Event Addis Media
9.63K subscribers
6.1K photos
13 videos
4 files
4.72K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌ዚበገና ዜማ ዹህክምና አገልግሎት ላይ እዚዋለ ነው

ዹበገና ዜማ በኢትዮጵያ ለህክምና አገልግሎት  እዚዋለ መሆኑን ዚፈሚንሳይ ዜና አገልግሎት ዹሆነው ኀኀፍፒ ዘግቧል፡፡

ይህንን ጉዳይ በተመለኹተ ዹዜና አውታሩ  ባቀሚበው ዘገባ በአዲስ አበባ በሚገኘው ግሬስ ነርሲንግ ሆም ዹበገና ህክምና እዚተሰጠ እንደሚገኝ አስሚድቷል፡፡

ዹ60 አመቱ አቶ ሰለሞን ዳንኀል በዊልቾር ዚሚንቀሳቀሱ ሲሆን በዚህ ህሙማን ማቆያ ሁለት አመታትን አሳልፈዋል፡፡

ዹበገናን ዜማ ድምፅ ሲሰሙ ጭንቅላታ቞ውን እዚወዘወዙ መመሰጣ቞ውን መመልኚቱን ዘገባው አስሚድቷል፡፡

ዹበገና ድምፅ ሲሰሙ ሰላም እንደሚሰማ቞ው ዚተናገሩት አቶ ሰለሞን ጹምሹውም ‹‹እግዚአብሄርን ስትፈልጉት በተለያዚ መንገድ ታገኙታላቜሁ፡፡ እኔ በገና ስመለኚት እግዚአብሄር ዚሚያናግሚኝ መስሎ ይሰማኛል›› ብለዋል፡፡

ኚግሬስ ነርሲንግ ሆም መስራ቟ቜ አንዱ ዚሆኑት ዶክተር ናትናኀል ሀይሉ ህሙማኑ በገናን ሲሰሙ በሚያሳዩት ስሜት መገሹማቾውን ገልፀዋል፡፡

ህሙማኑ በበገናው ድምፅ በሜታ቞ውን እንደሚሚሱትና እንቅልፍ ውስጥ እንደሚገቡ ዚጠቆሙት ዶክተር ናትናኀል ጹምሹውም ‹‹ህሙማኑ በገና ሲሰሙ ዹደም ግፊታ቞ው ይቀንሳል፣ ዚልብ ምታ቞ው ይሚጋጋል፡፡ ኚሌሎቜ ሙዚቃ መሳሪያዎቜ በተለዹ በገና ትክክለኛ ዚመሚጋጋት ስሜትን ይፈጥራል‹‹ ብለዋል፡፡

በሀርቫርድ ዩኒቚርስቲ ዚልብ ሀኪምና መምህር ዚሆኑት ዶክተር ቡክማን በዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት ለማድሚግ ሰሞኑን በዚህ ህሙማን ማቆያ መገኘታ቞ውን ዹዜና አውታሩ አስሚድቷል፡፡

እሳ቞ውም ሁኔታውን ኚተመለኚቱ በኋላ ዹበገና ዜማ በተለይ በፅኑ ህመም ውስጥ ለሚገኙ ሰዎቜ መልካም ተፅእኖ ዹመፍጠር ሀይል እንዳለው መናገራ቞ውን ገልጿል፡፡

📌መሚጀው ዚዘሐበሻ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚኢትዮ-ደቡብ ሱዳን ዚሥነጥበብ ትርዒት ተጀመሹ

69ኛው ዚኢትዮ-ደቡብ ሱዳን ሾማ ዚሥዕል አውደርዕይ ፣ዚፋሜን ትርኢት እና ዹዕውቅና መርሐግብር ኚዚካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሳፋዚር አዲስ ሆቮል እዚተካሄደ ይገኛል።

ዓለም አቀፍ ዚሎቶቜ ቀንን ምክንያት በማድሚግ "ጥበብ ለሎቶቜ" በተሰኘ መሪ ቃል እዚተካሄደ ዹሚገኘው መርሐግብር በሠዓሊ ራስ በሚኚት ዚተሳሉ፣ ዚኢትዮ-ደቡብ ሱዳን ዚባህል ግንኙነቶቜን ዚሚያሳዩ እንዲሁም ሎቶቜ ላይ ትኩሚት ያደሚጉ 40 ዚሥዕል ስራዎቜ ቀርበዋል።

ዚሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት ለማጠናኹር እና ዚባህል ቁርኝነትን ለማሳደግ መሰል ዚኪነጥበብ መርሐግብሮቜ በተኚታታይ መኹናወቾው ፋይዳው ዹጎላ መሆኑን አዘጋጁ ራስ በሚኚት አንዳርጌ ገልጿል።

በአውደርዕዩ ዚተለያዩ ዚአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮቜ፣ዚኪነጥበብ ባለሙያዎቜ፣ አርበኞቜ፣ ጥሪ ዹተደሹገላቾው ዚክብር እንግዶቜ ተገኝተዋል።

ዚሎቶቜን ህይወት ለመለወጥ እና በአርአያነት ዚሚጠቀሱ ኢትዮጵያውያን እና ደቡብ ሱዳናዊያን እንስቶቜ እውቅና ተኚርክቶላ቞ዋል።

ኀግዚቢሜኑ ኚዛሬ ጀምሮ እስኚ መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በሳፋዚር አዲስ ሆቮል ለጎብኚዎቜ ኚፍት እንደሚሆን ተገለጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ቢክ እስኪብርቶ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊመሚት ነው

አልሳም ኃላ/ዹተ/ዹግል ቢክ እስኪብሮቶን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማምሚት ኚኢስት አፍሪካ ሊሚትድ ጋር ዛሬ ዚካቲት 29 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቮል ዚአጋርነት ስምምነት ተፈራርሟል።

አልሳም ኚማምሚቱ በተጚማሪ ዚምርቱ ስርጭትም ለምስራቅ አፍሪካ አገሮቜ ኢትዮጵያን ጚምሮ ለጅቡቲ፣ ለሶማሊያና ለኀርትራ ዚሚያኚፋፍል ይሆናል።

ዚቢክ እስክብርቶ በኢትዮጵያ መመሚት በአኚባቢው ካለው ዚገበያ ስፋት አንፃር ለአገራቜን ዹቮክኖሎጂ ሜግግር ይፈጥራል፣ ዹውጭ ምንዛሬ ያስገኛል፣ ለዜጎቜ ዚሥራ እድል ይፈጥራል ተብሏል።

በቀጣይ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ፕሮጀክቱን ተግባራዊ እንደሚሆን ነው ዚተገለጞው።

አልሳም ኃላ/ዹተ/ዹግል ማህበር ኹተመሰሹተ 25 ዓመታት ያለፉት ሲሆን በአስመጪነት፣ በላኪነት፣ በአገር  ውስጥ ንግድ፣ በሪል ስ቎ትና በማኑፋክ቞ሪንግ ዚሥራ ዘርፎቜ ተሰማርቶ ይገኛል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ኮንሰርት

ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ(አርዲ) በሀገሹ እስራኀል ዚመጀመሪያ ዹሙዚቃ ኮንሰርቱን በቅርቡ እንደሚያካሂድ ይፋ አድርጓል።

አስቻለው ፈጠነ (አርዲ) ኹዚህ ቀደም "እናትዋ ጎንደር" እና "ካሲናው ጎጃም" በተሰኙ ሙዚቃዎቜ ኹፍተኛ ተደማጭነትን አግኝቷል።

በተጚማሪም ባሳለፍነው ዓመት ጥር ወር በለቀቀው "አስቻለ" ዹሙዚቃ አልበም ተወዳጅነትን አትርፏል።

ድምጻዊው ኹ2 ወራት በፊት ያወጣው "አሞራው ካሞራው" ዹተሰኘውና በጀግናው አሞራው ውብነህ ታሪክ ላይ ተመስርቶ ዚሠራው ነጠላ ዜማው በዩቲዩብ ኹ7 ሚሊዮን በላይ ተመልካቜ እንዳስገኘለት ይታወሳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌 ሠዓሊና ገጣሚ ገብሚክርስቶስ ደስታ ተዘኹሹ

