📌የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በአዲስ አበባ ኮንሰርቶች
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ውስጥ የመዝናኛ እና የዕድል ፍላጎትን ለማጣጣም በሚያስችል አዲስ እና ትኩረት የሚስብ አካሄድ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር በነገው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄዱ ሶስት ታዋቂ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ተከትሎ የፊታችን ግንቦት ወር የሚወጣውን 50 ሚሊዮን ሎተሪ እንደሚያስተዋውቅ ገለጸ።
በሙዚቃ ኮንሰርት ታዳሚዎች በመዝናናታቸው ጎን ለጎን የ50 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ሎተሪ የመቁረጥ ዕድል ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዛሬ በሚደረጉ ሶስቱም ኮንሰርቶች ላይ ለሚሳተፋ በነፃ ለሚመዘገቡ ባለዕድለኞች የ50,000 (የሃምሳ ሺህ ብር) ሽልማትም ቀርቧል።
ይህ ልዩ ዕድል ሽልማት ዛሬ በሚካሄዱት በሚሊኒየም አዳራሽ ሽርጉድ ኮንሰርት ፣ በግዮን ሆቴል ልዑል ኮንሰርት እና በማርዮት ሆቴል በሚካሄደው ኤሌጋንስ ኮንሰርቶች ላይ የሚሳተፉትን ተሳታፊዎች ሎተሪ በመቁረጥ በEthiolottery.et ድረ ገጽ ላይ በመመዝገብ በቀላሉ እድለኛ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ውስጥ የመዝናኛ እና የዕድል ፍላጎትን ለማጣጣም በሚያስችል አዲስ እና ትኩረት የሚስብ አካሄድ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር በነገው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄዱ ሶስት ታዋቂ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ተከትሎ የፊታችን ግንቦት ወር የሚወጣውን 50 ሚሊዮን ሎተሪ እንደሚያስተዋውቅ ገለጸ።
በሙዚቃ ኮንሰርት ታዳሚዎች በመዝናናታቸው ጎን ለጎን የ50 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ሎተሪ የመቁረጥ ዕድል ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዛሬ በሚደረጉ ሶስቱም ኮንሰርቶች ላይ ለሚሳተፋ በነፃ ለሚመዘገቡ ባለዕድለኞች የ50,000 (የሃምሳ ሺህ ብር) ሽልማትም ቀርቧል።
ይህ ልዩ ዕድል ሽልማት ዛሬ በሚካሄዱት በሚሊኒየም አዳራሽ ሽርጉድ ኮንሰርት ፣ በግዮን ሆቴል ልዑል ኮንሰርት እና በማርዮት ሆቴል በሚካሄደው ኤሌጋንስ ኮንሰርቶች ላይ የሚሳተፉትን ተሳታፊዎች ሎተሪ በመቁረጥ በEthiolottery.et ድረ ገጽ ላይ በመመዝገብ በቀላሉ እድለኛ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍3
📌"በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም"
የሠዓሊ አሸናፊ መስቲካ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ባሳፍነው ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኘው አርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ድርስ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ ተናግረዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሠዓሊ አሸናፊ መስቲካ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ባሳፍነው ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኘው አርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ድርስ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ ተናግረዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏5👍2❤1
📌የአይዳ ሙሉነህ የፎቶግራፍ ዓውደርዕይ
በአይዳ ሙሉነህ ተዘጋጅቶ በ ዘ-ኢንድ ፈንድ አዘጋጅነት እና በሪቺንግ ዘ-ላስት ማይል ድጋፍ ለህዝብ የቀረበው ሪፍሬሚንግ ኔግሌክት የተሰኘ የፎቶ ዓውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡
በዓውደ-ርዕዩ አይዳ ሙሉነህን ጨምሮ የሰባት አፍሪካዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ስራ ስብስብ የቀረበ ሲሆን በዋነኝነትም ደሀ ከሚባሉ አገራት ውስጥ ከሚከሰቱ በሽታዎች ያላቸውን ማህበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጫና ለተመልካች ለማቅረብና የአፍሪካዊያንን ድምፅ ለአለም ለማሰማት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በስራዎቻቸው ጠንካራ ታሪክን በፎቶ የማስቀረት እና ማህረሰቡ የሚያልፍበትን እውነታ የማንፀባረቅ ድንቅ ችሎታ ያላቸው የስድስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች 54 የስነጥበብ ስራዎችና ዘጋቢ‐ፎቶዎች የተካተተበት ዓውደ-ርዕይ ስነ-ጥበብ ምን ያህል ወሳኝ ጉዳዮችን የማጉላት ትልቅ አቅም እንዳለው ያሳያሉ ተብሏል፡፡
