Event Addis Media
9.61K subscribers
6.13K photos
14 videos
4 files
4.75K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌"ሊስቱ አይጊቜ" ተውኔት በይፋ ተመሹቀ !

በአራዳ ፊሊኚስ ፕሮዲዩስ ተደርጎ በኢትዮጲያ ብሔራዊ ቲያትር በመታዚት ላይ ያለውና በአርቲስት ኀልያስ ተስፋዬ ተፅፎ በአርቲስት ካሌብ ዋለልኝ እና በአርቲስት ህብሚ ቀለመወርቅ ዹተዘጋጀው "ሊስቱ አይጊቜ” ተውኔት ሰኞ ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም በርካታ ዚኪነጥበብ ባለሙያዎቜ፣ ዚኮርፖሬት ተቋማት ሃላፊዎቜ፣ ዚመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት አንደኛ ዓመቱን ምክንያት በማድሚግ በታላቅ ድምቀት በአንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር ቀት ተመርቋል።

በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ዚኢፌድሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስ቎ር ዚሥነ-ጥበብና ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዎኀታ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።

በ቎አትሩ ዚአንድ ዓመት ጉዞ ላይ ዚራሳ቞ውን አስተዋጜኊ ላበሚኚቱ ባለሞያዎቜ እውቅና ተሰጥቷ቞ዋል።

በተውኔቱ ላይ ካሌብ ዋለልኝ ፣ህሊና ሲሳይ ፣ህብሚ ቀለመወርቅ ፀ እንዳለ ብርሃኑ፣ ታሪክ አስተርአዚ፣አስመላሜ ታምርአዚሁ፣ ቞ርነት ፍቃዱ ፣መርዕድ ተስፋዬ፣ ሔኖክ ዘርዓብሩክ በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

"ሊስቱ አይጊቜ" ተውኔት ኹ20 ዓመታት በፊት "ዹተኹፈለ ልብ" በሚል ርዕስ በሀገር ፍቅር ቎አትር ቀት ተመድርኮ ነበር።

@EventAddis1
📌ዚበዕውቀቱ ስዩም ሶስት መጻሕፍት ድጋሚ ታተሙ

ዚበዕውቀቱ ስዩም ሶስት ተወዳጅ መጻሕፍት በድጋሚ ታትመው ለአንባቢያን ቀሚበዋል።

በአንባቢያን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተሚፉትና ኚገበያ ጠፍተው ዚነበሩ ዚበዕውቀቱ ስዩም "መግባት እና መውጣት" ፣"ስብስብ ግጥሞቜ" እና "ኹአሜን ባሻገር ዹተሰኙ ሶስት መጻሕፍት በድጋሚ ታትመው ገበያ ላይ ውለዋል::

ገጣሚና ደራሲ በዕውቀቱ ስዩም  በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይህን መልዕክት አስፍሯል"ውድ ዚመጜሀፍ ወዳጆቜ! ኚገበያ ጠፍተው ዚነበሩት ዚበእውቀቱ ስዩም መጻሀፍት መካኚል ፥ መግባት እና መውጣት፥ ስብስብ ግጥሞቜ እና ኹአሜን ባሻገር ' በድጋሜ ታትመው ለገበያ ቀርበዋልፀ መግዛት ወይም መሞጥ ዚምትፈልጉ ፥ ለገሐር አመልድ ህንጻ፥ አንደኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አይንአለም መጜሀፍ መደብር ጎራ በሉፀ ስልክ  0911814536"።

መሹጃው ዚይትባሚክ ዋለልኝ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ዚጣዕም ልኬት" ዝግጅት ወደ አዹር ሊመለስ ነው

ሙዚቃና ሙዚቃዊ ጉዳዮቜን ዚሚዳስሰው "ዚጣዕም ልኬት" ዚሬድዮ ፕሮግራም በቅርቡ ወደ አዹር እንደሚመለስ ኀቚንት አዲስ ድሚገፅ ኚአዘጋጆቹ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ዚሬድዮ ፕሮግራሙ ዚሬድዮ ጣቢያውን ኹሾገር 102.1 ወደ አንጋፋው ኀፍ ኀም አዲስ 97.1 ቀይሮ ዘወትር ቅዳሜ ኹቀኑ 6:00 እስኚ 8:00 ይተላለፋል ተብሏል።

"ዚጣዕም ልኬት" አዘጋጆቜ ዹሙዚቃ ባለሞያዎቹ ሰርፀ ፍሬስብሃት እና ምዕራፍ ተክሌ ና቞ው።

ዚፕሮግራሙ አዘጋጅና ዹሙዚቃ ባለሞያው ሰርፀ ፍሬስብሃት ማኀበራዊ ትስስር ገፁ" ምንም ብንዘገይ፣ በመጚሚሻ አድርገነዋል። ለበርካታ ዓመታት ኚጆሯቜሁ ርቃ ዚቆዚቜው "ዚጣዕም ልኬት" ተመልሳ ዐዹር ላይ ልትውል ነው።በFM ዐዲስ 97.1 ሬዲዮ ሠርክ ቅዳሜ ኹ6:00- 8:00።አዘጋጆቜ፥ ምዕራፍ ተክሌ እና ሠርፀ ፍሬስብሐ። "በሙዚቃዎቻቜን ዚጣዕም መሠሚቶቜ" ላይ ትኩሚቷን ያደሚገቜው ዚጣዕም ልኬት ተመልሳለቜበቅርብ ቀን" ብሏል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በእሚፍት ቀንዎ ቎አትር ይመለኚቱ !

አንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር  እና ዹቩሌው ዓለም ሲኒማ ሐሙስ፣ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶቜ ለታዳሚያን ያቀርባሉ።

📍 ጎዶ'ን ጥበቃ

ድርሰት: ሳሙኀል ቀኬት
ትርጉም: ሀይኹል ሙባሚክ
አዘጋጅ: ዳግም ሲሳይ
ቀን: ሐሙስ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር


📍 ዹፍቅር ካ቎ና

ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቊታ: ዓለም ሲኒማ

📍 "እሳት ወይ አበባ"

ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብሚመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሜፈራው ታሪኩ ቢሚጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ባሎቜ እና ሚስቶቜ

ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኀል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ባቡሩ

ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሟመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 ሾምጋይ

ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኀል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

📍 እምዩ ብሚቷ

ድርሰት: ቀልቶልት ብሬሜት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቊታ: ብሔራዊ ቎አትር

ዚእናንተው ኀቚንት አዲስ ድሚገፅ መልካም ዚእሚፍት ቀን ይሁንላቜሁ ይላል !

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚገጣሚ ዮሐንስ ሞላ "በኚንፈርሜ በራ'ፍ" መጜሐፍ በድምቀት ተመሚቀ።

ዚገጣሚ ዮሐንስ ሞላ "በኚንፈርሜ በራ'ፍ" ዹተሰኘ  ርዕስ ዹተሰጠው አዲስ  ዚግጥም መጜሐፍ ሚቡዕ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም  አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት ተመርቋል።

በዕለቱም ግጥሞና ወጎቜ ተነበዋል፣ ሥነጜሑፋዊ ዳሰሳዎቜና ዹሙዚቃ ዝግጅት ቀርቧል።

ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ ኹዚህ ቀደም "ዚብርሃን ልክፍት" እና "ዚብርሃን ሰበዞቜ" ዹተሰኙ መጻሕፍት አንባቢያን ማድሚሱ አይዘነጋም።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ፍቅር ኢትዮጵያ ዚአእምሮ እድገት ውስንነት ማህበር ዚተመሰሚተበትን 30ኛ ዓመቱን ሊያኚብር ነው

ፍቅር ኢትዮጵያ ዚአእምሮ እድገት ውስንነት ማህበር ሰላሰኛ አመት ዚምስሚታ በዓሉን ለተኚታታይ አስር ቀናቶቜ እንደሚያኚብር አስታወቀ።

ኚጥቅምት 25 አስኚ ህዳር  5 2017 ዓ.ም ሠላሰኛ ዓመቱን በተለያዩ ዝግጅቶቜ ዚሚያኚብሚው ፍቅር ኢትዮጵያ ዚአእምሮ እድገት ውስንነት ብሄራዊ ማህበር ይህ ጊዜ አዲስ ዚታሪክ ምዕራፍ ዚምንኚፍትበት ይሆናል ብሏል።

ዚማህበሩ ፕሬዚዳንት ምህሚት ንጉሮ
በዓሉ ዚአእምሮ እድገት ውስንነት ላለባ቞ው ዜጎቜ ድጋፍ ለመስጠት ፣ ለመብታ቞ው ለመሟገት እና አካታቜነትን ለመፍጠር ምን ያህል እንደተጋን እንድንገመግም ያስቜለናል ብለዋል።

በሶስት አሰርት ዓመታት ውስጥ በጀና ፣ በትምህርት፣በማህበራዊ ጥበቃ እድሎቜን ኚማሳደግ፣ዜጎቜን በራስ በመደገፍ እና ድምፃ቞ው እንዲሰማ በማድሚግ አመርቂ ውጀት ማምጣታቜን ግን እሙን ነው " ብለዋል።

ስኬታቜንን ስናኚብር ብዙ ዚሚቀሩን ስራዎቜ እንዳሉብንም እንገነዘባለን ሲሉም ፕሬዚዳንቷ ተናግሚዋል።

ዹ30ኛ ዓመት ዚምስሚታ ክበሹ በዓሉ ለሁሉም ጎብኝዎቜ ክፍት በሆነው ኚጥቅምት 25 እስኚ 29 ቀን 2017 ዓ/ም በኢትዮ ኩባ ወዳጅነት ፓርክ በሚዘጋጅ ኀግዚቢሜንና ዹመዝናኛ ፕሮግራም ተጀምሮ ህዳር 05 ቀን 2017ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቮል ይጠናቀቃል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በሲኒማ ቀቶቜ ዹፊልም ስርቆት መኚላኚያ ሲስተምን ጚምሮ ኹ140 በላይ ቜግር ፈቺ ዹሆኑ áŠ˜áˆ®áŒ€áŠ­á‰¶á‰œáŠ• ይዞ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ኀስ አር ኢ ኢትዮጵያ አስታወቀ

ኀስ አር ኢ ኢትዮጵያን በሳይንስ እና ቮክኖሎጂ ዹላቀ ለማድሚግ ኹ140 በላይ ቜግር ፈቺ ዹሆኑ  ኘሮጀክቶቜን ይዞ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገለጞ።

ኚአስር አመት በፊት በሀገሹ አሜሪካ በዋሜንግተን ዲሲ ዹተመሠሹተው ኀስ አር ኢ ዹተሰኘ መሠሚቱን ሳይንስና ቮክኖሎጂ ምርምርና እውቀት ላይ አድርጎ ዹሰው ልጆቜን ህይወት ለመቀዹር በማሰብ ዹተመሰሹተ ተቋም ሲሆን በቀጣይ አለምን በሳይንስ ቮክኖሎጂ ለመቀዹር ዓላማን ይዞ እዚሰራ እንደሚገኝ ዚድርጅቱ መስራቜ አቶ ሳመኀል ኹፈለኝ ገልጞዋል።

ተቋሙ ኚሰራ቞ው አበይት ዚፈጠራ ስራዎቜ መካኚል በሲኒማ ቀቶቜ ዹፊልም ስርቆት መኚላኚያ ሲስተም ፣ ኹ250 በላይ ትምህርት ቀቶቜ ፣ ኹ10 በላይ ኮሌጆቜ፣ ኚአስራ ስድስት በላይ ዩኒቚርሲቲዎቜ ዹአፍ ላይን ዲጂታል ላይብሚሪ ማሜን ተጠቃሚ ኚማድሚጉም በላይ  ለጎርፍ አደጋና ለመሬት መንቀጥቀጥ ዹአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ቎ኚኖሎጂ፣ ዚግለሰቊቜን ማንነት እራሱ ለይቶ ለማወቅ ዚሚያስቜል ሰው ሰራሜ አስተውሎት ( አር቎ፊሻል ኢንተለጀንስ ) ቮኹኖሎጂ እንዲሁም ኹ15 በላይ ዘመናዊ ቎ክኖሎጂዎቜን ማበርኚቱን ተቋሙ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

ተቋሙ ኢትዮጵያ በኹፍተኛ ዹውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ ዚሚገቡ ዹቮክኖሎጂ ምርቶቜን ሀገር ውስጥ በማምሚት ለበርካታ ወጣቶቜ ዚስራ እድል በመፍጠር በኩል ጉልህ ድርሻ ያበሚኚተ ሲሆን በሰው ሰራሜ አስተውሎት ዚሚታገዝና ዚሚመራ ዚትራፊክ መብራቶቜን ፣ ባዩሜትሪክ ፣ ለቱሪስቶቜ መሹጃ ዚሚሰጥ ዹመሹጃ ማዕኹል ጚምሮ በርካታ ዚፈጠራ ስራዎቜን ሰርቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ሠዓሊ ወንድወሰን ኹበደ  ዹ2024  ዚአፍሪካ ፋሜንና ሥነ-ጥበብ ሜልማት ( AFAA ) ተሾላሚ ሆነ

ላለፉት 25 ዓመታት ኚፋሜን ሰዎቜ ታዋቂዎቜን እነ ቺኒዋ አቌቀ፣ አለን ፔተን፣ ዹሚ አላዎ፣ ብሬንዳ ፋሮ እና ኚሰዓሊያን እነ ቌሪ ሳምባ፣ አብዱላሂ ኮን቎ እና  ኢብራሂም አል ሳላሂ በተለያዩ ዓመታት ዹሾለመው ዚአፍሪካ ፋሜንና ሥነ-ጥበብ ሜልማት ( AFRICAN FASHION & ART AWARD -AFAA ) ዘንድሮው  áŠšáˆšáˆžáˆáˆ›á‰žá‹ 100 አፍሪካዊያን ዚፋሜን እና ዚሥነ-ጥበብ ሰዎቜ  ውስጥ  ብ቞ኛው ኢትዮጵያዊ  ሠዓሊ ወንድወሰን ኹበደ ኟኗል።

ሠዓሊ ወንድወሰን ኹበደ ለሜልማቱ ቀጥታ ተመራጭ እንዲሆን ያበቃውፀ በአፍሪካ ስልጣኔ፣ ባህል እና ፓን አፍሪካኒዝም እንዲሁም በኢትዮጵያ ስልጣኔ ፣ ባህል እና ማንነት ላይ በሠራ቞ው ዚስዕል ሥራዎቜ እና በተለያዩ ዓለማት በተሳተፈባ቞ው ዐውደ ርዕዮቜ ባገኛ቞ው እውቅናና ሜልማቶቜ ነው።

ሠዓሊ እና ዚታሪክ ባለሙያ ወንድወሰንፀ  በአሁን ሰዓት ዚኢትዮጵያ ሠዓሊያንና ቀራፂያን ማኅበር ዋና ጾሐፊ ፀ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ዚሥነ-ጥበብ አማካሪ፣ በኢቲ - ሜትሮፖሊታን ጋለሪ ዳይሬክተር እና ኩሬተር፣ ዹሀገር አማን እና ሆርን ሪቪው መጜሔቶቜ ካርቱኒስት እና አምደኛ፣ በኢትዮጵያ ሀገር በቀል ዹሕክምና ማኅበር አምባሳደር በመሆን እያገለገለ ይገኛል።

