TIKVAH-ETHIO
671 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
#BREAKING

በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የ2012 ምርጫ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደማይካሄድ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

ቦርዱ በተፈጠረው ሁኔታ የተነሳ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ምርጫውን ማካሄድ የማይቻለው መሆኑን በመረዳት ያወጣውን የጊዜ ሰሌዳ በመሰረዝ በሰሌዳው መሰረት መከናወን ያለባቸው ተግባራት ለጊዜው እንዲቆሙ መወሰኑን ገልጿል።

የወረርሽኙ ሥጋት ተወግዶ ሁኔታዎች ሲመቻቹ እንደገና ግምገማ በማድረግ አዲስ የምርጫ ኦፕሬሽን እቅድና ሰሌዳ በማውጣት እንቅስቀሴውን የሚያስጀምር እንደሚሆንም አሳውቋል።

#NEBE
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#NEBE

ነገ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመጪውን ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ እንደሚያደርግ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በድረገፁ ዘግቧል።

ምርጫ ቦርድ በምርጫ የጊዜ ሰሌዳው ላይ ከ47 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ለመምከር ነገ በአዲስ አበባ ስብሰባ ጠርቷል።

በነገው ምክክር መድረክ ላይ ዝርዝር የምርጫ ክንውኖችን የያዘ የጊዜ ሰሌዳ ለፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚቀርብ የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ሶልያና ሽመልስ ተናግረዋል።

Via Ethiopia Insider
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛ አገራዊ ምርጫን አስመልክቶ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱ ምክክሮች በኋላ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን እንዲሁም መደረግ ስላለባቸው ተጨማሪ ጉዳዮች እና የጊዜ ሰሌዳን አስመልክቶ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር እየተወያየ ይገኛል።

ዛሬ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ይደረጋል።

አሁን ላይ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱኳን ሚደቅሳ የቀድሞ ምክክሮችን በማስከተል የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች በማቅረብ ላይ ናቸው።

#TikvahFamilyAA

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA