Event Addis Media
9.63K subscribers
6.1K photos
13 videos
4 files
4.72K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📌መልካም ዜና: ኚኀቚንት አዲስ ሚዲያ

ዚኀቚንት አዲስ ዚሐሙስ መሚጃዎቜ አደጉ ተመነደጉ

ዘውትር ሐሙስ በኀቚንት አዲስ ሚዲያ ዚማህበራዊ ትስስር ገፆቜ ሲሰራጭ ዹቆዹው "ዚሐሙስ መሚጃዎቜ" ልዩ ጣዕም ጚምሮ በ቎ሌቪዥን መስኮት መተላለፍ ጀምሯል።

ዚሐሙስ መሚጃዎቜን ዘውትር አርብ "አርትስ ስፔሻል" በሚል ርዕስ ምጥን ፕሮግራሙን ወደ እናንተ ያደርሳል።

"ዚአርትስ ስፔሻል" ምጥን ፕሮግራም ዘውትር አርብ ኚምሜቱ 1:00 እና በድጋሚ ኚምሜቱ 4:00 ላይ በአርትስ ቎ሌቪዥን ዹዜና ሠዓት ይተላለፋል።

በተጚማሪም በሚሊዮኖቜ ተኚታይ ባለው በArts tv World"  ዚዩቲዩብ ቻናል ይሰራጫል።

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ:

አርዕስት:

1.ጃፓናዊያን በአማርኛ ያዜሙበት ዹሙዚቃ አልበም ለአድማጮቜ ቀሚበ።

2.ሠዓሊ መዝገቡ ተሰማ ሀሳቡን ዚሚያጋራበት ልዩ መድሚክ ነገ ይካሄዳል።

3.በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ዚሎቶቜ ዹቁርአን ውድድር ሊካሄድ።

4.ዚደራሲ ሌሊሣ ግርማ አዲስ መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

5.ድምጻዊ አለማዹሁ ሄርጶ ወደ ሙዚቃ ተመለሰ።

6."ኚመስኮቶቜ በስተጀርባ" ዚሥዕል አውደርዕይ ለእይታ ሊበቃ ነው።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይሰሙ ሊንክ: https://youtu.be/y0XQ3babXY0?si=AFT46V5kf8BbVmUj

📌መልካም ምሜት


ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚ"ፈለገ ኪን" ዚኪነጥበብ ዝግጅት ዛሬ ይካሄዳል

በኢትዮጵያ አይነ ስውራን ብሄራዊ ማህበር ዹሚዘጋጀው "ዹፈለገ ኪን" አምስተኛ ዚኪነጥበብ ዝግጅት ዛሬ ቅዳሜ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው ዚማህበሩ ጜ/ቀት  ይካሄዳል።

ባለፉት አምስት መድሚኮቜ እንደተደሚገው ሁሉ ስድስተኛው መርሀግብር ዓይነ ስውራንና ዹዓይነ ስውራን ወዳጆቜ á‹šáˆ†áŠ‘ ባለተሰጥዖዎቜ ዚሙዚቃ፣ ዚሥነግጥምና ዚተለያዩ ዚስነ ጜሁፍ ቜሎታዎቻ቞ውን ዚሚያሳዩበት መድሚክ ነው ተብሏል።

በዕለቱም ገጣሚ ተስፋዬ ማሞ እና ሙዚቀኛ ዳዊት ይፍሩ ዚዕለቱ ተጋባዥ ዚክብር እንግዳ በመሆን እንደሚገኙ ተገልጿል።

አዘጋጆቹ "በመርሃግብሩ ላይ በመታደም ኚአይነስውራን አእምሮ ዹፈለቁ  áŠ¥áˆá‰…á£  ጥልቅ፣ ምጡቅ  ዚስነ ጜሁፍ፣ ዹሙዚቃና ዚፍልስፍና ጠለ በሚኚቶቜን ይቋደሱ " ብለዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ድምጻዊ ዘሩባቀል ሞላ በፕሪስ቎ጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል።

(መግቢያው በነፃ ነው)

ዚተለያዩ ዚጥበብ ባለሞያዎቜን እዚጋበዝ ልምዶቻ቞ውን እንዲያጋሩ እያደሚገ ያለው ፕሪስ቎ጅ አዲስ መርሐግብር ዘሩባቀል ሞላን ጋብዟል::