ዚዘንድሮውን ዚአፍሪካዊያን ዚፋሜን እና ዚሥነ-ጥበብ ሜልማት ኹNovember 6th - 8th /2024 በዋና ጜሕፈት ቀቱ ደቡብ አፍሪካ እንደሚያካሂድ አፋ (AFAA) ባወጣው መግለጫ አሳውቋል ።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚቀድሞ ድምጻዊ ተፈራ ነጋሜ አልበም በድጋሚ ተሰርቶ ለአድማጭ ሊደርስ ነው

በ1980 ዎቹ ኹተዜሙ ዚድምጻዊ ተፈራ ነጋሜ አልበሞቜ ዚተውጣጡ ሙዚቃዎቜ በድጋሚ ተሰርተው ለአድማጭ ሊደርሱ ነው ተባለ ።

በተለያዩ ነጠላ ዜማዎቹ ዚሚታወቀው ድምጻዊ ፍቃዱ ትዕዛዙ "ዘንድሮ'' በተሰኘ ዹሙዚቃ አልበም መጠሪያ ዹተሰጠውን ዚድምጻዊ ተፈራ  ነጋሜ ስራ ይዞ መምጣቱን አስታውቋል።

"ዘንድሮ" ዹሚል ስያሜ ዹተሰጠው አልበም ኚሰላሳ ዓመታት በፊት በተዜሙ ዜማዎቜ በልዩ ጥንቃቄ ለዚህ ዘመን በሚስማማ መልኩ እንደገና ዚተሰሩ ሙዚቃዎቜ ናቾው ተብሏል ፡፡

በድምፃዊ ተፈራ ነጋሜ በተለያዩ አልበሞቜ ላይ ዹተቀነቀኑ ሙዚቃዎቜን ድምጻዊው á‰ áˆ™á‹šá‰ƒ ፈጠራ ስራዎቹ ላይ ዚተሳተፉ ባለሞያዎቜን እና ዚቀተሰቊቜን መብት እና ጥቅም ባኚበሚ ሁኔታ እንዲሁም በማስፈቀድ ዹሙዚቃው ዚቀድሞ ለዛ እና ቃናቾውን በጠበቀ መልኩ ስራውንም በኹፍተኛ ጥንቃቄ እና ዘመኑ ባፈራ቞ው ዘመናዊ ዚድምፅ መሳሪያዎቜ በመታገዝ ኹፍተኛ ወጪ ተደርጎበት እንደተሰራ ገልጿል።

"ዘንድሮ” አልበም በትዝታ ፀ በፍቅር ፀ በውለታ ዚሚዳስሱ ደሹጃቾውን ዹጠበቁ ስራዎቜ ናቾው ተብሏል።

አልበሙንም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አራት ዓመታት እና ኹፍተኛ በጀት ማውጣቱን ድምጻዊው አስታውቋል።

ድምጻዊ ፍቃዱ ትዕዛዙ ኹዚህ ቀደም በሰራ቞ው ተዛዘብን ፀ ሲያዎ ፀ እንቅልፌን ደርበህ ፀ ላይ ላዩን ፀ አብሮ አደጌ(ተፈራ ነጋሜ) እና ምነው ቀዘቀዘ በተሰኙት ስራዎቹ ይታወቃል፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚ"ፈለገ ኪን" ዚኪነጥበብ ዝግጅት ነገ ይካሄዳል

በኢትዮጵያ አይነ ስውራን ብሄራዊ ማህበር ዹሚዘጋጀው "ዹፈለገ ኪን" ሶስተኛው ዚኪነጥበብ ዝግጅት ቅዳሜ ጥቅምት 23 ኹቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ ይካሄዳል።

