የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል የሚያደርገውን በረራ ማቋረጡ ተሰምቷል
የበረራ መቋረጡ “በክልሉ በሚገኙ ባንኮች እና የንግድ ተቋማት ላይ ውጥረት አስከትሏል”
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል የሚያደርገውን በረራ ማቋረጡ ተሰምቷል። የአየር መንገዱ በረራውን ማቋረጡ የተሰማው የትግራይ ኃይል እና የፌደራል መንግሥት በድጋሚ ግጭት ውስጥ ገብተዋል መባላቸው ከተዘገበ በኋላ ነው። በሁለቱ ኃይሎች እንደ አዲስ የተከሰተው ግጭት በአማራ እና ትግራይ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ነው።
ዓለም አቀፉ የዜና ምንጭ አልጀዚራ በጉዳዩ ላይ በሠራው ዘገባ “በምዕራብ ትግራይ ፀለምት በተሰኘው አካባቢ ግጭት መቀስቀሱን” አመላክቷል። የኤ አፌፍ ፒሲን ዘገባ ዋቢ ያደረገው መረጃ በግጭቱ ሳቢያ በክልሉ የተለያዩ ከተማዎች የሚደረገው በረራ መቋረጡን የደህንነት እና የዲፕሎማቲክ ምንጮች መናገራቸውን ያትታል።
የጀርመን ድምፅ በዚሁ ጉዳዩ ላይ በሰራው ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደትግራይ ክልል በረራ ማቋረጡን አረጋግጧል። ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በረራ መቋረጡን ከሰሙ በኋላ ነገሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑን ከክልሉ ከነዋሪዎች ተሰምቷል “በተለይ የምግብ እና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች መሸጫ የገበያ አካባቢዎች እንቅስቃሴ ጎልቶ እንደሚታይ” የመቐለ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ በመቐለ ከተማ የሚኖሩ የመንግስት ሠራተኛ “የአውሮፕላን በረራ መቋረጡን ተከትሎ አዲስ አበባ የሚገኙ ዘመዶቻቸው ወደ መቀሌ ለመመለስ መቸገራቸውን ተናግረዋል” ሲል ዘገባው ገልጿል። ነዋሪዋ አክለውም “የበረራው መቋረጥ በባንኮች እና የንግድ ተቋማት አካባቢ ውጥረት ማስከተሉንም” አመላክተዋል።
#Ethiopia #Tigray #EthiopianAirlines
የበረራ መቋረጡ “በክልሉ በሚገኙ ባንኮች እና የንግድ ተቋማት ላይ ውጥረት አስከትሏል”
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል የሚያደርገውን በረራ ማቋረጡ ተሰምቷል። የአየር መንገዱ በረራውን ማቋረጡ የተሰማው የትግራይ ኃይል እና የፌደራል መንግሥት በድጋሚ ግጭት ውስጥ ገብተዋል መባላቸው ከተዘገበ በኋላ ነው። በሁለቱ ኃይሎች እንደ አዲስ የተከሰተው ግጭት በአማራ እና ትግራይ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ነው።
ዓለም አቀፉ የዜና ምንጭ አልጀዚራ በጉዳዩ ላይ በሠራው ዘገባ “በምዕራብ ትግራይ ፀለምት በተሰኘው አካባቢ ግጭት መቀስቀሱን” አመላክቷል። የኤ አፌፍ ፒሲን ዘገባ ዋቢ ያደረገው መረጃ በግጭቱ ሳቢያ በክልሉ የተለያዩ ከተማዎች የሚደረገው በረራ መቋረጡን የደህንነት እና የዲፕሎማቲክ ምንጮች መናገራቸውን ያትታል።
የጀርመን ድምፅ በዚሁ ጉዳዩ ላይ በሰራው ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደትግራይ ክልል በረራ ማቋረጡን አረጋግጧል። ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ በረራ መቋረጡን ከሰሙ በኋላ ነገሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑን ከክልሉ ከነዋሪዎች ተሰምቷል “በተለይ የምግብ እና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች መሸጫ የገበያ አካባቢዎች እንቅስቃሴ ጎልቶ እንደሚታይ” የመቐለ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ በመቐለ ከተማ የሚኖሩ የመንግስት ሠራተኛ “የአውሮፕላን በረራ መቋረጡን ተከትሎ አዲስ አበባ የሚገኙ ዘመዶቻቸው ወደ መቀሌ ለመመለስ መቸገራቸውን ተናግረዋል” ሲል ዘገባው ገልጿል። ነዋሪዋ አክለውም “የበረራው መቋረጥ በባንኮች እና የንግድ ተቋማት አካባቢ ውጥረት ማስከተሉንም” አመላክተዋል።
#Ethiopia #Tigray #EthiopianAirlines
የመከላከያ ሠራዊት ዩኒፎርም በመልበስ እና ሀሰተኛ መታወቂያ በመያዝ ሰዎችን አግተው ዘረፋ ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
“ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለማምለጥ ሲሞክሩ ገደል ውስጥ ገብተው የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል”
መከላከያ ሠራዊት ዩኒፎርም በመልበስ እንዲሁም ሀሰተኛ መታወቂያ በመያዝ ሁለት የሆላንድ ዜጎችን እና ሁለት ኢትዮጵያንን አግተው ሲዘርፉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ወንጀሉን ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ ተይዘው ነው ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ ያገቷቸው የውጭ የውጭ ዜጎች እና ኢትዮጵያውያን ላይ የዝርፊያ ወንጀል በመፈጸም ላይ እንዳሉ፤ እንጦጦ ፓርክ አካባቢ በስራ ስምሪት ላይ የነበሩት ምክትል ኢንስፔክተር በሪሁን ፈንቴ እጅ ከፍንጅ ይዘው ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማስረከባቸው ፖሊስ ገልጿል።