እ.ኤ.አ በ2022 ተጀምሮ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአፍሪካ 2.8 ሚሊዮን ሰዎችን ተደራሽ ያደረገው ይሄው ዓውደ-ርዕይ በታላቅ ክብረበአል ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 2017ዓ.ም በገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል ለተመልካች ክፍት ይሆናል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በአይዳ ሙሉነህ ተዘጋጅቶ በ ዘ-ኢንድ ፈንድ አዘጋጅነት እና በሪቺንግ ዘ-ላስት ማይል ድጋፍ ለህዝብ የቀረበው ሪፍሬሚንግ ኔግሌክት የተሰኘ የፎቶ ዓውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡
በዓውደ-ርዕዩ አይዳ ሙሉነህን ጨምሮ የሰባት አፍሪካዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ስራ ስብስብ የቀረበ ሲሆን በዋነኝነትም ደሀ ከሚባሉ አገራት ውስጥ ከሚከሰቱ በሽታዎች ያላቸውን ማህበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጫና ለተመልካች ለማቅረብና የአፍሪካዊያንን ድምፅ ለአለም ለማሰማት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በስራዎቻቸው ጠንካራ ታሪክን በፎቶ የማስቀረት እና ማህረሰቡ የሚያልፍበትን እውነታ የማንፀባረቅ ድንቅ ችሎታ ያላቸው የስድስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች 54 የስነጥበብ ስራዎችና ዘጋቢ‐ፎቶዎች የተካተተበት ዓውደ-ርዕይ ስነ-ጥበብ ምን ያህል ወሳኝ ጉዳዮችን የማጉላት ትልቅ አቅም እንዳለው ያሳያሉ ተብሏል፡፡
እ.ኤ.አ በ2022 ተጀምሮ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአፍሪካ 2.8 ሚሊዮን ሰዎችን ተደራሽ ያደረገው ይሄው ዓውደ-ርዕይ በታላቅ ክብረበአል ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 2017ዓ.ም በገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል ለተመልካች ክፍት ይሆናል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤7👍7
📌ቴዲ አፍሮ በስምንት ሙዚቃዎች ላይ በግጥምና ዜማ የተሳተፈበት የአንጋፋዋ ድምጻዊት ኩኩ ሰብስቤ "ደጃዝማች" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም የፊታችን አርብ ይለቀቃል
ይህ የአንጋፋዋ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ "ደጃዝማች" የተሰኘ ስምንተኛ አዲስ የሙዚቃ አልበም ላይ አስራ ሶስት ሙዚቃዎችን ይዟል።
ከእነዚህ አስራ ሶስት ሙዚቃዎች ውስጥ የስምንቱ ሙዚቃዎች ግጥምና ዜማ የድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ / ሲሆን ሌሎቹን ሙዚቃዎች ደግሞ በግጥም ገጣሚ ይልማ ገብረአብ፣ገጣሚ መሰለ አስማማው፣ ገጣሚ ናትናኤል ግርማቸው የሰሩ ሲሆኑ ሞገስ ተካ እና ምስክር አወል ግጥምና ዜማ በመስራት በአልበሙ ላይ ተሳትፈዋል።
ከተቀሩት ስራዎች ውስጥ "ወለላዬ" የተሰኘው ሙዚቃ ደግሞ የኩኩ የድሮ ሙዚቃ ሲሆን ቴዲ ማክ እንደገና ሪአሬንጅ /Re Arrange/ አድርጎ የሰራው ሙዚቃ ነው።
የድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ " ደጃዝማች" በተሰኘው አዲስ አልበም ላይ ስመጥር የሆነ የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት ሲሆን የሙዚቃ አቀናባሪው አቤል ጳውሎስ ዘጠኙን ሙዚቃዎች በማቀናበር እንዲሁም አስራ አንዱን ሙዚቃዎች ሚክስ በማድረግ ተሳትፏል።
ሁለቱን ሙዚቃዎች አሬንጅ ያደረገው ማሩ ዓለማየሁ ሲሆን ሙዚቀኛ ያሬድ ተፈራ፣ ሙዚቀኛ አክሊሉ ወ/ዩሐንስ (ጆኒ ሳክስ) እና ሙዚቀኛ ዘሪሁን በለጠ በሳክስፎን፣ግሩም መዝሙር እና ሳሙኤል አሰፋ በጊታር ተሳትፈዋል።
"ደጃዝማች"ን ሙሉውን አልበም ማስተር ሳውንዱን /Sound Mastering/የሰራው ኪሩቤል ተስፋዬ ነው።
"ደጃዝማች" የተሰኘ ስምንተኛ አልበም የፊታችን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በራሷ ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ይህ የአንጋፋዋ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ "ደጃዝማች" የተሰኘ ስምንተኛ አዲስ የሙዚቃ አልበም ላይ አስራ ሶስት ሙዚቃዎችን ይዟል።
ከእነዚህ አስራ ሶስት ሙዚቃዎች ውስጥ የስምንቱ ሙዚቃዎች ግጥምና ዜማ የድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ / ሲሆን ሌሎቹን ሙዚቃዎች ደግሞ በግጥም ገጣሚ ይልማ ገብረአብ፣ገጣሚ መሰለ አስማማው፣ ገጣሚ ናትናኤል ግርማቸው የሰሩ ሲሆኑ ሞገስ ተካ እና ምስክር አወል ግጥምና ዜማ በመስራት በአልበሙ ላይ ተሳትፈዋል።
ከተቀሩት ስራዎች ውስጥ "ወለላዬ" የተሰኘው ሙዚቃ ደግሞ የኩኩ የድሮ ሙዚቃ ሲሆን ቴዲ ማክ እንደገና ሪአሬንጅ /Re Arrange/ አድርጎ የሰራው ሙዚቃ ነው።
የድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ " ደጃዝማች" በተሰኘው አዲስ አልበም ላይ ስመጥር የሆነ የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት ሲሆን የሙዚቃ አቀናባሪው አቤል ጳውሎስ ዘጠኙን ሙዚቃዎች በማቀናበር እንዲሁም አስራ አንዱን ሙዚቃዎች ሚክስ በማድረግ ተሳትፏል።
ሁለቱን ሙዚቃዎች አሬንጅ ያደረገው ማሩ ዓለማየሁ ሲሆን ሙዚቀኛ ያሬድ ተፈራ፣ ሙዚቀኛ አክሊሉ ወ/ዩሐንስ (ጆኒ ሳክስ) እና ሙዚቀኛ ዘሪሁን በለጠ በሳክስፎን፣ግሩም መዝሙር እና ሳሙኤል አሰፋ በጊታር ተሳትፈዋል።