ባለፉት ሁለት መድሚኮቜ እንደተደሚገው ሁሉ ሶስተኛውም መርሀግብር ዓይነ ስውራንና ዹዓይነ ስውራን ወዳጆቜ á‹šáˆ†áŠ‘ ባለተሰጥዖዎቜ ዚሙዚቃ፣ ዚሥነግጥምና ዚተለያዩ ዚስነ ጜሁፍ ቜሎታዎቻ቞ውን ዚሚያሳዩበት መድሚክ ነው ተብሏል።

በዕለቱም áˆŽáˆ¬á‰µ ጞጋዬ ገብሚ መድህን  ይዘኚራሉፀ አንጋፋው ኚያኒ አያልነህ ሙላት ደግሞ ዚዕለቱ ተጋባዥ እንግዳ ሆነው እንደሚገኙ ተገልጿል።

አዘጋጆቹ "በመርሃግብሩ ላይ በመታደም ኚአይነስውራን አእምሮ ዹፈለቁ  áŠ¥áˆá‰…á£  ጥልቅ፣ ምጡቅ  ዚስነ ጜሁፍ፣ ዹሙዚቃና ዚፍልስፍና ጠለ በሚኚቶቜን ይቋደሱ " ብለዋል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ሙዚቀኛ ያምሉ ሞላና ድምጻዊ ስለሺ ታምራት ድጋሚ ዚተጣመሩበት "ሞገድ" ገሚስ አልበም ተለቀቀ

"ጣዲቄ" በተሰኘው ሙዚቃው ዹምናውቀው ድምጻዊ ስለሺ ታምራት ኚሁለገቡ ሙዚቀኛ ያምሉ ሞላ ጋር ዚተጣምሩበት "ሞገድ" ገሚስ አልበም ትላንት ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በያምሉ ሞላ ዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮቜ ደርሷል።

በዚህ ገሚስ ዹሙዚቃ አልበም ውስጥ "እንዲህ እንዲያ" ፣"አንገቶዋ"፣ "ኧሹ ጉዮ" ፣"እንዳንቺማ" ዹተሰኙ ርዕስ ዚተሰጣ቞ው ዹሙዚቃ ስራዎቜ እንደተካተቱበት ኀቚንት አዲስ ድሚገፅ ተመልክቷል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚአንጋፋው ድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ  ዹሙዚቃ ሕይወት ስንብት ትልቅ ኮንሰርት ጥር 3 እንደሚካሄድ ተሰማ

"ዚትዝታው ንጉሥ" ዹሚል ቅጜል ስም ዚወጣለት አንጋፋው ድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ á‹šáˆ™á‹šá‰ƒ ሕይወት ስንብት ትልቅ ኮንሰርት ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም በሚሊኒዹም አዳራሜ እንደሚካሄድ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

በዚህ ዚስንበት ሙዚቃ ዝግጅት በአንጋፋው ድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ ዹሙዚቃ ሕይወት ላይ ዹተዘጋጀ መጜሐፍ እንደሚመሚቅም ተነግሯል።

በኢትዮጵያ ኹ50 ዓመታት በላይ ኚልጅነቱ አንስቶ ዚአገራቜንን ሙዚቃ በተለያዩ ዚአገራቜን ቋንቋዎቜ በመዝፈን፣ ዚአገራቜንን ሙዚቃ ኹአገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደሹጃ እንዲደመጡ ያደሚገው  ዹሙዚቃ አባት ኹሙዚቃ አለም ለማሰናበት ወይም ማይኩን ሊሰቅል ሲዘጋጅ እጃቜንን አወዛውዘን መሞኘት አግባብነት ዹለውም በሚል በጆርካ ኢቚንት አዘጋጅነት ሜኝቱን በደመቀ እና በታሪክ ማስታወሻነትም ለማስቀመጥ መታሰቡን ሰምተናል፡፡

በዚህም ጥቅምት 22 ቀን  ኚጋሜ ማሕሙድ ኮሚ቎ በመሚኚብ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በሚለኒዹም አዳራሜ ደሹጃውን ዹጠበቀ ዚድምጻዊው ዚመጚሚሻ ዚህይወት ዘመን ስንብት ኮንሰርት እንደሚዘጋጅ ተነግሯል ፡፡

