Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ
1.72K subscribers
467 photos
1.67K links
#NewsaboutEthiopia & the #Horn
ይህ የቴሌግራም ቻናል ትኩስ ዜናዎች፣ አዝናኝ መረጃዎች፣ ትንታኔዎች እና የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የሚቀርብበት ነው።

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ አድርገው ቤተሰብ ይሁኑ።

http://youtube.com/@ethionegari
Download Telegram
የሰላሌ ህዝብን ተሳድቧል በሚል ክስ የተመሰረተበት ፓስተር ሄኖክ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ

ከሁለት ወር በፊት የሰላሌ ህዝብን "ተሳድቧል" በሚል ክስ የተመሰረተበት ፖስተር ሄኖክ ግርማ ቦሎ ኤርፖርት በፖሊስ መያዙ ተገልጿል።

ፓስተር ሔኖክ ከቆየበት አሜሪካ ወደ አዲስ አበባ ትናንት ምሽት መመለሱ የተገለጸ ሲሆን ኤርፖት ላይ በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል።

ፓስተሩ ሀይማኖታዊ ስብከት እያካሄደ እያለ የሰላሌ እና አካባቢው ማህበረሰቦችን ገጽታ የሚጎዳ ንግግር በማህበራዊ ትስስር ገጾች ከተላለፉ በኋላ የሰላሌ ፖሊስ የእስር ማዘዣ ማውጣቱ ይታወሳል።

ከዚህ የገጽታ ማጠልሸት ክስ ጉዳይ ተሳትፈዋል የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

ፓስተር ሔኖክ ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን ጉዳዩን በሽምግልና ለመፍታት ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia    #Selale #Oromia
1
ኢትዮ ቴሌኮም 85 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 85 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል። የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር የ23 ቢሊዮን ብር ብልጫ አሳይቷል ብሏል።

ድርጅቱ አጠቃላይ የደንበኞቹ ቁጥር ከ87 ሚሊዮን በላይ ደርሷልም ብሏል።

ለመንግሥት ግብር 35 ቢሊዮን ብር እንደከፈለም አስታውቋል።

በቴሌብር 2 ትሪሊዮን ብር ልውውጥ ተደርጎበታል የተባለ ሲሆን የደንበኞቹ ብዛትም ወደ 58 ሚሊዮን ደርሷል ሲሉ የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ተናግረዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia   #ethiotelecom
1👍1
ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ ፕላስቲክ ይዞ መገኘት 5 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ

ኢትዮጵያ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በሚል ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ ምርቶችን መጠቀም ከልክላለች።

ከስድስት ወር በፊት የጸደቀው ይህ አዋጅ የፕላስቲክ አምራቾች ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ ምርቶችን መጠቀም፣ ማዘዋወር እና ማምረትን ይከለክላል።

ይህን የፌስታል ምርት ሲጠቀም የተገኘ ሰውም የአምስት ሺህ ብር ቅጣት ይጣልበታል።

ይሁንና ቸርቻሪ ሱቆች እና ፕላስቲክ አምራቾች ይህ አዋጅን የተቃወሙ ሲሆን የአዋጁ መተግበሪያ ጊዜ እንዲራዘምም ሲጠይቁ ቆይተዋል።

ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ስስ ፌስታሎችን የሚተኩ ምርቶች በገበያ እንደልብ አለመኖር ትልቁ ችግር እንደሆነም ተገልጿል።

የፕላስቲክ አምራቾች በበኩላቸው ፋብሪካዎችን ለመገንባት ከፍተኛ ወጪ ማውጣታቸውን ገልጸው ቀስበቀስ ወደ ተኪ ምርቶች እንዲሸጋገሩ እና ጊዜ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ግን ከነገ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ ምርቶችን ሲጠቀም አልያም ሲያመርት የተገኘ አካል ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል ብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia    #Plasticban
1
በአማራ፣አፋርና ትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በተፈጠረው አዲስ ግጭት ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች ከተቀሰቀሰው ግጭት ጋር በተያያዘ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል።

