EEP Communication
15.6K subscribers
10.8K photos
33 videos
32 files
2.02K links
EEP Communication
Download Telegram
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖራታል
.................///..................
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖራት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሩ ዛሬ በዌቢናር በተካሄደው የዩይትድ ኪንግደምና የአፍሪካ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ሲምፖዚየም ላይ እንደገለፁት በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አቅም ለመፍጠር አቅዳ እየሰራች ነው።

ኢትዮጵያ እስካሁን 6ዐ በመቶ የሚሆኑት ዜጎቿ የኃይል ተጠቃሚ እንዳልሆኑና የኃይል አቅርት ችግሩ ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን እያስከተለ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ይሁንና ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የተለያዩ እቅዶችን በማውጣት እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

እ.ኤ.አ በ2025 ኢትዮጵያ በግሪድና በኦፍ ግሪድ ለዜጎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ለማቅረብ ማቀዷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

ዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪና ቴክኖሎጂ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደ ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ ሃገራት ባለሃብቶች በዘርፉ ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሲምፖዚየሙ ላይ የኢትዮጵያ፣ የሞሮኮ፣ የግብጽ፣ የሞዛምቢክና የሞሪታኒያ ሃገራት የኢነርጂ ሚንስትሮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን 183 ባለድርሻዎችም የዌቢናር ውይይቱን ታድመውታል፡፡

ህዳር 24 ቀን 2013 ዓ/ም
የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው
=========////=========

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ቋሚ ሠራተኞች ሀብት የመመዝገብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና መምሪያ አስታወቀ፡፡


የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርጋ ተረፈ እንዳስታወቁት የፌዴራል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሀብትና ንብረትን ለማስመዝገብ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ ሁሉም የተቋሙ ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው፡፡

በተቋሙ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የሥራ መሪዎች እና በተመረጡ የሥራ መደቦች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች ሀብታቸውን አሳውቀው ማስመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ሁሉም የመንግስት ሠራተኛ ሀብቱን እንዲያሳውቅና እንዲያስመዘግብ የተደረገው የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ለማስፈፀም የወጣው የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር 1/2013 ስለሚያስገድድ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አቶ መርጋ ገለፃ በተቋሙ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ከሚጠበቅባቸው 6 ሺህ 565 ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ውስጥ ለ5 ሺህ 7 መቶ ሠራተኞች የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ ቅጽ ተደራሽ ተደርጓል፡፡

ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስም ከ3 ሺህ 7 መቶ በላይ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብትና ንብረታቸውን አስመዝግበዋል፡፡


ህዳር 25 ቀን 2013 ዓ/ም
ሴቶች ከሁሉም ዓይነት ጭቆና ነፃ እስካልሆኑ ድረስ ነፃነት ተጎናጽፈናል ማለት አይቻልም!
ኔልሰን ማንዴላ
በተቋሙ የድጋፍና እንክብካቤ ትግበራ እየተከናወነ ነው
………………////……………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤችአይቪ መከላከልና መቆጣጠር የሥራ ክፍል የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽንን ከመከላከል በተጨማሪ የድጋፍና እንክብካቤ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
ኤች.አ.ቪ / ኤድስ በተቋሙ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመከላከል በፖሊሲ የተደገፈ የድጋፍና ክብካቤ ሥርዐት ዘርግቶ እየሰራ መሆኑን የስራ ክፍሉ አስታውቋል፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞች ከኤችአይቪ ጋር የተያያዘ ህመም ከታከሙ ለሕክምና የሚያዋጡት የ10 በመቶ ወጪ መጋራት እንዲቀር ተደርጓል፡፡
እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ሠራተኞቹ ጤነኛ ሆነው በሥራቸው እንዲቀጥሉ የማድረግ ስራዎችም ተከናውነዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ በወር ብር 5 ብር በማዋጣት በድምሩ በየወሩ እስከ ብር 35 ሺህ በኤድስ አስተዋጽኦ (Contrubtion ) አካውንት እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡
በተሰብሳቢ ገንዘቡም ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝ 39 (ሰላሳ ዘጠኝ) የተቋሙ ሠራተኞች በየወሩ 7 መቶ ብር ከደሞዝ ጋር በአካውንታቸው እንዲገባ፣ ወላጆቻቸውን በኤች.አ.ቪ / ኤድስ ላጡ 21(ሃያ አንድ) ህፃናት በየወሩ በአሳዳጊዎቻቸው አካውንት ብር 500 እና በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ለትምህርት ቁሳቁስ መግዣ በአንድ ልጅ እስከ ብር 1650 ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሰራተኞች በወር 35 ሺህ ብር ቢሰበሰብም ወጪ ድጋፍ እየተደረገ ያለው ከሚሰበሰበው በላይ በመሆኑ ልዩነቱ ድጋፉ ከመጀመሩ በፊት በአካውንቱ ውስጥ ከተጠራቀመ ገንዘብ ላይ እየተከፈለ ይገኛል፡፡
ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.
ተቋሙ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እና የፀረ ሙስና ቀን አከበረ
………../////……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሰራተኞች “እኩልነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለጋራ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል 15ኛውን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ፡፡
የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበዓሉ ላይ እንደተናገሩት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር በህዝቦች እኩልነት ላይ የተመሰረተ እውነተኛና ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት ዲሞክራሲ ለመገንባት ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማገዝ ተቋማችን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሚከበረው ከሃዲው የህወሓት ጁንታ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባደረገው ታላቅ ተጋድሎ በተገኘው ድል ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ባሸነፈበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
በተያያዘ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች “የትውልድ ሥነ ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በመታገል የብልፅግና ጉዟችንን እናፋጥን” በሚል መሪ ቃል 16ኛው የፀረ ሙስና ቀን አክብረዋል፡፡

ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.
በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሠራ ነው
..............///........
በትግራይ ክልል ስግብግቡ የህወኃት ጁንታ ጉዳት ያደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ጠግኖ ሁሉንም የክልሉ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን አስታወቁ፡፡
የጥገና ስራውን በክልሉ ሙሉ በሙሉ ለማከናወንም ከተቋሙ የተውጣጣ የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን በሁለት መስመር መሰማራቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ አንደኛው ቡድን በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በመንቀሳቀስ ከባህርዳር ተነስቶ ወልቃይት፣ሁመራ፣ ወልቃይት፣ ሽሬ፣ አክሱም እና አድዋ ለሚገኙ የኃይል መሰረተ ልማቶች የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ላይ ሲሆን በሰሜን ምስራቅ የተንቀሳቀሰው ሁለተኛው ቡድን ደግሞ ከደሴ በመነሳት አላማጣ፣መሆኒ፣ሰቆጣ፣አሸጎዳ፣መቀሌና አዴግራት አካባቢዎች ላይ የጥገና ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
እስከአሁን በመተማ፣ሁመራ፣ወልቃይት እና ማይጨው የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ከአላማጣ-ሰቆጣ የተዘረጋውን ባለ 66 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን የአላማጣ እና ሰቆጣ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ መደረጉንም ነው አቶ ሞገስ ያብራሩት፡፡
በአሁኑ ጊዜ የመቀሌ-መሆኒ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል መስመር የጥገና ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ የመቀሌ ከተማ በቅርቡ የኤሌክትሪክ ኃይል እንድታገኝ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
እስከመጪው እሁድ አብዛኞቹ የትግራይ ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ በሙሉ አቅም ርብርብ እየተደረገ ነውም ብለዋል
የመቀሌ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ አግኝቷል
..................////............
የመቀሌ ከተማና አካባቢው ከሳምንታት የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቋረጥ በኋላ ዛሬ አገልግሎት አግኝቷል።

ከአላማጣ ከተማ አንስቶ እስከ መቀሌ ድረስ ባሉ ከተሞች በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሽቦዎች( ኮንዳክተሮች) እና ስኒዎች(ኢንሱሌተሮቸ) ላይ የህወሀት ጁንታ ቡድን ባደረሰው ጥቃት በአካባቢዎቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል።

በጁንታው ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ጠግኖ ሁሉንም የክልሉ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሁለት የጥገና ቡድኖችን አዋቅሮ ቀን ከሌት ሲሰራ ቆይቷል።

በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የተሰማራው የጥገና ቡድን በመተማ፣ሁመራና ወልቃይት የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ በማጠናቀቅ ከተሞቹ ኃይል እንዲያገኙ አድርጓል።

ከደሴ በመነሳት ወደሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ የተሰማራው የጥገና ቡድን ደግሞ ከቀናት በፊት የአላማጣ፣ ማይጨው፣ መሆኒነና ሰቆጣ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ያደረገ ሲሆን ዛሬ የመቀሌ፣ ኲዊሀ፣ አዲጉዶምና አካባቢው ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማድረግ ችሏል።

በስፍራው የተሰማሩ የጥገና ባለሙያዎች አስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታዎችን ታግለው ሌት ተቀን በመስራት ለዚህ ውጤት በመድረሳቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አልፎ ሀገርንና ህዝብን እንደማገልገል የሚያስደስት ነገር እንደማይኖር በተግባር ስላሳያችሁን በሥራችሁ ኮርተናል ሲሉ የተሰማቸውን ስሜት ገልፀዋል።

ታህሳስ 04 ቀን 2013 ዓ/ም
በአዲግራትና ውቅሮ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም ጀምሯል
................///..............
በአዲግራትና ውቅሮ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የመብራት አገልግሎት ዛሬ ማምሻውን ጀምሯል።

በህወሃት ጁንታ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በአፋጣኝ ወደ አገልግሎት ለመመለስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሲሰራ ቆይቷል።

የውቅሮና አዲግራት ከተሞች የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ የፍተሻ ስራ ተከናውኖ ከተሞቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል።

የሽሬ፣ አክሱምና አድዋ ከተሞች ኃይል እንዲያገኙም በቅንጅት በመሰራት ላይ ነው።

ታህሳስ 08 ቀን 2013 ዓ/ም
የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቀቀ
............../////...........
የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፊያ ጣቢያ ቢሮ አስታወቀ፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሠላሳ ዓመታት በላይ ለሻሸመኔ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በየጊዜው እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ማስተናገድ እንዳልቻለ ሪጅኑ ጠቁሟል፡፡
25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመሸከም አቅም በነበረው አንድ ትራንስፎርመር ለከተማውና አጎራባች አካባቢዎች ኃይል ለማዳረስ ጥረት ሲደረግ ቢቆይም ፍላጎቱ ከጣቢያው አቅም በላይ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ይህም በሻሸመኔ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ኤሌክትሪክ በፈረቃ እንዲሰጥ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ አሳድሮ እንደነበር ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ጣቢያው ያለበትን ችግር ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር መሸከም የሚችል የኃይል ትራንስፎርመር በመትከልና የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን አቅሙን በእጥፍ ለማሳደግ እንደተቻለ አስታውቋል፡፡
15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው 6 ወጪ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመቆጣጠሪያና የመከላከያ መሳሪያዎችን በአዲስ መልክ የመትከል ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡
ለማስፋፊያ እና ማሻሻያ ሥራው ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ መስጠት መቻሉን ሪጅኑ ገልጿል፡፡
ታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ/ም