Covenant Hub Law Firm LLP
197 subscribers
36 photos
4 videos
2 files
44 links
Make difference
Download Telegram
💡 የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ ሥርዓት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1142/2018

የታክስ አስተዳደር ሥርዓትን ማዘመንና ከወቅቱ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር ማጣጣም የአንድ አገር ኢኮኖሚ በጤናማ ሁኔታ ለመራመድ ካሉት መሠረታዊ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ይሁን እንጂ ይህ መመሪያ እስካሁን ሳይወጣ መቆየቱ በታክስ አሰባሰብ፣ በዲጂታል ንግድ ቁጥጥርና በሕግ ተፈጻሚነት ረገድ በርካታ መዋቅራዊ ክፍተቶችን ፈጥሮ ቆይቷል።

በተለይም ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው የኢኮሜርስ (e-Commerce) ዘርፍ፣ የኦንላይን የገበያ መድረኮች እና የተለያዩ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ግልጽና ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ስላልነበራቸው መንግሥት ማግኘት የሚገባውን የታክስ ገቢ እንዲያጣ ከማድረጉም በላይ ሕጋዊ ታክስ ከፋዮች ካልተመዘገቡ ነጋዴዎች ጋር ፍትሐዊ ያልሆነ የገበያ ውድድር ውስጥ እንዲገቡ አስገድዶ ነበር። በተጨማሪም የወረቀቱ የደረሰኝ አሰጣጥ ሥርዓት ለታክስ ስወራ፣ ለሐሰተኛ ደረሰኝ ዝውውርና ለአሠራር መጓተት ሰፊ በር ከፍቶ መቆየቱ ይታወቃል።

ይህ አዲስ የወጣው መመሪያ ቁጥር 1142/2018 እነዚህን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የሚከተሉት ከፍተኛ ፋይዳዎች አሉት፦
💡 የታክስ ስወራን መከላከልና ገቢን ማሳደግ፡ እያንዳንዱ ግብይት በተከናወነበት ቅጽበት (Real-time) በቀጥታ ከባለሥልጣኑ ማዕከላዊ ሥርዓት ጋር እንዲገናኝ በማድረጉ እና ደረሰኝ ማተም የሚቻለው የማዕከሉን መለያ ቁጥር (IRN) እና QR Code ሲያገኝ ብቻ በመሆኑ ሐሰተኛ ደረሰኞችን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
💡 ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግልጽ የሕግ ማዕቀፍ መፍጠር፡ መመሪያው የኢኮሜርስ ኦፕሬተሮችን፣ የክላውድ ሽያጭ መመዝገቢያዎችን እና ሶፍትዌርን እንደ አገልግሎት አቅራቢዎችን ሕጋዊ ኃላፊነት በግልጽ አስቀምጧል። በአንድ መድረክ ላይ ከአንድ በላይ ሻጮች ቢኖሩ እንኳ እያንዳንዱ አካል በገዛ የ-TIN ቁጥሩ ደረሰኝ እንዲቆርጥ በማስገደድ በዲጂታል ገበያው ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
💡 የንግድ አሠራርን ማቅለልና ወጪን መቀነስ፦ ታክስ ከፋዮች የሽያጭ መረጃዎችን በዲጂታል አማራጮች (በኢሜይል ወይም በ-SMS) ለገዥዎች መላክ እንዲችሉ በመፍቀድ የሕትመትና የካርቦን ወጪን ከመቀነሱም በላይ ንግዶች የራሳቸውን የውስጥ ሥርዓት ከታክስ ሥርዓቱ ጋር በቀላሉ እንዲያዋህዱ ዕድል ይሰጣል።
💡 የመረጃ ደህንነትና የኦዲት ተአማኒነት፡ ሥርዓቱ ከመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ዕውቅና ማግኘት ያለበት በመሆኑ እና የኦዲት መዝገብ (Audit Log) እንዲኖረው ስለሚያስገድድ፣ የታክስ ከፋዩ መረጃ በምስጠራ (Encryption) ተጠብቆ እንዲቆይና ባለሥልጣኑ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ሕጋዊ ኦዲት እንዲያደርግ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
💡 የአሠራር ቀጣይነትን ማረጋገጥ፡ የኢንተርኔት መቆራረጥ በሚኖርበት ጊዜ ንግዶች እንዳይደናቀፉ የራሱ የሆነ "ከቀጥታ ግንኙነት ውጭ ሥራ ማስቀጠያ ሥርዓት" (Offline Resiliency) መዘርጋቱ የንግድ እንቅስቃሴው ሳይቋረጥ ታክስ በአግባቡ እንዲመዘገብ ያስችላል።

በአጠቃላይ ይህ መመሪያ መውጣቱ በታክስ አስተዳደሩ ላይ የነበሩትን ክፍተቶች በመሙላት የዲጂታልና የሕግ ሥነ-ምኅዳሩን በማቀናጀት፣ ፍትሐዊ የንግድ ውድድር እንዲሰፍንና የአገሪቱ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ሕጋዊ መሠረት እንዲይዝ የሚያደርገው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው።
ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት
2
258350 (1).pdf
1.1 MB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 258350 የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ስለንግድ ማኅበር መፍረስ የሰጠው ውሳኔ
📌 ሕግና ሕንጻ፡ የኮንስትራክሽን ውሎች ስንክሳርና የ«ፎርሙላው» ሚስጥር!