"ደጃዝማች"ን ሙሉውን አልበም ማስተር ሳውንዱን /Sound Mastering/የሰራው ኪሩቤል ተስፋዬ ነው።
"ደጃዝማች" የተሰኘ ስምንተኛ አልበም የፊታችን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በራሷ ዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤14👍9👏1
📌ድምጻዊ ልዑል ሲሳይ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል
(መግቢያው በነፃ ነው)
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ልዑል ሲሳይን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከልዑል ጋር በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 28, 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከድምጻዊ ልዑል ሲሳይ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከልዑል ሲሳይ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ማክሰኞ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
📎 በ ዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://jazzio.land/register
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
(መግቢያው በነፃ ነው)
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ልዑል ሲሳይን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከልዑል ጋር በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 28, 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከድምጻዊ ልዑል ሲሳይ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከልዑል ሲሳይ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ማክሰኞ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
📎 በ ዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://jazzio.land/register
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍7❤3
📌የድምጻዊት ዘቢባ ግርማ "እንደምንም" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነው
አንጋፋውና ወጣት የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት “እንደምንም" የሙዚቃ አልበም 13 ሙዚቃዎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ዓመት እንዲወሰድባትም ተነግሯል።
ለአልበሙ ላይ የሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎች ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ በድምጻዊት ዘቢባ ግርማ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡
የሙዚቃ አልበሙ ስለ ፍቅር፤ ስለ ምስጋና እና ስለ እናት እና የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
የድምጻዊት ዘቢባ ግርሓጨ"እንደምንም" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ግንቦት አንድ በዘቢባ ግርማ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለአድማጮች ይቀርባል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
አንጋፋውና ወጣት የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት “እንደምንም" የሙዚቃ አልበም 13 ሙዚቃዎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ዓመት እንዲወሰድባትም ተነግሯል።
ለአልበሙ ላይ የሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎች ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ በድምጻዊት ዘቢባ ግርማ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡
የሙዚቃ አልበሙ ስለ ፍቅር፤ ስለ ምስጋና እና ስለ እናት እና የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
የድምጻዊት ዘቢባ ግርሓጨ"እንደምንም" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ግንቦት አንድ በዘቢባ ግርማ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለአድማጮች ይቀርባል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
👍1
📌የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ አውደርዕይ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ 17ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ ያካሂዳል።
በነዚህ ቀናት በዩኒቨርሲቲው በመገኘት አውደርዕዩን ጎብኙ፣መጽሐፍት ግዙ፣ስለ ንባብ ተወያዩ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ 17ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ ያካሂዳል።