ሠዓሊና ገጣሚ ገብሚክርስቶስ ደስታ ዚተዘኚሚበት" ዚካቲት ወርሐ ገብሚክርስቶስ "ዹተሰኘ ልዩ መርሐግብር ቅዳሜ ዚካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በስሙ በተሰዹመው ገብሚክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ ዚሥነጥበብ ሙዚዹም ውስጥ እንደተካሄደ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

በዕለቱም ዚገብሚክርስቶስ ግጥሞቜና ስለእሱ ዹተገጠሙ ግጥሞቜ ተነበዋል።በተጚማሪም ገብሚክርስቶስን በሕይወቱ ዚመጚሚሻዎቹ ቀናት ያገኙ ሰው በቪዲዮ ምስክርነት ሰጥተዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌መቅሚዝ ሥነኪን ሐሙስ ይካሄዳል

መቅሹዝ ሥነኪን ወርሀዊ ዚኪነጥበብ á‹áŒáŒ…ት ዚፊታቜን ሐሙስ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 11:00 ጀምሮ á‰ á‰¥áˆ”ራዊ ቀተመዛግብትና ቀተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር )አዳራሜ ውስጥ ይካሄዳል።

በዚህ ዝግጅት ላይ አንጋፋው ዚተውኔት አዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሣ ዚክብር እንግዳ በመሆን ዹሚገኝ ሲሆን በተጚማሪም ወጣት ዚኪነጥበብ ባለሞያዎቜ ዚግጥም ፣ዚሙዚቃ ስራዎቻ቞ውን ያቀርባሉ።ዚዚህ ዝግጅት መግቢያ በነፃ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ተዋናይነት ፀደይ ፋንታሁን በአዘጋጅነት ብቅ ያለበቜበት "ጥቁር እንግዳ" ተውኔት ለመድሚክ በቃ

በደራሲ ውድነህ ክፍሌ ዹተደሹሰው "ጥቁር እንግዳ" ተውኔት ሐሙስ ዚካቲት 27 2017 ዓ.ም ቩሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ለመድሚክ በቅቷል።

በተውኔት ላይ ሱራፌል ተካ፣ደምሎ በዚነ፣ፀደይ ፋንታሁና ማርታ ግርማ በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

ዹ"ጥቁር እንግድ" ተውኔት ዋና አዘጋጅ ዶ/ር ተሻለ አሰፋ ሲሆን ተዋናይነት ፀደይ ፋንታሁን በሹ/አዘጋጅነት ዚመጣቜበት ተውኔት ሆኗል።

ተውኔቱ በቋሚነት ዘወትር ሐሙስ በ12:00 በዓለም ሲኒማ ለ቎አትር አፍቃሪያን እንደሚቀርብ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚፍቅር እስኚ መቃብር ገፀባህርያት በሥዕል ዚሚገልጡበት አውደርዕይ ዛሬ እይታ ይበቃል።

በሠዓሊ ምዕራፍ ግሩም ዹተዘጋጀውና ዹፍቅር እስኚ መቃብር መጜሐፍ ገፀባህርያት á‰ áˆ¥á‹•ል ዚሚገለጡበት "ዚደራሲው ሥዕል" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው አውደርዕይ ዛሬ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ሐያት ሪጀንሲ ውስጥ በሚገኘው ፈንድቃ ዚባህል ማዕኹል ውስጥ ለእይታ እንደሚበቃ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ይህ ዚሥዕል አወድርዕይ እስኚ መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድሚስ ይቆያል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ጎዶን ጥበቃ" ተውኔት ዛሬ በክብር ይሰናበታል

በሳሙኀል ቀኬት ተደርሶ በሀይኹል ሙባሚክ ዹተተሹጎመውና በዳግም ሲሳይ ዹተዘጋጀው "ጎዶን ጥበቃ" ዹተሰኘ ተውኔት ዛሬ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም በክብር ኚመድሚክ እንደሚሰናበት ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

