ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ
……………….///……………..
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው አልፎ አልፎ የሚያጋጥመውን የግብዓት አቅርቦት እና የጥገና ሥራዎች ዙሪያ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ከተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡
በማመንጫው በሚከናወን የጥገና ስራ፣ የተረፈ ምርት አወጋገድ እና የኬሚካል አቅርቦት ላይ እየተሰሩ ስላሉ ሥራዎች ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ ተደርጎለታል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ ከተቋሙ ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አረጋግጠዋል፡፡
በ2010 ዓ.ም መጨረሻ ተመርቆ ከወራት የሙከራና ፍተሻ ሂደት በኋላ ሥራ የጀመረው ረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ በዓመት በአማካይ 185 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ባለፈው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ኢነርጂ ማምረት ከቻሉ የኃይል ማመንጫዎች መካከል አንዱ ነው፡፡
ምክትል ከንቲባዋ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ሥፍራውን የጎበኙ ሲሆን ከሠራተኞች ጋርም ተነጋግረዋል፡፡
ህዳር 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
……………….///……………..
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው አልፎ አልፎ የሚያጋጥመውን የግብዓት አቅርቦት እና የጥገና ሥራዎች ዙሪያ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ከተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡
በማመንጫው በሚከናወን የጥገና ስራ፣ የተረፈ ምርት አወጋገድ እና የኬሚካል አቅርቦት ላይ እየተሰሩ ስላሉ ሥራዎች ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ ተደርጎለታል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ ከተቋሙ ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አረጋግጠዋል፡፡
በ2010 ዓ.ም መጨረሻ ተመርቆ ከወራት የሙከራና ፍተሻ ሂደት በኋላ ሥራ የጀመረው ረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ በዓመት በአማካይ 185 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ባለፈው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ኢነርጂ ማምረት ከቻሉ የኃይል ማመንጫዎች መካከል አንዱ ነው፡፡
ምክትል ከንቲባዋ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ሥፍራውን የጎበኙ ሲሆን ከሠራተኞች ጋርም ተነጋግረዋል፡፡
ህዳር 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል
……………/////………………
ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል፡፡
በቴክኒክ ችግር የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የቴክኒክ ክፍል ባልደረቦቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ናቸው።
በቀጣይ አንድ ሰዓት ውስጥ ደረጃ በደረጃ ኃይል የማገናኘት ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል።
ህዳር 15 ቀን 2013
……………/////………………
ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል፡፡
በቴክኒክ ችግር የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የቴክኒክ ክፍል ባልደረቦቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ናቸው።
በቀጣይ አንድ ሰዓት ውስጥ ደረጃ በደረጃ ኃይል የማገናኘት ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል።
ህዳር 15 ቀን 2013
በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ከሁለት ሰዓት በላይ ተቋርጦ የነበረውን ኃይል በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ማገናኘት ተጀምሯል።
ደረጃ በደረጃ የተቀሩትን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ የማድረግ ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል።
ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም
ደረጃ በደረጃ የተቀሩትን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ የማድረግ ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል።
ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ
----------------------//------------------------
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች “ደም እንለግስ፤ ህይወት እንታደግ” በሚል መሪ ቃል ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም የደም እጥረት ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል ደም ለግሰዋል፡፡
ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ኃይል ከማመንጨት ሀገራዊ ተልዕኮው ባለፈ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል፡፡
በዛሬው ዕለትም በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸውና በደም ዕጦት ምክንያት ህይወታቸው አደጋ ላይ የወደቀ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ደም በመለገስ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡
የተደረገው የደም ልገሳ በጤና ተቋማት የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቅረፍ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡
‹
ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው የተቋሙ ሠራተኞች ደም መለገስ በመቻላቸው እንደተደሰቱ እና በቀጣይ መሰል ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
የደም ልገሳ መርሀ ግብሩ ለሀገር የሚከፈል ዋጋን መደገፍ ነው ያሉት ሠራተኞቹ የሚለገሰው ደም ለአንድ የቤተሰብ አባል እንደሚውል በማሰብ ሁሉም ሊሳተፍበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
¬
በብሄራዊ የደም ባንክ አገልግሎት የተንቀሳቃሽ ደም ለጋሾች ባለሙያ ሲስተር ዘውዴ ግዛቸው እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ የበርካታ ወገኖቻቸውን ህይወት መታደግ እንደሚቻል በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊመሰገኑ ይገባል፡፡
ሌሎች ተቋማትም ይህን አርዓያ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም.