ምክትል ኢንስፔክተር በሪሁን የፌደራል ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥርና የአደጋ ምርመራ መምሪያ ባልደረባ መሆናቸው ተመላክቷል። ወንጀሉን ሲፈጽሙ ከነበሩ ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለማምለጥ ሲሞክሩ ገደል ውስጥ ገብተው የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ባሰራጨው መረጃ ላይ አሳውቋል።
#Ethiopia #EthiopianFederalPolice #AddisAbaba #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
“ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለማምለጥ ሲሞክሩ ገደል ውስጥ ገብተው የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል”
መከላከያ ሠራዊት ዩኒፎርም በመልበስ እንዲሁም ሀሰተኛ መታወቂያ በመያዝ ሁለት የሆላንድ ዜጎችን እና ሁለት ኢትዮጵያንን አግተው ሲዘርፉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ወንጀሉን ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ ተይዘው ነው ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ ያገቷቸው የውጭ የውጭ ዜጎች እና ኢትዮጵያውያን ላይ የዝርፊያ ወንጀል በመፈጸም ላይ እንዳሉ፤ እንጦጦ ፓርክ አካባቢ በስራ ስምሪት ላይ የነበሩት ምክትል ኢንስፔክተር በሪሁን ፈንቴ እጅ ከፍንጅ ይዘው ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማስረከባቸው ፖሊስ ገልጿል።
ምክትል ኢንስፔክተር በሪሁን የፌደራል ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥርና የአደጋ ምርመራ መምሪያ ባልደረባ መሆናቸው ተመላክቷል። ወንጀሉን ሲፈጽሙ ከነበሩ ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለማምለጥ ሲሞክሩ ገደል ውስጥ ገብተው የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ባሰራጨው መረጃ ላይ አሳውቋል።
#Ethiopia #EthiopianFederalPolice #AddisAbaba #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
በትግራይ ክልል ተፈጽሟል በተባለ የድሮን ጥቃት የሰው ሕይወት አለፈ
በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መሀል በድጋሚ ግጭት ተቀስቅሷል መባሉ ከተሰማ በኋላ በድሮን ጥቃት የሰው ሕይወት ማለፉ ተነግሯል። በክልሉ እንትጮ እና ገንዳበታ በተባሉ አካባቢዎች የጭነት መኪና ላይ በተፈጸመው የድሮን ጥቃት የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ደግሞ መቁሰሉ ተሰምቷል።
ይህን ጥቃት አስመልክቶ የተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሽፋን ሰጥተውታል። ምንም እንኳን ከፌደራል መንግሥት ሆነ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጦርነት ስለመጀመሩ በይፋ አላሳወቁም። ሆኖም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ካለፈው ሳምንት እሁድ ጥር 17/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች መካከል በሚገኙ አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭቶች መቀስቀሳቸውን አስታውቋል።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ በመግለጫው ግጭት ተካሔዶበታል ሲል ከጠቀሳቸው አካባቢዎች አንዱ የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱበት “ጸለምት/ጠለምት” የተሰኘው ሥፍራ ነው። በተጨማሪ በመጋሌ እና አብአላ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን ተከትሎ የሰዎችን የሕይወት፣ የአካል ደኅንነት፣ ነጻነት እና ንብረት መብቶች ሥጋት ላይ የሚጥሉ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል።
በዚህ ሁኔታ በቀጠለው ግጭት “የፌደራል መንግሥት” የድሮን ጥቃት በማድረስ ሁለት የጭነት አይሱዙ መኪናዎችን እንዳወደመ አልጀዚራ ዘግቧል። የድሮን ቦምቡ ያረፈው "በመኪናዎቹ ጋቢና" ላይ መሆኑን የእንትጮ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተስፋይ አማረ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት አንድ አሽከርካሪ ሕይወቱ እንዳለፈ እና የተሽከርካሪው ረዳት ደግሞ ጉዳት ደርሶበት ወደ ሆስፒታል መወሰዱን አስረድተዋል።
#Ethiopia #Tigray
በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መሀል በድጋሚ ግጭት ተቀስቅሷል መባሉ ከተሰማ በኋላ በድሮን ጥቃት የሰው ሕይወት ማለፉ ተነግሯል። በክልሉ እንትጮ እና ገንዳበታ በተባሉ አካባቢዎች የጭነት መኪና ላይ በተፈጸመው የድሮን ጥቃት የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ደግሞ መቁሰሉ ተሰምቷል።
ይህን ጥቃት አስመልክቶ የተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሽፋን ሰጥተውታል። ምንም እንኳን ከፌደራል መንግሥት ሆነ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጦርነት ስለመጀመሩ በይፋ አላሳወቁም። ሆኖም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ካለፈው ሳምንት እሁድ ጥር 17/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች መካከል በሚገኙ አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭቶች መቀስቀሳቸውን አስታውቋል።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ በመግለጫው ግጭት ተካሔዶበታል ሲል ከጠቀሳቸው አካባቢዎች አንዱ የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱበት “ጸለምት/ጠለምት” የተሰኘው ሥፍራ ነው። በተጨማሪ በመጋሌ እና አብአላ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን ተከትሎ የሰዎችን የሕይወት፣ የአካል ደኅንነት፣ ነጻነት እና ንብረት መብቶች ሥጋት ላይ የሚጥሉ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል።
በዚህ ሁኔታ በቀጠለው ግጭት “የፌደራል መንግሥት” የድሮን ጥቃት በማድረስ ሁለት የጭነት አይሱዙ መኪናዎችን እንዳወደመ አልጀዚራ ዘግቧል። የድሮን ቦምቡ ያረፈው "በመኪናዎቹ ጋቢና" ላይ መሆኑን የእንትጮ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተስፋይ አማረ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት አንድ አሽከርካሪ ሕይወቱ እንዳለፈ እና የተሽከርካሪው ረዳት ደግሞ ጉዳት ደርሶበት ወደ ሆስፒታል መወሰዱን አስረድተዋል።
#Ethiopia #Tigray
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚቀጥለው ማክሰኞ ፓርላማ ሊቀርቡ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ማክሰኞ ጥር 26/2018 ዓ.ም. በፓርላማ ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ተሰምቷል።
በሕገ መንግሥቱ እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ- ምግባር ደንብ መሠረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለሥልጣናትን ለጥያቄ የመጥራት፣ የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በፓርላማ በሚኖራቸው ቆይታ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቀጥታ ሥርጭት በሚተላለፈው ውይይት፤ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ይገኛሉ ተብሏል።
#Ethiopia #EthiopianParliament #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa #AbiyAhmed #PMAbiy
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ማክሰኞ ጥር 26/2018 ዓ.ም. በፓርላማ ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ተሰምቷል።
በሕገ መንግሥቱ እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ- ምግባር ደንብ መሠረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለሥልጣናትን ለጥያቄ የመጥራት፣ የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በፓርላማ በሚኖራቸው ቆይታ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቀጥታ ሥርጭት በሚተላለፈው ውይይት፤ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ይገኛሉ ተብሏል።
#Ethiopia #EthiopianParliament #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa #AbiyAhmed #PMAbiy
መድፈኞቹ የማንችስተር ዩናይትድ እልሃቸውን ሊድስ ዩናይትድ ላይ ተወጥተዋል
ሊድስ ዩናይትድ 0-4 አርሰናል
አርሰናል ዘንድሮ ዋንጫውን ያነሳ ይሆን?
#PremierLeague #LeedsUnited #Arsenal #EPL
ሊድስ ዩናይትድ 0-4 አርሰናል
አርሰናል ዘንድሮ ዋንጫውን ያነሳ ይሆን?
#PremierLeague #LeedsUnited #Arsenal #EPL
ማንችስተር ዩናይትድ ሶስተኛ ድሉን በመደዳ ተቀዳጀ
ማንችስተር ዩናይትድ 3-2 ፉልሃም
ዩናይትድ ዘንድሮ ስንተኛ ይጨርሳል?
#PremierLeague #ManchesterUnited #Fulham #EPL
ማንችስተር ዩናይትድ 3-2 ፉልሃም
ዩናይትድ ዘንድሮ ስንተኛ ይጨርሳል?