ዚፕሪስ቎ጅ አዲስ አዘጋጆቜ"ኚድምጻዊ ዘሩባቀል ሞላ ጋራ በሚኖሹን ቆይታ ዚሥራ፣ ዚህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን ዚሚያካፍለን áˆ²áˆ†áŠ• ኚእናንተ ኚወዳጅ እና አድናቂዎቹ ዚሚቀርቡለትን ጥያቄዎቜ ደግሞ ዚፊታቜን  ማክሰኞ ጥር 27 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኀቚንት አዲስ ሚዲያ ገለጞዋል።

በዕለቱ ኚአርቲስቱ ጋር ዚፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ ዚማስፈሚም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::

ፕሪስ቎ጅ አዲስ ኚዘሩባቀል ሞላ ጋር  ዚሚያደሚገው አዝናኝ áŠ¥áŠ“ አስተማሪ ቆይታ  ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ኚስድስት ኪሎ ወደ ሜሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ኚታቜ ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
https://bit.ly/SatchmoCenterMembership

መታወቂያ መያዝ እንዳይሚሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ኚመጀመሩ ቀደም ብላቜሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላቜኋል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌“ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” ዚግጥም መድበል ተመሹቀ

በገጣሚ መሠሚት አዛገ “ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” በሚል ርዕስ ዹተዘጋጀው ዚግጥም መድብል በዋልያ መፅሐፍት ተመርቋል።

መጜሐፉ አንጋፋ ዚኪነጥበብ ሰዎቜ፣ ጋዜጠኞቜ፣ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜና ዚሥነጜሑፍ ቀተሰቊቜ በተገኙበት ነው ዚተመሚቀው።

በምሹቃው ሥነስርዓት ላይ ጾሐፌ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ፣  ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕልና መምህር ዚሻው ተሰማ በመፅሐፉ ዙሪያ አስተያዚት ሰጥተዋል።

እንዲሁም ወጣት ገጣሚያን ሥራ቞ውን አቅርበዋል፡፡

ዚግጥም መድብሉ በ92 ገፆቜ ዹተቀነበበና 47 ግጥሞቜን ዚያዘ ሲሆን በ250 ብር ለንባብ በቅቷል።

ገጣሚ መሠሚት አዛገ፣ ዚ”መሠሚት ዹበጎ አድራጎት ድርጅት” መሥራቜና ሥራ አስኪያጅ ስትሆን፥ ላለፉት 14 ዓመታት በህጻናትና በእናቶቜ ድጋፍና እገዛ ላይ በሠራቻ቞ው ሥራዎቜ በርካታ ሜልማቶቜን ኹሀገር ውስጥና ኚተለያዩ ዹውጭ ሀገራት እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ማግኘት ዚቻለቜ እንስት ናት፡፡

ዘገባው ዚአራዳ ኀፍ ኀም 95.1 ነው።

📞ተክሌ ማርኮን

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌ገጣሚ ምስሚቅ ተሹፈ በእስር ላይ ትገኛለቜ

በጊቢያ ግጥምን በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅነት ዚምናውቃት ገጣሚ ምስራቅ ተሹፈ "ለጥያቄ ትፈለጊያለሜ?" በሚል በፖሊስ ዚተወሰደቜ ሲሆን ፖሊስ ዹ7 ቀናት ዚምርመራ ጊዜ መጠዹቁ ተሰምቷል።

ፖሊስ፣ ምሥራቅን አዲስ አበባ፣ ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት አራዳ ምድብ ቜሎት እንዳቀሚባት፣ ፍርድ ቀቱም ፖሊስ ያቀሚበውን ጥያቄ በመቀበል፣ "ምርመራውን አጠናቆ እንዲያቀርባት" በሚል ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱን ተኚትሎ፣ ምሥራቅ አሁን በአዲስ አበባ ፖሊስ እስር ላይ እንደምትገኝ ወዳጆቿ ገልጞዋል።

ለተጚማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌አስር ሺህ ሰው ዚሚሳተፍበት ዚዳንስ ፊትነስ ኮንሰርት á‰ áŠ á‹µá‹‹ ሙዚዹም ሊካሄድ እንደሆነ ተነገሚ።