----------------------//------------------------
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች “ደም እንለግስ፤ ህይወት እንታደግ” በሚል መሪ ቃል ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም የደም እጥረት ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል ደም ለግሰዋል፡፡
ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ኃይል ከማመንጨት ሀገራዊ ተልዕኮው ባለፈ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል፡፡
በዛሬው ዕለትም በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸውና በደም ዕጦት ምክንያት ህይወታቸው አደጋ ላይ የወደቀ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ደም በመለገስ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡
የተደረገው የደም ልገሳ በጤና ተቋማት የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቅረፍ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡
‹
ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው የተቋሙ ሠራተኞች ደም መለገስ በመቻላቸው እንደተደሰቱ እና በቀጣይ መሰል ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
የደም ልገሳ መርሀ ግብሩ ለሀገር የሚከፈል ዋጋን መደገፍ ነው ያሉት ሠራተኞቹ የሚለገሰው ደም ለአንድ የቤተሰብ አባል እንደሚውል በማሰብ ሁሉም ሊሳተፍበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
¬
በብሄራዊ የደም ባንክ አገልግሎት የተንቀሳቃሽ ደም ለጋሾች ባለሙያ ሲስተር ዘውዴ ግዛቸው እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ የበርካታ ወገኖቻቸውን ህይወት መታደግ እንደሚቻል በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊመሰገኑ ይገባል፡፡
ሌሎች ተቋማትም ይህን አርዓያ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም.
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖራታል
.................///..................
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖራት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ በዌቢናር በተካሄደው የዩይትድ ኪንግደምና የአፍሪካ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ሲምፖዚየም ላይ እንደገለፁት በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አቅም ለመፍጠር አቅዳ እየሰራች ነው።
ኢትዮጵያ እስካሁን 6ዐ በመቶ የሚሆኑት ዜጎቿ የኃይል ተጠቃሚ እንዳልሆኑና የኃይል አቅርት ችግሩ ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን እያስከተለ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ይሁንና ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የተለያዩ እቅዶችን በማውጣት እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ2025 ኢትዮጵያ በግሪድና በኦፍ ግሪድ ለዜጎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ለማቅረብ ማቀዷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪና ቴክኖሎጂ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደ ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ ሃገራት ባለሃብቶች በዘርፉ ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በሲምፖዚየሙ ላይ የኢትዮጵያ፣ የሞሮኮ፣ የግብጽ፣ የሞዛምቢክና የሞሪታኒያ ሃገራት የኢነርጂ ሚንስትሮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን 183 ባለድርሻዎችም የዌቢናር ውይይቱን ታድመውታል፡፡
ህዳር 24 ቀን 2013 ዓ/ም
.................///..................