ክፍል ፡ ፪
በቢሊዮን የሚቆጠሩ የሃገራችን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች በሕግ ክርክርና በመዘግየት የሚታመሱት ለምንድን ነው? ውስብስብ የሆኑ የኮንስትራክሽን ውሎችን በቀላሉ የምንፈታበት «ቀመር» ይኖረው ይሆን?
በዚህ ሳምንት በ«ዲጂታል ነጋሪት» የሬዲዮ ፕሮግራማችን በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ሕግ ዘርፍ ግንባር ቀደም የሆኑትን እውቅ የሕግ ባለሙያና መምህር አቶ ዘውዱ ተፈራን ይዘንላችሁ እንቀርባለን።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እስከ ጀርመን ማርቲን ሉተር ዩኒቨርሲቲ የዘለቀው የሙያ ጉዟቸው፣ በፓሪስ ፍርድ ቤቶች የነበራቸው ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት (Arbitration) ተሞክሮ እና ለዘርፉ ያበረከቱት ልዩ የሕግ «ፎርሙላ» ምን እንደሆነ በሰፊው ያጋሩናል።
💡 በውይይታችን ከሚዳሰሱ ነጥቦች፡-
• በኮንስትራክሽን ውሎች ላይ በብዛት የሚሰሩ ገዳይ ስህተቶች
• የዋጋ ንረት እና የሥራ ለውጦች (Variation) በሕግ አግባብ እንዴት ይስተናገዳሉ?
• አለመግባባቶችን በፍርድ ቤት ፈንታ በአማራጭ ሙግት መፍቻ (ADR) መፍታት ያለው ጥቅም!
የኮንስትራክሽን ባለሀብቶች፣ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሐንዲሶችና የሕግ ባለሙያዎች መረጃ እና እውቀት የምታገኙትበት ውይይት ይዘን ቀርበናል!
📅 እሁድ፣ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
🕖 ከቀኑ 7፡00 – 8፡00 ሰዓት
📻 በአራዳ ኤፍኤም 95.1
ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት ከአራዳ ኤፍኤም 95.1 ጋር በመተባበር ያቀርባል።
📢 ዲጂታል ነጋሪትን ይከታተሉ፤ እውቀትዎን ያዳብሩ!
1👎1
📌 ሕግና ሕንጻ፡ የኮንስትራክሽን ውሎች ስንክሳርና የ«ፎርሙላው» ሚስጥር!
ክፍል ፡ ፫
በቢሊዮን የሚቆጠሩ የሃገራችን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች በሕግ ክርክርና በመዘግየት የሚታመሱት ለምንድን ነው? ውስብስብ የሆኑ የኮንስትራክሽን ውሎችን በቀላሉ የምንፈታበት «ቀመር» ይኖረው ይሆን?
በዚህ ሳምንት በ«ዲጂታል ነጋሪት» የሬዲዮ ፕሮግራማችን በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ሕግ ዘርፍ ግንባር ቀደም የሆኑትን እውቅ የሕግ ባለሙያና መምህር አቶ ዘውዱ ተፈራን ይዘንላችሁ እንቀርባለን።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እስከ ጀርመን ማርቲን ሉተር ዩኒቨርሲቲ የዘለቀው የሙያ ጉዟቸው፣ በፓሪስ ፍርድ ቤቶች የነበራቸው ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት (Arbitration) ተሞክሮ እና ለዘርፉ ያበረከቱት ልዩ የሕግ «ፎርሙላ» ምን እንደሆነ በሰፊው ያጋሩናል።
💡 በውይይታችን ከሚዳሰሱ ነጥቦች፡-
• በኮንስትራክሽን ውሎች ላይ በብዛት የሚሰሩ ገዳይ ስህተቶች
• የዋጋ ንረት እና የሥራ ለውጦች (Variation) በሕግ አግባብ እንዴት ይስተናገዳሉ?
• አለመግባባቶችን በፍርድ ቤት ፈንታ በአማራጭ ሙግት መፍቻ (ADR) መፍታት ያለው ጥቅም!
የኮንስትራክሽን ባለሀብቶች፣ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሐንዲሶችና የሕግ ባለሙያዎች መረጃ እና እውቀት የምታገኙትበት ውይይት ይዘን ቀርበናል!
📅 እሁድ፣ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
🕖 ከቀኑ 7፡00 – 8፡00 ሰዓት
📻 በአራዳ ኤፍኤም 95.1
ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት ከአራዳ ኤፍኤም 95.1 ጋር በመተባበር ያቀርባል።
📢 ዲጂታል ነጋሪትን ይከታተሉ፤ እውቀትዎን ያዳብሩ!