በዚህም ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በተለይም በጸለምት/ጠለምት፣ በመጋሌ እና አብአላ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን ተከትሎ የሰዎችን የሕይወት፣ የአካል ደኅንነት፣ ነጻነት እና ንብረት መብቶች ሥጋት ላይ የሚጥሉ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ተብሏል፡፡

በተጠቀሱት አካባቢዎች የተቀሰቀሰውን ግጭት እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ ወደ ጦርነት ሊሸጋገር ይችላል የሚል ሥጋት በመፈጠሩ ሳቢያ ነዋሪዎች ‘በኮማንድ ፖስት’ ሲተዳደሩ ከቆዩት አላማጣ ከተማ እና ሌሎች አካባቢዎች የተፈናቀሉ መሆኑን እንዲሁም በሰዎች እንቅስቃሴ ላይ ገደቦች መጣላቸውን ኢሰመኮ ገልጿል፡፡

ይህ ግጭት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ተከትሎ በአካባቢዎቹ ሰፍኖ የነበረውን አንጻራዊ ሰላም እና መረጋጋት ወደ ኋላ የሚመልስ የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች ለተጨማሪ ጉዳት፣ መፈናቀል እና ሌሎች ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያጋልጥ መሆኑንም አስታውቋል፡፡ 

በመሆኑም በግጭቱ ተሳታፊ የሆኑ ሁሉም አካላት ችግሩን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ፣ በሲቪል ሰዎች እና መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃቶችን ከማድረስ እንዲታቀቡ እንዲሁም ለግጭት መነሻ የሆኑ ልዩነቶችን በሕግ መሠረት በምክክርና በመግባባት ለመፍታት በቁርጠኝነት እንዲሠሩ ኢሰመኮ አሳስቧል።

ማናቸውም እርምጃዎች የሰብአዊ መብቶች መርሖችን ያከበሩ በተለይም በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚጣሉ ገደቦች በዓለም አቀፍና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ማዕቀፎች መሠረት የሕጋዊነት፣ የጥብቅ አስፈላጊነት እና የተመጣጣኝነት መርሖችን ያከበሩ መሆናቸውን እንዲረጋገጥም ጠይቋል።

ኢሰመኮ ከመደበኛው የሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ ሥራው ጎን ለጎን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን አካላት በማነጋገር የተፈጠረው ግጭት በውይይት የሚፈታበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ጥረት እንደሚያደርግም አስታውቋል።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ማሀሙድ አሊ የሱፍ ከሰሞኑ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲከበር አሳስቧል፡፡

ሊቀመንበሩ አክለውም ህብረቱ በአሁለቱ አዋሳኝ አካባቢዎች ያለው ሰሞንኛ ሁኔታዎችን እየተከታተለ መሆኑን ገልጸው ሁሉም አካላት ግጭቱን ከማባባስ ተቆጠቡ ሲል ጥሪውን አቅርቧል፡፡

ከሰሞኑ የተፈጠሩ ግጭቶች እንዳሳሰበው የገለጸው ህብረቱ ሁሉም ወገኖች የእርስ በርስ መተማንን የሚጎዱ ድርጊቶችን ከማድረግ እና ሀሳበችን ከመሰንዘር እንዲቆጠቡም አሳስቧል፡፡።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia    #Amhara #tigray #Afar
ተጠባቂው የማንችስተር ሲቲ እና ቶትንሀም ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተካሄደ ጨዋታ ቶትንሀም በሜዳው ማንችስተር ሲቲን አስተናግዷል።

ማንችስተር ሲቲ ጨዋታውን አስቀድሞ ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች ያሸነፈ ቢመስልም ቶትንሀም ዘግይቶ ባገባቸው ሁለት ጎሎች አቻ ሆኗል።

ማንችስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል።

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ53 ነጥብ ሲመራ ማንችስተር ሲቲ በ47 ነጥቦች ሁለተኛ እንዲሁም አስተንቪላ በ46 ነጥቦች እየመሩ ይገኛሉ።

በሌላ የሊግ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከፉልሀም ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3:2 ሲያሸንፍ በ41 ነጥቦች አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#football  #manchestercity
👍1
እንግሊዝ ዜጎቿ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች

የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት ለዜጎቹ ባወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ወደ ሶስት የሰሜን ኢትዮጵያ ክልሎች ትግራይ ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና በከፊል ሶማሊ ክልል አካባቢዎች እንሳይጓዙ ብሏል።

የጉዞ ማስጠንቀቂያው የወጣው በሰሜን ኢትዮጵያ አዲስ ግጭት መከሰቱን ተከትሎ መሆኑን የገለጸው የጉዞ ማስጠንቀቂያው በተለይም ኢትዮጵያ የምትዋሰንባቸው አካባቢዎች ዜጎቿ እንዳይጓዙ ሀገሪቱ አስጠንቅቃለች።

ከወራት በፊት ካናዳ ተመሳሳይ የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማውጣቷ ይታወሳል።

ህወሀት በጠለምት እና አካባቢው ከሰሞኑ በከፈተው አዲስ ጥቃት በአካባቢው ግጭት የተቀሰቀሰ ሲሆን ከአዲስ አበባ ወደ ትግራይ ከተሞች የአውሮፕላን በረራ ተቋርጧል።

እንዲሁም በራያ እና አካባቢው ነዋሪዎች ለደህንነታቸው በመስጋት እየተሰደዱ መሆኑ ተሰምቷል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #UK
በኒጀር የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች የሽብር ጥቃት ደረሰባቸው

አየር መንገዱ እንደገለጸው ባለፈው ሃሙስ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው ጥቃት ሁለት የአስካይ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል።

ሁለቱ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር የሆነው የአስካይ  አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ከአውሮፕላን አከራዮች የተከራያቸው እና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን የተመዘገቡ ናቸው ተብሏል።

በአውሮፕላኖቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም የተላከው የቴክኒክ ቡድን ጉዳቱ መጠነኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ የገለጸው አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹ ተጠግነው በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሎሜ (ቶጎ) መቀመጫውን ካደረገው አስካይ አየር መንገድ ጋር የ40% የባለቤትነት ድርሻና የቴክኒክ አጋርነት አለው።

የአስካይ አውሮፕላኖች የሽብር ጥቃት ኢላማ የሆኑት የሀገሪቱ ጦር የተተኳሽ እና ሌሎች ወታደራዊ የጦር መሳሪያ መካዝኖች ከኤርፖርቱ አቅራቢያ በመገኘታቸው ነው ተብሏል።

በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ ናቸው የተባሉ የሽብር ቡድኖች የሀገሪቱ ጦር ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል።

የኒጀር ወታደራዊ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የሽብር ቡድኖቹ ጥቃቱን ያደረሱት በፈረንሳይ እና አይቮሪኮስት መንግስታት ድጋፍ መሆኑን አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia   #Aviation #ethiopianairlines #Niger
1
የሊቢያው አይረሴ መሪ ሙዓመር ጋዳፊ ልጅ ተገደለ

ሰይፍ አልኢስላም ጋዳፊ በሚል ስሙ የሚታወቀው እና የሊቢያው አይረሴ ፕሬዝዳንት ሙዓመር ጋዳፊ የበኩር ልጅ መገደሉ ተገልጿል።

ሰይፍ አልኢስላም አባቱ ከ15 ዓመት በፊት በተነሳ ህዝባዊ ተቃውሞ ምክንያት ከተገደለ በኋላ ህይወት ከብዳበት ቆይቷል።

ባንድ ወቅት ከአባቱ ጋር ሆኖ የሊቢያ ዋነኛ ሰው የነበረው ይህ ሰው ለዓመታት በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ተከሶ በእስር ላይ አሳልፏል።