ኹ10 ሺ ያላነሱ ኢትዮጵያውያን ይሳተፍበታል ተብሎ ዹሚጠበቀው ታላቁ ዚኢትዮጵያ ዳንስ ፊትነስ ኮንሰርት ዚፊታቜን ዚካቲት 2 2017 ዓ.ም በአድዋ መታሰቢያ ሙዚዹም ኹቀኑ 10:30 ጀምሮ ሊካሄድ ነው።

ይህ በኢትዮ ፊትነስ ዳንስ እና በአዲስ አበባ ወጣቶቜ እና ስፖርት አማካኝነት ዹሚዘጋጀው ዚዳንስ ፊትነስ ኮንሰርት ዋና ዓላማው ሀገራቜንን በዓለም አቀፍ መድሚክ ማስተዋወቅ ነው።

በፕሮግራሙ ዹኹተማው ነዋሪዎቜ እና ኹውጭ ሀገር ትውልደ ኢትዮጵያን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

ዚዳንስ ፊትነስ በኚተማቜን መዘጋጀቱ  ባህላዊውን ውዝዋዜ ኹዘመናዊው ዳንስ ጋር በማዋሐድ ዹሚዘጋጅ በመሆኑ ለሀገር ገጜታ ግንባታ ኹፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ዚአዲስ አበባ ኹተማ ወጣቶቜ እና ስፖርት ቢሮ ዚማህበሚሰብ ስፖርት ማስፋፊያና ማደራጃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንግዳወርቅ ዳንኀል ገልፀዋል።

ዚኢትዮ ዳንሰ ፊትነስ አሰልጣኝ እና መስራቜ ቶማስ ኃይሉ (ቶሚ ፕላስ) በበኩሉ በፕሮግራሙ ኹ10ሺ በላይ ሰዎቜ ለማሳተፍ እዚተሰራ መሆኑን ገልጟ  ይህ ኚተሳካ  በዳንስ ፊትነስ በአፍሪካ ደሹጃ ቀዳሚ እንደሚሆን አሳውቋል።

ቲሞርቱን ኚኢትዮ ዳንስ ፊትነስ ጂም ያገኙታል፣ ዚመግቢያ ዋጋ በነፃ ሲሆን ለቪአይፒ ዚመስሪያ ቲሞርቶቜ ተዘጋጅተዋል። በሁሉቱም አማራጮቜ ለመሳተፍ በኢትዮ ዳንስ ፊትነስ ድሚገፅ https://www.ethiodancefitness.com ላይ መመዝገብ ያስፈልጋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ጥሎሜ ሐር ብራንድ ሟሟል!

ዝነኛዋ ቾሊና ኚጥሎሜ ሐር ጋር ዚብራንድ አምባሳደርነት ዚስራ ውል ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራርማለቜ።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተገለጞው ዚብራንድ አምባሳደርነት ስምምነት ዹሚቆዹው ለሁለት ዓመት ነው።

እንዲሁም ቾሊና በጥሎሜ ሐር ቢል ቊርድ እና ሶሻል ሚዲያዎቜ ላይ ማስታወቂያዎቜ ለመስራት ተፈራርማለቜ፡፡

ጥሎሜ ሐር ዹሰርግ ቀሚሶቜን፣ ማስዋቢያዎቜን እና ዚህንድ እና ተመሳሳይ ባህላዊ ቀሚሶቜን ዚሚያቀርብ ድርጅት ነው ተብሏል።

ጥሎሜ ሐር በሠርግ ዘርፍ ውስጥ ታዋቂ እና መሰሚት ያለው ዚንግድ ምልክት ነው።

ጥሎሜ ሐር ዹሠርግ አልባሳት መሞጫ እና ማኚራያ ስቶር ኹፍተኛ ጥራት ያላ቞ው ዹሠርግ  አልባሳትን እና መገልገያዎቜን በሜያጭ እና በኪራይ በማቅሚብ በተጚማሪም ልዩ ልዩ ዓለምአቀፍ ዹሠርግ áŠ áˆá‰£áˆ³á‰µáŠ• እንዲሁም ዚተለያዚ ስታይል ያላ቞ው ዹሠርግ መገልገያዎቜን ወደ ገበያ ይዞ በመምጣት ላይ ይገኛል።

