ሪፖርተር (Ethiopian Reporter)
38.6K subscribers
3.54K photos
191 videos
7 files
3.98K links
Ethiopian Reporter (ሪፖርተር) በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሴንተር በሳምንት ሁለቴ እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ ነው፡፡ ጋዜጣው ለነጻ ፕሬስ፣ ለነጻ ሐሳብናና ለነጻ መንፈስ መስፈን ይተጋል፡፡ Facebook: https://www.facebook.com/EThReporter Twitter: @EthioReporter LinkedIn: linkedin.com/in/ሪፖርተር-ሪፖርተር-123415146
Download Telegram
የሪፖርተር ስራዎችን በእነዚህ አማራጮች ማግኘት ይችላሉ፦
💯 Website: www.EthiopianReporterJobs.com
💯 Facebook: http://bit.ly/2mPD7EG
💯 Telegram: https://bit.ly/3exwhdn
💯 Linkedin: https://bit.ly/2XJzm45
💯 Twitter: https://bit.ly/3cuJTnF
💯 Instagram: https://bit.ly/3fCE5j1
ይጎብኙን፤ ይከተሉን፤ ላይክ ሼር ያድርጉ። እናመሰግናለን።
ዘወትር ዕረቡ የሚጠብቁት የሪፖርተር ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎችን ይዞ በገበያ ላይ ይገኛል
በድረገጻችን https://www.ethiopianreporter.com/ ላይም ያገኙታል።

----------||----------
የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር↠ https://bit.ly/35qeNwV
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/3Qb4N1M
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3p0jUQY
ቲክቶክ ↠ https://bit.ly/3Ruxsyv

የ ስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com
አይሻሻል የሚል ሙግት የገጠመው የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ማሻሻያ መፅደቅ አንድምታ

በኢትዮጵያ ፖለቲካ አዋጁ ቢሻሻል፣ ሕጉ ቢከለስና ቢለወጥ የሚል ጥያቄ ተደጋግሞ ሲሰማ እንጂ አዋጁ ባይሻሻል ይሻላል የሚል ሙግት መስማት ብዙም አልተለመደም፡፡ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. በስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለውይይት ቀርቦ በአንድ ተቃውሞ በአብላጫ ድምፅ የፀደቀው የተሻሻለው የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1374/2017 ግን፣ ባልተለመደ ሁኔታ በባለድርሻ አካላት ‹‹ባይሻሻል ይበጃል›› የሚል ተቃውሞ ሲቀርብበት ነው የታየው፡፡

ማሻሻያ አዋጁ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ነበር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ቀርቦ ለዝርዝር ዕይታ ለዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተመራው፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ኅዳር ወር ላይ የአስረጂዎች መድረክ በማዘጋጀትና ለሕዝብ ውይይት በማቅረብ በአዋጁ ላይ ምክክር አድርጎ ነበር፡፡ ለጥቂት ዓመታት ብቻ በሥራ ላይ በቆየውን...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140582/
የበዓላት መተሳሰብና መደጋገፍ በአዘቦቱም ይቀጥል!

ሕዝበ ሙስሊሙ የረመዳን ፆም አብቅቶ በኢድ አል ፈጥር፣ እንዲሁም ሕዝበ ክርስቲያኑ የሁዳዴ ፆም ተጠናቆ በትንሳዔ በዓል በማኅበረሰቡ ውስጥ በስፋት ሲስተዋሉ የነበሩ የመተሳሰብና የመደጋገፍ መልካም እሴቶች ተስፋ ሰጪ ነበሩ፡፡ የሁለቱ ታላላቅ እምነቶች ምዕመናን ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው አዛውንቶችን፣ ወላጅ አልባ ሕፃናትን፣ አቅመ ደካሞችንና ኑሮ የከበዳቸው ወገኖችን ለመደገፍ ያሳዩት ርብርብ አስደሳች ነበር፡፡ በመንግሥት፣ በግብረ ሰናይ ማኅበራትና ሰብዓዊነት በሚሰማቸው ግለሰቦች ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች ለተደረገላቸው ዕገዛ ምሥጋና ሲያቀርቡ ሁሉም ሊባል በሚችል ሁኔታ ለአገር ሰላም መሆን ምኞታቸውን ሲገልጹ ተስተውለዋል፡፡ ሰጪና ተቀባይ በእንዲህ ዓይነቱ አስደሳች ስሜት ውስጥ ሆነው ለአገር ሰላምና መረጋጋት የሚረዳ ሐሳብ የተንፀባረቀበት ዓውድ ሲፈጥሩ፣ ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ብታልፍም ተስፋ እንደማይቆረጥባት እንደ ማሳያ ይቆጠራል፡፡ ይህ ስሜት ተጠናክሮ ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140507/
ኢትዮ ፊደሊቲ ሴኪውሪቲስ ወደ ኢንቨስትመንት ባንክ የማደግ ዕቅድ እንዳለው አስታወቀ