እንደ አልጀዚራ ዘገባ ከሆነ ሰይፍ አልኢስላም በሚኖርባት የምዕራብ ሊቢያዋ ዚንታን ከተማ ውስጥ በጥይት ተገድሏል።

እስካሁን ስለ አሟሟቱ በግልጽ ይፋ የተደረገ መረጃ ባይኖርም ግድያው የተከፋፈለውን የሊቢያ ፖለቲካ የበለጠ እንደሚጎዳ ተገልጿል።

ግለሰቡ ከዚህ በፊት በሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ውድድር ላይ ለመወዳደር እጩ ሆኖ ቢመዘገብም የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን መስፈርቱን አያሟላም በሚል ከእጩነት ሰርዞታል።

ሰይፍ አል ኢስላም ሊቢያ አሁን ላለችበት ቀውስ የዳረጋትን ህዝባዊ አመጽ አስመልክቶ በወቅቱ ባደረገው ንግግር አመጹ ሊቢያን ያፈርሳታል፣ እንደገና ሀገር ለመባል ቢያንስ 40 ዓመት ሊፈጅብን ይችላል ሲል ያደረገው ንግግር አሁን ላይ በብዙዎች ይነሳል።

ሊቢያዊያን በተለይም ከሙዓመር ጋዳፊ መንግሥት መገርሰስ በኋላ የተከፋፈሉ ሲሆን አሁን ላይ እንደ ሀገር ባንድ መሪ መተዳደር አልቻሉም።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Libya  #Africa #Gaddafi
1
የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተለው የባለሙያዎች ቡድን መቐለ ገባ



ለሁለት ዓመት የዘለቀውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆም ምክንያት የሆነው የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት አፈጻጸም የሚከታተል የባለሙያዎች ቡድን ትግራይ ክልል መቐለ መግባቱ ተገልጿል።

ስምምነቱ እንዲፈረም ያደራደረው የአፍሪካ ህብረት የባለሙያዎችን ቡድን ያቋቋመው ከኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጀሪያ እና አልጀሪያ የተውጣጡ ናቸው።

ይህ የባለሙያዎች ቡድን በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታታቸውን፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቀጠላቸውን፣ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀዬአቸው መመለሳቸውን የመከታተል ሀላፊነት ተሰጥቶታል።

ዛሬ መቐለ መድረሱ የተገለጸው ይህ የባለሙያዎች ቡድን መቀመጫውን መቐለ በማድረግ የስምምነቱን አፈጻጸም ሲከታተል የቆየ ሲሆን ላለፉት ወራት በዕረፍት ላይ መቆየቱን የትግራይ ሰላምና ደህንነት ቢሮ አስታውቋል።

ይህ የባለሙያዎች ቡድን ከአስተዳድራዊ ዕረፍት በኋላ ወደ መቐለ የተመለሰው በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚነሳባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ጠለምት በትግራይ ታጣቂዎች እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል ግጭት በተከሰተ በሳምንቱ ነው።

ግጭቱን ተከትሎ ከአዲስ አበባ ወደ ትግራይ ከተሞች የደርሶ መልስ በረራዎች እንዲቆሙ አድርጓል።

ግጭቱ መቆሙን ተከትሎም በረራዎቹ ከአምስት ቀናት በኋላ ዳግም የቀጠሉ ሲሆን በራያ እና አላማጣ ከተሞች ግን ከስፍራው የለቀቀው እና አካባቢውን ሲያስተዳድር የነበረው የፌደራል ኮማንድ ፖስት እስካሁን አልተመለሰም።

ለደህንነታቸው ሰግተው ከራያ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎችን እስካሁን ወደ ቤታቸው አልተመለሱም።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በትናንትናው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ የወልቃይት ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ መኖሪያ ቤታቸው ያልተመለሱት በህወሀት የፖለቲካ መያዣ በመደረጋቸው መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia   #Africa #tigray #peace
1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ52 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከሀይል ሽያጭ ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች በአጠቃላይ 52.26 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተናግረዋል፡፡

