የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቀቀ
............../////...........
የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፊያ ጣቢያ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሠላሳ ዓመታት በላይ ለሻሸመኔ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በየጊዜው እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ማስተናገድ እንዳልቻለ ሪጅኑ ጠቁሟል፡፡
25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመሸከም አቅም በነበረው አንድ ትራንስፎርመር ለከተማውና አጎራባች አካባቢዎች ኃይል ለማዳረስ ጥረት ሲደረግ ቢቆይም ፍላጎቱ ከጣቢያው አቅም በላይ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ይህም በሻሸመኔ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ኤሌክትሪክ በፈረቃ እንዲሰጥ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ አሳድሮ እንደነበር ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ጣቢያው ያለበትን ችግር ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር መሸከም የሚችል የኃይል ትራንስፎርመር በመትከልና የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን አቅሙን በእጥፍ ለማሳደግ እንደተቻለ አስታውቋል፡፡
15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው 6 ወጪ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመቆጣጠሪያና የመከላከያ መሳሪያዎችን በአዲስ መልክ የመትከል ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡
ለማስፋፊያ እና ማሻሻያ ሥራው ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ መስጠት መቻሉን ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ/ም
............../////...........
የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፊያ ጣቢያ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሠላሳ ዓመታት በላይ ለሻሸመኔ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በየጊዜው እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ማስተናገድ እንዳልቻለ ሪጅኑ ጠቁሟል፡፡
25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመሸከም አቅም በነበረው አንድ ትራንስፎርመር ለከተማውና አጎራባች አካባቢዎች ኃይል ለማዳረስ ጥረት ሲደረግ ቢቆይም ፍላጎቱ ከጣቢያው አቅም በላይ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ይህም በሻሸመኔ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ኤሌክትሪክ በፈረቃ እንዲሰጥ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ አሳድሮ እንደነበር ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ጣቢያው ያለበትን ችግር ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር መሸከም የሚችል የኃይል ትራንስፎርመር በመትከልና የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን አቅሙን በእጥፍ ለማሳደግ እንደተቻለ አስታውቋል፡፡
15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው 6 ወጪ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመቆጣጠሪያና የመከላከያ መሳሪያዎችን በአዲስ መልክ የመትከል ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡
ለማስፋፊያ እና ማሻሻያ ሥራው ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ መስጠት መቻሉን ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ/ም
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠ ማሳሰቢያ
*********************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራ ስለሚያከናውን እሁድ ታህሳስ 18 ቀን 2013 ዓ.ም ከጥዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በምስራቅ ኢትዮጵያ ማለትም በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በአሰበተፈሪ፣ በጅግጅጋ፣ በፊቅ ፣ በደገሃቡር፣ በአዋሽ ሰባት ኪሎ፣ በአዲጋላ፣ በሁርሶ፣ በአሰላ፣ አዳማ፣ አዳሚ ቱሉ እና ሻሸመኔ እንዲሁም በምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በኖሪያ፣ ደብረዘይት፣ በኢላላገዳ፣ በጆርጅ ጫማ ፋብሪካ፣ በሞጆ፣ በራም፣ በጎዴ፣ በኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር እና አካባቢዎቻቸው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደረጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
*********************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራ ስለሚያከናውን እሁድ ታህሳስ 18 ቀን 2013 ዓ.ም ከጥዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በምስራቅ ኢትዮጵያ ማለትም በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በአሰበተፈሪ፣ በጅግጅጋ፣ በፊቅ ፣ በደገሃቡር፣ በአዋሽ ሰባት ኪሎ፣ በአዲጋላ፣ በሁርሶ፣ በአሰላ፣ አዳማ፣ አዳሚ ቱሉ እና ሻሸመኔ እንዲሁም በምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በኖሪያ፣ ደብረዘይት፣ በኢላላገዳ፣ በጆርጅ ጫማ ፋብሪካ፣ በሞጆ፣ በራም፣ በጎዴ፣ በኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር እና አካባቢዎቻቸው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደረጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
ወደ ከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ተጠግተው ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኑ
..............///........
ከሰኮሩ ጊቤ 2 የሚያገናኝ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመርን ተጠግተው ለመኖሪያ ቤት ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ለ30 ደቂቃዎች አካባቢ በከፊል ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት ሆነዋል።
ኤሌክትሪክ የተቋረጠው ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤታቸው ከጎረቤት በአየር ላይ የሳቡት የኤሌክትሪክ ሽቦ ወደ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመር በመቅረቡ በተፈጠረ የኤሌክትሪክ መሳሳብ ነው።
በዚህም በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ለግማሽ ሰዓት ሲቋረጥ አንድ የሳር ቤትና ለመሰብሰብ የደረሰ ሰብል ተቃጥሏል።
የአካባቢው ነዋሪ ተረባርቦ እሳቱን ባያጠፋው ኖሮ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችል የነበረ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱን ፈፃሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ህብረተሰቡ ወደከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮች ተጠግቶ ምንም ዓይነት መሰረተልማት እንዳይዘረጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል።
ታህሳስ 17 ቀን 2013 ዓ/ም
..............///........
