Event Addis Media
9.64K subscribers
6.09K photos
13 videos
4 files
4.71K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ታዋቂው ሙዚቀኛ አቶ አለማዹሁ ፋንታ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

በባህላዊ ዹሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋጭነታ቞ው ዚሚታወቁት ሙዚቀኛው አለማዹሁ ፋንታ ስራ቞ውን ዚጀመሩት ሃገር ፍቅር ቲያትር ቀት በመቀጠር ነውፀ እዚያም ለ10 ዓመታት ሰርተዋል፡፡

ለ40 ዓመታት ያህል በ ያሬድ ዹሙዚቃ ትምህርት ቀት በመምህርነት ሲያገለግሉ ዚቆዩት ሙዚቀኛውፀ በዕድሜአ቞ው መጚሚሻ ጡሚታ ኚውጡ በኋላ በዚሁ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቀት ማገልገላቾውን ዹሙዚቀኛው ዚቅርብ ሰው ሆኑት ታዋቂው ዹበገና መምህር መጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ነግሚውናል፡፡

ባህላዊዎቹን ዚኢትዮጵያ ዹሙዚቃ መሳሪያዎቜ በገናን በመደርደር፣ ክራርና መሰንቆን  አሳምሚው በመጫወት ይታወቁ እንደነበር ኚመጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ሰምተናል፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማዹሁ ፋንታ ዹቀለም ትምህርትን ዚተማሩ እንዲሁም ዚድቁና ትምህርትም ዚነበራ቞ው ነበሩ፡፡

ሙዚቀኛው ኹ6 ወራት በፊት በድንገት ወድቀው እግራ቞ው በመሰበሩ በህክምና ሲሚዱ ቆይተው በትናንትናው እለት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ኹዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራ቞ው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ኹቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈፀምም ሰምተናል፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማዹሁ ፋንታ ባለ ትዳርና 6 ልጆቜ አባት ነበሩ፡፡

📌Via ሾገር 102.1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
Event Addis Media
Photo
📌ኚድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ጋር በተያያዘ እስካሁን ያሉ መሚጃዎቜ

ዚድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ሞትን በተመለኹተ በርካታ መሚጃዎቜ እዚወጡ ይገኛሉ።

ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ዚት ነበሚቜ? ዚድምጻዊው ማናጀር ስለልጅቷ ተናግሯል።

በኢንጂነሪንግ ድግሪ ኚአርባምንጭ ዩኒቚርሲቲ ዚተመሚቀቜው ቀነኒ በሞዮሊንግ በማስታወቂያ ሥራዎቜ በማኅበራዊ ሚድያ ዝናን አትርፋለቜ።

በሚቀጥለው ቅዳሜ ልደቷን ለማክበር በሚል ፎቶዎቜ እዚተነሳቜ እንደነበር ኚቅርብ ሰዎቿ ዹተገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ልጅቱ ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ዚት ነበሚቜ?

ልጅቱ ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ለልደቷ ፎቶ ስትነሳ እንደነበር በወቅቱ ፎቶ ያነሳት ዹነበሹው ዚወንዎክስ ስቱዲዮ ባለቀት ወንድወሰን ጋሻው ተናግሯል ።

ፎቶግራፈሩም "በፎቶግራፍ  ስራዎቜ ካፈራዋ቞ው ወዳጆቌ መካኚል ዹቀኝ እጄ ዚምላት እህ቎ ቀነኒ አዱኛ መካሪዬ ጎደኛዬ ዹክፉ ቀን ወዳጄ ነበሚቜ።

ትላንት መጋቢት 1 2017 á‹“.ም ኹቀኑ 10:00 ጀምሮ  ዚልደት ፎቶዎቜ ሳነሳት ነበር ማታ 1:00 በሰላም ተለያዚትን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 2 2017 ዓ.ም ጠዋት ማሹፏን አሚዱኝ" ብሏል።

በተጚማሪም ትላንትና መጋቢት 1 2017 ዓ.ም አመሻሹን ቀነኒ አዱኛ ኚእጮኛዋ ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ ጋር  በመዝናኛ ስፍራ አብሚው እንዳሳለፉም ኚተለያዩ ምንጮቜ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ማናጀር ዹሆነው ለሊሣ እንድሪስ ዹተፈጠሹውን ለቢቢሲ አፋን ኊሮሞ ተናግሯል።