ይህም በዕቅድ ለመሰብሰብ ከተያዘው 54.23 ቢሊዮን ብር አንፃር 96 ከመቶ አፈፃፀም ያለው መሆኑን ጨምረው አንስተዋል፡፡

ዋና ስራ አሰፈፃሚው በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከኢነርጂ ሽያጭ ብቻ 34.34 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡ ከተሰበሰበዉ 34.3 ቢሊዮን ብር ገቢ ዉስጥ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል 20.5 ቢሊዮን ብር ለኢነርጂ ግዥ ክፍያ በመፈፀም 99.5 በመቶ አፈፃፀም መመዝገቡን ገልጸዋል።

ኢንጅነር ጌቱ አክለውም ባለፉት ስድስት ወራት 266 ሺህ 916 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መደረጋቸዉን ጠቅሰዋል።

በተቋሙ የዲጂታል ክፍያ ስርአትን ለማጠናከር እየተደረገ ባለው ጥረት በኢ-ፔይምነት ክፍያ የፈፀሙት ደንበኞች ቁጥር 94.8 በመቶ መድረሱ ተገልጿል ።

ምንጭ:- ብስራት ኤፍ ኤም

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #electricity
የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ከህግ አግባብ ውጪ እየተቆረጠባቸው መሆኑን የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ገለጸ


የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም የመንግስት ሰራተኞች ለልማት እና ለኤችአይ ቪ በሚል ከህግ አግባብ ውጪ ደሞዝ እየተቆረጠባቸው መሆኑን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት በ6 ወራት ውስጥ በዕቅድ ከያዛቸው ተግባራት መካከል በ20 ጉዳዮች እና በ46 ተቋማት ላይ ቁጥጥር አድርጎል።

በተደረገው ቁጥጥር በተለዩት በ 100 የአሰራር ክፍተቶች ላይ ስምምነት የተደረሰባቸው ግኝቶች ናቸው፡፡

በዚህም  አንደኛው በፌዴራልና በተመረጡ ክልሎች በማዕድን ዘርፍ ላይ ፈቃድ መስጠት፣ ማደስ እና ማገድ ጋር በተያያዘ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የተከናወነ ቁጥጥር መሆኑን  የኢትዮጵያ  እምባ ጠባቂ የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አንለይ ወርቄ ተናግረዋል።

በዚህም ከተለዩ ክፍተቶች መካከል በአንዳንድ ክልሎች በማዕድን ዘርፉ ፈቃድ አሰጣጥ አንጻር ከተሰጣቸው ስልጣንና ተግባር ውጪ ፈቃድ የሚሰጡበት ሁኔታ መኖሩና ይህንንም ለመግታት በፌዴራል በኩል የተሰራው ስራ በቂ አለመሆኑ ተጠቁሟል።

በተለይም  በአማራ እና በትግራይ ክልሎች በብረት ማዕድን፣ ሌላው በአንዳንድ ክልሎች ከፌዴራሉ አዋጅ በሚጻረር መንገድ የራሳቸውን አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ የሚያወጡበት አካሄድ መኖሩ ተነግሯል፡፡

ሁለተኛው በፌዴራልና በተመረጡ ክልሎች በሲቪል ሰርቪስ መ/ቤቶች የመንግስት ሰራተኞች ከህግ ውጭ የሚፈጸሙ፣ ቅጥር፣ ደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር እና የደመወዝ መቆረጥ ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ አስተዳደራዊ በደሎች መሆናቸው ተገልጿል።

በዚህም የሰራተኞች የወር ደመወዛቸው በወቅቱ አለመከፈሉና በፐርሰንት እንደሚከፈል ቀሪ ክፍያቸው ደግሞ አሁንም ድረስ በተለያዩ ክልሎች፣ በአንዳንድ ዞኖች እና ወረዳዎች ያልተከፈላቸው ሰራተኞች ላይ የአስተዳር በደል እየተፈፀመ ነው። 

