ተቋሙ ከኦፕሬሽን ዘርፎች ለተውጣጡ ሠራተኞች የአሰልጣኞች ስልጠና እየሠጠ ነው
….....///…......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኃይል ማመንጫዎች፣ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለተውጣጡ ሠራተኞች የአሰልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ።
በኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በሦስት ዙር ተከፋፍሎ ለአስር ቀናት የሚሰጠውን ሥልጠና የመጀመሪያ ዙር ሠልጣኞች ትናንት ሥልጠናቸውን ጀምረዋል።
በተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠና እና ልማት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ በስልጠናው ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ እንደገለጹት ሥልጠናው በዋናነት ሰልጣኞች ከሥልጠና በኋላ የስልጠና አሰጣጥ ጥበብ እና ስልቶችን ተከትለው እውቀታቸውን በተገቢው መንገድ ለሌሎች ማስተላለፍ እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በተቋሙ የብዙ ልምድ ባለቤት የሆኑ አንጋፋ ሠራተኞች የሚገኙ ቢሆንም ያላቸውን እውቀትና ልምድ ለሌሎች በማካፈል ረገድ ውስንነቶች እንደነበሩ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
ሥራ አስኪያጁ በነባር የተቋሙ የሰው ኃይል እና አዲስ በሚቀላቀሉ ሠራተኞች መካከል ከ15 እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የዕድሜ ክፍተት እንዳለ በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው ይህም ሰፊ የእውቀት ክፍተት እና ልዩነት እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
ስለሆነም በተቋሙ የውስጥ አቅም ስልጠናን በማሳደግ እና በሁሉም ዘርፎች ተደራሽ በማድረግ የእውቀት ክፍተት እንዳይፈጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት።
የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ በበኩላቸው በአስተዳደራዊ እና በቴክኒክ ዘርፉ ላይ ያሉ እውቀቶችን በመጠቀም የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ማሳካት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ተቋሙ በስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ካስቀመጣቸው ግቦች ለመድረስ የሰው ኃይል አቅም ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በአግባቡ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
ስልጠናን በተቋሙ የውስጥ አቅም በመስጠት ብቃት ያለው የሰው ሀብት ለመገንባት በኦፕሬሽን ዘርፉ ላይ የተጀመረው የአሰልጣኞች ስልጠና በቀጣይ በተቋሙ ሁሉም ዘርፎች የሚሰጥ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በማከፋፈያ ጣቢያዎች የትራንስፎመሮችን ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚስችል ስልጠና ለማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል፡፡
በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝንስ ዘርፍ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ እንደገለፁት ሥልጠናው በየማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ ትራንስፎርመሮች ከብልሽት የፀዱና ደኅንነታቸው የተጠበቁ እንዲሆኑ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡
በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ 154 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ ከ45 በላይ የሚሆኑት ከአቅም በላይ የኃይል ጭነት የተሸከሙ በመሆናቸው ጥብቅ የደኅንነት ክትትልና የፍተሻ ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል፡፡
በተቋሙ የፓወር ግሪድ ትንተና ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑትና ሥልጠናውን እየሰጡ ያሉት አቶ አበባው ጋሻው በበኩላቸው ሥልጠናው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ትራንስፎርመሮችን የአገልግሎት ዘመናቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
….....///…......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኃይል ማመንጫዎች፣ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለተውጣጡ ሠራተኞች የአሰልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ።
በኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በሦስት ዙር ተከፋፍሎ ለአስር ቀናት የሚሰጠውን ሥልጠና የመጀመሪያ ዙር ሠልጣኞች ትናንት ሥልጠናቸውን ጀምረዋል።
በተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠና እና ልማት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ በስልጠናው ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ እንደገለጹት ሥልጠናው በዋናነት ሰልጣኞች ከሥልጠና በኋላ የስልጠና አሰጣጥ ጥበብ እና ስልቶችን ተከትለው እውቀታቸውን በተገቢው መንገድ ለሌሎች ማስተላለፍ እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በተቋሙ የብዙ ልምድ ባለቤት የሆኑ አንጋፋ ሠራተኞች የሚገኙ ቢሆንም ያላቸውን እውቀትና ልምድ ለሌሎች በማካፈል ረገድ ውስንነቶች እንደነበሩ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
ሥራ አስኪያጁ በነባር የተቋሙ የሰው ኃይል እና አዲስ በሚቀላቀሉ ሠራተኞች መካከል ከ15 እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የዕድሜ ክፍተት እንዳለ በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው ይህም ሰፊ የእውቀት ክፍተት እና ልዩነት እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