በነዚህ ቀናት በዩኒቨርሲቲው በመገኘት አውደርዕዩን ጎብኙ፣መጽሐፍት ግዙ፣ስለ ንባብ ተወያዩ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤7👍2👏1
📌ፈስቲቫሉን ላይ በነፃ ይታደሙ
ቅዳሜ እና እሁድ ሚያዝያ 25 እና 26 2017 ዓ.ም የሚደረገው የዓለም የጥበብ ቀን እና የኢትዮጵያ ጃዝ ፌስቲቫል መግቢያ በነፃ ሆኗል።
የዓለም አቀፍ የሥነጥበብ ቀን እና የኢትዮጵያ ጃዝ ፌስቲቫል ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሚያዚያ 25 እና 26 2017 ይከናወናል፡፡ የዘንድሮው ፌስቲቫል ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገር ታዋቂና ተወዳጅ የሆኑ ሙዚቀኞችን ያሳተፈ እንደሆነ ተነግሯል።
በዚህ ዓመት ፌስቲቫል ላይ ለኢትዮ-ጃዝ አባት ለታዋቂው ሙላቱ አስታጥቄ በዘርፉ ላበረከቱት ፈር ቀዳጅ ሥራቸውና እና በዓለም የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ላኖሩት ሙዚቃዊ ትሩፋት ክብር የሚሰጥበት እንደሆነም ተገልጿል።
በተጨማሪም በፌስቲቫሉ ላይ ከ41 ዓመታት በኃላ አድማስ ባንድ የሙዚቃ ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ዝግጅቱ ቅዳሜ ሚያዚያ 25 እና እሁድ ሚያዚያ 26 2017 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ከቀኑ 7፡00 እስከ ምሽት 1፡00 በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ይካሄዳል።
አዘጋጆቹ የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚና SAY Records ናቸው።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
ቅዳሜ እና እሁድ ሚያዝያ 25 እና 26 2017 ዓ.ም የሚደረገው የዓለም የጥበብ ቀን እና የኢትዮጵያ ጃዝ ፌስቲቫል መግቢያ በነፃ ሆኗል።
የዓለም አቀፍ የሥነጥበብ ቀን እና የኢትዮጵያ ጃዝ ፌስቲቫል ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሚያዚያ 25 እና 26 2017 ይከናወናል፡፡ የዘንድሮው ፌስቲቫል ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገር ታዋቂና ተወዳጅ የሆኑ ሙዚቀኞችን ያሳተፈ እንደሆነ ተነግሯል።
በዚህ ዓመት ፌስቲቫል ላይ ለኢትዮ-ጃዝ አባት ለታዋቂው ሙላቱ አስታጥቄ በዘርፉ ላበረከቱት ፈር ቀዳጅ ሥራቸውና እና በዓለም የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ላኖሩት ሙዚቃዊ ትሩፋት ክብር የሚሰጥበት እንደሆነም ተገልጿል።
በተጨማሪም በፌስቲቫሉ ላይ ከ41 ዓመታት በኃላ አድማስ ባንድ የሙዚቃ ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ዝግጅቱ ቅዳሜ ሚያዚያ 25 እና እሁድ ሚያዚያ 26 2017 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ከቀኑ 7፡00 እስከ ምሽት 1፡00 በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ይካሄዳል።
አዘጋጆቹ የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚና SAY Records ናቸው።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
❤6👍3
📌የአርብ ምሽቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
1. ድምጻዊ ብስራት ሱራፌል ለአንደኛ ደረጃ ት/ቤት መምህሩ ያዜመበትን ሙዚቃ ጨምሮ 6 የሙዚቃ ስብስቦችን የያዘው "የጠይም ፈረንጅ" የሙዚቃ አልበምን ለአድማጮች አቀረበ።
2.ሁለት ጎራ ክፍሎ ሲያነጋገር የቆየው የድምጻዊ ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርት ከትላንትና በስቲያ በእስራኤል ቴላቪቭ ተካሄደ። በሌላ ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በ8 ሙዚቃዎች ላይ በግጥምና የተሳተፈበት የአንጋፋዋ ድምጻዊት ኩኩ ሰብስቤ አልበም ዛሬ አመሻሹን ለአድማጮች ቀረበ።
3.በመድረክ መሪና ጋዜጠኛ ወንድወሰን ከበደ የተዘጋጀው "የመድረክ ማስታወሻ" መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
4.ኢትዮጵያዊቷ በአሜሪካ ትልቅ የሥነጽሑፍ ሽልማት ተሸለመች።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/c6JUGt_BOl0?si=M28Ec0VbDN6xYOBs
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
1. ድምጻዊ ብስራት ሱራፌል ለአንደኛ ደረጃ ት/ቤት መምህሩ ያዜመበትን ሙዚቃ ጨምሮ 6 የሙዚቃ ስብስቦችን የያዘው "የጠይም ፈረንጅ" የሙዚቃ አልበምን ለአድማጮች አቀረበ።
2.ሁለት ጎራ ክፍሎ ሲያነጋገር የቆየው የድምጻዊ ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርት ከትላንትና በስቲያ በእስራኤል ቴላቪቭ ተካሄደ። በሌላ ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በ8 ሙዚቃዎች ላይ በግጥምና የተሳተፈበት የአንጋፋዋ ድምጻዊት ኩኩ ሰብስቤ አልበም ዛሬ አመሻሹን ለአድማጮች ቀረበ።
3.በመድረክ መሪና ጋዜጠኛ ወንድወሰን ከበደ የተዘጋጀው "የመድረክ ማስታወሻ" መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