"ንጋት 11:00 ሰዓት ስልክ ተደውሎ «ቀነኒ ተጎድታ ሆስፒታል ገብታለቜ ቶሎ ድሚስ» እንደተባለ ዹሚናገሹው ለሊሳ እሱ ሩቅ በመሆኑ በሰዓቱ መድሚስ እንዳልቻለ ይናገራል።

ቩሌ አራብሳ ኚዓመት በላይ በጋራ ኚሚኖሩበት መኖሪያ ቀታ቞ው ኚአምስተኛ ፎቅ እንደወደቀቜ እና ምን እንደተፈጠሚ ፖሊስ እያጣራ መሆኑ ተነግሯል።

ክስተቱ ኹተፈጠሹ በኋላ በቅርብ በሚገኘው ያኔት ሆስፒታል ኚገባቜ በኋላ ጠዋት ፖሊስ መጥቶ ሬሳዋን ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለምርመራ ኹወሰደ በኋላ ዚምርመራ ውጀት እስኪወጣ አስክሬኗ ወደ ቀተሰቊቿ ሱሉልታ መሄዱ ነው ዚተገለፀው።

ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ኚሆስፒታል ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ እዛ ዹሚገኝ ሲሆን እኛ ዹምናውቀው እስካሁን አለመታሰሩን ነው ምርመራ እናድርግ ብሎ ነው ፖሊስ ዹወሰደው ሲል ማናጀሩ ይናገራል።

ለሁለት አመታት በፍቅር ኚቆዩ በኋላ በቅርቡ ጋብቻ቞ውን ለመፈፀም እዚተዘጋጁ እንደሆነ አውቃለሁ ሲል ለሊሳ ይናገራል።

ፖሊስ ምን አለ?

ዚልጅቱ አሟሟት ምን እንደሆነ ዚምርመራ ስራ ተሰርቶ እስኪገለጥ ድሚስ ህብሚተሰቡ በትዕግሥት ይጠብቅ በሌላ በኩል አንዳንድ ግለሰቊቜ ተገቢ ካልሆነ ትንታኔ ይታቀቡ ብሏል።

📞ፎቶው ትላንት ለልደቷ ዚተነሳቜው ፎቶ ነበር።

@EventAddis1
📌ሆ቎ሎቜን ዚጎዳው ዚአሜሪካ እርዳታ መቋሚጥ

በኢትዮጵያ ዚአሜሪካ ድጋፍ በመቋሚጡ በሆ቎ሎቜ ዹሚደሹጉ ስብሰባዎቜና ሥልጠናዎቜ መቀነሳ቞ው ተገለጞ።

ዚአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኊ ድርጅት (ዩኀስኀአይዲ) በተለያዩ መንገዶቜ ለአገሮቜ ሲያደርገው ዹነበሹውን ድጋፍ በማቋሚጡ ምክንያት በአዲስ አበባ ኹተማ በሚገኙ ሆ቎ሎቜ ይካሄዱ ዚነበሩ ሥልጠናዎቜ፣ ስብሰባዎቜና አጫጭር ዓውደ ጥናቶቜ መቀነሳ቞ውን ዹሆቮል ዘርፍ ተዋናዮቜ ተናገሩ፡፡

እ.ኀ.አ. በ2024 ብቻ ወደ 38 ቢሊዮን ዶላር በጀት በመላው ዓለም ወጪ ማድሚጉ ዚሚነገርለት ዩኀስኀአይዲ ለኢትዮጵያ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ያደሚገ ግዙፍ ዚተራድኊ ድርጅት መሆኑ ይነገርለታል፡፡