ከሰኮሩ ጊቤ 2 የሚያገናኝ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመርን ተጠግተው ለመኖሪያ ቤት ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ለ30 ደቂቃዎች አካባቢ በከፊል ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት ሆነዋል።
ኤሌክትሪክ የተቋረጠው ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤታቸው ከጎረቤት በአየር ላይ የሳቡት የኤሌክትሪክ ሽቦ ወደ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመር በመቅረቡ በተፈጠረ የኤሌክትሪክ መሳሳብ ነው።
በዚህም በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ለግማሽ ሰዓት ሲቋረጥ አንድ የሳር ቤትና ለመሰብሰብ የደረሰ ሰብል ተቃጥሏል።
የአካባቢው ነዋሪ ተረባርቦ እሳቱን ባያጠፋው ኖሮ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችል የነበረ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱን ፈፃሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ህብረተሰቡ ወደከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮች ተጠግቶ ምንም ዓይነት መሰረተልማት እንዳይዘረጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል።
ታህሳስ 17 ቀን 2013 ዓ/ም
ለቁፋሮ ከሚያገለግሉ ሁለት የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኖች መካከል የአንድ ማሽን ተከላ ተጠናቋል
…………..////……………
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ ከሚያስፈልጉት ሁለት የቁፋሮ ማሽኖች መካከል የአንዱ ማሽን ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት አስታውቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛው ማሽን ተከላም እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ማሽኖቹ የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን ያሟሉና ከ2 እስከ 2 ነጥብ 5 ኪ.ሜ ጥልቀት መቆፈር የሚያስችል አቅም እንዳላቸውና 350 ቶን ያህል ክብደት የመሳብ ወይም የመሸከም አቅም ያላቸው መሆኑን አቶ መሳይ ተናግረዋል፡፡
ከማሽን ተከላው ጎን ለጎን ለጉድጓድ ቁፋሮ የሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የውሃ ታንከሮች ገጠማ እና የውሃ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡
የውሃ መስመር ዝርጋታው እንደተጠናቀቀ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራው በይፋ እንደሚጀመርም ነው ያስታወቁት፡፡
የፕሮጀክቱ የሠው ኃይል አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወርቁ ዱቄ በበኩላቸው በእስካሁኑ ሒደት ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን በፕሮጀክቱ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ገልፀዋል፡፡
የቻይናው ኬሩይ /KERUI/ ኩባንያ የመቆፈሪያ ማሽኑን አምርቶ የገጠማ ስራውን በማከናወን ላይ ሲሆን የኬንያው ኬንጀን /KENJEN/ እና የቻይናው ኬሩይ ኦይል ፊልድ /KERUI Oil field/ ኩባንያዎች ደግሞ የጉድጓድ ቁፋሮውን ያከናውናሉ፡፡
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ከምድር በሚወጣ ተፈጥሯዊ እንፋሎት አማካኝነት 70 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ያለመ ነው፡፡
ታህሳስ 20 ቀን 2013 ዓ.ም
…………..////……………
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ ከሚያስፈልጉት ሁለት የቁፋሮ ማሽኖች መካከል የአንዱ ማሽን ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት አስታውቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛው ማሽን ተከላም እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ማሽኖቹ የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን ያሟሉና ከ2 እስከ 2 ነጥብ 5 ኪ.ሜ ጥልቀት መቆፈር የሚያስችል አቅም እንዳላቸውና 350 ቶን ያህል ክብደት የመሳብ ወይም የመሸከም አቅም ያላቸው መሆኑን አቶ መሳይ ተናግረዋል፡፡
ከማሽን ተከላው ጎን ለጎን ለጉድጓድ ቁፋሮ የሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የውሃ ታንከሮች ገጠማ እና የውሃ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡
የውሃ መስመር ዝርጋታው እንደተጠናቀቀ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራው በይፋ እንደሚጀመርም ነው ያስታወቁት፡፡
የፕሮጀክቱ የሠው ኃይል አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወርቁ ዱቄ በበኩላቸው በእስካሁኑ ሒደት ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን በፕሮጀክቱ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ገልፀዋል፡፡
የቻይናው ኬሩይ /KERUI/ ኩባንያ የመቆፈሪያ ማሽኑን አምርቶ የገጠማ ስራውን በማከናወን ላይ ሲሆን የኬንያው ኬንጀን /KENJEN/ እና የቻይናው ኬሩይ ኦይል ፊልድ /KERUI Oil field/ ኩባንያዎች ደግሞ የጉድጓድ ቁፋሮውን ያከናውናሉ፡፡
የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ከምድር በሚወጣ ተፈጥሯዊ እንፋሎት አማካኝነት 70 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ያለመ ነው፡፡
ታህሳስ 20 ቀን 2013 ዓ.ም
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ
……………///…………...
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ በሚደረገው ዘመቻ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮች እና ሠራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ሊሞ ወረዳ ቆቃ ነገዎ ቀበሌ በመገኘት ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መለስ ሲሎ እንደገለፁት የዘመቻው ዋና ዓላማ መጤ አረሙ በሐይቁና በግድቡ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ተፅዕኖ ለመቀነስ ነው፡፡
በዕለቱም አንድ ሔክታር የሚሸፍን የእምቦጭ አረም የመንቀል እና ለአረሙ ምቹ የሆኑ ደለሎችን የማፅዳት ሥራ መከናወኑንም ነው የጣቢያው ኃላፊ የተናገሩት፡፡
በሐይቁ ላይ የእምቦጭ አረም በፍጥነት እየተስፋፋ የሚሄድ ከሆነ ወደ ግድቡ የሚገባውን የውሃ መጠን በመቀነስ የሚመረተውን ኃይል ሊቀንስ ይችላል ሲሉም ኃላፊው ተፅዕኖውን ገልፀዋል፡፡
ከ50 በላይ የጣቢያውን ሠራተኞች ያሳተፈው ዘመቻ የመጤ አረሙን የመስፋፋት ጉዞ ለመግታት ያለመ ቢሆንም ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑ አንፃር ድጋፉ እና ርብርቡ መቀጠል እንዳለበት አቶ መለስ ተናግረዋል፡፡
መንግሥት ልዩ ትኩረት በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ሐይቁን እና የኃይል ማመንጫ ግድቡን ከመጤ አረም ለመታደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ 60 ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ታህሳስ 27 ቀን 2013 ዓ/ም
……………///…………...
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ በሚደረገው ዘመቻ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮች እና ሠራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ሊሞ ወረዳ ቆቃ ነገዎ ቀበሌ በመገኘት ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መለስ ሲሎ እንደገለፁት የዘመቻው ዋና ዓላማ መጤ አረሙ በሐይቁና በግድቡ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ተፅዕኖ ለመቀነስ ነው፡፡
በዕለቱም አንድ ሔክታር የሚሸፍን የእምቦጭ አረም የመንቀል እና ለአረሙ ምቹ የሆኑ ደለሎችን የማፅዳት ሥራ መከናወኑንም ነው የጣቢያው ኃላፊ የተናገሩት፡፡
በሐይቁ ላይ የእምቦጭ አረም በፍጥነት እየተስፋፋ የሚሄድ ከሆነ ወደ ግድቡ የሚገባውን የውሃ መጠን በመቀነስ የሚመረተውን ኃይል ሊቀንስ ይችላል ሲሉም ኃላፊው ተፅዕኖውን ገልፀዋል፡፡
ከ50 በላይ የጣቢያውን ሠራተኞች ያሳተፈው ዘመቻ የመጤ አረሙን የመስፋፋት ጉዞ ለመግታት ያለመ ቢሆንም ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑ አንፃር ድጋፉ እና ርብርቡ መቀጠል እንዳለበት አቶ መለስ ተናግረዋል፡፡
መንግሥት ልዩ ትኩረት በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ሐይቁን እና የኃይል ማመንጫ ግድቡን ከመጤ አረም ለመታደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ 60 ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ታህሳስ 27 ቀን 2013 ዓ/ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!!
መልካም በዓል!
የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል
መልካም በዓል!
የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል
የኢንዱስትሪ ፍሰቱን ታሳቢ ያደረጉ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው
............////.............
በአማራ ክልል የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየጨመረ በመምጣቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሳድጉ መሠረተ ልማቶችን የመገንባትና አቅም የማሳደግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን እና ጥገና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበቱ አቤ እንደገለፁት ከአሁን በፊት በተዘረጋው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በክልሉ የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ፈላጊ ደንበኞችን ጥያቄ ማስተናገድ አልተቻለም፡፡
ባህርዳር ላይ ባለ 400/230 /132 እና 66 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቢገነባም ተጨማሪ የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ እና የማሻሻያ ሥራ ይፈልጋል ብለዋል።
ይሁንና የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በአዘዞ - ጭልጋ ፣ በለስ - ጃዊ እና ደጀን - ደብረ ማርቆስ አዳዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ግንባታቸው እየተከናወነ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ የቡሬና ባህርዳር ኢንዱስትሪ ዞኖችን ጨምሮ ጥናታቸው የተጠናቀቀ የኤሌክትሪክ ማከፋፊያ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 07 ቀን 2013 ዓ.ም
............////.............
በአማራ ክልል የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እየጨመረ በመምጣቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሳድጉ መሠረተ ልማቶችን የመገንባትና አቅም የማሳደግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን እና ጥገና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ውበቱ አቤ እንደገለፁት ከአሁን በፊት በተዘረጋው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በክልሉ የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ፈላጊ ደንበኞችን ጥያቄ ማስተናገድ አልተቻለም፡፡
ባህርዳር ላይ ባለ 400/230 /132 እና 66 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቢገነባም ተጨማሪ የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ እና የማሻሻያ ሥራ ይፈልጋል ብለዋል።
ይሁንና የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በአዘዞ - ጭልጋ ፣ በለስ - ጃዊ እና ደጀን - ደብረ ማርቆስ አዳዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ግንባታቸው እየተከናወነ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ የቡሬና ባህርዳር ኢንዱስትሪ ዞኖችን ጨምሮ ጥናታቸው የተጠናቀቀ የኤሌክትሪክ ማከፋፊያ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ጥር 07 ቀን 2013 ዓ.ም