4.ኢትዮጵያዊቷ በአሜሪካ ትልቅ የሥነጽሑፍ ሽልማት ተሸለመች።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/c6JUGt_BOl0?si=M28Ec0VbDN6xYOBs
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍6
📌የኢትዮፒካር እና አሚጎስ ጥምረት
ኢትዮፒካር መኪና አስመጪ ከአሚጎስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ጋር በመተባበር፣ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ዘመናዊ መኪኖችን ለ15 ደንበኞች ማስረከባቸውን ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮፒካር ዋና መ/ቤት በተካሄደ ሥነሥርዓት ላይ አስታውቀዋል።
በኢትዮፒካር በቀጥታ ግዢ እንዲሁም በባንክ ብድር አማራጭ እየቀረቡ የሚገኙት እነዚህ የኤሌክትሪክ መኪኖች የፋብሪካ ዋስትና እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን፤እስካሁንም ከ1000 በላይ ለሚሆኑ ፈላጊዎች ከባንክ እንዲሁም ከብድርና ቁጠባ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ውል በመግባት መኪኖቹን ማስረከቡን የኢትዮፒካር ማርኬቲንግ ኃላፊ ወወይዘሪት አቤኔዘር ደበበ ገለጸዋል።
ኢትዮፒካር መኪኖቹን የሚሸጠው ከባትሪና መለዋወጫ ዕቃዎች ዋስትና ጋር መሆኑን የጠቆሙት የማርኬቲንግ ኃላፊዋ፤ በቻይና በ3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የተለያዩ ሞዴል መኪኖችን እንደሚያስመጣ ተናገረዋል።
አሚጎስ ከኢትዮፒካር ጋር ስምምነት ከፈጸመ ወዲህ ቅድመ ቁጠባውን ላሟሉ 100 ደንበኞቻቸው የኤሌክትሪክ መኪኖችን ያስረከቡ ሲሆን፤ እስከ መጪው ሰኔ 30 ባለው ጊዜም 50 ለሚደርሱ ደንበኞች መኪኖችን ለማስረከብ መታቀዱም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ኢትዮፒካር መኪና አስመጪ ከአሚጎስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ጋር በመተባበር፣ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ዘመናዊ መኪኖችን ለ15 ደንበኞች ማስረከባቸውን ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮፒካር ዋና መ/ቤት በተካሄደ ሥነሥርዓት ላይ አስታውቀዋል።
በኢትዮፒካር በቀጥታ ግዢ እንዲሁም በባንክ ብድር አማራጭ እየቀረቡ የሚገኙት እነዚህ የኤሌክትሪክ መኪኖች የፋብሪካ ዋስትና እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን፤እስካሁንም ከ1000 በላይ ለሚሆኑ ፈላጊዎች ከባንክ እንዲሁም ከብድርና ቁጠባ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ውል በመግባት መኪኖቹን ማስረከቡን የኢትዮፒካር ማርኬቲንግ ኃላፊ ወወይዘሪት አቤኔዘር ደበበ ገለጸዋል።
ኢትዮፒካር መኪኖቹን የሚሸጠው ከባትሪና መለዋወጫ ዕቃዎች ዋስትና ጋር መሆኑን የጠቆሙት የማርኬቲንግ ኃላፊዋ፤ በቻይና በ3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የተለያዩ ሞዴል መኪኖችን እንደሚያስመጣ ተናገረዋል።
አሚጎስ ከኢትዮፒካር ጋር ስምምነት ከፈጸመ ወዲህ ቅድመ ቁጠባውን ላሟሉ 100 ደንበኞቻቸው የኤሌክትሪክ መኪኖችን ያስረከቡ ሲሆን፤ እስከ መጪው ሰኔ 30 ባለው ጊዜም 50 ለሚደርሱ ደንበኞች መኪኖችን ለማስረከብ መታቀዱም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍5🔥1
📌የሮፍናን ኮንሰርት ጋምቤላ ሊካሄድ ነው
የሁለገቡ ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ"የኔ ትውልድ " የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 2 2017 ዓ.ም በጋምቤላ ከተማ ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
ይህ የሮፍናን የሙዚቃ ኮንሰርት በጋምቤላ ስታዲየም እንደሚካሄድም ሙዚቀኛው በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሁለገቡ ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ"የኔ ትውልድ " የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 2 2017 ዓ.ም በጋምቤላ ከተማ ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
ይህ የሮፍናን የሙዚቃ ኮንሰርት በጋምቤላ ስታዲየም እንደሚካሄድም ሙዚቀኛው በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🔥6👍2❤1🥰1
📌"ቍናማት" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
በገጣሚ ሐዋዝ የሻነህ የተዘጋጀው "ቍናማት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።
መጽሐፉ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ205 ገፆች ተቀንብቦ በ400 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚና ደራሲ ሐዋዝ የሻነህ ከዚህ መጽሐፍ አስቀድሞ "ኢካቦድ"የግጥም ስብስብ)፣ "የአዳም ፊርማ" እና "ሰውነት" የተሰኘ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በገጣሚ ሐዋዝ የሻነህ የተዘጋጀው "ቍናማት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።