በያሬድ ንጉሤ
በቅርቡ በሙዓለ ንዋይ ገበያ ሰነድ አከናዋኝነት (Securities Dealer) ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ ያገኘው ኢትዮ ፊደሊቲ ሴኪውሪቲስ አክሲዮን ማኅበር፣ ወደ ኢንቨስትመንት ባንክ የማደግ ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል፡፡
የባለሥልጣኑ መመርያ በተለይም በሙዓለ ንዋዮች ገበያ ሰነድ አከናዋኝ ወይም (Securities Dealer) በ25 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ባንክ በማቋቋም መሥራት እንደሚቻል እንደሚፈቅድ የተቋሙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ አበባው ዘውዴ አስታውሰዋል፡፡
ኢትዮ ፊደሊቲ ሴኪውሪቲስ አክሲዮን ማኅበር ይህንን ዕቅዱን ያስታወቀው ትናንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሲሆን፣ ከዚሁ ጎን ለጎን ባካሄደው የመጀመሪያው የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ላይ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሴኪውሪቲስ ዲለር (የሙዓለ ንዋዮች ገበያ ሰነድ አከናዋኝ ፈቃድ) ማግኘቱንም ገልጿል፡፡
ኢትዮ ፊደሊቲ በፋይናንስ ዘርፍ ልምድና...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140574/
የኢትዮጵያን የዋጋ ግሸበት ወደ ነጠላ አኃዝ የማውረድ ትልም ከ2028 በፊት አይሳካም ተባለ


የበጀት ድጋፍ መቀነስ ተግዳሮት ይኖረዋል ተብሏል

የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በተያዘው እ.ኤ.አ. 2025 ሃያ በመቶ ሆኖ እንደሚቀጥልና ወደ ነጠላ አኃዝ የመውረድ ዕድሉ እ.ኤ.አ. በ2028 ሊሆን እንደሚችል፣ የዓለም የገንዘብ ድርጅትን ጠቅሶ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የልማት ድርጅት አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን የ2025 የሦስት ወራት የኢኮኖሚ ሁኔታ በተመለከተ ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ የውጭ ምንዛሪ ክምችት 3.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ መድረሱንና ለአንድ ወር ከ18 ቀናት ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች ወጪ መሸፈኛ ይሆናል ብሏል፡፡
የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ከጎረቤት አገሮች በተለይም ከኬንያ፣ ከታንዛኒያና ከኡጋንዳ ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑን የሚያብራራው ሪፖርቱ፣ በብሔራዊ ባንክ የባንኮች የብድር ጣሪያ ከተወነ በኋላ ወደ ኢኮኖሚው እየገባ ያለው ብድር እየቀነሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ ለአብነት እ.ኤ.አ. በ2023 በየወ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140515/
‹‹አሥር ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ረሃብ ተጋርጦባቸዋል›› የዓለም የምግብ ፕሮግራም