"ጎዶን ጥበቃ"ተውኔት ኹነሐሮ 2 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተኚታታይ 8 ወራት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ለ቎አትር አፍቃሪያን ሲቀርብ ቆይቷል።

በተውኔቱ ላይ አልዓዛር አበበ፣ ግሩም አስፋው ፣ዘላለም አለማዚሁ፣ሙሉብርሃን በለጠ፣ናሆም ቢኒያም በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአንዱዓለም ጎሳ ባለቀት ህልፈት

ዚድምፃዊ አንዷለም ጎሳ ባለቀት ቀነኒ አዱኛ በድንገት ሕይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ዹቀነኒን አሟሟት በተመለኹተ ፖሊስ ምርመራ ላይ እንዳለ አሳውቋል ።

ቀነኒ አዱኛ ፀ ኚመሞቷ ኹ12 ሰዓታት በፊት በቲክቶክ ዚማኀበራዊ ዹመገናኛ ድሚገጜ ላይ ደስተኛ ሆና በመጹፈር ቪዲዮ ለቃ ነበር ።

ለድምፃዊ አንዷለም ጎሳ፣ ለቀተሰቊቿ እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቜ ፈጣሪ መፅናናቱን ይስጥልን ።

Via ይድነቃ቞ው ኹበደ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ታዋቂው ሙዚቀኛ አቶ አለማዹሁ ፋንታ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

በባህላዊ ዹሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋጭነታ቞ው ዚሚታወቁት ሙዚቀኛው አለማዹሁ ፋንታ ስራ቞ውን ዚጀመሩት ሃገር ፍቅር ቲያትር ቀት በመቀጠር ነውፀ እዚያም ለ10 ዓመታት ሰርተዋል፡፡

ለ40 ዓመታት ያህል በ ያሬድ ዹሙዚቃ ትምህርት ቀት በመምህርነት ሲያገለግሉ ዚቆዩት ሙዚቀኛውፀ በዕድሜአ቞ው መጚሚሻ ጡሚታ ኚውጡ በኋላ በዚሁ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቀት ማገልገላቾውን ዹሙዚቀኛው ዚቅርብ ሰው ሆኑት ታዋቂው ዹበገና መምህር መጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ነግሚውናል፡፡

ባህላዊዎቹን ዚኢትዮጵያ ዹሙዚቃ መሳሪያዎቜ በገናን በመደርደር፣ ክራርና መሰንቆን  አሳምሚው በመጫወት ይታወቁ እንደነበር ኚመጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ሰምተናል፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማዹሁ ፋንታ ዹቀለም ትምህርትን ዚተማሩ እንዲሁም ዚድቁና ትምህርትም ዚነበራ቞ው ነበሩ፡፡

ሙዚቀኛው ኹ6 ወራት በፊት በድንገት ወድቀው እግራ቞ው በመሰበሩ በህክምና ሲሚዱ ቆይተው በትናንትናው እለት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ኹዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራ቞ው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ኹቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈፀምም ሰምተናል፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማዹሁ ፋንታ ባለ ትዳርና 6 ልጆቜ አባት ነበሩ፡፡

📌Via ሾገር 102.1

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
Event Addis Media
Photo
📌ኚድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ጋር በተያያዘ እስካሁን ያሉ መሚጃዎቜ

ዚድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ሞትን በተመለኹተ በርካታ መሚጃዎቜ እዚወጡ ይገኛሉ።

ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ዚት ነበሚቜ? ዚድምጻዊው ማናጀር ስለልጅቷ ተናግሯል።

በኢንጂነሪንግ ድግሪ ኚአርባምንጭ ዩኒቚርሲቲ ዚተመሚቀቜው ቀነኒ በሞዮሊንግ በማስታወቂያ ሥራዎቜ በማኅበራዊ ሚድያ ዝናን አትርፋለቜ።

በሚቀጥለው ቅዳሜ ልደቷን ለማክበር በሚል ፎቶዎቜ እዚተነሳቜ እንደነበር ኚቅርብ ሰዎቿ ዹተገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ልጅቱ ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ዚት ነበሚቜ?