መጽሐፉ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ205 ገፆች ተቀንብቦ በ400 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚና ደራሲ ሐዋዝ የሻነህ ከዚህ መጽሐፍ አስቀድሞ "ኢካቦድ"የግጥም ስብስብ)፣ "የአዳም ፊርማ" እና "ሰውነት" የተሰኘ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤5🔥2
📌"ለጋስ አድማስ" መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው
በገጣሚ ወልደገብርኤል ደሳለኝ(ወገደ) የተዘጋጀው "ለጋስ አድማስ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ በቅርቡ ንባብ ይበቃል ተብሏል።
"ለጋስ አድማስ" የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ350 ብር በቅደመ ሽያጭ ለአንባቢያን ይቀርባል።
መጽሐፉን መግዛት ለሚፈልጉ የባንክ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦ 1000530618661
ወልደገብርኤል ደሳለኝ
ቴሌ ብር ፦0992269755
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በገጣሚ ወልደገብርኤል ደሳለኝ(ወገደ) የተዘጋጀው "ለጋስ አድማስ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ በቅርቡ ንባብ ይበቃል ተብሏል።
"ለጋስ አድማስ" የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ350 ብር በቅደመ ሽያጭ ለአንባቢያን ይቀርባል።
መጽሐፉን መግዛት ለሚፈልጉ የባንክ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦ 1000530618661
ወልደገብርኤል ደሳለኝ
ቴሌ ብር ፦0992269755
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤3👍3
“የአፍሪካ ቀንድ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው
“የአፍሪካ ቀንድ” የተሰኘው መጽሐፍ በመጪው አርብ ገበያ ላይ ይውላል ተብሏል።
በታዋቂው የአፍሪካ ቀንድ እና የኢትዮጵያ ጉዳይ ተመራማሪ በሆኑት ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ክላፋም ተጽፎ፣ በጋዜጠኛ ኅይለመስቀል በሸዋምየለህ ወደ አማርኛ የተመለሰው ይኽ መጽሐፍ፣ በ231 ገጾች ተቀንብቦ በ450 ብር እንደሚሸጥ ሰምተናል።
መጽሐፉ፣ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ ባሏቸው ፖለቲካዊ ግንኙነቶች ላይ አተኩሮ፣ የመጪውን የቀንዱን ዕጣ ፈንታም ይዳስሳል ተብሏል።
መጽሐፉ በኹሉም የጃፋር መጽሐፍት ቤቶች እንደሚገኝም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
“የአፍሪካ ቀንድ” የተሰኘው መጽሐፍ በመጪው አርብ ገበያ ላይ ይውላል ተብሏል።
በታዋቂው የአፍሪካ ቀንድ እና የኢትዮጵያ ጉዳይ ተመራማሪ በሆኑት ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ክላፋም ተጽፎ፣ በጋዜጠኛ ኅይለመስቀል በሸዋምየለህ ወደ አማርኛ የተመለሰው ይኽ መጽሐፍ፣ በ231 ገጾች ተቀንብቦ በ450 ብር እንደሚሸጥ ሰምተናል።
መጽሐፉ፣ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ ባሏቸው ፖለቲካዊ ግንኙነቶች ላይ አተኩሮ፣ የመጪውን የቀንዱን ዕጣ ፈንታም ይዳስሳል ተብሏል።
መጽሐፉ በኹሉም የጃፋር መጽሐፍት ቤቶች እንደሚገኝም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍13❤1🔥1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ አውደርዕይ ተከፍቷል
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የመጽሀፍ አውደ-ርዕይ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ ውስጥ ከዛሬ ሚያዝያ 28 2017 ዓ.ም ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።
17ኛው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የመጽሀፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል፡፡
በዚህ አውደርዕይ ላይ አዳዲስ መጻሕፍት ይመረቃሉ፣ ዳግም የታተሙ መጻሕፍት ለሽያጭ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የመጽሀፍ አውደ-ርዕይ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ ውስጥ ከዛሬ ሚያዝያ 28 2017 ዓ.ም ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።
17ኛው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የመጽሀፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል፡፡
በዚህ አውደርዕይ ላይ አዳዲስ መጻሕፍት ይመረቃሉ፣ ዳግም የታተሙ መጻሕፍት ለሽያጭ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍5
4 የኢቤኤስ ሰራተኞች በዋስትና እንዲለቀቁ ተወሰነ
በሽብር ወንጀል ጉዳይ ተጠረጥረው በእስር ላይ የሚገኙ አራት የኢቤኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች፤ ዋስትና በማስያዝ እንዲለቀቁ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ።