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌በዶ/ር ተሻለ አሰፋ ዹተፃፈው "ዚተውኔት ዝግጅት መሰሚታዊያን" መጜሐፍ በሚቀጥለው ሳምንት ለንባብ ይበቃል

ዚአዲስ እበባ ዩንቚርስቲ ዚ቎አትር ትምህርት ክፍል መምህር በሆነው በዶ/ር ተሻለ አሰፋ ዹተፃፈው "ዚተውኔት ዝግጅት መሰሚታዊያን " ዹተሰኘው መጜሐፍ በሚቀጥለው ሳምንት ለንባብ እንደሚበቃ አሳታሚው ዚሳይንስ አካዳሚ  አስታውቋል::

"ዚተውኔት ዝግጅት መሰሚታዊያን " መጜሐፍ ስድስት ምዕራፎቜፀ 364 ገጜያለው ሲሆን ፀ ስለ ተውኔት ዝግጅት ምንነት እና ጜንሰ ሐሳባዊና ተግባራዊ ብያኔዎቜ፣ ዹአዘጋጅ ማንነት፣ዚዝግጅት አላባውያን እና ዚዝግጅት ቅደም ተኚተሎቜን ዚመሳሰሉ አርእስተ ጉዳዮቜን በጥልቀት ዚሚተነትን መፅሐፍ ነው::

ዶ/ር ተሻለ አሰፋ ዚተውኔት ዝግጅት ምንነትን ለሹጅም ዓመታት በሙያው ላይ ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማድሚግ ኚልምዱ ጋር በማዋሃድ ያዘጋጀው መጜሐፍ እንደሆነ ገልፆአል::

መፅሐፉ በሙያው ላይ ለሚገኙ እንዲሁም በግልና በመንግስት ዩንቚርሲቲዎቜ ለሚያስተምሩ መምህራን እና ተማሪዎቜ እንዲሁም ሙያውን ለሚወዱ ሁሉ እንዲመቜ ተደርጎ በጥሩ ቋንቋ እንደተዘጋጀ ዚአሳታሚው ዚሳይንስ አካዳሚ አርታኢ አቶ ቎ዎድሮስ አጥላው ተናግሹዋል::

መጜሐፉ ኚሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለንባብ እንደሚበቃም ተገልፆል::

📍መሚጃው ዚይትባሚክ ዋለልኝ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚፊልም ባለሞያው በኃይሉ ዋሮ(ዋጄ) ዚክብር እንግዳ ዚሆነበት ስብሐቲዝም ዚሀሳብ ውይይት ዝግጅት ነገ ይካሄዳል።

"ምን ልታዘዝ ?" ተኚታታይ ድራማ፣"በእናት መንገድ" ፊልምን ጚምሮ በርካታ ፊልሞቜ ላይ በድርሰትና ዝግጅት ምናውቀው ዹፊልም ባለሞያ በኃይሉ ዋሮ(ዋጄ) ዚክብር እንግዳ ዚሆነበት ስብሐቲዝም 77ተኛ መድሚክ "ጥበብ እና ዘመን" በሚል ዚሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።

ውይይቱ ነገ ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም  ኹቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቀተመዛግብት እና ቀተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሜ ውስጥ ይኚናወናል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"ዚሕይወት ታሪክ" ተውኔት ዛሬ ይመሹቃል

ድርሰቱ እና ዝግጅቱ ዚነብዩ ባዬ እና ዚቢንያም ወርቁ ዹሆነው "ዚሕይወት ታሪክ" አዲስ ተውኔት ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአንጋፋው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቎አትር በልዩ ዝግጅት ተመርቆ ዘወትር አርብ መቅሚብ እንደሚጀምር ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መሹጃ ያመለክታል።