በኹተማው ውስጥ ኹሚገኙ ሆ቎ሎቜ ይህ ድጋፍ በመቋሚጡ ዹገጠማቾውን ቜግር በተመለኹለተ ሪፖርተር ያነጋገራ቞ውና ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዹፈለጉ አንድ ዚማርኬቲንግ ባለሙያ፣ እ.ኀ.አ. በመጋቢትና በሚያዝያ 2025 ብቻ ለሆቮላቾው ይገባ ዹነበሹ 25,000 ዶላር በፕሮግራሙ መታጠፍ ምክንያት መሰሹዙን ተናግሚዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ዹማይገኘውን ገንዘብ ለማካካስ ኹዚህ ቀደም ኹነበሹው ዹሆቮሉ ዋጋ ባነሰ ገንዘብ ዚሚመጡ ፕሮግራሞቜንና እንግዶቜን ዚመቀበል፣ እንዲሁም በማርኬቲንግ ባለሙያዎቜ አማካይነት ወደ ድርጅቶቜና ተቋማት በመሄድ ዚማካካሻ እንግዳና ዚመሳብ ሥራ እዚተኚናወነ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በካዛንቺስ አካባቢ ዹሚገኝ አንድ ዹሆቮል አዳራሜ ባለሙያ ለሪፖርተር በሰጡት አስተያዚት፣ ዹሆቮሉ አዳራሜ በሳምንት ሊስ቎ አንዳንዎም ለአምስት ቀናት በሙሉ ተይዘው ዚነበሚበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን ግን ዹሚደሹጉ ስብሰባዎቜ ቁጥር መቀነሱን ገልጞዋል፡፡

Via ሪፓርተር ጋዜጣ (ሲሳይ ሳህሉ)

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌 ‘ናኊታ’ ዚልጆቜ መጜሔት ለንባብ በቃቜ

ዚኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአፋን ኊሮሞ ያዘጋጃት ‘ናኊታ’ ዚልጆቜ መጜሔት ለንባብ በቅታለቜ።

‘ናኊታ’ ዚተሰኘቜዉ ዚልጆቜ መጜሄት ባለ 40 ገጜ እና ባለ ሙሉ ቀለም ህትመት ያላት ወራዊ መጜሄት ስትሆንፀ ኚዚካቲት ወር ጀምሮ በገበያ ላይ ትገኛለቜ፡፡

መጜሔቷ ትዉልዱን በመልካም ስነ ምግባር እና እውቀት ማነጜን ታሳቢ ያደሚገቜ ናት።
በዋናነት በሳይንስ እና ቎ክኖሎጂ፣ ባህልና ታሪክ፣ ተፈጥሮ፣ ማህበራዊ እና ሌሎቜ ጉዳዮቜ ዚተካተቱባት ነቜ።

በዚህም ልጆቜን እያዝናናቜ በስነ መግባር ዚምታንጜ፣ ዚንባብ ልምድን ዚምታዳብር እንዲሁም ልጆቜን ኚሳይንስና ጋር ዚምታስተዋዉቅ መጜሄት ተደርጋ ዚተዘጋጀቜ ሆናለቜ።

ኹ3  እስኚ እና 15 ዓመት ዹሚገኙ ልጆቜ ዚመጜሄቷ ዋና ታላሚ አንባቢያን ና቞ዉ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣርና እሑድ ይካሄዳል

ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድር እና ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት በመጪው እሁድ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አስታውቋል፡፡

‘ቁርዓን - ዚእውቀትና ዹሰላም ምንጭ’ በሚል መሪ ሃሳብ ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድሩ ዚማጣሪያ መድሚክ በአዲስ አበባ እዚተካሄደ ነው።

ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ም/ቀት ፕሬዚዳንት ጜ/ቀት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበኚር አሕመድ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ቁርዓን በሁሉም መስክ ዚሰዎቜን ሕይወት በቀና መንገድ በመምራት ለማህበሚሰብ ኚፍታ መሰሚት መሆን ዚቻለ ነው።

በዚህ አግባብ ውድድሩ ይህን ዹቁርዓን ክብርና ኚፍታ ለመግለጥ ዹተዘጋጀ መሆኑን ነው ዚተናገሩት።

ውድድሩ ቁርዓንን በልቩናቾው ዹተሾኹሙ ሃፊዝ ወጣቶቜን ለማበሚታታትና ቀጣይ ተተኪ ትውልዶቜን ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።

ዋናው ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድር እሑድ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ አመልክተዋል፡፡

በዚሁ ቀን በርካታ አማኞቜ ዚሚታደሙበት ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ ሥርዓት ‘ኚኢፍጣር እስኚ ቁርዓን’ በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚኚናወን ጠቁመውፀ ሕዝበ ሙስሊሙ በሁለቱ ታላላቅ መርሐ ግብሮቜ ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

© FMC

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚድምጻዊት ዹማ ዹሙዚቃ ቪዲዮ ተለቀቀ

ድምጻዊት ዚማርያም ቞ርነት(ዹማ) "ስንት ነው?" ለተሰኘው ዹሙዚቃ ሥራዋ ያስናዳቜው ዹሙዚቃ ቪዲዮ  ዛሬ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም በዩቲዩብ ቻናሏ በኩል ለአድማጮቜ ደርሷል።