በአዲስ ጌታቸው
አሥር ሚሊዮን ኢትዮጵያን ረሃብ እንደተጋረጠባቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ትናንት ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ፡፡ በመላው ኢትዮጵያ ለከፋ ረሃብ ከተጋለጡት ውስጥ ሦስት ሚሊዮን ያህሉ በግጭትና በአየር ፀባይ መለዋወጥ (Extreme Weather) ከቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያው ሲረዱ የነበሩ ናቸው ብሏል፡፡
የድርጅቱ ነፍስ የማዳን ተግባራት አቅም በመዋዕለ ንዋይ እጥረት የተነሳ እጅግ መዳከሙን ያወሳው የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ ከአሥር ሚሊዮን ረሃብተኞች 3.5 ሚሊዮን ያህሉ እጅግ ተጠቂ ተብለው የተያዙና ዕርዳታ ከእነ አካቴው ሊቋረጥባቸው እንደሚችል አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ ከፈረሰ በኋላ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ዕርዳታ የማድረስ አቅሙ በእጅጉ እንደተጎዳ በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140520/
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከማዕድን ኢንቨስትመንት በነፃ አክሲዮን እንዲኖረው የሚያስገድድ ደንብ ሥራ ላይ አዋለ


የክልሉን መሬት ለማዕድን ሥራዎች ክፍት የማድረግ ሥልጣን ለአስተዳደሩ ይሰጣል

ከሦስት ሳምንታት በፊት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሆነው በተሾሙት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ተፈርሞ፣ በክልሉ ሥራ ላይ የዋለው የማዕድን አስተዳደርና የተለያዩ የማዕድን ሥራዎች ክፍያና ፈቃድን ለመወሰን የወጣ ደንብ፣ ከማንኛውም ባለፈቃድ አነስተኛና ከፍተኛ ደረጃ የማዕድን ኢንቨስትመንት ሥራ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ አምስት በመቶ (5%) የአክሲዮን ድርሻ ያለ ምንም ክፍያ በነፃ መያዝ የሚያስችለውን አስገዳጅ ድንጋጌ ሥራ ላይ አዋለ።
በፕሬዚዳንቱ ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ተፈርሞ የጸደቀውን ደንብ ሪፖርተር የተመለከተው ሲሆን፣ ለክልሉ መሬትና ማዕድን ቢሮ ከተጻፈ ደብዳቤ ጋር ተያይዞ የቀረበው ደንብ፣ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ለአስተዳደሩ ካቢኔ ቀርቦ መፅደቁን የሚገልጽ ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከፈረሙበት ዕለትም ጀምሮ በሥራ ላይ መዋሉን ይገልጻል።
ከዚሁ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140517/
#ማስታወቂያ

Appilikeeshinii Dijiitaal Baankiingii Baankii Siinqee 'Play Store' irraa  buufachuun ammuma galmaa'aa, tajaajila isaa jalqabsisaa.

የሲንቄ ባንክ የዲጅታል ባንኪንግ መተግበሪያን ከplay store በማውረድ አሁኑኑ ይመዝገቡ፣ አገልግሎቱን ያስጀምሩ!

#Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan
#Siinqee_Bank    #Baankii_Siinqee    #ሲንቄ_ባንክ
#EMPOWERED_TOGETHER
የፖፕ ፍራንሲስ ሥርዓተ ቀብር ቅዳሜ ይፈጸማል


በአዲስ አበባ ዓርብና ቅዳሜ የጸሎት መርሐ ግብር ይካሄዳል

የፖፕ ፍራንሲስ ሥርዓተ ቀብር ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. እንደሚፈጸም የቫቲካን የቅድስት መንበር ፕሬስ ክፍል አስታውቋል፡፡
ከ1.4 ቢሊዮን በላይ ካቶሊካውያን መሪ የነበሩት ፖፕ ፍራንሲስ ባደረባቸው ሕማም ምክንያት በ88 ዓመታቸው ያረፉት ሚያዝያ 13 ቀን ነበር፡፡
‹‹ክርስቶስ የሚወዳቸውን ታላቅ አባታችንን በትንሣኤው ማግስት ወደ ዘለዓለማዊ ማረፊያው ወስዷቸዋል፤›› በማለት የሐዘን መልዕክት ያስተላለፈችው የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡



የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ የፖፑን ዜና ዕረፍት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የትንሣኤ በዓል መልካም ምኞታቸውንና ለዓለም ሰላም ያላቸውን ፍላጎት በቫቲካን ቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ በመገኘት ለመላው ምዕመናን ማስተላለፋቸውን አስታውሰው፣ ሰኞ ጧት በሮም ሰ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140562/
የሪፖርተር ጋዜጠኛ ታሰረ

የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ ጋዜጠኛ አበበ ፍቅር ታሰረ፡፡ ጋዜጠኛ አበበ የታሰረው ትናንት ሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት አካባቢ ነው፡፡

ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው ከልደታ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች መረጃ በማሰባሰብ ላይ እያለ ሲሆን፣ የታሰረበት ምክንያት እስካሁን ግልጽ አልሆነም፡፡ ጋዜጠኛ አበበ በዕለቱ በፖሊሶች ተይዞ ከመወሰዱ በስተቀር በወቅቱ ወዴት እንደተወሰደና እንደታሰረ ባለመታወቁ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት በማድረግ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባደረገው ትብብር ጋዜጠኛው በልደታ ክፍል ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጌጃ ሰፈር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩ ታውቋል፡፡

ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው እየሠራው ለነበረው ዘገባ ሚዛኑን ለመጠበቅ፣ የክፍለ ከተማውን ኃላፊዎች ለማነጋገር በሥፍራው በተገኘበት ወቅት ነበር፡፡
የጤና ባለሙያዎችን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል የመንግሥት ኃላፊነት ብቻ አለመሆኑ ተነገረ

የጤና ባለሙያዎች ያሉባቸው ችግሮች እንዲቀረፉ፣ ኑሯቸው እንዲሻሻልና ፍላጎታቸው ተሟልቶ ኅብረተሰቡን በሚፈለገው ልክ እንዲያገለግሉ ማድረግ ከመንግሥት የሚጠበቅ ኃላፊነት ብቻ አለመሆኑ ተነገረ፡፡
ይህ የተነገረው፣ ድሮጋ ፋርማ የተባለ ድርጅት የጤና ባለሙያዎችን ችግር ያቃልላል ያለውን የብድርና ቁጠባ ተቋም መመሥረቱን ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው፡፡
በጤና ሚኒስቴር የሕክምና አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኢሉባቦር ቡኖ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ የጤና ባለሙያዎች ከክፍያ ማነስ የተነሳ አገራቸውን ጥለው እንዳይሄዱና ኅብረተሰቡንም በቅንነት እንዲያገለግሉ የሚያስፈልጓቸው ነገሮች ሊሟሉላቸው ይገባል፡፡ የጤና ባለሙያዎች ፍላጎቶቻቸው እንዲሟሉና ኑሯቸው እንዲሻሻል ማድረግ የመንግሥት ኃላፊነት ብቻ አለመሆኑንም ገልጸዋል፡፡
‹‹አብዛኛዎቹ የጤና ባለሙያዎች ትምህርታቸውን የተከታተሉት ብዙ ችግርና ውጣ ውረዶችን አልፈው ነው፡፡›› ያሉት ሥራ አስፈ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140512/
አጎዋ በመታገዱ ከኢትዮጵያ ምርት መቀበል ያቆሙ ኩባንያዎች ለመመለስ እየጠየቁ መሆናቸው ተነገረ


ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አሜሪካ በጣለች ቀረጥ ላይ ጥናት እያደረግኩ ነው ብሏል

