EEP Communication
15.6K subscribers
10.8K photos
33 videos
32 files
2.02K links
EEP Communication
Download Telegram
ወደ ከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ተጠግተው ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኑ
..............///........
ከሰኮሩ ጊቤ 2 የሚያገናኝ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመርን ተጠግተው ለመኖሪያ ቤት ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ለ30 ደቂቃዎች አካባቢ በከፊል ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት ሆነዋል።
ኤሌክትሪክ የተቋረጠው ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤታቸው ከጎረቤት በአየር ላይ የሳቡት የኤሌክትሪክ ሽቦ ወደ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመር በመቅረቡ በተፈጠረ የኤሌክትሪክ መሳሳብ ነው።
በዚህም በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ለግማሽ ሰዓት ሲቋረጥ አንድ የሳር ቤትና ለመሰብሰብ የደረሰ ሰብል ተቃጥሏል።
የአካባቢው ነዋሪ ተረባርቦ እሳቱን ባያጠፋው ኖሮ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችል የነበረ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱን ፈፃሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ህብረተሰቡ ወደከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮች ተጠግቶ ምንም ዓይነት መሰረተልማት እንዳይዘረጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል።
ታህሳስ 17 ቀን 2013 ዓ/ም
ለቁፋሮ ከሚያገለግሉ ሁለት የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኖች መካከል የአንድ ማሽን ተከላ ተጠናቋል
…………..////……………
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ ከሚያስፈልጉት ሁለት የቁፋሮ ማሽኖች መካከል የአንዱ ማሽን ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት አስታውቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛው ማሽን ተከላም እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ማሽኖቹ የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን ያሟሉና ከ2 እስከ 2 ነጥብ 5 ኪ.ሜ ጥልቀት መቆፈር የሚያስችል አቅም እንዳላቸውና 350 ቶን ያህል ክብደት የመሳብ ወይም የመሸከም አቅም ያላቸው መሆኑን አቶ መሳይ ተናግረዋል፡፡
ከማሽን ተከላው ጎን ለጎን ለጉድጓድ ቁፋሮ የሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የውሃ ታንከሮች ገጠማ እና የውሃ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡
የውሃ መስመር ዝርጋታው እንደተጠናቀቀ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራው በይፋ እንደሚጀመርም ነው ያስታወቁት፡፡
የፕሮጀክቱ የሠው ኃይል አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወርቁ ዱቄ በበኩላቸው በእስካሁኑ ሒደት ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን በፕሮጀክቱ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ገልፀዋል፡፡
የቻይናው ኬሩይ /KERUI/ ኩባንያ የመቆፈሪያ ማሽኑን አምርቶ የገጠማ ስራውን በማከናወን ላይ ሲሆን የኬንያው ኬንጀን /KENJEN/ እና የቻይናው ኬሩይ ኦይል ፊልድ /KERUI Oil field/ ኩባንያዎች ደግሞ የጉድጓድ ቁፋሮውን ያከናውናሉ፡፡
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ከምድር በሚወጣ ተፈጥሯዊ እንፋሎት አማካኝነት 70 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ያለመ ነው፡፡

ታህሳስ 20 ቀን 2013 ዓ.ም
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ
……………///…………...
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ በሚደረገው ዘመቻ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮች እና ሠራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ሊሞ ወረዳ ቆቃ ነገዎ ቀበሌ በመገኘት ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መለስ ሲሎ እንደገለፁት የዘመቻው ዋና ዓላማ መጤ አረሙ በሐይቁና በግድቡ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ተፅዕኖ ለመቀነስ ነው፡፡
በዕለቱም አንድ ሔክታር የሚሸፍን የእምቦጭ አረም የመንቀል እና ለአረሙ ምቹ የሆኑ ደለሎችን የማፅዳት ሥራ መከናወኑንም ነው የጣቢያው ኃላፊ የተናገሩት፡፡
በሐይቁ ላይ የእምቦጭ አረም በፍጥነት እየተስፋፋ የሚሄድ ከሆነ ወደ ግድቡ የሚገባውን የውሃ መጠን በመቀነስ የሚመረተውን ኃይል ሊቀንስ ይችላል ሲሉም ኃላፊው ተፅዕኖውን ገልፀዋል፡፡
ከ50 በላይ የጣቢያውን ሠራተኞች ያሳተፈው ዘመቻ የመጤ አረሙን የመስፋፋት ጉዞ ለመግታት ያለመ ቢሆንም ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑ አንፃር ድጋፉ እና ርብርቡ መቀጠል እንዳለበት አቶ መለስ ተናግረዋል፡፡
መንግሥት ልዩ ትኩረት በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ሐይቁን እና የኃይል ማመንጫ ግድቡን ከመጤ አረም ለመታደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ 60 ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