ድምጻዊት ስለዚህ ዹሙዚቃ ቪዲዮ በማህበራዊ ትስስር ገጿ"ዹደጋ ሰው አልበም ኹተለቀቀ አንድ ዓመት ዹሆነው ሲሆን በዚህ መካኚል በነበሩኝ 70 ዹሚሆኑ ዓለም አቀፍ ዚመድሚክ ስራዎቜ እና ዝግጅቶቜ  ምክንያት ዚቪዲዮ ስራ ሳላቀርብ ቆይቻለሁ።

በቅርቡ በአዲስ አበባ በመድሚክ ዹምንገናኝ ሆኖ ኹዚህ አልበም ውስጥ “ስንት ነው? “ዹተሰኘውን ዹሙዚቃ ቪዲዮ በዹማ (YEMa) YouTube channel ስለተለቀቀ እንድትመለኚቱት እና ኚወደዳቜሁት እንድታጋሩት እጋብዛለሁ" ብላለቜ።

በዚህ ዹሙዚቃ ላይ ጎላ ጎህ  በግጥም  ዚተሳትፈ ሲሆን በዜማ፣ ቅንብር፣ ቀሹፃ እና ድምፅ ውህደት ኢዩኀል መንግስቱ ተሳትፏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

አርዕስት መሚጃዎቜ:

1.ተወዳጁ "ባቢሎን በሳሎን " ተውኔት ወደ መድሚክ ሊመለስ ነው።

2.ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ 13 ቀናት በእስር ቀት እንዲቆም ተወሰነበት።

3.ኹ30 ዓመታት በላይ እንደወሰደ ዚተነገሚለት ዹአንጋፋው ዹፊልም ባለሙያ ፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ ዘጋቢ ፊልም ተሰርቶ ተጠናቀቀ።

4.አስር ሁለቱ እንግዶቜ" ዹተሰኘ ተውኔት ዚፊታቜን እሁድ ለመድሚክ ይበቃል።

5."ስሜ ደበላ ታላቁ ዚግብርና ምርምር ሥርዓት መሪ" ዹተሰኘ መጜሐፍ ነገ ይመሚቃል።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/FL6kxm4BGNw?si=mErTv7NAFWzE0nY1

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ብስክሌት አዲስ" ዹተሰኘ ፌስቲቫል ነገ ይካሄዳል

ነፍ ኮምኒኬሜን እና ኀቚንት ኚአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እና ኚሚመለኚታ቞ው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኹተማ ኚወራት በፊት ዹጀመሹውና ዓመቱን ሙሉ ዚወሩ ዚመጚሚሻ እሁድ ዚሚካሄደው "ብስክሌት በአዲስ" ወርሀዊ ፌስቲቫል 3ኛው ዙር ነገ እሁድ መጋቢት 07 ኚጠዋቱ 1:30 ጀምሮ እስኚ 7:00 ድሚስ ኹ4ኪሎ ቀበና ባለው ጎዳና ይካሄዳል።

ዚፌስቲቫሉ ዋና ዓላማ ዚብስክሌት ልምድን መፍጠር በመሆኑ ኚውድድር ፍፁም ነፃና ኚህፃናት እስኚ አዛውንት ድሚስ ተሳታፊ ዚሚያደርግ ነው ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ባቢሎን በሳሎን"ተውኔት ወደ መድሚክ ይመለሳል

በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ሐና ዹተዘጋጀውና በበርካቶቜ ዘንድ ተወዳጅ ዹሆነው "ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ኚሁለት ዓመት በኃላ ለአጭር ጊዜ ወደ መድሚክ ሊመለስ እንደሆነ አርትስ ስፔሻል ኚደራሲው ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

"ባቢሎን በሳሎን" ተውኔትን በአውሮፓ ለሁለተኛ ጊዜ ለማሳዚት እንቅስቃሎዎቜ እንደተጀመሩ ዹተገለፀ ሲሆን ተውኔቱ ወደ አውሮፓ ኹመጓዙ በፊት ለአጭር ጊዜ በዓለም ሲኒማ እንዲታይ ኚሲኒማ ቀቱ አስተዳደር ጋር ንግግር እንደተጀመሚ እና በቅርቡ በድጋሚ ለመድሚክ እንደሚበቃ ውድነህ ክፍሌ ለአርትስ ስፔሻል ተናግሯል።