በሳሙኤል አባተ
በአሜሪካ ከኮታና ታክስ ነፃ ዕድል (አጎዋ) ዕገዳ ምክንያት ከኢትዮጵያ ምርት መቀበል ያቆሙ ኩባንያዎች እንደገና ለመመለስ እየጠየቁ መሆናቸው ተገለጸ። እ.ኤ.አ. በ2021 በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት፣ ኢትዮጵያ ከአጎዋ በመታገዷ ምክንያት ወደ አሜሪካ ገበያዎች ምርቶችን በነፃ መላኳ መቅረቱ ይታወሳል።
አሜሪካ ከአንድ ወር በፊት ኢትዮጵያን ጨምሮ በ60 አገሮች ላይ እስከ 245 በመቶ ታሪፍ ጥላለች። ኢትዮጵያ አሥር በመቶ ታሪፍ ሲጣልባት መንግሥት ይህን ቀረጥ እንደ መልካም አጋጣሚ እወስደዋለሁ ሲል፣ አምራቾች ደግሞ ቀረጡን በሥጋትና እንደ ጥሩ ዕድል እንደሚያዩት ተናግረዋል።
በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች አዲሱ የአሜሪካ ታሪፍ በአጎዋ ዕገዳ ምክንያት እንደገና ወደ ኢትዮጵያ ፊታቸውን እንዲያዞሩ ማድረጉ ተገልጿል። በአጎዋ ዕድ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140525/
ማዕድ ከማጋራት ባለፈ

ሃይማኖታዊ በዓላትን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች የኢኮኖሚ ውስንነት ላለባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች የምግብ፣ የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍን ሲያበረክቱ ይስተዋላሉ፡፡
ሚያዝያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም. በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተከበረውን የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ግለሰቦችና ተቋማት በልዩ ልዩ ችግር ውስጥ ሆነው በዓሉን ለሚያሳልፉ አቅመ ደካሞች፣ ወላጅ ላጡ ሕፃናት እንዲሁም በማረሚያ ቤት ለሚገኙ ሰዎችና ጎዳና ላይ ለወደቁ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል፡፡
የኤንኤምሲ ሪል ስቴት በዓሉን ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ ካደረጉ ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ሁለት መቶ አቅመ ደካሞችንና ሦስት መቶ ወላጅ ያጡ ሕፃናትን በማሰባሰብ በዓሉን በጋራ አስበው ውለዋል፡፡
ቱሉ ዲምቱ በሚገኘው የድርጅቱ የግንባታ ቦታ ላይ የማዕድ ማጋራትና የተለያዩ የበዓል ስጦታዎችን ማበርከታቸውን የኤንኤምሲ ሪስ ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140547/
ከዩክሬን እስከ ኮንጎ የዘለቀው የትራምፕ የማዕድን ፍለጋ

ባለፈው ሳምንት ከተከሰቱና የዓለም አቀፉን መገናኛ ብዙኃን ቀልብ ከገዙ ክስተቶች መካከል አንደኛው፣ አሜሪካ የጓጓችለትንና ብዙ የተባለለትን የማዕድን ውል ለማሰር መንደርደሪያ የሚሆን የመግባቢያ ስምምነት ከዩክሬን ጋር መፈራረሟ ነው፡፡ ይህ ስምምነት ወደ ይፋዊ የማዕድን ውል አድጎ የሚፈጸምበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ባይሆንም፣ ሁለቱ አገሮች ቀጣይ በሆነ የድርድር ሒደት ውስጥ እንደነበሩ ዕሙን ነው፡፡



በውሉ ዩክሬን በምድሯ ታምቀው ያሉ ‹ሬር ኧርዝ› በመባል የሚታወቁ፣ እጀግ ውድና ወሳኝ ለሆኑ ኢንዱስትሪዎች እንደ ዋና ግብዓት የሚያገለግሉ ማዕድናትን ለአሜሪካ ክፍት ታደርጋለች፡፡ በገቢው ዩክሬንን መልሶ መገንባት ዓላማው ያደረገ ፈንድ ይቋቋማል፡፡  
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዩክሬንን ሬር ኧርዝ ማዕድናት የማልማት ዕቅዳቸውን ይፋ ያደረጉት፣ ተከታታይ ያልሆነውን ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን ለመጀመር እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 20 ቀን 2025 ወደ ነጩ ቤተ መ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140550/
#ማስታወቂያ

ከባንክ ሂሳብዎ በሲቢኢ ብር ፕላስ ይክፈሉ!
***
ሲቢኢ ብር ፕላስን በመጠቀም ከባንክ ሂሳብዎ

👉 የነዳጅ ክፍያ መፈፀም⛽️
👉 ዕቃ መግዛት 🛒
👉 ለአገልግሎት መክፈል
👉 ገንዘብ መላክ
👉 ወደሲቢኢ ብር ሂሳብዎ ገንዘብ ማስተላለፍ ይችላሉ።