ጥሎሜ ሐር ዹሠርግ አልባሳት መሞጫ እና ማኚራያ ሱቅ ዚፊታቜን ቅዳሜ ዚካቲት 1 2017 ዓ.ም በታላቅ ሥነሥርዓት (Grand Opening ) ጋራድ ሞል ላይ ይካሄዳል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚጋዜጠኛ ተስፋ ፈሩ "አንሶላ ውስጥ ሟቜ እና ሌሎቜም ወጎቜ" መጜሐፍ ነገ ይመሚቃል።

በጋዜጠኛ ተስፋ ፈሩ ዹተፃፈው 57 ቁም ነገር አዘል አዝናኝ ወጎቜ ዚተካተቱበት  "አንሶላ ውስጥ ሟቜ እና ሌሎቜም ወጎቜ" መጜሐፍ ነገ ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ኹቀኑ 10፡ 30 አራት ኪሎ በሚገኘው ዚኢትዮጜያ ፕሬስ ድርጅት አዳራሜ (ብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፊት ለፊት) ይመሚቃል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌አስደሳቜ ጉዞ ወደ ወንጪ:

Camping 🏕 Trip To Wenchi Crater lake

ጉዞ ወደ ተወዳጁ እና ዹአለም ምርጥ ዚቱሪዝም መንደር : ወንጪ :  ዚካቲት 1እና 2/ 2017

It’s time to spend your weekends embarking on an unforgettable camping trip to Wenchi crater lake ! Explore the stunning natural beauty and live the adventure with 👉🏟 @dembeltours

Date 📅): February 8 & 9 2025
Duration(⏱): 2 days & 1 night
Departure: Mexico, Wabi Shebelle Hotel
6:00 AM @ 12:00 LT

Price(💵): 5900 ETB For Locals

Package includes
🚎 ትራንስፖርት / Transport
🥪ቁርስ / Breakfast /X2/
🍔 ምሳ / Lunch / X2 /
🥩 እራት / barbecue 🍖
🥀ዚታሞገ ውሃ / Bottled Water
🎫ዚመግቢያ ዋጋ / Entrance
🗺 ዚአስጎብኚ / Local Guide
🏖 ዋና / Swimming
🏕 ዚምሜት እሳት ዳር ጚዋታCampfire 🔥
🌊ዚተፈጥሮ ፍል ውሀ / Hot Spring Water & bath
⛺ ማደሪያ ድንኳን (Tent)
📷 ፎቶግራፍ /🌅 Photograph

For more info call 📞 0919874598
@dembeltours
📌አላቲኖስ ዹፊልም ውይይት ዛሬ ይካሄዳል።

አላቲኖስ ኢትዮጵያዊ ፊልም ሰሪዎቜ ማሕበር ፒያሳ በሚገኘው ዚሩሲያ ሳይንስና ባህል ማዕኹል (ፑሜኪን) አዳራሜ ውስጥ በሚያዘጋጀው ዹፊልም ውይይት መርሐግብር ዛሬ áˆáˆ™áˆµ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 10:30 ጀምሮ ያካሄዳል።በዕለቱም በበርካታ ፊልሞቜ ላይ በድምፅ ባለሞያነት ዚተሳተፈው ሐብታሙ አዲስ በእንግዳነት ይቀርባል ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ዚጉድ ሰፈር" ተውኔት በቢሟፍቱ ኹተማ

በወሰን ግዛው ተደርሶ በአማኑኀል ክፍሌ ዹተዘጋጀው"ዚጉድ ሰፈር" ተውኔት በቢሟፍቱ ኹተማ ዚፊታቜን እሁድ ለእይታ ይቀርባል ተብሏል።

በይሳኮሮ ኪነጥበባት ተቋም ተዘጋጅቶ ዹቀሹበው "ዚጉድ ሰፈር" ተውኔት ዚፊታቜን እሁድ ዚካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 7:00 ጀምሮ በቢሟፍቱ ኹተማ በሚገኘው በእታለም ሲኒማ ለተመልካቜ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ ለኀቚንት አዲስ ሚዲያ አስታውቋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ዓይነ ርግብ" መጜሐፍ ነገ ይመሹቃል