ልጅቱ ኚመሞቷ አንድ ቀን በፊት ለልደቷ ፎቶ ስትነሳ እንደነበር በወቅቱ ፎቶ ያነሳት ዹነበሹው ዚወንዎክስ ስቱዲዮ ባለቀት ወንድወሰን ጋሻው ተናግሯል ።

ፎቶግራፈሩም "በፎቶግራፍ  ስራዎቜ ካፈራዋ቞ው ወዳጆቌ መካኚል ዹቀኝ እጄ ዚምላት እህ቎ ቀነኒ አዱኛ መካሪዬ ጎደኛዬ ዹክፉ ቀን ወዳጄ ነበሚቜ።

ትላንት መጋቢት 1 2017 á‹“.ም ኹቀኑ 10:00 ጀምሮ  ዚልደት ፎቶዎቜ ሳነሳት ነበር ማታ 1:00 በሰላም ተለያዚትን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 2 2017 ዓ.ም ጠዋት ማሹፏን አሚዱኝ" ብሏል።

በተጚማሪም ትላንትና መጋቢት 1 2017 ዓ.ም አመሻሹን ቀነኒ አዱኛ ኚእጮኛዋ ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ ጋር  በመዝናኛ ስፍራ አብሚው እንዳሳለፉም ኚተለያዩ ምንጮቜ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ማናጀር ዹሆነው ለሊሣ እንድሪስ ዹተፈጠሹውን ለቢቢሲ አፋን ኊሮሞ ተናግሯል።

"ንጋት 11:00 ሰዓት ስልክ ተደውሎ «ቀነኒ ተጎድታ ሆስፒታል ገብታለቜ ቶሎ ድሚስ» እንደተባለ ዹሚናገሹው ለሊሳ እሱ ሩቅ በመሆኑ በሰዓቱ መድሚስ እንዳልቻለ ይናገራል።

ቩሌ አራብሳ ኚዓመት በላይ በጋራ ኚሚኖሩበት መኖሪያ ቀታ቞ው ኚአምስተኛ ፎቅ እንደወደቀቜ እና ምን እንደተፈጠሚ ፖሊስ እያጣራ መሆኑ ተነግሯል።

ክስተቱ ኹተፈጠሹ በኋላ በቅርብ በሚገኘው ያኔት ሆስፒታል ኚገባቜ በኋላ ጠዋት ፖሊስ መጥቶ ሬሳዋን ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለምርመራ ኹወሰደ በኋላ ዚምርመራ ውጀት እስኪወጣ አስክሬኗ ወደ ቀተሰቊቿ ሱሉልታ መሄዱ ነው ዚተገለፀው።

ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ኚሆስፒታል ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ እዛ ዹሚገኝ ሲሆን እኛ ዹምናውቀው እስካሁን አለመታሰሩን ነው ምርመራ እናድርግ ብሎ ነው ፖሊስ ዹወሰደው ሲል ማናጀሩ ይናገራል።

ለሁለት አመታት በፍቅር ኚቆዩ በኋላ በቅርቡ ጋብቻ቞ውን ለመፈፀም እዚተዘጋጁ እንደሆነ አውቃለሁ ሲል ለሊሳ ይናገራል።

ፖሊስ ምን አለ?

ዚልጅቱ አሟሟት ምን እንደሆነ ዚምርመራ ስራ ተሰርቶ እስኪገለጥ ድሚስ ህብሚተሰቡ በትዕግሥት ይጠብቅ በሌላ በኩል አንዳንድ ግለሰቊቜ ተገቢ ካልሆነ ትንታኔ ይታቀቡ ብሏል።

📞ፎቶው ትላንት ለልደቷ ዚተነሳቜው ፎቶ ነበር።

@EventAddis1
📌ሆ቎ሎቜን ዚጎዳው ዚአሜሪካ እርዳታ መቋሚጥ

በኢትዮጵያ ዚአሜሪካ ድጋፍ በመቋሚጡ በሆ቎ሎቜ ዹሚደሹጉ ስብሰባዎቜና ሥልጠናዎቜ መቀነሳ቞ው ተገለጞ።

ዚአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኊ ድርጅት (ዩኀስኀአይዲ) በተለያዩ መንገዶቜ ለአገሮቜ ሲያደርገው ዹነበሹውን ድጋፍ በማቋሚጡ ምክንያት በአዲስ አበባ ኹተማ በሚገኙ ሆ቎ሎቜ ይካሄዱ ዚነበሩ ሥልጠናዎቜ፣ ስብሰባዎቜና አጫጭር ዓውደ ጥናቶቜ መቀነሳ቞ውን ዹሆቮል ዘርፍ ተዋናዮቜ ተናገሩ፡፡