ተውኔቱ ወደ መድሚክ መቌ ይመለሳል ዹሚለው ጥያቄ ዚበርካታ ቎አትር አፍቃሪን ጥያቄ እንደሆነ ዹገለፀው ደራሲው "ባቢሎን በሳሎን" ወደ መድሚክ እንዲመለስ "ዹዓለም ሲኒማ ኃላፊዎቜም ያሻነውን ቀን እንደሚሰጡን ቃል ገብተውልናል" ብሏል።

"ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ወደ መድሚክ ሲመለስ አርቲስት አለማዹሁ ታደሰን ጚምሮ ሁሉም ተዋናዮቜ እንደሚኖሩም ተገልጿል።

ለ22 ዓመታት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር መድሚክ ላይ ሲቀሚብ ዹቆዹው "ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ኚሁለት ዓመት በፊት ኚመድሚክ መሰናቱ ይታወሳል።

📌 ArtsSpecial

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በኩናማ ሙዚቃው ዚሚታወቀው ኪዳኔ ኃይሌ አሹፈ

"ኊማኒንዳ ጉዳ"በተሰኘው ዚኩናማ ሙዚቃው በበርካቶቜ ዘንድ ዚሚታወቀው ድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ኹዚህ ዓለም በሞት እንደተለዚ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ዚኩናማ ሙዚቃ ኀልያስ መልካ ካቀናበራ቞ዉ አልበሞቜ "ብፍቅሪ ሾፊተ" አልበም ውስጥ ዹሚገኝ ሙዚቃ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
ዚድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ዚቀብር ሥነሥርዓት ተፈጾመ

ኪዳኔ ሃይሌ ፀባዚ ሾጋ ቀልድና ጚዋታ አዋቂ፣ በኩናማ ዜማና ግጥም ድርሰት ኚፊት ዚሚቀመጥ፣በተጚማሪም ድምፃዊና ሳክስፎኒስት ነበር።

ቀተሰቊቹን ጥዚቃ ሞራሮ በሄደበት በአደሚበት ሕመም በሕክምና ሲሚዳ ቆይቶ መጋቢት 06 ቀን 2017 ዓ.ም. ሕይወቱ አልፏል።

ኀልያስ መልካ በቅንብር ዚተሞለመበትን ዚኩናምኛ ዘፈን ድርሰትን ግጥሙን ዚፃፈው፣ ዜማውን ዹደሹሰውና በድምፅ ያቀነቀነው ኪዳኔ ነበር።

ድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ - "ኊማኒንዳ ጉዳ" በተሰኘው ዚኩናማ ሙዚቃው በበርካቶቜ ዘንድ ይታወቃል።

ዚድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ዚኩናማ ሙዚቃ ኀልያስ መልካ ካቀናበራ቞ዉ አልበሞቜ "ብፍቅሪ ሾፊተ" አልበም ውስጥ ዹሚገኝ ሙዚቃ ነው።

በ1956 ዓ.ም ዹተወለደው ኪዳኔ ኃይሌ ባለትዳር እና ዚአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበር።

ሥርዓተ ቀብሩ ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 2:00 ሰዓት ላይ በመድኃኔዓለም ቀተክርስቲያን ተፈጜሟል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
አንጋፋው አርቲስት መርዓዊ ስጊት አሹፈ

አንጋፋው ዚኪነ-ጥበብ ሰው መርዓዊ ሥጊት ኹዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

ክላርኔት በመጫወት ዚሚታወቀው አርቲስት መርዓዊፀ ኚሙዚቀኛነቱ ባለፈ በትወና መድሚክ ተወዳጅነትን ማትሚፍ ቜሏል፡፡

አርቲስት መርዓዊ ስጊት በኢትዮጵያ ዘመናዊ ዹሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ግንባር ቀደም ቊታ ኹሚይዙ አንጋፋ ሙዚቀኞቜ መካኚል አንዱ መሆኑ ይነገርለታል፡፡

ኹ55 ዓመታት በላይ በቆዚበት ዹሙዚቃ ሕይዎቱፀ በድምጻዊነት፣ በክላርኔትና አልቶ ሳክስ ዹሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋቜነት፣ በሙዚቃ ግጥምና ዜማ ደራሲነት እንዲሁም በአቀናባሪነት እና ሌሎቜ ተዘርፎቜ ማገልገሉ ይታወሳል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለአጭር ጊዜ ድርጅትዎን በነፃ ያስተዋውቁ!