በደራሲ ትዕግሥት ሳሙኀል ዹተዘጋጀው "ዓይነ ርግብ" መጜሐፍ ነገ አርብ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 11:00 ጀምሮ በወመዘክር (ብላ቎ን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሎ አዳራሜ)ውስጥ ይመሚቃል።

በዕለቱም ልዩ ልዩ ኪነጥበባዊና ዚትውውቅ መርሐግብሮቜ እንደሚኖሩ አዘጋጆቹ አስታውቋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በእሚፍት ቀንዎ ቎አትር ይመለኚቱ !

አንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር  እና ዹቩሌው ዓለም ሲኒማ ሐሙስ፣ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶቜ ለታዳሚያን ያቀርባሉ።

📍 ጎዶ'ን ጥበቃ

ድርሰት: ሳሙኀል ቀኬት
ትርጉም: ሀይኹል ሙባሚክ
አዘጋጅ: ዳግም ሲሳይ
ቀን: ሐሙስ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር


📍 ዋዋጎ

ድርሰት: ታሚቀኝ ብርሃኑ
አዘጋጅ: ጥላሁን ዘውገ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቊታ: ዓለም ሲኒማ

📍ዚሕይወት ታሪክ

ድርሰትና ዝግጅት ነብዩ ባዬ እና ቢንያም ወርቁ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ባሎቜ እና ሚስቶቜ

ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኀል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ባቡሩ

ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሟመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ሾምጋይ

ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኀል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 እምዩ ብሚቷ

ድርሰት: ቀልቶልት ብሬሜት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

ዚእናንተው ኀቚንት አዲስ ድሚገፅ መልካም ዚእሚፍት ቀን ይሁንላቜሁ ይላል !

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚሌሊሳ ግርማ አዲስ ዛሬ ለንባብ ይበቃል።

ዚደራሲ ሌሊሳ ግርማ “በታቜም በምድር” ዹተሰኘው ወጥ ዚልቊለድ መፅሐፍ በዛሬው ዕለት በንባብ ይበቃል ተብሏል።

በተለያዩ መጣጥፎቜና አጭር ልብ ወለድ ጜሁፎቜ በአንባቢያን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተሚፈው ሌሊሳ ግርማፀ አሁን ደግሞ በመጀመሪያ ዚወጥ ልቊለድ ድርሰት መጥቻለሁ እያለ ነው፡፡

ደራሲ ሌሊሳ ግርማፀ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚያቀርባ቞ው ጥበባዊ መጣጥፎቹም ይታወቃል፡፡

ደራሲው ኹዚህ ቀደም “ዚንፋስ ህልም እና ሌሎቜ አጫጭር ታሪኮቜ”፣ “አፍሮ ጋዳ”፣ “መሬት - አዹር - ሰማይ”፣ “ዹሰኹሹ እውነታ”፣ “እስቲ ሙዚቃ”፣ “ነፀብራቅ”፣ “ይመስላል ዘላለም”፣ ዹሚሰኙ ዚመጣጥፍና ዹአጭር ልብ ወለድ ስብስብ መድበሎቜን ለአንባቢያን ማበርኚቱ ይታወሳል፡፡

ዚመጜሐፉ አሳታሚ ዋሊያ መፅሐፍት ድርጅት ሲሆንፀ መጜሐፉ ኚዛሬ ጀምሮ በኹተማዋ በሚገኙ መጻሕፍት ቀቶቜ ሁሉ ለገበያ እንደሚውል ታውቋል ሲል አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአርብ ምሜቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

ዘውትር ሐሙስ በኀቚንት አዲስ ሚዲያ ዚማህበራዊ ትስስር ገፆቜ ሲሰራጭ ዹቆዹው "ዚሐሙስ መሚጃዎቜ" ልዩ ጣዕም ጚምሮ በ቎ሌቪዥን መስኮት መተላለፍ ጀምሯል።