#PremierLeague #ManchesterUnited #Fulham #EPL
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፤ በክልሉ ግጭት የተቀሰቀሰበት ምክንያት የትግራይ ኃይሎች ወደ ጸለምት አካባቢ ለመግባት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት የተፈጠረ መሆኑን ተናገሩ
ከሰሞኑ በትግራይ ኃይሎች እና በፌደራል መንግሥት መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት፤ የትግራይ ኃይሎች ወደ ጸለምት አካባቢ ለመግባት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት የተፈጠረ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደረ ወረደ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህን የተናገሩት ጉዳዩን አስመልክቶ በትግራይ ቴሌቭዥን በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባለፈው አርብ ጥር 22/2018 ዓ.ም. ባወጥው መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች መካከል በሚገኙ "አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች" ግጭቶች መቀስቀሳቸውን አረጋግጧል። ኮሚሽኑ በመግለጫው ከአንድ ሳምት በፊት ጥር 17/2018 ዓ.ም. ጀምሮ ግጭት ከተካሄደባቸው ቦታዎች አንዱ የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱበት አካባቢዎች አንዱ በሆነው “ጸለምት/ጠለምት” መሆኑን አመላክቷል። በዚህ አካባቢ የጀመረው ግጭት ምክንያት ከተፈናቃዮች አለመመለስ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ጀነራል ታደሰ ተናግረዋል።
“ወደ ላይኛው ጸለምቲ እና በትንሹም ወደ ታችኛው ፀለምቲ የተወሰነ ኃይል እንዲሻገር ተወስኗል” ሲሉ የታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውሳኔ የተከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል። ይህ ውሳኔ የተወሰነው ከተፈናቃዮች አለመመለስ ጋር በተገናኘ እንደሆነም ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ በዛሬ ዘገባ አመላክቷል።
ጀነራል ታደሰ ጸለምት አካባቢ "ሊፈርስ የሚገባው ሕገ-ወጥ አስተዳደር እየተጠናከረ" በመሄዱ ምክንያት ተደናቅፏል ያሉትን "የማንነት አደጋም" በምክንያትነት ጠቅሰዋል።
#Ethiopia #Tigray
ከሰሞኑ በትግራይ ኃይሎች እና በፌደራል መንግሥት መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት፤ የትግራይ ኃይሎች ወደ ጸለምት አካባቢ ለመግባት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት የተፈጠረ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደረ ወረደ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህን የተናገሩት ጉዳዩን አስመልክቶ በትግራይ ቴሌቭዥን በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባለፈው አርብ ጥር 22/2018 ዓ.ም. ባወጥው መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች መካከል በሚገኙ "አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች" ግጭቶች መቀስቀሳቸውን አረጋግጧል። ኮሚሽኑ በመግለጫው ከአንድ ሳምት በፊት ጥር 17/2018 ዓ.ም. ጀምሮ ግጭት ከተካሄደባቸው ቦታዎች አንዱ የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱበት አካባቢዎች አንዱ በሆነው “ጸለምት/ጠለምት” መሆኑን አመላክቷል። በዚህ አካባቢ የጀመረው ግጭት ምክንያት ከተፈናቃዮች አለመመለስ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ጀነራል ታደሰ ተናግረዋል።
“ወደ ላይኛው ጸለምቲ እና በትንሹም ወደ ታችኛው ፀለምቲ የተወሰነ ኃይል እንዲሻገር ተወስኗል” ሲሉ የታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውሳኔ የተከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል። ይህ ውሳኔ የተወሰነው ከተፈናቃዮች አለመመለስ ጋር በተገናኘ እንደሆነም ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ በዛሬ ዘገባ አመላክቷል።
ጀነራል ታደሰ ጸለምት አካባቢ "ሊፈርስ የሚገባው ሕገ-ወጥ አስተዳደር እየተጠናከረ" በመሄዱ ምክንያት ተደናቅፏል ያሉትን "የማንነት አደጋም" በምክንያትነት ጠቅሰዋል።
#Ethiopia #Tigray
“በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ፀብ የተጀመረው በትግራይ ጦርነት ወቅት የኤርትራ ሠራዊት ንጹኃን በጅምላ ሲረሽን እና ንብረት ሲዘርፍ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
በወቅቱ ለኤርትራ መንግሥት “የትግራይ ሕዝቤን አታጎሳቅሉ፣ ሀብቱን አትዝረፉ” ብዬ መልዕክት ልኬያለሁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ፀብ የጀመረው በትግራይ ጦርነት ወቅት የኤርትራ ሰራዊት “ወጣቶችን በጅምላ ሲረሽን”፣ “የግለሰቦችን ቤት ማፍረስ ሲጀምር” እና “ፋብሪካዎችን ሲነቅል እና ሲያፈራርስ” መሆኑን ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማክሰኞ ጥር 26/2018 ዓ.ም. በፓርላማ ተገኝተው ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው። ዐቢይ ማብራሪያ ከሰጡባቸው በርከት ያሉ ጉዳዮች ውስጥ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ስለተፈጠረው አለመግባባት አንዱ ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል ቅራኔ የተፈጠረው በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ምክንያት እንደሆነ ተደጋግሞ ይነገራል። ይሁን እንጂ ዐቢይ በዛሬ ማብራሪያቸው የፀቡ መነሻ የኤርትራ ሰራዊት ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ በፈጸማቸው ወንጀሎች ነው ሲሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤርትራ ሰራዊት ተፈጽሟል ብለው ከዘረዘሯቸው ወንጀሎች መካከል ንጹኃን መረሸን፣ የግለሰብ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረስ ፋብሪካዎችን ማውደም እና መስረቅ የሚሉት ይገኙበታል።
“አንዳንድ ሰዎች በኢትዮጵያ እና ከኤርትራ መካከል ችግር የተፈጠረው የኢትዮጵያ መንግሥት የቀይ ባሕር ጥያቄ ስላነሳ ነው ይላሉ፣ ያስባሉ፣ ይተነትናሉ ግን አይደለም። ፀቡ የተጀመረው ብዙዎች እንደሚያስቡት የቀይ ባሕር ጉዳይ ሲመጣ አይደለም።
#Ethiopia #Eritrea #Tigray
በወቅቱ ለኤርትራ መንግሥት “የትግራይ ሕዝቤን አታጎሳቅሉ፣ ሀብቱን አትዝረፉ” ብዬ መልዕክት ልኬያለሁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ፀብ የጀመረው በትግራይ ጦርነት ወቅት የኤርትራ ሰራዊት “ወጣቶችን በጅምላ ሲረሽን”፣ “የግለሰቦችን ቤት ማፍረስ ሲጀምር” እና “ፋብሪካዎችን ሲነቅል እና ሲያፈራርስ” መሆኑን ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማክሰኞ ጥር 26/2018 ዓ.ም. በፓርላማ ተገኝተው ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው። ዐቢይ ማብራሪያ ከሰጡባቸው በርከት ያሉ ጉዳዮች ውስጥ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ስለተፈጠረው አለመግባባት አንዱ ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል ቅራኔ የተፈጠረው በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ምክንያት እንደሆነ ተደጋግሞ ይነገራል። ይሁን እንጂ ዐቢይ በዛሬ ማብራሪያቸው የፀቡ መነሻ የኤርትራ ሰራዊት ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ በፈጸማቸው ወንጀሎች ነው ሲሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤርትራ ሰራዊት ተፈጽሟል ብለው ከዘረዘሯቸው ወንጀሎች መካከል ንጹኃን መረሸን፣ የግለሰብ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረስ ፋብሪካዎችን ማውደም እና መስረቅ የሚሉት ይገኙበታል።
“አንዳንድ ሰዎች በኢትዮጵያ እና ከኤርትራ መካከል ችግር የተፈጠረው የኢትዮጵያ መንግሥት የቀይ ባሕር ጥያቄ ስላነሳ ነው ይላሉ፣ ያስባሉ፣ ይተነትናሉ ግን አይደለም። ፀቡ የተጀመረው ብዙዎች እንደሚያስቡት የቀይ ባሕር ጉዳይ ሲመጣ አይደለም።
#Ethiopia #Eritrea #Tigray
በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ብቻ እስከ 1,000 ብር የጨመረው ፈሳሽ የምግብ ዘይት
ፈሳሽ የምግብ ዘይት ከጊዜ ወደ ጊዜ ዋጋው እየጨመረ ነው። ባለፉት ሁለት ሳምንታት እስከ 1400 ብር ይሸጥ የነብረው 5 ሊትር ዘይት አሁን ላይ 1,000 ብር ጨምሮ 2400 እየተሸጠ ይገኛል። ይህ ከፍተኛ የጋዋ ጭማሪ ከጅምላ አከፋፋዮች አንስቶ እስከ ቸርቻሪዎች ድረስ የተያያዘ መሆኑ ተመልክቷል።
ፎርቹን ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ በሠራው ተመሳስይ ዘገባ የዘይት ዋጋ የመናሩ ምክንያት ምርቱን ከውጭ የሚያስገቡ ነጋዴዎች ዋጋ በመጨመራቸው ነው ሲሉ በመርካቶ አካባቢ የሚገኙ የጅምላ አከፋፋዮች ነግረውኛል ብሏል። ከ ሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ በፊት በ 1700 እና 1800 ብር ሲሸጥ የነበረው አምስት ሊትር ዘይት እንደ ምርቱ ዓይነት እስከ 1,000 ብር ጨምሯል።