ዚእርስዎን ፍላጎት በአንድ ላይ ዚሚያገናኝ መድሚክ!

በርካታ ዘርፎቜ እና ዚአገልግሎት ሰጪዎቜን ለማግኘት ቀላል መድሚክ፣ኪራዮቜ፣ህጋዊ አገልግሎቶቜ፣ዚውበት አገልግሎቶቜ፣ጉዞ፣ ኀሌክትሮኒክስ እና ሌሎቜም 🙏

Download now!
App store:
https://apps.apple.com/us/app/meda-app/id6657988238

Google Play:
https://play.google.com/store/apps/details?id=come.meda.app

Instagram:
https://www.instagram.com/medamobileapp?igsh=MzRlODBiNWFlZA==
Telegram:
https://t.me/medamobileapp
📌"ኑ ታላቅ እናክብር" ዹተሰኘ ዝግጅት ነገ ይካሄዳል

አንጋፋው ዚሥነጜሑፍ ባለሞያ አስፋው ዳምጀ ዚሚመሰገንበት "ኑ ታላቅ እናክብር" ዹተሰኘ ዝግጅት ነገ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 7:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ይካሄዳል።

በዝግጅቱ ላይ አንጋፋ ደራሲያን፣ ሠዓሊያን፣ዚጥበብ ሰዎቜ ይገኙበታል ተብሏል።

ዚደራሲ አስፋው ዳምጀን 90ኛ ዓመት ዚልደት በዓል ለማክበር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር በተሰናዳው በዚህ ዝግጅት ላይ ልዩና በውድ ዋጋ ዚታተመ መጜሔት ለጥቂት ሰዎቜ ብቻ እንደሚታደልም ተነግሯል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ገመሃልያ" ፊልም ዚፊታቜን ሰኞ ይመሹቃል

በኪማ ፊልምስ ተሰርቶ á‰ á€áŒ‹ መልቲ ሚዲያ ዹቀሹበው "ገመሃልያ" ፊልም ዚፊታቜን ሰኞ መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም ቩሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ በልዩ ዝግጅት ይመሚቃል።

ዹፊልሙ ዳይሬክተር ዳይሬክተር ሳሙኀል (ባዩሜ ልጅ) ሲሆን በድርሰት ኀፍሬም ሀጎስ ተሳትፏል፣ 1 ሰዓት ኹ50 ደቂቃ ርዝመት ያለው ፊልሙ በፀጋ መልቲ ሚዲያ ፕሮዲውስ ተደርጓል።

በትወና ሰለሞን ቊጋለ፣ አዜብ ወንድሰን፣ ድምፃዊያን ቃልኪዳን ዳንኀል እና ሌሎቜም ተሳትፈውበታል።

ፊልሙ ለቀሹፃ አንድ ዓመት ኚስድስት ወር ዹወሰደ ሲሆን ኹ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ወጥቶበታል።

ዚፊታቜን ሰኞ መጋቢት 15 ኚምሜቱ 11:30 ጀምሮ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜና ታዋቂ ዚኪነጥበብ ባለሞያዎቜ በተገኙበት በዓለም ሲኒማ ዹሚመርቅ ሲሆን áˆ˜áŒ‹á‰¢á‰µ 19,20,21 እና መጋቢት 26,27,28 በሁሉም ሲኒማ ቀቶቜ ይመሹቃል እንዲሁም በተመሳሳይ ሠዓት በአሜሪካን ሀገር ይመሚቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

አርዕስት መሚጃዎቜ:

1.ዚሎሬት ፀጋዬ ገብሚመድህን "እሳት ወይ አበባ" ዚግጥም መጜሐፍ ኚዓመታት በኃላ በድጋሚ ታትሞ ለንባብ ሊበቃ ነው።

2.ዶ/ር አለማዹሁ ዋሮ ለዚት ባለ አጻጻፍ ዚመጡበት አዲስ መጜሐፋ቞ው ለንባብ በቃ።

3.መቌቱን በአንድ ዚፋሲካ ዋዜማ ምሜት ላይ ያደሚገው ፊልም ለእይታ በቃ።

4.ተኚታታይ ዚ቎ሌቪዥን ድራማዎቜ ላይ ትኩሚቱን ያደሚገ ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል።