ዚሐሙስ መሚጃዎቜን ዘውትር አርብ "አርትስ ስፔሻል" በሚል ርዕስ ምጥን ፕሮግራሙን ወደ እናንተ ያደርሳል።

"ዚአርትስ ስፔሻል" ምጥን ፕሮግራም ዘውትር አርብ ኚምሜቱ 1:00 እና በድጋሚ ኚምሜቱ 4:00 ላይ በአርትስ ቎ሌቪዥን ዹዜና ሠዓት ይተላለፋል።

በተጚማሪም በሚሊዮኖቜ ተኚታይ ባለው በ"Arts tv World" á‹šá‹©á‰²á‹©á‰¥ ቻናል ይሰራጫል።

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮቜ ታገኛላቜሁ:

አርዕስት:

1.ዚድምጻዊ ዮሐና "ታማ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ሙዚቃ መነጋገሪያ ሆነ።

2.ዓመታዊው አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል መካሄድ ጀመሚ።

3.ዚጥቁር ሕዝቊቜ ታሪክ ለአንድ ወር በኢትዮጵያ ሊዘክር ነው።

4.ዚአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል በአዲስ አበባ  እዚተካሄደ ይገኛል።

5. ዹዝነኛው ድምጻዊ አቀል ተስፋዬ (ዘ ዊኬንድ) ያልተጠበቀ ዚመድሚክ ሥራ ዓለምን እያነጋገሚ ነው።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታቜንን ይመለኚቱ: https://youtu.be/A1NyEwkdI_4?si=i2A4hF20mlJjeDHX

📌መልካም ምሜት


ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ነገሹ መጻሕፍት" ዛሬ ይካሄዳል

በዛጎል ዚመጻህፍት ባንክ ዹሚዘጋጀው "ነገሹ መጻሕፍት" ዚመጻህፍት ውይይት  ዛሬ á‰…ዳሜ ዚካቲት 1 2017 ዓ.ም ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሜ ውስጥ ይካሄዳል። በዚህ መሰናዶ ላይ áŠ áˆáˆ³áˆ‰ መሐሪ እና ቀተማርያም ተሟመ ተጋባዥ እንግዶቜ ና቞ው።ዚፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ኹበደ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ኚራሚ ኚራማ" መጜሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

በወጣቱ ገጣሚ ዳንኀል ወዳጄ ዚተጻፈው "ኚራሚ ኚራማ" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ዚግጥም መጜሐፍ በቅርቡ ለአንባቢያን እንደሚቀሚብ ገጣሚው ለኀቚንት አዲስ ሚዲያ አስታውቋል።

ዚመጜሐፍ ርዕስ ዹሆነው "ኚራሚ ኚራማ" ሲተርጉም "ኚራሚ"በግዕዝ ወይን ጠጅ ጠማቂ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል"ኚራሚ" ማለት ዹሚኖር ዹኖሹ ዚተሻገሚ ዹኹሹመ"ማለት እንደሆነም ገለጿል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚሬጌው ድምፃዊ ራስ ብሩክ ሊስት አዳዲስ ዹሙዚቃ ቪዲዮዎቜን ለቀቀ

ኢትዮጵያዊው ዚሬጌ አርቲስት ራስ ብሩክ ፀሀይ ወይም “ራስ ባርኪ” ሊስት አዳዲስ ዹሙዚቃ ቪዲዮዎቜን ለቋል፡፡

እነዚህ ዹሙዚቃ ስራዎቜ በዳንስሆል እና ሬጌ ስልት ዚተሠሩ ሲሁኑ “ልስልስ ያለቜ”፣ “ይቅናህ” እና “አፍሪካን ፓርቲ” ዹሚሉ ርዕሶቜን ይዘዋል፡፡

ራስ ብሩክ ኹዚህ ቀደም በርካታ ሙዚቃዎቜን ያስደመጠ ሲሆን በተለይ ኹ10 ዓመት በፊት ዹለቀቀው “ብዙ ወሬ” ዹተሰኘው ዘፈኑ ተወዳጅነትን አትርፎለታል፡፡

በተጚማሪም ኚተለያዩ ዹሃገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ዚሬጌ አርቲስቶቜ ጋር በመጣመር ሥራዎቹን አቅርቧል፡፡ ራስ ብሩክ በኢቢኀስ ቎ሌቪዥን ለሚዥም ጊዜያት ዚሬጌ ሙዚቃ ፕሮግራም አቅራቢ ሆኖም  ሰርቷል፡፡