ሁለት የጣቢያው ሰራተኞችን ጨምሮ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት አስታውቋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በሽብር ወንጀል ጉዳይ ተጠረጥረው በእስር ላይ የሚገኙ አራት የኢቤኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች፤ ዋስትና በማስያዝ እንዲለቀቁ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ።
ሁለት የጣቢያው ሰራተኞችን ጨምሮ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት አስታውቋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍8🔥1
📌ኮሜዲያን ደረጄ ኃይሌ እና ጋዜጠኛ የአብሥራ ገዛኸኝ በጂንካ ዩኒቨርስቲ ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ነው
በጂንካ ዩኒቨርስቲ ልዩ ኪነጥበብ ተዘጋጅቷል።በዚህ ዝግጅት ላይ አንጋፋው ኮሜዲያን ደረጄ ኃይሌና የአርትስ ቴሌቪዥኑ አመለሸጋው ጋዜጠኛ የአብሣራ ገዛኸኝ በክብር እንግድነት ይገኙበታል።
በተጨማሪም ፕሮግራሙ ላይ በአቢሲኒያ የኪነጥበብ ቡድን አባላት የግጥም፣ የሙዚቃ ፣የመነባንብ ፣ጭውውትና በአጠቃላይ የኪነጥበብና የሥነጽሑፍ ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ።
ዝግጅቱ ዛሬ ሚያዝያ 30 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በጂንካ ዩኒቨርስቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በጂንካ ዩኒቨርስቲ ልዩ ኪነጥበብ ተዘጋጅቷል።በዚህ ዝግጅት ላይ አንጋፋው ኮሜዲያን ደረጄ ኃይሌና የአርትስ ቴሌቪዥኑ አመለሸጋው ጋዜጠኛ የአብሣራ ገዛኸኝ በክብር እንግድነት ይገኙበታል።
በተጨማሪም ፕሮግራሙ ላይ በአቢሲኒያ የኪነጥበብ ቡድን አባላት የግጥም፣ የሙዚቃ ፣የመነባንብ ፣ጭውውትና በአጠቃላይ የኪነጥበብና የሥነጽሑፍ ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ።
ዝግጅቱ ዛሬ ሚያዝያ 30 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በጂንካ ዩኒቨርስቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍1
📌የኢትዮጵያ ተመራማሪዎች ሳይንሳዊ ጽሑፍ ከየትኛውም ሀገር በበለጠ ተሰርዟል ተባለ
በቅርቡ ይፋ የሆነ አንድ አዲስ ጥናት በኢትዮጵያ ተመራማሪዎች የተጻፉት ሳይንሳዊ ጽሑፎች ዓለም ውስጥ ካሉ ከማንኛውም ሀገር ተመራማሪዎች በበለጠ መጠን ተሰርዘዋል ወይም ተመልሰው ተወስደዋል ሲል አመልክቷል ።
ይህም በኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎች የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ፅሁፎች ከእውነት የራቁ ወይም ከፍተኛ የጥራት ችግር ያለባቸው በመሆናቸው ከአሳታሚዎች እንዲሰረዙ መደረጉን አመልክቷል።
በህንድ የሚገኝ የውሂብ ሳይንቲስት የሆኑት አቻል አግራዋል ባካሄዱት ይህ ጥናት፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ ስትሆን ሳውዲ አረቢያ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና እና ግብፅ በመቀጠል ከፍተኛውን የፅሁፍ መሰረዝ መጠን ያሳዩ ሀገራት ናቸው።
ተመራማሪው አግራዋል እንዳሉት፣ ይህ ሊሆን የቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በንቃት የሚከታተሉና የሚያጋልጡ ጠንካራ የሳይንስ ባለሙያዎች ማህበረሰብ ባለመኖሩ ሊሆን ይችላል።
በአንጻሩ እንደ ፈረንሳይ ያሉ ሀገራት የምርምርን ታማኝነት በማረጋገጥ ረገድ ግንባር ቀደም ሲሆኑ፣ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በመለየትና በማስወገድ ረገድም ውጤታማ ናቸው ብለዋል።
ጥናቱ አብዛኛዎቹ ፅሁፎች የተሰረዙበት ምክንያት በግልጽ እንደሚታየው በሐቀኛ ስህተት ሳይሆን፣ "አብዛኛው" የሚሆነው በተለያዩ የሥነ ምግባር ጉድለቶች የተነሳ እንደሆነ ይጠቁማል። ይህም የውሸት መረጃዎችን ማቅረብ፣ የሌሎችን ስራ ያለ ፈቃድ መጠቀም (ስርቆት) ወይም በምርምር ሂደቱ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶችን መፈጸምን ያካትታል።
Via ካፒታል ጋዜጣ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በቅርቡ ይፋ የሆነ አንድ አዲስ ጥናት በኢትዮጵያ ተመራማሪዎች የተጻፉት ሳይንሳዊ ጽሑፎች ዓለም ውስጥ ካሉ ከማንኛውም ሀገር ተመራማሪዎች በበለጠ መጠን ተሰርዘዋል ወይም ተመልሰው ተወስደዋል ሲል አመልክቷል ።
ይህም በኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎች የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ፅሁፎች ከእውነት የራቁ ወይም ከፍተኛ የጥራት ችግር ያለባቸው በመሆናቸው ከአሳታሚዎች እንዲሰረዙ መደረጉን አመልክቷል።
በህንድ የሚገኝ የውሂብ ሳይንቲስት የሆኑት አቻል አግራዋል ባካሄዱት ይህ ጥናት፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ ስትሆን ሳውዲ አረቢያ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና እና ግብፅ በመቀጠል ከፍተኛውን የፅሁፍ መሰረዝ መጠን ያሳዩ ሀገራት ናቸው።