5.ነገሹ መጻሕፍት ዚመጜሐፍ ውይይት ነገ ይካሄዳል።

6."ገመሃልያ" ፊልም ዚፊታቜን ሰኞ ለእይታ ይበቃል።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/OwAYLBrkeYU?si=W1TtMma0IAB7PqO5

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌አል ዐይን አማርኛ ሥራ ሊያቆም ነው

ባለቀትነቱ ዚተባበሩት ዓሚብ ኀምሬቶቜ መንግሥት ዚኟነው አል ዐይን አማርኛ ዹበይነ መሚብ ዹዜና ማሠራጫ ሥራ ሊያቆም ነው ፡፡

ዹዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎቜንና ዘገባዎቜን ዚሚያዘጋጁ ዚኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን ዚቅጥር ውል አቋርጧል ፡፡

ተቋሙ ዚሠራተኞቹን ውል ያቋሚጠው፣ ዹአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ ዚኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መኟኑን ዋዜማ ዘግባለቜ ፡፡

ዘጋቢዎቹ ሥራ቞ውን እዚሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳ቞ው፣ በድንገት ዚሥራ ውላቾው መቋሚጡን ዚሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደሚሳ቞ው ዋዜማ ሰምታለቜ፡፡

ኚአምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ዹዜና አገልግሎት ዹጀመሹው አል ዐይን አማርኛ ኚትናት በስትያ ጀምሮ ዜናዎቜን አላሠራጚም፡፡ ዹዜና ድሚሚገጹ በዋናነት ትኩሚቱን በመካኚለኛው ምሥራቅ ላይ አድርጎ ዹአገር ውስጥና ዓለማቀፍ ዜናዎቜን በአማርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያዊን አንባቢዎቜ ሲያቀርብ ነበር፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ዚደራው" መጜሔት ለንባብ በቃ

"ዚደራው" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዲጂታል መጜሔት ዚመጀመሪያው እትም ለንባብ በቅቷል።

ዲጂታል መጜሔቱ በዚህኛው እትም ልዩ ልዩ ጉዳዮቜን ይዞ ይዟል።

ኚእዚህም መካኚል ቬሮኒካ አዳነ ኚዚት ወዎት፣ቢመሜም በር መዝጋት አይቻልም፣ሪቫን ልንቆርጥ ይሆን?፣መስሪያ ቀት እስር ቀት አይደለም፣Big Habesha ዹጠቆመን መኪና እና ሌሎቜም በርካታ ጉዳዮቜን ዚያዘ ሲሆን በነፃ ይኮምኩሙ ተብላቜኋል።

መጜሔቱን ለንባብ ሊንክ:https://t.me/yederaw
📌ድምጻዊት ፀደኒያ ገ/ማርቆስ በፕሪስ቎ጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ትቀርባለቜ

(መግቢያው በነፃ ነው)

ዚተለያዩ ዚጥበብ ባለሞያዎቜን እዚጋበዝ ልምዶቻ቞ውን እንዲያጋሩ እያደሚገ ያለው ፕሪስ቎ጅ አዲስ መርሐግብር ፀደኒያ ገ/ማርቆስን ጋብዟል::

ዚፕሪስ቎ጅ አዲስ አዘጋጆቜ "ኚፀዲ ጋራ በሚኖሹን ቆይታ ዚሥራ፣ ዚህይወት ልምድ እና ተሞክሮዋን ዚምታካፍለን áˆ²áˆ†áŠ• ኚእናንተ ኚወዳጅ እና አድናቂዎቿ ዚሚቀርቡላትን ጥያቄዎቜ  ማክሰኞ መጋቢት 16 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኀቚንት አዲስ ሚዲያ ገለጞዋል።

በዕለቱ ኚአርቲስቷ ጋር ዚፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ ዚማስፈሚም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::

ፕሪስ቎ጅ አዲስ ኚፀደኒያ ገብሚማርቆስ  ጋር  ዚሚያደሚገው አዝናኝ áŠ¥áŠ“ አስተማሪ ቆይታ  ማክሰኞ መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ኚስድስት ኪሎ ወደ ሜሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ኚታቜ ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
https://jazzio.land/register

መታወቂያ መያዝ እንዳይሚሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ኚመጀመሩ ቀደም ብላቜሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላቜኋል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1