👍5
በኮንስትራክሽን ሕግ እና ወሎች ዙሪያ ከ40 ዓመት በላይ የማማከር ልምድ ካላቸው አቶዘውዱ ተፈራ ወርቄ ጋር ላለፉት ሶስት ሳምንት ውይይት ስናደርግ ነበር፡፡ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ሰፊ እና ውስብስብ ብዙ አካላት የሚሰታፉበት እንደ ሀገርም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዘርፍ ሕግ ያለው ወሳኝነት እና ሚና መነሻ በማድረግ ዝርዝር ጉዳዮችን እያነሳን እንገኛለን፡፡ ነገ እሁድ ሐምሌ 5-2018 ዓ.ም በሚኖረው ወይይትም ሀሳብ ፣ ጥያቄ ካላችሁ በአጭር መልዕክት ቁጥር 8545 / በስልክ ቁጥር 0115585431 እና 0115585432 በመደወል መሳተፍ ይቻላል፡፡
ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት ከአራዳ ኤፍኤም 95.1 ጋር በመተበባበር
👍5
በኮንስትራክሽን ሕግ እና ወሎች ዙሪያ ከ40 ዓመት በላይ የማማከር ልምድ ካላቸው አቶዘውዱ ተፈራ ወርቄ ጋር ላለፉት ሶስት ሳምንት ውይይት ስናደርግ ነበር፡፡ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ሰፊ እና ውስብስብ ብዙ አካላት የሚሰታፉበት እንደ ሀገርም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዘርፍ ሕግ ያለው ወሳኝነት እና ሚና መነሻ በማድረግ ዝርዝር ጉዳዮችን እያነሳን እንገኛለን፡፡ ነገ  እሁድ ሐምሌ 12-2018 ዓ.ም በሚኖረው ወይይትም ሀሳብ ፣ ጥያቄ ካላችሁ በአጭር መልዕክት  ቁጥር 8545 / በስልክ ቁጥር 0115585431 እና 0115585432 በመደወል መሳተፍ ይቻላል፡፡
ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት ከአራዳ ኤፍኤም 95.1 ጋር በመተበባበር
በእስረኞች የሕክምና መብት እና በጸጥታ ስጋት መካከል ያለው ሚዛን
የሰ/መ/ቁ. 203051 | የካቲት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. | ቅፅ 25
በሕግ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ተጠርጣሪዎች ሕክምና የማግኘት መብት እና የመንግሥት የጸጥታ ስጋት መከራከሪያ በሚጋጩበት ጊዜ ፍርድ ቤቶች እንዴት ሊያመዛዝኑት ይገባል? የሰበር ሰሚ ችሎት በዚህ መዝገብ የሰጠው ውሳኔ 3 ቁልፍ ነጥቦችን በግልጽ አስቀምጧል፦
የመታከም መብት እና የመንግሥት ኃላፊነት፡ ታካሚዎች እምነት በሚጥሉበትና በመረጡት ሐኪም እንዲሁም የሕክምና ተቋም የመታከም ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው መሠረታዊ ሰብዓዊ መብት ነው። መንግሥት በፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ የሚያልፉ ተጠርጣሪዎች ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ግዴታ ያለበት ሲሆን ይህ ግዴታ በማረሚያ ቤት በሚገኙበት፣ ፍርድ ቤት በሚቀርቡበት እና ወደ ሕክምና ተቋማት በሚሄዱበት ጊዜ ሁሉ በጥብቅ ሊተገበር ይገባል።
የመንግሥት አዎንታዊ ግዴታ፡ መንግሥት የጸጥታ ስጋት አለኝ በሚል ሰበብ የመታከም መብትን ከመገደብ ይልቅ አስፈላጊውን ጥበቃ በመመደብ ስጋቱን የመቆጣጠርና የማስወገድ አዎንታዊ ግዴታ አለበት።
ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ ውሳኔዎች፡ የሕክምና መሣሪያዎችና ተቋማት ባህሪ ቋሚ በመሆናቸው ሆስፒታልን እንደ ተንቀሳቃሽ አካል ቆጥሮ ማረሚያ ቤት ድረስ ሄዶ እንዲያክም ማዘዝ በተግባር ሊፈጸም የማይችል ስህተት ነው።
የሰበር ችሎቱ የይግባኝ ሰሚውን ውሳኔ በመሻር መንግሥት ተገቢውን የደህንነት ጥበቃ በማድረግ አመልካቾች ቀድሞ በመረጡት ሆስፒታል ሕክምናቸውን እንዲያገኙ ወስኗል። ይህም የመንግሥት ቀዳሚ ሚና መብቶችን መገደብ ሳይሆን መብቶች በተሟላ ሁኔታ እንዲከበሩ ማመቻቸትና ጥበቃ ማድረግ መሆኑን ያረጋገጠ ውሳኔ ነው፡፡
#CovenantHubLawFirmLLP
👍1