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖራት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ በዌቢናር በተካሄደው የዩይትድ ኪንግደምና የአፍሪካ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ሲምፖዚየም ላይ እንደገለፁት በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አቅም ለመፍጠር አቅዳ እየሰራች ነው።
ኢትዮጵያ እስካሁን 6ዐ በመቶ የሚሆኑት ዜጎቿ የኃይል ተጠቃሚ እንዳልሆኑና የኃይል አቅርት ችግሩ ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን እያስከተለ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ይሁንና ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የተለያዩ እቅዶችን በማውጣት እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ2025 ኢትዮጵያ በግሪድና በኦፍ ግሪድ ለዜጎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ለማቅረብ ማቀዷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
ዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪና ቴክኖሎጂ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደ ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ ሃገራት ባለሃብቶች በዘርፉ ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በሲምፖዚየሙ ላይ የኢትዮጵያ፣ የሞሮኮ፣ የግብጽ፣ የሞዛምቢክና የሞሪታኒያ ሃገራት የኢነርጂ ሚንስትሮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን 183 ባለድርሻዎችም የዌቢናር ውይይቱን ታድመውታል፡፡
ህዳር 24 ቀን 2013 ዓ/ም
የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው
=========////=========
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ቋሚ ሠራተኞች ሀብት የመመዝገብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርጋ ተረፈ እንዳስታወቁት የፌዴራል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሀብትና ንብረትን ለማስመዝገብ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ ሁሉም የተቋሙ ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው፡፡
በተቋሙ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የሥራ መሪዎች እና በተመረጡ የሥራ መደቦች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች ሀብታቸውን አሳውቀው ማስመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ሁሉም የመንግስት ሠራተኛ ሀብቱን እንዲያሳውቅና እንዲያስመዘግብ የተደረገው የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ለማስፈፀም የወጣው የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር 1/2013 ስለሚያስገድድ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አቶ መርጋ ገለፃ በተቋሙ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ከሚጠበቅባቸው 6 ሺህ 565 ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ውስጥ ለ5 ሺህ 7 መቶ ሠራተኞች የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ ቅጽ ተደራሽ ተደርጓል፡፡
ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስም ከ3 ሺህ 7 መቶ በላይ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብትና ንብረታቸውን አስመዝግበዋል፡፡
ህዳር 25 ቀን 2013 ዓ/ም
=========////=========
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ቋሚ ሠራተኞች ሀብት የመመዝገብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርጋ ተረፈ እንዳስታወቁት የፌዴራል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሀብትና ንብረትን ለማስመዝገብ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ ሁሉም የተቋሙ ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው፡፡
በተቋሙ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የሥራ መሪዎች እና በተመረጡ የሥራ መደቦች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች ሀብታቸውን አሳውቀው ማስመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ሁሉም የመንግስት ሠራተኛ ሀብቱን እንዲያሳውቅና እንዲያስመዘግብ የተደረገው የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ለማስፈፀም የወጣው የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር 1/2013 ስለሚያስገድድ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አቶ መርጋ ገለፃ በተቋሙ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ከሚጠበቅባቸው 6 ሺህ 565 ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ውስጥ ለ5 ሺህ 7 መቶ ሠራተኞች የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ ቅጽ ተደራሽ ተደርጓል፡፡
ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስም ከ3 ሺህ 7 መቶ በላይ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብትና ንብረታቸውን አስመዝግበዋል፡፡
ህዳር 25 ቀን 2013 ዓ/ም
በተቋሙ የድጋፍና እንክብካቤ ትግበራ እየተከናወነ ነው
………………////……………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤችአይቪ መከላከልና መቆጣጠር የሥራ ክፍል የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽንን ከመከላከል በተጨማሪ የድጋፍና እንክብካቤ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
ኤች.አ.ቪ / ኤድስ በተቋሙ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመከላከል በፖሊሲ የተደገፈ የድጋፍና ክብካቤ ሥርዐት ዘርግቶ እየሰራ መሆኑን የስራ ክፍሉ አስታውቋል፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞች ከኤችአይቪ ጋር የተያያዘ ህመም ከታከሙ ለሕክምና የሚያዋጡት የ10 በመቶ ወጪ መጋራት እንዲቀር ተደርጓል፡፡
እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ሠራተኞቹ ጤነኛ ሆነው በሥራቸው እንዲቀጥሉ የማድረግ ስራዎችም ተከናውነዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ በወር ብር 5 ብር በማዋጣት በድምሩ በየወሩ እስከ ብር 35 ሺህ በኤድስ አስተዋጽኦ (Contrubtion ) አካውንት እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡
በተሰብሳቢ ገንዘቡም ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝ 39 (ሰላሳ ዘጠኝ) የተቋሙ ሠራተኞች በየወሩ 7 መቶ ብር ከደሞዝ ጋር በአካውንታቸው እንዲገባ፣ ወላጆቻቸውን በኤች.አ.ቪ / ኤድስ ላጡ 21(ሃያ አንድ) ህፃናት በየወሩ በአሳዳጊዎቻቸው አካውንት ብር 500 እና በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ለትምህርት ቁሳቁስ መግዣ በአንድ ልጅ እስከ ብር 1650 ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሰራተኞች በወር 35 ሺህ ብር ቢሰበሰብም ወጪ ድጋፍ እየተደረገ ያለው ከሚሰበሰበው በላይ በመሆኑ ልዩነቱ ድጋፉ ከመጀመሩ በፊት በአካውንቱ ውስጥ ከተጠራቀመ ገንዘብ ላይ እየተከፈለ ይገኛል፡፡
ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.
