አውደ ፋጎስ" ዚውይይት መድሚክ እሁድ ይካሄዳል

60ኛው ዙር አውደ ፋጎስ ዚውይይት መድሚክ እሁድ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር ዶ/ር ይሁኔ አዹለ "ቡዳ! እውነት ወይስ ሀሰት" በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያቀርባል።ይህም ውይይት እሁድ ግንቊት 17  2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቀተመዛግብት እና ቀተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሜ ውስጥ ይካሄዳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚኢትዮጵያ አባቶቜ ቀን ዛሬ ይኚበራል

ዚኢትዮጵያ አባቶቜ ቀን ኢትዮጵያውያን በራሳቜን ወግና እሎት ብሎም ዚመኚባበር ባህል መሰሚት ኢትዮጵያዊ ቀለም ባለው መልኩ "ክብር ለአባትነት" በሚል ኹ2003 ዓ.ም ጀምሮ በዚዓመቱ ግንቊት 15 በሃገር አቀፍ ደሹጃ መኹበር ዹጀመሹ ቀን ነው።

ግንቊት 15 ዚተመሚጠበት ምክንያት ዚጣልያን ወራሪ ኃይልን አድዋ ላይ መክተው ያሞነፉት ጀግኖቜ አባቶቻቜን በድል አድራጊነት ወደ መናገሻ ኹተማቾው ዚተመለሱበት በመሆኑ ብዙሃኑ አባቶቜ ኚቀተሰብ ባሻገር ለሃገር መፅናት ላደሚጉት ተግባር ዚሚታወሱበትና ምስጋና ዚሚቀርብበት ዕለት እንዲሆንም በማሰብ ነው፡፡

ላለፉት 17 አመታት በኢትዮጵያ ዚአባቶቜ ቀንን ግንቊት 15 ላይ ሲያኚብር በቀተሰባ቞ው፣ በአካባቢያ቞ው፣ በወዳጆቻ቞ው እና በዙሪያ቞ው ባሉ ሁሉ ስማ቞ው በመልካም ዚሚነሳ፣ አርአያ መሆን ዚቻሉ፣ ኚቀተሰብ እስኚ ሃገር በመልካም አባትነትና አበርክቶ ዚሚነሱ አባቶቜንፀ ዚኢትዮጵያ አባቶቜ ዚክብር መገለጫ ዹሆነውን ጋቢ በመደሚብ፣ ዝቅ ብሎ እግር በማጠብ፣ ዹዕውቅና ምስክር ወሚቀት በመስጠትና ታሪካ቞ውን በመሰነድ ሲያመሰግን እና ሲያኚብር ቆይቷል።

ግንቊት 15 እንደሌላው ዓለም ሁሉ ኢትዮጵያዊ መልክ ዚያዘ፣ ኢትዮጵያውያን አባቶቜ ዚሚመሰገኑበት፣ በኢትዮጵያ ካላንደር ኢትዮጵያዊ ምክንያት ኖሮት ዹሚኹበር "ዚኢትዮጵያ አባቶቜ ቀን" ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍5❀4🔥1
📌"ሥዕልና ጃዝ" ዹተሰኘ ዝግጅት ነገ ይካሄዳል

(መግቢያው በነፃ)

"ሥዕልና ጃዝ" ዹተሰኘ ዝግጅት ነገ ቅዳሜ ግንቊት 16 2017 ዓ.ም ኚጠዋቱ 4 ሰዓት እስኚ ምሜቱ 3 ሰዓት ድሚስ መካኒሳ አካባቢ በሚገኘው ጃዝ ኮፊ ውስጥ ይካሄዳል።

በዕለቱም ዚሥዕልና ጃዝ ፌስቲቫል እንዲሁም ሌሎቜ አሳታፊና አዝናኝ ዝግጅቶቜ ይኖራሉ ተብሏል። መግቢያው በነፃ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍11❀2🔥1
📌ኢቢኀስ ቁጥር አንድ ብራንድ ሆኖ ተመሹጠ