እ.ኀ.አ. በ2024 ብቻ ወደ 38 ቢሊዮን ዶላር በጀት በመላው ዓለም ወጪ ማድሚጉ ዚሚነገርለት ዩኀስኀአይዲ ለኢትዮጵያ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ያደሚገ ግዙፍ ዚተራድኊ ድርጅት መሆኑ ይነገርለታል፡፡

በኹተማው ውስጥ ኹሚገኙ ሆ቎ሎቜ ይህ ድጋፍ በመቋሚጡ ዹገጠማቾውን ቜግር በተመለኹለተ ሪፖርተር ያነጋገራ቞ውና ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዹፈለጉ አንድ ዚማርኬቲንግ ባለሙያ፣ እ.ኀ.አ. በመጋቢትና በሚያዝያ 2025 ብቻ ለሆቮላቾው ይገባ ዹነበሹ 25,000 ዶላር በፕሮግራሙ መታጠፍ ምክንያት መሰሹዙን ተናግሚዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ዹማይገኘውን ገንዘብ ለማካካስ ኹዚህ ቀደም ኹነበሹው ዹሆቮሉ ዋጋ ባነሰ ገንዘብ ዚሚመጡ ፕሮግራሞቜንና እንግዶቜን ዚመቀበል፣ እንዲሁም በማርኬቲንግ ባለሙያዎቜ አማካይነት ወደ ድርጅቶቜና ተቋማት በመሄድ ዚማካካሻ እንግዳና ዚመሳብ ሥራ እዚተኚናወነ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በካዛንቺስ አካባቢ ዹሚገኝ አንድ ዹሆቮል አዳራሜ ባለሙያ ለሪፖርተር በሰጡት አስተያዚት፣ ዹሆቮሉ አዳራሜ በሳምንት ሊስ቎ አንዳንዎም ለአምስት ቀናት በሙሉ ተይዘው ዚነበሚበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን ግን ዹሚደሹጉ ስብሰባዎቜ ቁጥር መቀነሱን ገልጞዋል፡፡

Via ሪፓርተር ጋዜጣ (ሲሳይ ሳህሉ)

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌 ‘ናኊታ’ ዚልጆቜ መጜሔት ለንባብ በቃቜ

ዚኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአፋን ኊሮሞ ያዘጋጃት ‘ናኊታ’ ዚልጆቜ መጜሔት ለንባብ በቅታለቜ።

‘ናኊታ’ ዚተሰኘቜዉ ዚልጆቜ መጜሄት ባለ 40 ገጜ እና ባለ ሙሉ ቀለም ህትመት ያላት ወራዊ መጜሄት ስትሆንፀ ኚዚካቲት ወር ጀምሮ በገበያ ላይ ትገኛለቜ፡፡

መጜሔቷ ትዉልዱን በመልካም ስነ ምግባር እና እውቀት ማነጜን ታሳቢ ያደሚገቜ ናት።
በዋናነት በሳይንስ እና ቎ክኖሎጂ፣ ባህልና ታሪክ፣ ተፈጥሮ፣ ማህበራዊ እና ሌሎቜ ጉዳዮቜ ዚተካተቱባት ነቜ።

በዚህም ልጆቜን እያዝናናቜ በስነ መግባር ዚምታንጜ፣ ዚንባብ ልምድን ዚምታዳብር እንዲሁም ልጆቜን ኚሳይንስና ጋር ዚምታስተዋዉቅ መጜሄት ተደርጋ ዚተዘጋጀቜ ሆናለቜ።