ይህ ተውኔት ኹዚህ ቀደም በሾገር ራዲዮ በሬድዮ ድራማ መልክ ቀሚቡ ዹነበሹ ሲሆን አሁን በመድሚክ ተውኔት ቅርጜ ተሰርቷል ተብሏል።

በ"ሕይወት ታሪክ" በተውኔት ላይ ቢንያም ወርቁ እና ፀደይ ፋንታሁን áˆˆáˆáˆˆá‰µ ይተውናሉ።

ተውኔቱ በነባ ጥበባት እና ኮምኒኬሜን ዹቀሹበ ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚዳዊት ፅጌ "ዳር ዳር" ነጠላ ሙዚቃ ነገ ይለቀቃል

ዚድምጻዊ ዳዊት ፅጌ "ዳር ዳር" ዹተሰኘ ርዕስ ዹተሰጠው ነጠላ ሙዚቃ ነገ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በራሱ ዚዩቲዩብ ቻናል በኩል ይለቀቃል ተብሏል።

በዚህ ዹነጠላ ሙዚቃ ስራ ላይ ድምጻዊ አብዱ ኪያር በግጥምና ዜማ ተሳትፏል። አበጋዝ ክብሚወርቅ ሺዎታ ዹሙዚቃ ቅንብሩን ሰርቷል።

ድምጻዊ ዳዊት ፅጌም ስለዚህ ዹሙዚቃ ስራው በማህበራዊ ትስስር ገፁ" እጅግ በምወደውና በማኚብሚው ታላቅ ወንድሜና ዚሙያ አጋሬ አብዱ ኪያር (ABD) ግጥምና ዜማ ደራሲነት ”ዳር  ዳር “ ዹተሰኘ አዲስ ነጠላ ዘፈን ዚሰራሁ ሲሆንፀ በአሜሪካ በነበሹን ቆይታ በ "ዹኔ ዜማ" ባንድ አጃቢነት ዚተጫወትነውንና አበጋዝ ክብሚወርቅ ሺዎታ ያቀናበሚውን ይህን ዜማ ማክሰኞ ጥቅምት 26 2017 11:00 ላይ በ Dawittsige official youtube channel ላይ እንደሚለቀቅ ስገልፅ በታላቅ ደስታ ነው"ብሏል።

በተያያዘ መሹጃም ዚድምጻዊ ዳዊት ፅጌ "ዹኔ ዜማ" ኮንሰርቱ ዚፊታቜን ህዳር 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒዹም አዳራሜ እንደሚካሄድ ኀቚንት አዲስ ሚዲያ ኚድምጻዊው ያገኘው መሹጃ ያመለኚታል።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዚድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ አልባሳትና ቁሳቁስ ለዕይታ ሊቀርብ ነው

ዚድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ አልባሳት እና ቁሳቁስ ትውልድ እንዲያዚው በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ጥናትና ምርምር ተቋም ጥቅምት 29 ቀን 2017 በክብር ይቀመጣል ተባለ፡፡

በዕለቱም ዚአርቲስቱ ቀተሰቊቜ፣ አድናቂዎቜ እና ሌሎቜ እንግዶቜ  እንደሚገኙ ዚድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ ዚመታሰቢያ ዝግጅት አስተባባሪ ኮሚ቎ አስታውቋል፡፡

ታሪካዊ ዹሆኑ እና በትውልድ ቅብብሎሜ ውስጥ ኅያው ሆነው እንዲኖሩ ኚድምጻዊያው ቀተሰቊቜ ዚተሰበሰቡ አልባሳት እና ቁሳቁሶቜንም አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ተሹክቩ ለዕይታ እንዲበቃ በባለቀትነት ይሚኚባል ተብሏል፡፡

ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠን ዚሚያስታውስ ዚፎቶ ዐውደ-ርዕይ እና ሥራቜ በዕለቱ ለታዳሚያን እንደሚቀርቡም ተጠቁሟል፡፡

📌 መሹጃው ዹፋና ነው።

ለተጚማሪው: https://t.me/EventAddis1