ዚአዳዲሶቹ ሊስት ሙዚቃዎቜ ግጥምና ዜማ በራሱ በድምፃዊው ራስ ብሩክ ዚተሠሩ ሲሆን “ይቅናህ” ዹተሰኘው ዘፈን ቪዲዮ ዩጋንዳ ውስጥ ቀሹፃው ተኚናውኗል፡፡ “አፍሪካን ፓርቲ” ዹተሰኘው ሙዚቃ ላይ ደግሞ ሊስት ዝነኛ ዩጋንዳዊያን አርቲስቶቜ ተሳትፈዋል፡፡ ዘፈኖቹ በአርቲስቱ ዚዩቲዩብ ገፅ (Ras Biruk Tsehay) ላይ ተለቀዋል፡፡
https://www.youtube.com/@RasBirukTsehay_BarkyOfficial/videos

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚሙዚቀኛ ተፈሪ አሰፋ ዚስንብትና ዚመታሰቢያ ሥነሥርዓት ተካሄደ

ዹሙዚቃ ባለሙያው ዚተፈሪ አሰፋ ዚስንብትና ዚመታሰቢያ ስነ ስርዓት ባሳለፍነው ዚካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም በሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ ተካሄደ።

በዚህ መርሐግብር ላይ ወ\ሮ መልካም ሰው አበበ ዚተፈሪ አሰፋ አጭር ዚህይወት ታሪክ ያነበቡ ሲሆን ህይወቱን እና ስራዎቹን ዚሚያሳይ አጭር ቪድዮም ለእይታ ቀርቧል።

ለሙዚቃ መምህር እና ተመራማሪ ተፈሪ አሰፋ በተዘጋጀው ዚስንብትና ዚመታሰቢያ መርሐግብር ላይ ዚባለቀቱ ዚአርቲስት አብነት አስናቀ እና ዚሁለት ልጆቹ ዹአማኑ ተፈሪ እና ዚሚድኀት ተፈሪ መልዕክት በአቶ ያፌት ተክሌ ኹተላለፈ በኋላ በአቶ አብይ ጥላሁን ግጥም ቀርቧል።

እህትና ወንድሞቹ ግርማቾው አሰፋ ፣ ሰዋሰው አሰፋ ፣ እስክንድር አሰፋ ፣ ህሩይ አሰፋ ፣ ናኊድ አሰፋ እና ቅድስት አሰፋ ስለሙዚቀኛ ወንድማ቞ው ስለልጅነቱና አስተዳደጋ቞ው ተናግሚዋል።

አባ ላዕኹ ማሪያም አባታዊ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ አቶ ምስጋናው ሙላት ፣ አቶ ክብሮም ብርሃኔ እና አቶ ኪሩቀል አሰፋ ኚተፈሪ እሰፋ ጋር ስለነበራ቞ው ወዳጅነት እና ስለሙያዊ አብርክቶው  ተናግሚዋል።


ዚስመ ብዙው ዹሙዚቃ ሰው ዚተፈሪ እሰፋ አስክሬን በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በብሔራዊ ቎ያትር ዚመታሰቢያ እና ዚክብር ሜኝት ኚተደሚገለት በኋላ በቅድስት ስሥላሎ ካ቎ድራል ዚቀብር ስነ ስሚዓቱ ይፈፀማል።

ሚያዚያ 15 ቀን 1964 ዓ.ም ኚአባቱ አቶ አሰፋ ፀጋዬ እና ኚእናቱ ወ\ሮ መንበሹ ተሰማ በአዲስ አበባ ኹተማ ዹተወለደው ሙዚቀኛ ተፈሪ አሰፋ ህክምናውን ሲኚታተል  በነበሚበት ሎስ አንጀለስ ኹተማ በተወለደ በ52 ዓመቱ ዕሚቡ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ማሹፉ ይታወሳል።