ኹ3  እስኚ እና 15 ዓመት ዹሚገኙ ልጆቜ ዚመጜሄቷ ዋና ታላሚ አንባቢያን ና቞ዉ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣርና እሑድ ይካሄዳል

ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድር እና ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት በመጪው እሁድ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አስታውቋል፡፡

‘ቁርዓን - ዚእውቀትና ዹሰላም ምንጭ’ በሚል መሪ ሃሳብ ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድሩ ዚማጣሪያ መድሚክ በአዲስ አበባ እዚተካሄደ ነው።

ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ም/ቀት ፕሬዚዳንት ጜ/ቀት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበኚር አሕመድ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ቁርዓን በሁሉም መስክ ዚሰዎቜን ሕይወት በቀና መንገድ በመምራት ለማህበሚሰብ ኚፍታ መሰሚት መሆን ዚቻለ ነው።

በዚህ አግባብ ውድድሩ ይህን ዹቁርዓን ክብርና ኚፍታ ለመግለጥ ዹተዘጋጀ መሆኑን ነው ዚተናገሩት።

ውድድሩ ቁርዓንን በልቩናቾው ዹተሾኹሙ ሃፊዝ ወጣቶቜን ለማበሚታታትና ቀጣይ ተተኪ ትውልዶቜን ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።

ዋናው ሀገር አቀፍ ዹቁርዓን ውድድር እሑድ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ አመልክተዋል፡፡

በዚሁ ቀን በርካታ አማኞቜ ዚሚታደሙበት ታላቁ ዚጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ ሥርዓት ‘ኚኢፍጣር እስኚ ቁርዓን’ በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚኚናወን ጠቁመውፀ ሕዝበ ሙስሊሙ በሁለቱ ታላላቅ መርሐ ግብሮቜ ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

© FMC

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚድምጻዊት ዹማ ዹሙዚቃ ቪዲዮ ተለቀቀ

ድምጻዊት ዚማርያም ቞ርነት(ዹማ) "ስንት ነው?" ለተሰኘው ዹሙዚቃ ሥራዋ ያስናዳቜው ዹሙዚቃ ቪዲዮ  ዛሬ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም በዩቲዩብ ቻናሏ በኩል ለአድማጮቜ ደርሷል።

ድምጻዊት ስለዚህ ዹሙዚቃ ቪዲዮ በማህበራዊ ትስስር ገጿ"ዹደጋ ሰው አልበም ኹተለቀቀ አንድ ዓመት ዹሆነው ሲሆን በዚህ መካኚል በነበሩኝ 70 ዹሚሆኑ ዓለም አቀፍ ዚመድሚክ ስራዎቜ እና ዝግጅቶቜ  ምክንያት ዚቪዲዮ ስራ ሳላቀርብ ቆይቻለሁ።

በቅርቡ በአዲስ አበባ በመድሚክ ዹምንገናኝ ሆኖ ኹዚህ አልበም ውስጥ “ስንት ነው? “ዹተሰኘውን ዹሙዚቃ ቪዲዮ በዹማ (YEMa) YouTube channel ስለተለቀቀ እንድትመለኚቱት እና ኚወደዳቜሁት እንድታጋሩት እጋብዛለሁ" ብላለቜ።

በዚህ ዹሙዚቃ ላይ ጎላ ጎህ  በግጥም  ዚተሳትፈ ሲሆን በዜማ፣ ቅንብር፣ ቀሹፃ እና ድምፅ ውህደት ኢዩኀል መንግስቱ ተሳትፏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ

አርዕስት መሚጃዎቜ:

1.ተወዳጁ "ባቢሎን በሳሎን " ተውኔት ወደ መድሚክ ሊመለስ ነው።

2.ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ 13 ቀናት በእስር ቀት እንዲቆም ተወሰነበት።

3.ኹ30 ዓመታት በላይ እንደወሰደ ዚተነገሚለት ዹአንጋፋው ዹፊልም ባለሙያ ፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ ዘጋቢ ፊልም ተሰርቶ ተጠናቀቀ።