………………////……………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤችአይቪ መከላከልና መቆጣጠር የሥራ ክፍል የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽንን ከመከላከል በተጨማሪ የድጋፍና እንክብካቤ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
ኤች.አ.ቪ / ኤድስ በተቋሙ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመከላከል በፖሊሲ የተደገፈ የድጋፍና ክብካቤ ሥርዐት ዘርግቶ እየሰራ መሆኑን የስራ ክፍሉ አስታውቋል፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞች ከኤችአይቪ ጋር የተያያዘ ህመም ከታከሙ ለሕክምና የሚያዋጡት የ10 በመቶ ወጪ መጋራት እንዲቀር ተደርጓል፡፡
እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ሠራተኞቹ ጤነኛ ሆነው በሥራቸው እንዲቀጥሉ የማድረግ ስራዎችም ተከናውነዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ በወር ብር 5 ብር በማዋጣት በድምሩ በየወሩ እስከ ብር 35 ሺህ በኤድስ አስተዋጽኦ (Contrubtion ) አካውንት እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡
በተሰብሳቢ ገንዘቡም ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝ 39 (ሰላሳ ዘጠኝ) የተቋሙ ሠራተኞች በየወሩ 7 መቶ ብር ከደሞዝ ጋር በአካውንታቸው እንዲገባ፣ ወላጆቻቸውን በኤች.አ.ቪ / ኤድስ ላጡ 21(ሃያ አንድ) ህፃናት በየወሩ በአሳዳጊዎቻቸው አካውንት ብር 500 እና በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ለትምህርት ቁሳቁስ መግዣ በአንድ ልጅ እስከ ብር 1650 ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሰራተኞች በወር 35 ሺህ ብር ቢሰበሰብም ወጪ ድጋፍ እየተደረገ ያለው ከሚሰበሰበው በላይ በመሆኑ ልዩነቱ ድጋፉ ከመጀመሩ በፊት በአካውንቱ ውስጥ ከተጠራቀመ ገንዘብ ላይ እየተከፈለ ይገኛል፡፡
ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.
ተቋሙ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እና የፀረ ሙስና ቀን አከበረ
………../////……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሰራተኞች “እኩልነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለጋራ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል 15ኛውን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ፡፡
የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበዓሉ ላይ እንደተናገሩት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር በህዝቦች እኩልነት ላይ የተመሰረተ እውነተኛና ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት ዲሞክራሲ ለመገንባት ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማገዝ ተቋማችን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሚከበረው ከሃዲው የህወሓት ጁንታ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባደረገው ታላቅ ተጋድሎ በተገኘው ድል ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ባሸነፈበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
በተያያዘ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች “የትውልድ ሥነ ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በመታገል የብልፅግና ጉዟችንን እናፋጥን” በሚል መሪ ቃል 16ኛው የፀረ ሙስና ቀን አክብረዋል፡፡
ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.
………../////……….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሰራተኞች “እኩልነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለጋራ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል 15ኛውን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ፡፡
የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበዓሉ ላይ እንደተናገሩት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር በህዝቦች እኩልነት ላይ የተመሰረተ እውነተኛና ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት ዲሞክራሲ ለመገንባት ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማገዝ ተቋማችን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሚከበረው ከሃዲው የህወሓት ጁንታ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባደረገው ታላቅ ተጋድሎ በተገኘው ድል ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ባሸነፈበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
በተያያዘ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች “የትውልድ ሥነ ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በመታገል የብልፅግና ጉዟችንን እናፋጥን” በሚል መሪ ቃል 16ኛው የፀረ ሙስና ቀን አክብረዋል፡፡
ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.