ስለሆነም በተቋሙ የውስጥ አቅም ስልጠናን በማሳደግ እና በሁሉም ዘርፎች ተደራሽ በማድረግ የእውቀት ክፍተት እንዳይፈጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት።
የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ በበኩላቸው በአስተዳደራዊ እና በቴክኒክ ዘርፉ ላይ ያሉ እውቀቶችን በመጠቀም የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ማሳካት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ተቋሙ በስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ካስቀመጣቸው ግቦች ለመድረስ የሰው ኃይል አቅም ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በአግባቡ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
ስልጠናን በተቋሙ የውስጥ አቅም በመስጠት ብቃት ያለው የሰው ሀብት ለመገንባት በኦፕሬሽን ዘርፉ ላይ የተጀመረው የአሰልጣኞች ስልጠና በቀጣይ በተቋሙ ሁሉም ዘርፎች የሚሰጥ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በማከፋፈያ ጣቢያዎች የትራንስፎመሮችን ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚስችል ስልጠና ለማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል፡፡
በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝንስ ዘርፍ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ እንደገለፁት ሥልጠናው በየማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ ትራንስፎርመሮች ከብልሽት የፀዱና ደኅንነታቸው የተጠበቁ እንዲሆኑ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡
በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ 154 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ ከ45 በላይ የሚሆኑት ከአቅም በላይ የኃይል ጭነት የተሸከሙ በመሆናቸው ጥብቅ የደኅንነት ክትትልና የፍተሻ ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል፡፡
በተቋሙ የፓወር ግሪድ ትንተና ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑትና ሥልጠናውን እየሰጡ ያሉት አቶ አበባው ጋሻው በበኩላቸው ሥልጠናው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ትራንስፎርመሮችን የአገልግሎት ዘመናቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤18👍4👏2🤨1
ተቋማቱ በመቀናጀት ጊዜን የቀደሙ ሥራዎች መስራት አለባቸው - የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች
……..///…....
አስተማማኝና ተደራሽ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎችን ማከናወን እንዳለባቸው የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማናጅመንት ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየሁ ሊካሳ እንደገለፁት ሁለቱ ተቋማት እስከ 2006 ዓ.ም ድረስ በአንድ ተቋም ሥር የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡
የኃይል ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ እና ዘርፉ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በመረዳት ዓለምአቀፋዊ ተሞክሮዎችን በመገምገም አቅርቦቱንና ተደራሽነቱን ለማሳደግ ሲባል በጥናት ላይ በመመስረት ሁለቱ ተቋማት ራሳቸውን ችለው እንዲደራጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል።
የተቋማቱ ወደ ሁለት መከፈል ትኩረት እንዳይበታተን በማድረግ እንዲሁም የፋይናንስ ጫናዎችን በማቃለል አቅርቦቱን ከማዘመን እና ተደራሽነቱን ከማስፋት አንጻር አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ዶ/ር ገበየሁ አክለውም የውስጥ አሰራርን በማዘመን የነባር ኔትወርኮችን መልሶ ግንባታ እና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በማከናወን የኃይል መቆራረጡን በመቀነስ ተደራሽነቱን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም ባለፉት 11 ዓመታት ተቋማቱ ባከናወኗቸው ሥራዎች የደንበኞችን ቁጥር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ወደ 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን እንዲሁም የተደራሽነት ሽፋኑን ከ30 በመቶ ወደ 54 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
ተቋማቱ በአደረጃጀት ለሁለት ቢከፈሉም ሥራቸው ተመጋጋቢ እና ኔትወርኩም የተያያዘ በመሆኑ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስና ተደራሽነቱን ለማሳደግ የጋራ የግንኙነት ጊዜ አስቀምጠው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላቸው 78 ከመቶ ከግሪድ እንዲሁም 22 ከመቶ ከግሪድ ውጭ የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ የተያዘውን ሀገራዊ ዕቅድ ለማሳካት ሁለቱ ተቋማት ተናበው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡
የኃይል ተደራሽነቱን ከማሳደግ በተጨማሪ ቀደም ሲል የኃይል ተጠቃሚ የነበሩ አካባቢዎች የኃይል ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መሆኑንና ይሄን ጥያቄ ለመመለስ ሁለቱ ተቋማት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎች መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ መናበቡን መዋቅራዊ አድርጎ ለመቀጠል በሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራና ሥራዎችን የሚገመግም ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
……..///…....