©ሚካኀል አለማዹሁ

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ ዚሬድዮ ቀን ነው

በዓለም ዙሪያ ኹ44 ሺህ በላይ ሬዲዮ ጣቢያዎቜ በዚዕለቱ መሚጃዎቜን ለዓለም ህዝብ ያደርሳሉ።

📌ኚ5 ቢሊዚን በላይ ዹሚሆኑ ዚዓለማቜን ህዝቊቜ ዚሬዲዮ አድማጮቜ መሆናቾውንም መሚጃዎቜ ይጠቁማሉ።

📌 ዹዓለም ራዲዮ ቀን እንዲኚበር በስፔን ዚራዲዮ አካዳሚ አነሳሜነት ጥያቄው በፈሚንጆቹ በ2010 ለ(UNESCO) ዚስራ አመራር ኹቀሹበ በኋላ ዚተባበሩት መንግስታት ጉዳዩን ተቀብሎ ዓለም አቀፍ ዚራዲዮ ቀን በዚዓመቱ ዚካቲት 13(በኛ ዚካቲት 6) እንዲኚበር ወስኗል።

📌ኚ152 ዓመታት በፊት እንደተፈጠር ዚሚነገርለት ሬድዮ ኹ100 ዓመታት በላይ ሰዎቜ በዚዕለቱ በስራ ቊታ቞ው፣ በትራንስፖርት ላይ እንዲሁም በመኖሪያ ቀታ቞ው ሆነው ያደምጡታል።

📌በሀገራቜን ዚመጀመሪያው ሬድዮ ዚኢትዮጵያ ሬድዮ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በስርጭት ላይ ዹሚገኙ ኹ50 በላይ ዚሬዲዮ ጣቢያዎቜ አሉ፡፡

📌ዚመጀመሪያው ኀፍ.ኀም ዚሬዲዮ ጣቢያ ኀፍ.ኀም 97.1 ነው። ዚመጀመሪያው ዹግል ዚሬዲዮ ጣቢያ ሾገር ኀፍ.ኀም 102.1 ነው።

📌ዚካቲት 23 1997 ስርጭቱን ዹጀመሹው ዚደቡብ ድምፅ ኀፍ ኀም 100.9 ሬድዮ ዘንድሮ 20 ዓመት ይሞላዋል።

📌ሞገር 102.1፣ ፋና ኀፍ ኀም 98.1፣ ዛሚ (ዹአሁኑ አዋሜ)፣ ብስራት 101.1፣ ኢትዮ ኀፍ ኀም 107.8፣አሐዱ 94.3፣ አራዳ ኀፍ ኀም 95.1 እና ሌሎቜም በስርጭት ዹሚገኙ ዚኚተማቜን ኀፍ ኀም ሬድዮ ጣቢያዎቜ ና቞ው።

📌ዚኢኮኖሚና ዋልታ ቡና ቡና፣ ፀሐዬ ደመቀቜ፣ ዚተስፋዬ ገብሬ ስፖርት ለጀንነት ፣ዚአሞናፊ ኹበደ እሚኛው ባለዋሜንት ክላሲካል ፣ ዚኢትዮጵያን እንቃኝ ዚኪሮስ ኃይለስላሎ ድምፅ፣ዚአይሬ አሆይ፣ ዹዘፈን ምርጫ ኢንትሮ እና ሌሎቜም ዚማይሚሱ ዚሬድዮ ዹሙዚቃ ድምፆቜ ና቞ው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚጠርሲዳ ኹበደ መጜሐፍ ሊመሹቅ ነው።

በደራሲ ጠርሲዳ ኹበደ ዹተዘጋጀው "ውሃዬን ሜጬ ኮዳ ዚገዛኹለት" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው መጜሐፍ በይፋ ተመርቆ ለንባብ ይበቃል ተብሏል።

መጜሐፉም በርካታ ልዩ ልዩ እንግዶቜ በተገኙበት ዚፊታቜን ሰኞ ዚካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ኚምሜቱ 11:00 ጀምሮ በአንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ይመሚቃል።

በዕለቱም አርቲስት ተስፉ ብርሃኔ፣ አርቲስት ዋሲሁን በላይ ፣ ድምጻዊ አንተነህ ምናሉ፣ ገጣሚ ሒክማ ፋንቱ እና ሌሎቜም በመድሚኩ ሀሳቊቻ቞ውን ያጋራሉ ተብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1