ኢቢኀስ ቎ሌቪዥን በሚዲያ ዘርፍ ኚኢትዮጵያ ተቀባይነት ያለው ቀዳሚ ብራንድ ተብሎ ዹተመሹጠው መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደሚገው ብራንድ አፍሪካ ዹተሰኘው ተቋም ባዘጋጀው ዚእውቅና መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡

በዚሁ ዚእውቅና ዝግጅት ላይ  ኢቢኀስ ቎ሌቪዥን በኢትዮጵያ ተቀባይነት ካላ቞ው ዹመገናኛ ብዙኃን ብራንዶቜ መካኚል ቁጥር 1 ዹሆነው ቢቢሲና አልጀዚራን በማስኚተል መሆኑን ነው ብራንድ አፍሪካ ያሳወቀው፡፡

ኢቢኀስ ቎ሌቪዥን በሚዲያ ዘርፍ ኚኢትዮጵያ ቀዳሚ ብራንድ ስለመሆኑ እውቅና በተሰጠበት በዚህ መድሚክ ላይ ዹሀገርን አርማ ይዞ በመላው አለም ዹሚበሹው አንጋፋውና ግዙፉ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ኹ10 ተኚታታይ ዓመታት በላይ ግዙፍ ስማ቞ውን ይዘው ኹዘለቁ 5 ብራንዶቜ መካኚል አንዱ በመባል እውቅና ተቜሮታል፡፡

ይህም ብቻ ሳይሆን አዹር መንገዱ በአፍሪካ በአቪዬሜን ዘርፍ ካሉ ተመራጭ ብራንዶቜ ውስጥ ቀዳሚው በመሆን ኀምሬትስና ኳታር አዹር መንገዶቜን አስኚትሎ ዚአፍሪካ ተመራጭ አዹር መንገድ ስለመሆኑ ነው በዝግጅቱ ላይ ዚተነገሚው፡፡

Via EBS

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
👍6👎3❀2🀔1🀣1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

1.ድምጻዊት ሀይማኖት ግርማ "ጅንኑ" ስትል ዚሰዚመቜውን ዹሙዚቃ አልበም ኹ12 ዓመታት በኃላ ዛሬ ለሙዚቃ አድማጮቜ አቀሚበቜ።ድምጻዊት ኃይማኖት "ተሚስቻለሁ ዹሚል ስጋት አለኝ፣አደጋ አጋጥሞኝ ነበር። ሙዚቃ ባቆምኩበት ሰዓት ተመልሌ ዚምመጣ አልመሰለኝም ነበር" ስትል ተናገራለቜ ስለጉዳዩ በአርትስ ስፔሻል ትሰማላቜሁ።

2.በአሜሪካውያን ዚተሰራው "ኢትዮጵያ" ዹተሰኘ ተውኔት ኹ88 ዓመታት በኃላ ኹሰሞኑ በዋሜንግተን ዲሲ ለመድሚክ በቅቷል። ተውኔቱ በ1930ዎቹ ኹተዘጋጀ በኋላ በጊዜው ዚአሜሪካ ፕሬዚደንት በነበሩት ቎ዎዶር ሩዝቬልት አስተዳደር አማካኝነት ለህዝብ ለዕይታ እንዳይቀርብ በይፋ á‰³áŒá‹¶ ዹቆዹ እንደሆነ ተነግሯል።በዝርዝር እንነግራቜኋለን።

3.በአዲስ አበባው ዚጣይቱ ዚባህል እና ትምህርት ማዕኹል ውስጥ ዚፊታቜን ሰኞ በማዕኹሉ ታሪክ ዚመጀመሪያው ግዙፍ ዚሥነጥበብ አውደርዕይ ለእይታ ሊበቃ ነው።

4.ዹ"ድንቅነሜ" ወይንም "ሉሲ" አጜም ዚተገኘበት 50ኛ ዓመት á‰°áŠšá‰ áˆšá¢ እንዲሁም  በእድሳት ምክንያት ተዘግቶ ዹቆዹው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚዹም ዛሬ አገልግሎት መስጠት ጀመሚ።