አንድ ጊዜ ብቻ ወደ ሚቀርብዎት ቅርንጫፍ በመሄድ የሲቢኢ ብር ሂሳብዎን ከመደበኛው የባንክ ሂሳብዎ ጋር ያስተሳስሩ፡፡
***
አሁኑኑ ወደ Google Play ወይም App Store በመግባት ሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያን ያውርዱ/ያዘምኑ
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#cbe #cbebirr #ethiopia #digitalbanking #banking #business
#ማስታወቂያ

ከሕብረት ባንክ - ይቀበሉ!

ለበዓል ከተለያየ የዓለም ክፍሎች የሚላክልዎትን ገንዘብ ከሕብረት ባንክ ይቀበሉ!

ከባንኩ ጋር ከሚሰሩ አለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች ማለትም ዌስተርን ዪኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስፋስት፣ ሪያ ፣ዳሃብሺል እና ዩፔሲ በስዊፍት ኮድ - UNTDETAA አማካኝነት ይቀበሉ፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡

🌐 ትክክለኛውን የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን ይጎብኙ፡፡

Telegram | Facebook | Instagram | LinkedIn | X | YouTube | Website

#Remittances #MoneyTrasnfer #HibretBank #Swift #SwiftCode #Bank
#ማስታወቂያ

ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የሚሰጣቸው አገልግሎቶች
=== አልፋ ለስኬትዎ ጉልህ ድርሻ! ===

📍አዲስ አበባ፣ ቦሌ  ክፍለ-ከተማ ወረዳ 3 ሽልም ህንፃ 4ተኛ ፎቅ

☎️ +251930020395 Bole Branch
      +251903441155 Adama Branch
      +251988010611 Sengatera Branch

website | Facebook |Telegram| Instagram | TikTok | X | Youtube   | LinkedIn
#ማስታወቂያ

Appilikeeshinii mobaayilaa Baankii Siinqee "play store" irraa buufachuun tajaajila baankii dhala irraa bilisaa baankii keenyaa fayyadamaa. .

የሲንቄ ሞባይል አፕሊኬሽንን ከፕሌይ ስቶር አሁኑኑ በማውረድ፣ የባንካችንን ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት በተቀላጠፈ ሁኔታ ይጠቀሙ፣

To Download
Link : url https://bit.ly/SiinqeeMB

#Siinqee_Bank    #Baankii_Siinqee    #ሲንቄ_ባንክ
#EMPOWERED_TOGETHER
በአዲስ አበባ ለጨረታ ከወጡ ቦታዎች በአራዳ ክፍለ ከተማ የቀረበው መሰረዙ ተሰማ


ከጨረታው ስድስት ቢሊዮን ብር ገቢ ይጠበቃል ተብሏል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለጨረታ ካቀረበው 18 ሔክታር መሬት ውስጥ፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ የተዘጋጀው 1.2 ሔክታር መሬት፣ መንግሥት ለልማት ስለፈለገው ሙሉ ለሙሉ ከጨረታ መሰረዙን አስታወቀ፡፡
የመሬት ልማት አስተደደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት ባንክና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ለጨረታ ከቀረቡ ዘጠኝ ክፍላተ ከተሞች ሥር ከሚገኙ ቦታዎች መካከል፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ መሬት መንግሥት ለልማት በመፈለጉ ምክንያት ከጨረታ ተሰርዟል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ በሊዝ አዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ በከተማዋ ለጨረታ ከቀረቡ ቦታዎች ውስጥ ከዚህ በፊት ሙሉ ለሙሉና በከፊል ቦታዎችን መሰረዙን አስታውሰዋል፡፡   
ለጨረታ ከቀረቡ ቦታዎች ውስጥ ካዛንቺስ የሚገኝ አንድ ቦታ በካሬ ሜት...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140509/