ተመራማሪው አግራዋል እንዳሉት፣ ይህ ሊሆን የቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በንቃት የሚከታተሉና የሚያጋልጡ ጠንካራ የሳይንስ ባለሙያዎች ማህበረሰብ ባለመኖሩ ሊሆን ይችላል።
በአንጻሩ እንደ ፈረንሳይ ያሉ ሀገራት የምርምርን ታማኝነት በማረጋገጥ ረገድ ግንባር ቀደም ሲሆኑ፣ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በመለየትና በማስወገድ ረገድም ውጤታማ ናቸው ብለዋል።
ጥናቱ አብዛኛዎቹ ፅሁፎች የተሰረዙበት ምክንያት በግልጽ እንደሚታየው በሐቀኛ ስህተት ሳይሆን፣ "አብዛኛው" የሚሆነው በተለያዩ የሥነ ምግባር ጉድለቶች የተነሳ እንደሆነ ይጠቁማል። ይህም የውሸት መረጃዎችን ማቅረብ፣ የሌሎችን ስራ ያለ ፈቃድ መጠቀም (ስርቆት) ወይም በምርምር ሂደቱ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶችን መፈጸምን ያካትታል።
Via ካፒታል ጋዜጣ
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👍8🤔7❤1🔥1
📌 የነገረ መጻሕፍት አዘጋጆችና ታደሚያን ቅዳሜ "አበሻው " በተሰኘ መጽሐፍ ላይ ይወያያሉ
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ነገ ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አበሻው " የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት አያሌው ምትኩ ብሩ ይገኛሉ ተብሏል። የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ነገ ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አበሻው " የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት አያሌው ምትኩ ብሩ ይገኛሉ ተብሏል። የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
❤2👍1
📌የአርብ ምሽቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
የአርትስ ስፔሻል መረጃዎች ዋና ዋና ጉዳዮች:
1. የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ካደረሰ ሃያ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት መለሠ እና ሚካኤል በላይነህ የተጣመሩበት የሙዚቃ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።
2.ጦቢያ የኪነጥበብና የሀሳብ መሰናዶ በዘጠኝ የአውሮፓ ሃገራት በ16 የአውሮፓ ትልልቅ ከተሞች ትርዒቱን ሊያቀረብ ነው።
3.ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ከፍተኛ ወጪ አውጥቼበታለሁ ያለውን የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች እንደሚያቀርብ ተናገረ።
4.የደራሲ አድኃኖም ምትኩ ሁለተኛ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
5.'የተሸመኑ ትውስታዎች' የሥዕል አውደርዕይ ነገ ይከፈታል።
6.ኮሜዲያን እሸቱ መለሠ የኮሜዲ ዝግጅቱን ነገ በለንደን ከተማ ያቀርባል።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/XBpZW2u7i3M?si=jPI7dBJ4hx5gLsrd
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
የአርትስ ስፔሻል መረጃዎች ዋና ዋና ጉዳዮች:
1. የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ካደረሰ ሃያ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት መለሠ እና ሚካኤል በላይነህ የተጣመሩበት የሙዚቃ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።
2.ጦቢያ የኪነጥበብና የሀሳብ መሰናዶ በዘጠኝ የአውሮፓ ሃገራት በ16 የአውሮፓ ትልልቅ ከተሞች ትርዒቱን ሊያቀረብ ነው።
3.ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ከፍተኛ ወጪ አውጥቼበታለሁ ያለውን የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች እንደሚያቀርብ ተናገረ።
4.የደራሲ አድኃኖም ምትኩ ሁለተኛ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
5.'የተሸመኑ ትውስታዎች' የሥዕል አውደርዕይ ነገ ይከፈታል።
6.ኮሜዲያን እሸቱ መለሠ የኮሜዲ ዝግጅቱን ነገ በለንደን ከተማ ያቀርባል።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/XBpZW2u7i3M?si=jPI7dBJ4hx5gLsrd
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
🔥6👍5❤2
📌"ጦቢያ" በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት
"ጦቢያ" የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።
ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።
ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ጦቢያ" የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።
ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።
ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
👏5❤2👍1