4.አስር ሁለቱ እንግዶቜ" ዹተሰኘ ተውኔት ዚፊታቜን እሁድ ለመድሚክ ይበቃል።

5."ስሜ ደበላ ታላቁ ዚግብርና ምርምር ሥርዓት መሪ" ዹተሰኘ መጜሐፍ ነገ ይመሚቃል።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ:

https://youtu.be/FL6kxm4BGNw?si=mErTv7NAFWzE0nY1

📌መልካም ምሜት

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ብስክሌት አዲስ" ዹተሰኘ ፌስቲቫል ነገ ይካሄዳል

ነፍ ኮምኒኬሜን እና ኀቚንት ኚአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እና ኚሚመለኚታ቞ው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ኹተማ ኚወራት በፊት ዹጀመሹውና ዓመቱን ሙሉ ዚወሩ ዚመጚሚሻ እሁድ ዚሚካሄደው "ብስክሌት በአዲስ" ወርሀዊ ፌስቲቫል 3ኛው ዙር ነገ እሁድ መጋቢት 07 ኚጠዋቱ 1:30 ጀምሮ እስኚ 7:00 ድሚስ ኹ4ኪሎ ቀበና ባለው ጎዳና ይካሄዳል።

ዚፌስቲቫሉ ዋና ዓላማ ዚብስክሌት ልምድን መፍጠር በመሆኑ ኚውድድር ፍፁም ነፃና ኚህፃናት እስኚ አዛውንት ድሚስ ተሳታፊ ዚሚያደርግ ነው ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ባቢሎን በሳሎን"ተውኔት ወደ መድሚክ ይመለሳል

በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ሐና ዹተዘጋጀውና በበርካቶቜ ዘንድ ተወዳጅ ዹሆነው "ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ኚሁለት ዓመት በኃላ ለአጭር ጊዜ ወደ መድሚክ ሊመለስ እንደሆነ አርትስ ስፔሻል ኚደራሲው ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

"ባቢሎን በሳሎን" ተውኔትን በአውሮፓ ለሁለተኛ ጊዜ ለማሳዚት እንቅስቃሎዎቜ እንደተጀመሩ ዹተገለፀ ሲሆን ተውኔቱ ወደ አውሮፓ ኹመጓዙ በፊት ለአጭር ጊዜ በዓለም ሲኒማ እንዲታይ ኚሲኒማ ቀቱ አስተዳደር ጋር ንግግር እንደተጀመሚ እና በቅርቡ በድጋሚ ለመድሚክ እንደሚበቃ ውድነህ ክፍሌ ለአርትስ ስፔሻል ተናግሯል።

ተውኔቱ ወደ መድሚክ መቌ ይመለሳል ዹሚለው ጥያቄ ዚበርካታ ቎አትር አፍቃሪን ጥያቄ እንደሆነ ዹገለፀው ደራሲው "ባቢሎን በሳሎን" ወደ መድሚክ እንዲመለስ "ዹዓለም ሲኒማ ኃላፊዎቜም ያሻነውን ቀን እንደሚሰጡን ቃል ገብተውልናል" ብሏል።

"ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ወደ መድሚክ ሲመለስ አርቲስት አለማዹሁ ታደሰን ጚምሮ ሁሉም ተዋናዮቜ እንደሚኖሩም ተገልጿል።

ለ22 ዓመታት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር መድሚክ ላይ ሲቀሚብ ዹቆዹው "ባቢሎን በሳሎን" ተውኔት ኚሁለት ዓመት በፊት ኚመድሚክ መሰናቱ ይታወሳል።

📌 ArtsSpecial

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በኩናማ ሙዚቃው ዚሚታወቀው ኪዳኔ ኃይሌ አሹፈ

"ኊማኒንዳ ጉዳ"በተሰኘው ዚኩናማ ሙዚቃው በበርካቶቜ ዘንድ ዚሚታወቀው ድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ኹዚህ ዓለም በሞት እንደተለዚ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚድምጻዊ ኪዳኔ ኃይሌ ዚኩናማ ሙዚቃ ኀልያስ መልካ ካቀናበራ቞ዉ አልበሞቜ "ብፍቅሪ ሾፊተ" አልበም ውስጥ ዹሚገኝ ሙዚቃ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1