ኦርኪድ የተሰኘው 5 ሊትር ዘይት 2,200 ብር እየተሸጠ ይገኛል። 1,750 ብር ይሸጥ የነበረው ባድሪያ የተሰኘው ዘይት ደግሞ 400 መቶ ብር ጨምሮ 2,150 ብር ገብቷል። 1,700 ብር የነበረው ሰንፍላዎር ፈሳሽ የምግብ ዘይት በሳምንታት ውስጥ 2,100 ብር ገብቷል። ከዚህ በተጨማሪ ኦማር የተባለው ዘይት በ2,400 ብር ለገበያ ቀርቧል።
በዘይት ላይ የታየው ከፍተኛ ጭማሪ የነዋሪውን ሕይወት በእጅጉ እንደፈተነው ዘገባው አመላክቷል። በጉዳዩ ላይ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ካለዘይት የተሰራ ምግብ መመገብ የግድ እንደሆነባቸው ተናግረዋል። የዋጋ ጭማሪው በተመሳሳይ መልኩ ባለ 3 ሊትር ፈሳሽ ዘይት ላይም በመሆኑ አቅም ያላቸው ባለ 1 ሊትሩን ዘይት በ 450 ብር ገዝተው እየተጠቀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አስመጪዎች እንደገለጹት ከሆነ ለምርቱ መወደድ ዋና መንስዔ “የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ለተለዩ የሥራ እንቅስቃሴዎች የሚያወጡት ዋጋ መጨመሩ ነው ብለዋል።
#Ethiopia
ፈሳሽ የምግብ ዘይት ከጊዜ ወደ ጊዜ ዋጋው እየጨመረ ነው። ባለፉት ሁለት ሳምንታት እስከ 1400 ብር ይሸጥ የነብረው 5 ሊትር ዘይት አሁን ላይ 1,000 ብር ጨምሮ 2400 እየተሸጠ ይገኛል። ይህ ከፍተኛ የጋዋ ጭማሪ ከጅምላ አከፋፋዮች አንስቶ እስከ ቸርቻሪዎች ድረስ የተያያዘ መሆኑ ተመልክቷል።
ፎርቹን ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ በሠራው ተመሳስይ ዘገባ የዘይት ዋጋ የመናሩ ምክንያት ምርቱን ከውጭ የሚያስገቡ ነጋዴዎች ዋጋ በመጨመራቸው ነው ሲሉ በመርካቶ አካባቢ የሚገኙ የጅምላ አከፋፋዮች ነግረውኛል ብሏል። ከ ሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ በፊት በ 1700 እና 1800 ብር ሲሸጥ የነበረው አምስት ሊትር ዘይት እንደ ምርቱ ዓይነት እስከ 1,000 ብር ጨምሯል።
ኦርኪድ የተሰኘው 5 ሊትር ዘይት 2,200 ብር እየተሸጠ ይገኛል። 1,750 ብር ይሸጥ የነበረው ባድሪያ የተሰኘው ዘይት ደግሞ 400 መቶ ብር ጨምሮ 2,150 ብር ገብቷል። 1,700 ብር የነበረው ሰንፍላዎር ፈሳሽ የምግብ ዘይት በሳምንታት ውስጥ 2,100 ብር ገብቷል። ከዚህ በተጨማሪ ኦማር የተባለው ዘይት በ2,400 ብር ለገበያ ቀርቧል።
በዘይት ላይ የታየው ከፍተኛ ጭማሪ የነዋሪውን ሕይወት በእጅጉ እንደፈተነው ዘገባው አመላክቷል። በጉዳዩ ላይ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ካለዘይት የተሰራ ምግብ መመገብ የግድ እንደሆነባቸው ተናግረዋል። የዋጋ ጭማሪው በተመሳሳይ መልኩ ባለ 3 ሊትር ፈሳሽ ዘይት ላይም በመሆኑ አቅም ያላቸው ባለ 1 ሊትሩን ዘይት በ 450 ብር ገዝተው እየተጠቀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አስመጪዎች እንደገለጹት ከሆነ ለምርቱ መወደድ ዋና መንስዔ “የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ለተለዩ የሥራ እንቅስቃሴዎች የሚያወጡት ዋጋ መጨመሩ ነው ብለዋል።
#Ethiopia
አራተኛው ተከታታይ ድል ለቀያይ ሰይጣኖቹ
ማንችስተር ዩናይትድ 2-0 ቶተንሃም
ማንችስተር ዩናይትድ ስንተኛ ሆኖ ይጨርሳል?
#PremierLeague #ManchesterUnited #Tottenham #EPL
ማንችስተር ዩናይትድ 2-0 ቶተንሃም
ማንችስተር ዩናይትድ ስንተኛ ሆኖ ይጨርሳል?
#PremierLeague #ManchesterUnited #Tottenham #EPL
የመድፈኞቹ የድል ጉዞ ዮኬሬስን ይዞ
አርሰናል 3-0 ሰንደርላንድ
አርሰናል ዘንድሮ ስንት ዋንጫ ያነሳል? 🤔
#PremierLeague #Arsenal #Sunderland #EPL
አርሰናል 3-0 ሰንደርላንድ
አርሰናል ዘንድሮ ስንት ዋንጫ ያነሳል? 🤔
#PremierLeague #Arsenal #Sunderland #EPL
“ከመንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት በመፈፀሜ ወንድሜን ገደሉት” ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ
በቅርቡ ከመንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት የፈጸሙት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበቀል ሳቢያ ወንድማቸው መገደሉን ተናገሩ።ወንድሜ ቢገደልም “እኔ ግን ሀገር አድኛለሁ ደስታ ይሰማኛል” ብለዋል። በአማራ ክልል በትጥቅ ትግል ሲንቀሳቀስ የነበረው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋህድ) አመራር የነበሩት ማስረሻ፤ ይህን የተናገሩት ከሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
“የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን በደል” በመቃወም ከሶስት ዓመት በፊት ወደ ትጥቅ ትግል እንደገቡ የሚናገሩት ካፒቴን ማስረሻ የትጥቅ ትግሉ በሌሎች የውጭ ኃይሎች መጠለፉን በነበራቸው ቆይታ አብራርተዋል። ማስረሻ የውጭ ኃይሎች ሲሉ የጠሯቸው ግብጽን እና የሻዕቢያን መንግሥት ነው። ጽምዶ በሚል ስያሜ “በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው የፋኖ ኃይል እና ኦነግ ሸኔ ጥምረት መፍጠራቸውንም በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
“ግብጽ በዋናነት ፋይናንስ መድባ እየሰራች ነው። ህወሓት፣ ሻዕቢያ፣ ኦነግ ሸኔ እና አማራ አካባቢ ያለው አፋብን [ብሎ] ራሱን ሰይሞ እየተንቀሳቀሰ ያለ ቡድን የራሳቸውን ጥምረት ፈጥረዋል። ጽምዶ በሚል። የመጨረሻ ግቡ የዚህ ጥምረት ምንድነው ካልህ ሀገር ማፍረስ ነው” በማለት ስለ ጥምረቱ ዓላማ አስረድተዋል። ካፒቴን ማስረሻ አክለውም “ተራ ዝምብሎ የመበጥበጥ እና የአሸባሪነት ተግባር ነገር እንጂ ሕዝብ ይዞ፣ የሕዝብን ጥያቄ ይዞ የመሔድ ነገሮች አይታይም” በማለት ጽምዶ ስላሉት ግንኙነት ተናግረዋል።
ይህን የትግል አካሔድን በመቃወም፤ የአማራ ሕዝብ ጥያቄን በድርድር ለማስመለስ እና ሰላማዊ አማራጮችን ለመከተል መወሰናቸውን የሚናገሩት ማስረሻ፤ በዚህ እርምጃቸው የተቃወሙ አካላት በቤተሰባቸው ላይ የበቀል እርምጃ መወሰዳቸውን ተናግረዋል።
በቅርቡ ከመንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት የፈጸሙት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበቀል ሳቢያ ወንድማቸው መገደሉን ተናገሩ።ወንድሜ ቢገደልም “እኔ ግን ሀገር አድኛለሁ ደስታ ይሰማኛል” ብለዋል። በአማራ ክልል በትጥቅ ትግል ሲንቀሳቀስ የነበረው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋህድ) አመራር የነበሩት ማስረሻ፤ ይህን የተናገሩት ከሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
“የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን በደል” በመቃወም ከሶስት ዓመት በፊት ወደ ትጥቅ ትግል እንደገቡ የሚናገሩት ካፒቴን ማስረሻ የትጥቅ ትግሉ በሌሎች የውጭ ኃይሎች መጠለፉን በነበራቸው ቆይታ አብራርተዋል። ማስረሻ የውጭ ኃይሎች ሲሉ የጠሯቸው ግብጽን እና የሻዕቢያን መንግሥት ነው። ጽምዶ በሚል ስያሜ “በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው የፋኖ ኃይል እና ኦነግ ሸኔ ጥምረት መፍጠራቸውንም በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
“ግብጽ በዋናነት ፋይናንስ መድባ እየሰራች ነው። ህወሓት፣ ሻዕቢያ፣ ኦነግ ሸኔ እና አማራ አካባቢ ያለው አፋብን [ብሎ] ራሱን ሰይሞ እየተንቀሳቀሰ ያለ ቡድን የራሳቸውን ጥምረት ፈጥረዋል። ጽምዶ በሚል። የመጨረሻ ግቡ የዚህ ጥምረት ምንድነው ካልህ ሀገር ማፍረስ ነው” በማለት ስለ ጥምረቱ ዓላማ አስረድተዋል። ካፒቴን ማስረሻ አክለውም “ተራ ዝምብሎ የመበጥበጥ እና የአሸባሪነት ተግባር ነገር እንጂ ሕዝብ ይዞ፣ የሕዝብን ጥያቄ ይዞ የመሔድ ነገሮች አይታይም” በማለት ጽምዶ ስላሉት ግንኙነት ተናግረዋል።
ይህን የትግል አካሔድን በመቃወም፤ የአማራ ሕዝብ ጥያቄን በድርድር ለማስመለስ እና ሰላማዊ አማራጮችን ለመከተል መወሰናቸውን የሚናገሩት ማስረሻ፤ በዚህ እርምጃቸው የተቃወሙ አካላት በቤተሰባቸው ላይ የበቀል እርምጃ መወሰዳቸውን ተናግረዋል።
በድራማ የተጠናቀቀው የሊቨርፑል ሽንፈት
ሊቨርፑል 1-2 ማንችስተር ሲቲ
አርሰናሎች እንዴት ናችሁ? 🤔
#PremierLeague #Liverpool #ManCity #EPL
ሊቨርፑል 1-2 ማንችስተር ሲቲ
አርሰናሎች እንዴት ናችሁ? 🤔
#PremierLeague #Liverpool #ManCity #EPL
በኢትዮጵያ የሱዳን አማፂ ኃይሎች የሚሰለጥኑበት “ሚስጥራዊ ካምፕ” መገንባቱ ተሰማ
ከሱዳን መንግሥት ጋር እየተፋለመ ያለው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የተሰኘ ታጣቂ ቡድን የሚሰለጥንበት “ሚስጥራዊ ካምፕ” በኢትዮጵያ ተገንብቷል ሲል ሮይተርስ በሰራው የምርመራ ዘገባ ገልጿል።
በጄነራል መሐመድ ሐምዳን ደጋሎ ወይም ሄሜቲ የሚመራው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አባላት የሚሰለጥኑበት ነው የተባለው ወታደራዊ ካምፕ የገነባችው የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ መሆኑን ስማቸው ያልተገለጸ አንድ የኢትዮጵያ ባለሥልጣን ጭምሮ ከስምንት የመረጃ ምንጮች ሰምቻለሁ ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