ታህሳስ 27 ቀን 2013 ዓ/ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!!
መልካም በዓል!
የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!!
መልካም በዓል!
የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል
የኢንዱስትሪ ፍሰቱን ታሳቢ ያደረጉ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው
............////.............
በአማራ ክልል የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየጨመረ በመምጣቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሳድጉ መሠረተ ልማቶችን የመገንባትና አቅም የማሳደግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን እና ጥገና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበቱ አቤ እንደገለፁት ከአሁን በፊት በተዘረጋው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በክልሉ የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ፈላጊ ደንበኞችን ጥያቄ ማስተናገድ አልተቻለም፡፡

ባህርዳር ላይ ባለ 400/230 /132 እና 66 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቢገነባም ተጨማሪ የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ እና የማሻሻያ ሥራ ይፈልጋል ብለዋል።

ይሁንና የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በአዘዞ - ጭልጋ ፣ በለስ - ጃዊ እና ደጀን - ደብረ ማርቆስ አዳዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ግንባታቸው እየተከናወነ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ የቡሬና ባህርዳር ኢንዱስትሪ ዞኖችን ጨምሮ ጥናታቸው የተጠናቀቀ የኤሌክትሪክ ማከፋፊያ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et

ጥር 07 ቀን 2013 ዓ.ም
የደጀን ደብረ ማርቆስ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ሥራ አፈጻፀም 16 በመቶ ደረሰ
.........////........
በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ የተጀመረው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ አፈጻፀሙ 16 በመቶ ደርሷል፡፡
ከአዲስ አበባ በ229 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ደጀን ከተማ የተጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ በአሁኑ ወቅት የትራንስፎርመር መትከያ ስፍራ መሰረት ተጠናቋል።
የደጀን ደብረማርቆስ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚሊዮን ታምራት እንደገለፁት የፕሮጀክቱ የቁፋሮ፣ የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የአጥር እና የኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታዎች ሥራ እየተከናወኑ ነው።
ለማከፋፈያ ጣቢያው ከደብረ ማርቆስ - ደጀን የሚደርስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር ሰርኪዩት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር እንደሚዘረጋ ተገልጿል፡፡
የሲቪል ሥራ አፈጻፀሙ 16 በመቶ የደረሰ ሲሆን ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በደጀን እና ደብረ ማርቆስ ከተሞች ለተገነቡት ፋብሪካዎች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ ለማቅረብ እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡
ፕሮጀክቱን በ14 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን ለግንባታውም ከ133 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቧል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 10 ቀን 2013 ዓ.ም
የአድዋ ከተማ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ጀመረ
............////.................
በትግራይ ክልል በጁንታው ጉዳት ደርሶበት የነበረው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠግኖ ዛሬ የአድዋ ከተማ የኤሌክትሪክ አገልገሎት አግኝቷል።
መሠረተ ልማቱን ለመጠገን የፌዴራል መንግስት ባደረገው ከፍተኛ ጥረት አብዛኞቹ የትግራይ ኣካባቢዎች የመብራት አገልግሎት እንዳገኙ መግለፃችን ይታወሳል።
በዛሬው ዕለትም በጁንታው ጉዳት ደርሶበት ከጥቅም ውጭ ሆኖ የቆየው የአድዋ የኤሌክትሪክ መስመር በመጠገኑ ከተማው የመብራት አገልገሎት አግኝቷል።
የአክሱም፣ ሽሬና ሑመራ ከተሞችም ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ ነው።
ጁንታው በሀገር መከላከያ ሰራዊት በተወሰደበት የህግ ማስከበር ዘመቻ በሽንፈት ከከተሞች ለቆ ሲወጣ በተለያዩ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ማድረሱና የከፍተኛ የአሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን መበጣጠሱ አይዘነጋም።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 10 ቀን 2013 ዓ.ም