አክለውም የመንግስት ሰራተኞች ለተለያዩ የልማት ስራዎች በሚል የኤችአይ ቪ፣ የልማት ማህበር በሚል ያለ ሰራተኛ ፈቃድ እየተቆረጠባቸው መሆኑ ከህግ አግባብ ውጪ በአንድ የስራ መደብ መታወቂያ ቁጥር ከአንድ በላይ ቅጥር እየተፈፀመ መሆኑ የኢትዮጵያ  እምባ ጠባቂ የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አንለይ ወርቄ  አክለዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia   #ombudsman #salary
አርሰናል ፕሪሚየር ሊጉን በዘጠኝ ነጥብ ልዩነት መምራት ጀመረ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መሪው አርሰናል በሜዳው ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3:0 አሸንፏል።

የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ጎሎች ዙቢመንዲ እና ዮኬሬሽ ሁለት ጎሎችን በድምሩ 3:0 ረቷል።

አርሰናል ማሸነፉን ተከትሎ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ዘጠኝ ከፍ አድርጓል።

ማንችስተር ሲቲ ከሊቨርፑል በነገው ዕለት የሚያደርጉት ጨዋታ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ ሆኗል።

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ56 ነጥቦች ሲመራ፣ ማንችስተር ሲቲ እና አስተን ቪላ በእኩል 47 ነጥቦች ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#arsenal    #football #premiereleague
የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ



የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳስታወቀው ኤርትራ ባለፉት ቀናት አዲስ ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋልል።

ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ለኤርትራ አቻቸው ኦስማን ሳሌህ በጻፉት ደብዳቤ የኤርትራ ጦር ከአማጺያን ጋር በመተባበር በሰሜን ምስራቅ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን አስታውቋል።

ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የኤርትራ ወታደሮችም ከአማጺያን ጋር በመቀናጀት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆኑም ተገልጿል።

በመሆኑም እነዚህ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡም ጠይቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ በደብዳቤው ላይ ከኤርትራ ጋር የገቡበትን አለመግባባት በዲፕሎማሲ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነም ገልጿል።

ሚንስትሩ አክለውም በተለይ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት እና የአሰብ ወደብን ለማግኘት ያቀረበቻቸውን ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎች ፍላጎቶችን ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ለመወያየት ዝግጁ እንደሆነችም ተጠቅሷል።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሳምንት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት እንዳሉት ኤርትራ በትግራይ ክልል "ጭፍጨፋ" ፈጽመዋል ማለታቸው ይታወሳል።

እንዲሁም የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ ታጣቂዎችን የሎጅስቲክስ ድጋፍ እያደረገች እንደሆነም ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል።

ኤርትራ ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አስተያየት በሰጠችው ምላሽ ኢትዮጵያ የባህር በር ይገባኛል በሚል ሊያካሂደው ላሰበው ወታደራዊ ጥቃት ለመሰንዘር ምክንያት እያስቀመጠ እንደሆነ አስታውቃለች።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #eritrea #tplf
2
ተጠባቂው  የአንፊልድ ጨዋታ በማንችስተር ሲቲ የበላይነት ተጠናቀቀ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተካሄደ ጨዋታ ሊቨርፑል ከማንችስተር ሲቲያደረጉት ጨዋታ በሲቲ የበላይነት ተጠናቋል።

ሊቨርፑል በስቦዝላይ አስደናቂ ጎል ጨዋታውን መምራት ቢጀምርም በርናርዶ ሲልቫ እና ኧርሊንግ ሀላንድ ጎሎች አሸንፏል።

ሲቲ ጨዋታውን ማሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የጎል ልዩነት ወደ ስድስት ነጥብ ዝቅ ማድረግ ችሏል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #football #liverpool #manchestercity
ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው ልማት ባንክ እና አማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሀንስ አያሌው በኪሳራ ላይ ላለው ጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል።