አስተማማኝና ተደራሽ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎችን ማከናወን እንዳለባቸው የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማናጅመንት ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየሁ ሊካሳ እንደገለፁት ሁለቱ ተቋማት እስከ 2006 ዓ.ም ድረስ በአንድ ተቋም ሥር የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡
የኃይል ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ እና ዘርፉ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በመረዳት ዓለምአቀፋዊ ተሞክሮዎችን በመገምገም አቅርቦቱንና ተደራሽነቱን ለማሳደግ ሲባል በጥናት ላይ በመመስረት ሁለቱ ተቋማት ራሳቸውን ችለው እንዲደራጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል።
የተቋማቱ ወደ ሁለት መከፈል ትኩረት እንዳይበታተን በማድረግ እንዲሁም የፋይናንስ ጫናዎችን በማቃለል አቅርቦቱን ከማዘመን እና ተደራሽነቱን ከማስፋት አንጻር አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ዶ/ር ገበየሁ አክለውም የውስጥ አሰራርን በማዘመን የነባር ኔትወርኮችን መልሶ ግንባታ እና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በማከናወን የኃይል መቆራረጡን በመቀነስ ተደራሽነቱን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም ባለፉት 11 ዓመታት ተቋማቱ ባከናወኗቸው ሥራዎች የደንበኞችን ቁጥር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ወደ 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን እንዲሁም የተደራሽነት ሽፋኑን ከ30 በመቶ ወደ 54 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
ተቋማቱ በአደረጃጀት ለሁለት ቢከፈሉም ሥራቸው ተመጋጋቢ እና ኔትወርኩም የተያያዘ በመሆኑ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስና ተደራሽነቱን ለማሳደግ የጋራ የግንኙነት ጊዜ አስቀምጠው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላቸው 78 ከመቶ ከግሪድ እንዲሁም 22 ከመቶ ከግሪድ ውጭ የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ የተያዘውን ሀገራዊ ዕቅድ ለማሳካት ሁለቱ ተቋማት ተናበው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡
የኃይል ተደራሽነቱን ከማሳደግ በተጨማሪ ቀደም ሲል የኃይል ተጠቃሚ የነበሩ አካባቢዎች የኃይል ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መሆኑንና ይሄን ጥያቄ ለመመለስ ሁለቱ ተቋማት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎች መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ መናበቡን መዋቅራዊ አድርጎ ለመቀጠል በሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራና ሥራዎችን የሚገመግም ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👎5❤4
ተቋሙ የጣና ነሽ 2 ጀልባ ጉዞ በስኬታማ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል
……///……
የጣና ነሽ 2 ጀልባ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
በተቋሙ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይ ዘወልዴ እንደገለፁት በተሸከርካሪ ተጭነው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ስር የሚያቋርጡ ከፍታ ያላቸው ብረት ነክ ዕቃዎች ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በጠበቀ መልኩ እንዲያልፉ እየተደረገ ነው፡፡
በጣና ሀይቅ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠትና የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ታስቦ ከጅቡቲ ዶራሌህ ወደብ ወደ ባህር ዳር እየተጓጓዘች የምትገኘው ጣና ነሽ 2 ጀልባ አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ የኃይል መስመሮች ጉዳት እንዳያደርሱ የመጠበቅ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
ጀልባዋ ጉዞ ማድረግ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ ባለ 230 እና 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉባቸው 53 ቦታዎችን ችግር ሳያጋጥም በተሳካ ሁኔታ ማቋረጧን ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹን ለአጭር ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ለጀልባዋ ጉዞ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተችሏል፡፡
የማዕከላዊ 2 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ባለሙያ አቶ ሙሉቀን ወልደማሪያም በበኩላቸው ከአዋሽ ሰባት ኪሎ እስከ ቆቃ በተዘረጋው መስመር ላይ የጀልባዋን ጉዞ ለማሳለጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
ተቋሙ ጀልባዋ ጉዞ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በቀጣይም በምታልፍባቸው ቦታዎችም ተመሳሳይ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡
የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ያላቸውን ከፍታ በዘመናዊ መሳሪያ በመለካት መረጃዎችን ማደራጀት መቻሉም ተገልጿል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
……///……
የጣና ነሽ 2 ጀልባ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
በተቋሙ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይ ዘወልዴ እንደገለፁት በተሸከርካሪ ተጭነው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ስር የሚያቋርጡ ከፍታ ያላቸው ብረት ነክ ዕቃዎች ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በጠበቀ መልኩ እንዲያልፉ እየተደረገ ነው፡፡
በጣና ሀይቅ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠትና የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ታስቦ ከጅቡቲ ዶራሌህ ወደብ ወደ ባህር ዳር እየተጓጓዘች የምትገኘው ጣና ነሽ 2 ጀልባ አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ የኃይል መስመሮች ጉዳት እንዳያደርሱ የመጠበቅ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
ጀልባዋ ጉዞ ማድረግ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ ባለ 230 እና 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉባቸው 53 ቦታዎችን ችግር ሳያጋጥም በተሳካ ሁኔታ ማቋረጧን ገልፀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹን ለአጭር ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ለጀልባዋ ጉዞ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተችሏል፡፡
የማዕከላዊ 2 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ባለሙያ አቶ ሙሉቀን ወልደማሪያም በበኩላቸው ከአዋሽ ሰባት ኪሎ እስከ ቆቃ በተዘረጋው መስመር ላይ የጀልባዋን ጉዞ ለማሳለጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
ተቋሙ ጀልባዋ ጉዞ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በቀጣይም በምታልፍባቸው ቦታዎችም ተመሳሳይ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡
የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ያላቸውን ከፍታ በዘመናዊ መሳሪያ በመለካት መረጃዎችን ማደራጀት መቻሉም ተገልጿል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤6👍5