እነዚህንና ሌሎቜንም ዚአርትስ ስፔሻል ዚኪነት እና ኩነት መሚጃዎቜ እናቀርብላቜኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/8zfvUnde4nA?si=YcyoId-NFm08fa_g

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍12🔥2
📌ዚሞገሩ ስንክሳር ፕሮግራም መጜሐፍ ሆነ

በጋዜጠኛ መኮንን ወ/አሹጋይ ዹተዘጋጀውና በርካታ ጉዳዮቜ ዚተካተቱበት "እነሆ ስንክሳር" ዹተሰኘ መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

በሾገር 102.1 ኀፍ ኀም ሬድዮ ለዓመታት ሲተላለፈ ዹቆዹው "ስንክሳር" ዚሬድዮ ፕሮግራም አሁን በመጜሐፍ መልክ እንደተዘጋጀም ተነግሯል።

"እነሆ ስንክሳር"መጜሐፍ ዚፊታቜን ግንቊት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለንባብ እንደሚበቃም ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጀ ያመለክታል።

መጜሐፉ በጃፋር እና በዕውቀት በር መጻሕፍት መደብሮቜ በኩል ለአንባቢያን ይኹፋፈላም ተብሏል።

ኹዚህ ቀደም በሾገር ኀፍ ኀም 102.1 ሬድዮ ላይ በሚያቀርባ቞ው ዚስንክሳር፣  ዚማሟሻ፣ ዚሃኪሞ መልዕክት፣ ዚአርብ ምሜት ቆዚት ያሉ ሙዚቃዎቜ እና በኢንቢሲ ቎ሌቪዥን በልዩ ልዩ ዝግጅቶቜ ዹምናውቀው ጋዜጠኛ መኮንን ወ/አሹጋይ "እነሆ ማሟሻ" ዹተሰኘ ዚመጀመሪያ ቅጜ አንድ እና ተኚታዩን ቅጜ ሁለት መጻህፍትን በተኚታታይ ኹዚህ ቀደም ለአንባቢያን ማድሚሱ ይታወሳል።

Telegram: https://t.me/EventAddis1
👏7👍4🔥2
📌ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ወደ አዹር ተመለሰ

ተወዳጁ ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ጣቢያ ለተወሰነ ጊዜ ኹአዹር ወርዶ እንደቆዚ ይታወሳል።

቎ሌቪዥን ጣቢያው ኚትላንት ጀምሮ ወደ አዹር እንደተመለሰም ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን በDstv ቻናል 468 እና በኢትዮሳት 11605 አሁን በስርጭት ይገኛል ተብሏል።

ትኩሚቱን ልጆቜ ላይ አድርጎ ዚሚሰራውና በጥቂት ጥሪት፣ ዹሰው ሀይል እዚህ ዹደሹሰው ዚኢትዮጵያ ልጆቜ ቎ሌቪዥን ጣቢያ በልጆቜና በቀተሰብ ዘንድ ተወዳጅ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያ እንደሆነ በርካቶቜ ይመሰክራሉ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍18❀7😱1
📌ቻናል 1 ዹመዝናኛ ቎ሌቪዥን ሊኚፈት ነው

ቻናል 1 (Channel 1) ዹተሰኘ አዲስ ዹመዝናኛ ዚ቎ሌቭዥን ጣቢያ ዚኢትዮጵያ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያዎቜን ዘርፍ ሊቀላቀል እንደሆነ ተሰምቷል።

ሰኔ ወር ላይ ዚሙኚራ ስርጭቱን እንደሚጀምር ዹተሰማዉ  ቻናል 1 ፣ ባሳለፍነዉ ሳምንት ኚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዚሳተላይት ስርጭት ፍቃድን ተሚክቧል።

ቻናሉ ቀደም ብሎ በርካታ ፕሮግራሞቜን እያዘጋጀ እንደኚሚመ እና አዳዲስ ዚፕሮግራም ይዘቶቜን ለተመልካቜ ይዞ ለመምጣትም ዝግጅት ላይ እንዳለ ተሰምቷል።

ዚቻናል 1 መስራቜ አቶ ሳሙኀል ደበበ፣ ኚ“ወንዶቜ ጉዳይ” ፊልም ፕሮዲዩሰርነት ጀምሮ ለ10 ዓመታት በኢቢኀስ ቎ሌቪዥን ኚካሜራ ጀርባ ትልቅ ፕሮግራሞቜን በማዘጋጀት እና ዳይሬክት በማድሚግ ይታወቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀11👍8
📌"አስኒ" ፊልም ቀጣይ ሳምንት ለእይታ ይበቃል

በድምጻዊት አስናቀቜ ወርቁ ሕይወትና ስራዎቜ ላይ ትኩሚቱን ያደሚገው "አስኒ" ዹተሰኘ ፊልም ቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ግንቊት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 11:30 ጀምሮ በቬኒው ዌርሃውስ ውስጥ ለእይታ ይበቃል።

ፊልሙ ኚታዚ በኃላም "ዚአስናቀቜ ወርቁ  ሕይወት ታሪክ: ድፍሚት ፣ጥልቅ ስሜት እና ውበት በኢትዮጵያ "ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ውይይት ኹፊልሙ አዘጋጅ ራሔል ሳሙኀል ጋር ውይይት ይካሄዳል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
❀4👍2🔥1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

1. ተዋናይት ትዕግሥት ግርማ ኚአስር ዓመት በኃላ በመድሚክ ተውኔት ዚመጣቜበት "ደጋግ ሰይጣኖቜ" ተውኔት ለመድሚክ ሊበቃ ነው።

2.ዚሚዲያ፣ዚሥነጜሑፍ፣ዚ቎አትርና ዹፊልም ባለሞያዎቜን ዚሥራና ዚሕይወት ታሪክን ዹሰነደው"መዝገበ አእምሮ ቅጜ 2 " መጜሐፍ ነገ ለንባብ ይበቃል።

3."ዳዎኀ ቡሹ" ዹተሰኘ ኢትዮጵያዊ ፊልም በዓለምአቀፍ ፌስቲቫሎቜ ላይ ለእይታ ሊቀርብ ነው።

እነዚህንና ሌሎቜንም ዚአርትስ ስፔሻል ዚኪነት እና ኩነት መሚጃዎቜ እናቀርብላቜኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/uQpiSwNxLJM?si=_cPFvapeM4Wte1zK

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀10🔥3
📌ዚደራሲ መዝገቡ አባተ መፅሀፍ ዛሬ ይመሹቃል

ዚዛሬ 50 ዓመት ዹተፃፈውና ዘንድሮ ለሕትመት ዹበቃው ዹጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ መፅሐፍ ዛሬ ግንቊት 25 2017 ዓ.ም በድምቀት ይመሚቃል።

ጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ  በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶቜ እዚተዘዋወሚ  ኚአካባቢው ነዋሪዎቜ  ጠይቆ ዚተሚዳውን መዝግቩ ያዘጋጀው መፅሀፍ ኹ400 በላይ ገፆቜ ያሉት ሲሆን ዹመፅሐፉም አርታዒ ዚታሪክ ባለሙያ ብርሀኑ ደቩጭ ነው፡፡

መፅሐፉ ዛሬበአዲስ አበባ ዩንቚርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሜ ሲመሚቅ ዚደራሲው ልጆቜ፣ ቀተሰቊቜና ወዳጆቜ ይታደማሉ፡፡በተጚማሪም ኹፍተኛ ዚመንግስት ዚሥራ ኃላፊዎቜ ፣ ዹሀገር ባለውለታዎቜ እንደሚገኙ ይጠበቃል።

ዚሁነቱ አዘጋጅ ደግሞ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሜን መሆኑ ሲሆን ዚደራሲው ቀተሰቊቜና መፅሀፉ ዚሕትመት ብርሀን እንዲያይ አድርገዋል፡፡