የአማራ ብድርና ቁጠባ ድርጅት በሚል ሲጠራ የነበረው በኋላም ጸደይ ባንክ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያን የባንክ ቢዝነስ የተቀላቀለው ጸደይ ባንክ በኪሳራ ላይ ይገኛል።

ባንኩ በ2024/25 በጀት ዓመት ብቻ የሁለት ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ከአንድ ወር በፊት ዓመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ገልጿል።

ይህን ተከትሎም ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የባንኩ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደተሾሙለት ባንኩ ከደቂቃዎች በፊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስታውቋል።

በኪሳራ ላይ ያሉ የገንዘብ ድርጅቶችን በመታደግ የሚታወቁት ዶክተር ዮሀንስ ከዚህ በፊት ልማት ባንክን እንዲሁም የአማራ ባንክን ከኪሳራ ወደ ትርፍ መመለሳቸው ይገለጿል።

የክፉ ቀኑን መሪ ያጣው አማራ ባንክ እስካሁን በፕሬዝዳንትነት ማንን እንደሾመ አልገለጸም።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ፀደይባንክ  #Tsedeybank
ብልጽግና ምልክቱን ከአምፖል ወደ ስንዴ ዘለላ ቀየረ

ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የተጠቀመውን የምርጫ ምልክት በዘንድሮው ምርጫ ቀይሬያለሁ ብሏል።

ፓርቲው ከዚህ በፊት ይታወቅበት የነበረውን አምፖል ምልክት ወደ ስንዴ ዘለላ ቀይሯል።

የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እንደገለጹት በሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚወዳደር ገልጸዋል።

ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የፊታችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

ፓርቲዎች በዚህ ምርጫ ላይ የሚወዳደሩ እጩዎቻቸውን በማስመዝገብ ላይ ናቸው።

የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገሪቱ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል የጸጥታ ሁኔታ እንደሌለ እየገለጹ ይገኛሉ።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #Prosperityparty #election2026
2
የኢቢኤስ ቲቪ መስራቹ አማን ፍስህጽዮን ህይወታቸው አለፈ

በኢትዮጵያ ሚዲያ ታሪክ ተወዳጅ ከሆኑ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች መካከል አንዱ የሆነው ኢቢኤስ ቲቪን መስርተው በስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የነበሩት አቶ አማን ፍስሀጽዮን ህይወታቸው ማለፉን ሚዲያቸው ኢቢኤስ ቲሺ ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ አቶ አማን ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አልፏል።

አቶ አማን የኢትዮጵያ ብሮድካስተሮች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉም ቆይተዋል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #EBStv #Aman
ኢትዮጵያዊያን በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ዘመዶቻቸው እስከ 3 ሺህ ዶልር እንዲልኩ ተፈቀደ

ብሔራዊ ባንክ ውጭ ምንዛሬን አሰመልክቶ ያደረጋቸውን ዝርዝር ማሻሻያዎች ይፋ አድርጓል፡፡

በማሻሻያው ከተጠቀሱ ጉዳዮች መካከል ኢትዮጵያዊን በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዘመዶቻቸውን ለመደጎም እስከ 3 ሺህ ዶላር ድረስ መላክ እንደሚችሉ ተፈቅዷል፡፡

ሌላኛው ማሻሻያ የተደረገበት ጉዳይ በኢትዮጵያ የተሰማሩ የውጭ ኢንቨስተሮች በትርፍ ክፍፍል ያገኙትን ምንዛሬ ከሀገር እንዲያስወጡ ፈቅዷል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በውጭ ሀገር ለሚደረጉ የትምህርት እና ህክምና አገልግሎቶች እስከ 20 ሺህ ዶላር ድረስ መፈቀዱን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡

እንዲሁም ኢትዮጵያዊን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊን የውጭ ምንዛሬ ቁጠባ ሂሳብ ለመክፈት ይጠየቁት የነበረው አነስተኛ 100 ክፍያ እንዲቀር ተደርጓል ተብሏል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #nationalbank #Forex #NBE
ለኤሌክትሪ አገልግሎት ሚውሉ መሰረተ ልማቶች ውስጥ 80 በመቶውን በሀገር ውስጥ እንደሚመረቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት 80 በመቶ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶችን ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች አሟልቻለሁ ብሏል።

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ለመገንባትና ለማስፋፋት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ ሲሆን፤ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ጥራታቸውን የጠበቁ የተለያዩ ግብዓቶችን ለሀገር ውስጥ አቅራቢዎች ቅድሚያ በመስጠት እንዲያቀርቡ ማድረጉን ገልጻል፡፡ 

ይህም መንግስት የጀመረውን ሃገር-በቀል ኢኮኖሚን ለማበረታታና የሃገር ውስጥ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት አገልግሎቱ ከወሰዳቸው ትልቅ እርምጃዎች ዋንኛው ነው ብሏል፡፡ 

ከቀረቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶች የዲስትሪቡዩሽን ትራንስፎርመር አንዱ ሲሆን፤ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ 3 ሺህ 944 ትራንስፎርመሮች ከሃገር ውስጥ አምራቾች ቀርበው አገልግሎት ላይ እንደዋሉ ተቃሙ አስታውቋል፡፡ 

በተመሳሳይ ከ32 ሺህ በላይ ኢንሱሌተሮች፣ ከ97 ሺህ በላይ የትራንስፎርመር ፕሮቴክሽን እቃዎችን፣ ከ32 ሺህ ሜትር በላይ ኮንዳክተርና ኬብሎችንና ከ201 ሺህ በላይ የተለያዩ የሀርድዌር ዕቃዎች በሀገር ውስጥ አቅርቦት ተሸፍኗል ተብሏል፡፡

አገልግሎቱ የአገር ውስጥ አምራቾችን በማበረታታት ጥራት ያለው ግብዓት እንዲያቀርቡ የቴክኒካል እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጾ አምራቾችም ከአገልግሎቱ ጋር ውል በመዋዋል የግብዓቶች ጥራት እየተረጋገጠ እያቀረቡ መሆኑም ተጠቅሷል።

አገልግሎቱ ከደንበኞች ለሚቀርቡለት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ጥያቄ በፍጥነት እንዳይመልስ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ የግብዓት አቅርቦት ውስንነት ሲሆን  ከሃገር-በቀል አምራቾች በመቀበል እየሰራ መሆኑንም አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #electricity
1
ለጋብቻም ሲኦሲ ግዴታ ሊሆን ነው?

የኢትዮጵያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚንስቴር እየጨመረ የመጣው የትዳር መፍረስን ለመግታት መፍትሔ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

እንደ ሚንስቴሩ መረጃ ከሆነ ለአዲስ ተጋቢዎች የጋብቻ ስልጠና መውሰድን እንደ ግዴታ የሚቆጥር ረቂቅ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።

በረቂቅ መመሪያው ላይ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ከተወያዩበት በኋላ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ሊተገበር እንደሚችልም ተገልጿል።

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፍቺ የሚደመደሙ ትዳሮች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን ተጋቢዎች ስለ ትዳር በቂ እውቀት አለመያዝ ለፍቺው ዋነኛው ምክንያት እንደሆነም ይነሳል።

ቤተሰብ ለሀገር እና ትውልድ አለኝትል ሲሆን በትዳር መፍረስ ምክንያት ተጋቢዎችን ለኢኮኖሚ ድቀት እና ለማህበራቂ ቀውስ ሲዳርግ ልጆችን ለውስብስብ ጉዳቶች ያጋልጣል።

በእርስዎ አመለካከት ለትዳር መፍረስ ዋና ዋና ምክንያቶች ምን ምን ናቸው?

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

  #ethiopia #Family #marriages #divorce