EEP Communication
15.6K subscribers
10.8K photos
33 videos
32 files
2.02K links
EEP Communication
Download Telegram
የሴቶችን ተጠቃሚነትና ውሳኔ ሰጭነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ውሳኔዎች ተላልፈዋል
………///………
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴት ሠራተኞችን ተጠቃሚነትና ውሳኔ ሰጭነትን ለማሳደግ የሚያግዙ የተለያዩ አወንታዊ የድጋፍ እርምጃ (Affirmative action) ዉሳኔዎች መተላለፋቸውን በተቋሙ የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢዲኤ እንደገለፁት የተላለፉት ውሳኔዎች የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ ውሳኔ ሰጪነትን ለማሳደግና እኩልነትን በተግባር ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ውሳኔዎች የተላለፉት በተቋሙ ሥራ አመራር እና መሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር በተመሰረተ ኮሚቴ አማካይነት ጥናትና ውይይቶች ከተካሄዱ በኋላ ነው፡፡

በዚህ መሰረት በተቋሙ በጀት ተይዞ በየዓመቱ እስከ ዲፕሎማ የትምህርት ደረጃ 25 ሴቶችን፣ በመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት መስክ 20 ሴቶችን እና በሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ 10 ሴቶችን ለማሰልጠን የሰው ኃይል እና የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በጋራ በሚያወጡት ግልፅ መስፈርት ተወዳድረው እንዲማሩ ከስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል - ዳይሬክተሯ፡፡

ወ/ሮ ሌንሴ እንደገለጹት ተቋሙ የሴቶችን ፍትሐዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አዲስ ቅጥር በሚያከናውንበት ጊዜ ለፈተና ከሚመረጡ ተወዳዳሪዎች መካከል 30 በመቶው ለሴቶች ዕድል እንዲሰጥና ፈተናውን ካለፉት ተወዳዳሪዎች መካከልም 30 በመቶ ድርሻ ለሴቶች ብቻ እንዲሰጥ ተደርጎ 70 ከመቶ ከወንዶች ጋር ዕድል እንዲሰጥ የሚያደርግ ውሳኔ ተላልፏል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
1
ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ስድስት ወራት ከዕቅድ በላይ ኃይል ማመንጨት ችሏል
…………////………..
የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በግማሽ ዓመቱ 958 ጌጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 1028 ነጥብ 5 ጌጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐብታሙ ገረመው አስታወቁ፡፡
ጣቢያው ያመነጨው ከዕቅዱ የ 7 በመቶ ብልጫ እንዳለው ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
ከጊቤ 3 እና ከበለስ ቀጥሎ ትልቁ የኃይል ማመንጫ የሆነው የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 420 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ሲኖረው የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት አንፃር የጎላ ሚና በመጫዎት ላይ የሚገኝ ጣቢያ ነው፡፡
ከሰው ኃይል ልማት አኳያም ለዘጠኝ አዲስ መሐንዲሶች እና ለአራት ቴክኒሺያኖች ለሁለት ወራት ያህል የስራ ላይ ስልጠና መሰጠቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
የጣቢያው የጥገና ክፍል ተወካይ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ተስፋ በበኩላቸው ከኦፕሬሽን ተግባራት ጎን ለጎን ጣቢው ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የጥገና ሥራዎች ሲከናወኑ እንደነበር ገልፀዋል፡፡
ዘይት እያፈሰሰ የኃይል ማመንጨቱን ስራ ያስተጓጉል የነበረውን የውሃ መቀበያ ዋና አሸንዳ እና የመቆጣጠሪያ ክፍል የአየር ማቀዝቀዣ በጥገና ክፍሉ ባለሙያዎች ተጠግኖ ወደ ስራ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ የጀመረው የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሶስት ትራንስፎርመሮችን የያዘ ባለ 400 ኪ.ቮ ስዊችያርድ አለው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric

ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 15 ቀን 2013
በቀጣዮቹ አስር ዓመታት የሚተገበር የሲስተም ልማት ዕቅድ ተዘጋጅቷል
…………….///…………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ለመተግበር ባዘጋጀው የሲስተም ልማት ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመምከር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡
በዕቅዱ መሰረት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅሙን ከ4 ሺህ 515 ሜጋዋት ወደ 17 ሺህ 56 ሜጋዋት ለማሳደግ፣ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮችን ርዝመት አሁን ካለበት19 ሺህ 746 ኪ.ሜ. ወደ 33 ሺህ 497 ኪ.ሜ. ለማድረስ ታቅዷል፡፡
በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የተዘጋጀው የአስር ዓመት ዕቅድ እንደሚያሳየው በዕቅድ ዘመኑ ከ132 ኪሎ ቮልት በላይ አቅም ያላቸው 176 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቁጥር ወደ 265 ለማሳደግም ይሰራል፡፡
በኃይል ማስተላለፍ ወቅት የሚያጋጥመውን የ6 በመቶ የኤሌክትሪክ ብክነት ወደ 3 ነጥብ 5 በመቶ ለመቀነስና የተቋሙን ገቢ ደግሞ ከ300 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወደ 5 ነጥብ 32 ቢሊየን ለማሳደግ ዕቅድ ተይዟል፡፡
አሁን ከግሪድ ጋር ያለውን የ33 በመቶ ግንኙነት ወደ 96 በመቶ ለማሳደግ፤ ከውሃ የሚገኘውን የ93 በመቶ የማመንጨት ድርሻ ወደ 73 በመቶ በመቀነስ በአንፃሩ ከንፋስ፣ ከጂኦተርማልና ከፀሐይ ኃይል የማመንጨት ድርሻን ለማሳደግ እንደሚሰራም በዕቅዱ ተመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric

ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 16 ቀን 2013 ዓ.ም
ተቋሙ ኤች አይ ቪ እና ኮሮናን ለመከላከል የሚያስግዝ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ
............/////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችን ከኤች አይቪ ኤድስ እና ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ከዲኬቲ ኢትዮጵያና ከፌደራል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተገለፀው ስምምነቱ በፕሮጀክቱ የተሳተፉ ሠራተኞችንና የአካባቢው ማህበረሰብን ከኤች አይ ቪ ኤድስና ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግና ሌሎች ቴክኒካል ስራዎችን ለማከናወን የሚያግዝ ነው፡፡
በስምምነቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ስራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ፣ በኢትዮጵያ የዲኬቲ ኢትዮጵያ ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማይ እና የፌደራል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጽጌሬዳ ክፍሌ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ የሁሉም ዜጋ እንደሆነ በመረዳት ተቋማቱ እያደረጉት ያለውን ድጋፍ አቶ አታላይ አመስግነዋል፡፡
በህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችን ደህንነትና ጤንነት ለመጠበቅ ተቋማቱ ከዚህ በፊት ሲያከናውኑ የነበረውን ድጋፍ ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
ቫይረሱ በፕሮጀክቱ ሰራተኞች ላይ እንዳይሰራጭ ተቋሙ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አቶ አታላይ አረጋግጠዋል፡፡
የፌደራል ኤች አይ ቪኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጽጌሬዳ ክፍሌ በበኩላቸው ኤች አይ ቪ ኤድስ በአሁኑ ሰዓት በሃገራችን የስርጭት አድማሱ እየተስፋፋ መሆኑን በመረዳት ለቫይረሱ ተጋላጭ በሆኑ ቦታዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የዲኬቲ ኢትዮጵያ ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማይ እንደገለጹት ድርጅታቸው የግድቡ ፕሮጀክት ከተጀመረ ጀምሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል ሲያደርግ የቆየውን የፋይናንስና ሌሎች ቴክኒካል ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡
በዛሬው እለት የተካሄደው የድጋፍ ስምምነት ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን ይህም ለሦስት ዓመታት የሚቆይ ድጋፍ እንደሆነ በተቋሙ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር አስተባባሪ አቶ መስፍን ደርሶ ተናግረዋል፡፡
ስምምነቱ በፕሮጀክቱ ላይ ለተሳተፉ ሠራተኞችና የአካባቢው ማህበረሰብ ስልጠና ለመስጠት፣ ሠራተኛው በትርፍ ጊዜው ወደ አልባሌ ቦታ እንዳይሄድ በፕሮጀክቱ የመዝናኛ ቦታዎችን ለማዘጋጀት እና ሌሎች የንቅናቄ ስራዎችን ለማከናወን የሚውል መሆኑን ነው አቶ መስፍን የገለጹት፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric

ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 17 ቀን 2013 ዓ.ም
20210115_105134.jpg
2.3 MB
የጊቤ አንድ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በርካታ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ
............/////..............
የጊቤ አንድ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ስድስት ወራት ስኬታማ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ማከናወኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሴ አስታውቁ፡፡
በስድስት ወራት ውስጥ 534 ነጥብ 2 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት ታቅዶ 600 ጌጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማመንጨት የዕቅዱን 120 በመቶ ማሳካት መቻሉን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
ጣቢያው 230/132 ኪ.ቮ አቅም ያለው ስዊች ያርድ ባለቤት ሲሆን ለጌዶ፣ ሰበታና ሰኮሩ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኤሌክትሪክ የሚያቀርቡ ሶስት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡
ከኦፕሬሽን ሥራዎች ባሻገር በማቀዝቀዣ፣ በዲዝል፣ በስካዳ ሲስተም እና በስዊችያርድ ላይ የጥገና ሥራዎች የተከናወኑ መሆኑን አቶ ደሳለኝ ገልፀዋል፡፡
በብልሽት ምክንያት ለሥራ እንቅፋት ሆኖ የቆየውን የዩኒት አንድ ሰርቨር የኮምፒውተር ሰሌዳ ወይም ስክሪን በመጠቀም እንደገና አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ መቻሉን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡
በስዊችያርድ ላይ የሞደፊኬሽን ሥራዎች በማከናወን ስዊች ያርድ ላይ ያጋጥም የነበረውን ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ ማስቀረት መቻሉንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 19 ቀን 2013 ዓ.ም
ሪጅኑ ባለፉት 6 ወራት ከዕቅዱ በላይ የቅድመ ብልሽት ፍተሻና የጥገና ሥራ አከናወነ
………..////………..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ባለፉት 6 ወራት የዕቅዱን 102 ነጥብ 38 በመቶ የቅድመ ብልሽት ፍተሻና የጥገና ሥራ ማከናወኑን አስታወቀ፡፡
ቢሮው የስድስት ወር አፈፃፀሙን በጅግጅጋ ሲገመግም ዳይሬክተ ሩ አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከዛፍ ንኪኪ የማፅዳት፣ የተሰበሩ ኢንሱሌተሮችን በሌላ የመተካት፣ የመሬት መንሽራተት ምሰሶዎችን እንዳይጎዳ የጋቢዮን ማንጠፍና የተበጠሱ ገመዶችን በሌላ የመተካት ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡
የፖርሲሊን ኢንሱሌተሮችን በፕላስቲክ ኢንሱሌተር የመተካት ስራ መስራቱንም ገልፀዋል፡፡
ይህም የሪጅኑን አፈፃፀም 102 ነጥብ 38 በመቶ አድርሶታል ብለዋል፡፡
ከተመሠረተ ሦስት ወራት ያስቆጠረው የጅግጅጋ ንዑስ ሪጅን የተቋቋመበትን ዓላማ መውጣት እንዲችል ተገቢው ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በሪጅኑ ከሪፖርት አቀራረብ፣ የሚሞሉ ዕለታዊ ሎግ ሺቶችን ኦዲት ካለማድረግና ከስልጠና ጋር የተያያዙ የአፈፃፀም ክፍተቶች መታየታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠

https://www.facebook.com/Ethioelectric

ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2013 ዓ.ም
የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ነው
……………../////……………
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች በአረንጓዴ ልማት መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን ለመንከባከብ ውሀ የማጠጣት ተግባር አከናወኑ፡፡
በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ደርባ ፊንጫ በተባለ አካባቢ በ2012 ዓ/ም የክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ለመንከባከብ በወጣው መርሃ ግብር መሠረት ዛሬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በቦታው ተገኝተው ችግኞቹን ውሃ አጠጥተዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ የቴክኒክ አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብም ለጽድቀት መጠኑ ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ችግኞቹ የተተከሉበት አካባቢ በአባይ ተፋሰስ ሥር የሚገኝ በመሆኑ ከወዲሁ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መሠራቱ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በደለል እንዳይሞላ ያግዛል ብለዋል፡፡

በተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ችግኞች የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከፍ ከማድረጋቸው ባሻገር ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት በመሆኑ የግድቦቻችንን ዕድሜ እንደሚጨምር አማካሪው ገልፀ ዋል፡፡
ችግኞቹም ከእንስሳት ንኪኪ ተጠብቀው በጥሩ የዕድገት ሁኔታ ላይ በመገኘታቸው መደሰታቸውን በመጥቀስ የአካባቢው ህብረተሰብ ላከናወነው ተግባር አመስግነዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት አስተዳድር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ችግኞችን የመንከባከብና ውሀ የማጠጣት ፕሮግራሙ ከየሥራ ክፍሉ የተወጣጡ አመራሮችና ሠራተኞች የተሳተፉበት በመሆኑ ውጤታማ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት ደግሞ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ ከሁሉም ህብረተሰብ የሚጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ነው፡፡

ሀገሪቱ የጀመረችውን የአረንጓዴ ልማት መርሃ ግብር ለማሳካት ባለፈው ዓመት ክረምት ላይ 5 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠

https://www.facebook.com/Ethioelectric

ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 21 ቀን 2013 ዓ.ም
የግድቡ ግንባታ በታቀደለት መርሃግብር እየተከናወነ ነው
...........////.........
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በታቀደለት መርሃግብር እየተከናወነ መሆኑን በስፍራው በመገኘት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም የገመገሙት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚሩስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ አባላት አረጋገጡ፡፡
ሚኒስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታው ሂደት በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ መሆኑን ምልከታ በማድረግ በግንባታው ላይ እየተሳተፉ ካሉት ተቋራጮች፣ አማካሪ ድርጅትና ከባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል ፡፡
የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በዕቅዱ መሰረት እንዲጠናቀቅና አስቀድሞ በሁለት ዩኒቶች ኃይል ለማመንጨት የተያዘው ዕቅድ እንዲሳካ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 23 ቀን 2013 ዓ.ም