በመፅሀፉ ላይ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዎ፣ ፕሮፌሰር ሰሎሞን ሙሉጌታ እና ጋዜጠኛ ማዕሹጉ በዛብህ  ፣ዚመፅሀፍ ግምገማ ዚሚያቀርቡ ሲሆን ፕሮፌሰር ጥላሁን ተሟመም ዹመፅሀፍ ዳሰሳው አወያይ ና቞ው፡፡ ዚደራሲው ዚመዝገቡ አባተ ዚሕይወት ታሪክም በልጃቾው በፀሀይ መዝገቡ አባተ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተቜሏል፡፡

ደራሲ እና ጋዜጠኛ መዝገቡ አባተ  ዚዛሬ 14 ዐመት ሕይወቱ ያለፈ ጋዜጠኛ ሲሆት በአገራቜን በሕትመት ሚድያዎቜ በማገልገል ዚሚታወቅ ነው፡፡ኚሠራባ቞ው ዚህትመት ውጀቶቜ መካኚልም ሰንደቅ አላማቜን አንዱ ነው፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀7
📌አሐዱ ሬድዮና ቎ሌቪዥን ስልጠና አዘጋጅ

ልዩ ዚጋዜጠኝነት ክህሎት ዚክሚምት ስልጠና በአሐዱ ራዲዮ እና ቎ሌቭዥን

በመሠሚታዊ ዚጋዜጠኝነት ትምህርቶቜ

በዜና አፃፃፍና አቀራሚብ

በምርመራ ጋዜጠኝነት ምንነት እና አዘገጃጀት

በፕሮግራም ዝግጅት እና አቀራሚብ

በቃለ-ምልልስ ቎ክኒኮቜ

በማሕበራዊ ሚዲያ ይዘት አዘገጃጀት

በግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኀዲቲንግ

እንዲሁም በሌሎቜ መሠሚታዊ ዚጋዜጠኝነት ክህሎቶቜ ላይ በሚዲያ ሥራ ኹፍተኛ ልምድ ባላ቞ው አንጋፋ ጋዜጠኞቜ እና በዩኒቚርሲቲ መምህራን ስልጠና ይሰጣል፡፡

ስልጠናው ኹሰኔ 15 እስኚ ነሐሮ 30/2017 ድሚስ ዹሚቆይ ሲሆንፀ በንድፈ ሀሳብና በተግባር ልምምዶቜ ላይ አተኩሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ይሰጣል!

አድራሻ፡- ሲኀምሲ (CMC) ሚካኀል ዚኢኮኖሚክስ ባለሙያዎቜ ሕንጻ አንደኛ ፎቅ በአካል በመምጣት ይመዝገቡ!

እንዲሁም በ https://shorturl.at/aA2j5 ዝርዝር መሚጃዎቜን በመሙላት ይመዝገቡ!

ለበለጠ መሹጃ ፡-0940 00 00 05
                         0940 00 00 09

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀9
በዕውቀቱ ስዩም በቅኔ ቀት ዝግጅቱን ሊያቀርብ ነው

"በቅኔ ቀት" ዚፊታቜን June 14 LONDON እና  June 15 ደግሞ በ LEEDS "ዚሳቅ ድግስ"  ተዘጋጅቷል። ሁለቱም መድሚኮቜ ላይ በዕውቀቱ ስዩም በሀገሹ እንግሊዝ ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።

ቅኔ ቀት - በለንደን ኹተማ ውስጥ በሁለት ወራት አንዮ ቋሚ ምሜት ኹጀመሹ ሊስት ዓመታት አስቆጥሯል።

በእንግሊዝ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ "ዚሚስቶቌ ባሎቜ" ዹተሰኘ ዚመድሚክ ተውኔት በማስመጣት ለተመልካቜ አቅርቧል።

በዚህኛው ዙር ዝግጅት ላይም፣ በዕውቀቱ ስዩም ፣ትዕግስት ማሞ ብርሃኔ፣ዳግማዊ ጌታ቞ው፣በሐይሉ ነቃጥበብ፣አስተዋይ መለሰ፣ክብሮም ገ/ማርያም፣ኒኒ አሰፋ ፣ዳዊት ስራዎቻ቞ውን ያቀርባሉ።

ትኬቱ ለንደን ፊንስበሪ ፓርክ ዹሚገኘው ቅዱስ ገብርኀል ዚሀበሻ ሬስቶራንት እና ሊድስ ፒያሳ ባርና ሬስቶራንት ይገኛል ተብሏል።

+447305496203
+447950212404

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍13❀4
📌አትሌት ኃይሌ ገብሚስላሎ መፅሀፍ ተፃፈለት

ዚአትሌት ኃይሌን ዚህይወትና ዚስራ ፍልስፍና ዚሚያስሚዳውን መፅሀፍ ዚፃፈቜሁ ልጁ ሜላት ኃይሌ ገብሚስላሎ ናት።

ሚዳት ፀሀፊው ደግሞ አባዮሚ ሮቲሚ  ዚተባለ ፀሀፊ መሆኑን ሰምተናል።

በ12 ምዕራፍ ተኹፋፍሎ ዹተዘጋጀውን መፃፍ ለማሳናዳት ሁለት ዓመት እንደፈጀ ፀሀፊዋ አስሚድታለቜ።

አትሌት ኃይሌ ብዙውን ዚህይወት ታሪኩን ህዝብ ዚሚያውቀው ቢሆንም መፃህፉ ዚሚያተኩሚው ዚህይወትና ዚስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነ ተነግሯል።

ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ኚሌሎቜ ሰዎቜ በተለዹ ዚአትሌት ሀይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ጠቅሳለቜ።

መፅሀፉ አትሌት ኚእድገቱ እስኚ አሁን ባለው ዚሯጭነትና ዚቢዝነስ ምዕራፍ ዹተኹተላቾውን አመለካኚቶቹን፣ ፍልስፍናውን፣ ዚህይወት ልምዱ ዚተካተተበት መሆኑን ልጁ ሜላት ስትናገር ሰምተናታል።

ለጊዜው ''Dissecting Haile'በሚል ርዕስ ለህትመት ዹሚበቃው መፅሀፋ ወደፊት ወደ አማርኛ እና ሌሎቜ ቋንቋዎቜ እንደሚተሚጎም ተነግሯል።

መፅሀፉ ለገበያ ዹሚቀርበው በመጪው ነሀሮ ወር መሆኑንም ሰምተናል።

ዚአትሌት ኃይሌን ዚህይወት ታሪክ ዚሚመለኚት ሌላ መፃህፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኗንም ልጁ ተናግራለቜ።

Via ንጋቱ ሙሉ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
❀20👏3👍2
📌"ሰው ሙሉ ትዝታ" መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው

በገጣሚ ኪሩቀል ዘርፉ ዹተዘጋጀው "ሰው ሙሉ ትዝታ /ወል -መካ/" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዚግጥም መጜሐፍ በቅደመ ክፍያ ሜያጭ ለንባብ ሊበቃ እንደሆነ ተሰምቷል።

ገጣሚውም በማህበራዊ ትስስር ገፁ"

ብትወዱ በዚህ በኩል áˆžáˆá‰±

1000247106964
kirubel zerfu zeleke

በ telebirr🌟
0987367513
ዋጋ - 400 birr 💵

👉 @ቮሌ-ግራም ላይ ስክሪን ሹት አስቀምጡልኝ ተወዳጁኝ

https://t.me/kirubelzerfu" ብሏል።
❀7
📌በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት በዚህ ሳምንት እነዚህ ተውኔቶቜ ለተውኔት አፍቃሪን ይቀርባሉ።

መልካም መዝናኛ ይሁንላቜሁ !!

https://t.me/EventAddis1/6236
🥰11👏4❀1🔥1