ከኢትዮጵያ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላት የሚነገረው ኤሜሬትስ የሎጀስቲክስ እና የወታደራዊ ሥልጠና ወጪዎችንም እንደምትሸፍን በዘገባው ተመላክቷል። ሮይተርስ ሳተላይት በመጠቀም በቤኒሻንጉልጉሙዝ ክልል መንጌ በተሰኘ አካባቢ የተገነባውን ወታደራዊ ካምፕ የሚያሳዩ ምስሎችን ይፋ አድርጓል።
ከዋና ከተማዋ አሶሳ ኤርፖርት 53 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተገባው ካምፕ በርካታ ኢትዮያውያን ምልምሎችን ጭምር የሚያሰለጥኑበት ቢሆንም ከጥር ወር አንስቶ 4,300 የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኅይል አባላት ስልጠና ወስደዋል ተብሏል።
በተጨማሪ ከደቡብ ሱዳን የመጡ ዜጎችም በካምፑ ስልጠና እንደሚወስዱ ተገልጿል። ይህ የሰራዊት ማሰልጠኛ ካምፕ 10,000 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።
ይህን ካምፕ በማስገንባቱ እና በመቆጣጠር ረገድ ኃላፊነቱን የተረከቡት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የመረጃ ዋና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና መሆናቸው በዘገባው ላይ ተመላክቷል።
#Ethiopia #Sudan
ከሱዳን መንግሥት ጋር እየተፋለመ ያለው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የተሰኘ ታጣቂ ቡድን የሚሰለጥንበት “ሚስጥራዊ ካምፕ” በኢትዮጵያ ተገንብቷል ሲል ሮይተርስ በሰራው የምርመራ ዘገባ ገልጿል።
በጄነራል መሐመድ ሐምዳን ደጋሎ ወይም ሄሜቲ የሚመራው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አባላት የሚሰለጥኑበት ነው የተባለው ወታደራዊ ካምፕ የገነባችው የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ መሆኑን ስማቸው ያልተገለጸ አንድ የኢትዮጵያ ባለሥልጣን ጭምሮ ከስምንት የመረጃ ምንጮች ሰምቻለሁ ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
ከኢትዮጵያ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላት የሚነገረው ኤሜሬትስ የሎጀስቲክስ እና የወታደራዊ ሥልጠና ወጪዎችንም እንደምትሸፍን በዘገባው ተመላክቷል። ሮይተርስ ሳተላይት በመጠቀም በቤኒሻንጉልጉሙዝ ክልል መንጌ በተሰኘ አካባቢ የተገነባውን ወታደራዊ ካምፕ የሚያሳዩ ምስሎችን ይፋ አድርጓል።
ከዋና ከተማዋ አሶሳ ኤርፖርት 53 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተገባው ካምፕ በርካታ ኢትዮያውያን ምልምሎችን ጭምር የሚያሰለጥኑበት ቢሆንም ከጥር ወር አንስቶ 4,300 የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኅይል አባላት ስልጠና ወስደዋል ተብሏል።
በተጨማሪ ከደቡብ ሱዳን የመጡ ዜጎችም በካምፑ ስልጠና እንደሚወስዱ ተገልጿል። ይህ የሰራዊት ማሰልጠኛ ካምፕ 10,000 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።
ይህን ካምፕ በማስገንባቱ እና በመቆጣጠር ረገድ ኃላፊነቱን የተረከቡት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የመረጃ ዋና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና መሆናቸው በዘገባው ላይ ተመላክቷል።
#Ethiopia #Sudan
ዜና እረፍ:
የኢቤኤስ ቴሌቭዥን ዋና ስራ አስፈጻሚ እና መስራች የነበሩት አቶ አማን ፍስሃጽዮን ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 4, 2018 (February 11, 2026) ቀን ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ጣቢያው አስታወቀ።
ኢትዮትዩብ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
#EBS #Ethiopia #AddisAbaba #AmanFissehatsion
የኢቤኤስ ቴሌቭዥን ዋና ስራ አስፈጻሚ እና መስራች የነበሩት አቶ አማን ፍስሃጽዮን ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 4, 2018 (February 11, 2026) ቀን ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ጣቢያው አስታወቀ።
ኢትዮትዩብ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
#EBS #Ethiopia #AddisAbaba #AmanFissehatsion
መድፈኞቹ 2 ነጥብ ጣሉ!
ብሬንትፎርድ 1-1 አርሰናል
ከሲቲ ጋር ያላቸው ልዩነት ወደ 4 ወርዷል - አርሰናል ዘንድሮም 2ኛ ይጨርስ ይሆን?
#PremierLeague #Brentford #Arsenal #EPL
ብሬንትፎርድ 1-1 አርሰናል
ከሲቲ ጋር ያላቸው ልዩነት ወደ 4 ወርዷል - አርሰናል ዘንድሮም 2ኛ ይጨርስ ይሆን?
#PremierLeague #Brentford #Arsenal #EPL