የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ
……………./////……………
የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እና የዕድገት መሰላል ትግበራ የተቋሙን የአፈፃፀም አቅም ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ገለፁ፡፡
ተቋሙ 27 ለሚሆኑ የስራ መሪዎችና ሠራተኞች የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እንዲሁም የዕድገት መሰላል ቀረፃና ትግበራ ላይ ያተኮረ የ5 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ሠልጣኞች በቆይታቸው በብቃት ማዕቀፍ ሞዴል፣ የብቃት ማዕቀፍ አስተዳደር ጥቅሞች ፣ የብቃት ማዕቀፍ ማፒንግ፤ የዕድገት መሰላል ዕቅድ እና ልማት እንዲሁም በሌሎች ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች የፅንሰ ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አግኝተዋል፡፡
በተቋሙ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ እንዳሉት በእያንዳንዱ የስራ መደብ የተለያዩ እርከን ያላቸው የብቃት ማዕቀፍ ደረጃዎች ተዘጋጅተዋል፡፡
የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ካላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ-ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ልምድ መወሰዱን ዶ/ር ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ላይ የተገኙ ግብአቶችን በማካተት በቀጣይ አንድ ተጨማሪ ውይይት ከተካሔደ በኋላ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ነው ዶ/ር ወንድወሰን ያስታወቁት፡፡
ህዳር 09 ቀን 2013 ዓ/ም
……………./////……………
የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እና የዕድገት መሰላል ትግበራ የተቋሙን የአፈፃፀም አቅም ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ገለፁ፡፡
ተቋሙ 27 ለሚሆኑ የስራ መሪዎችና ሠራተኞች የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት እንዲሁም የዕድገት መሰላል ቀረፃና ትግበራ ላይ ያተኮረ የ5 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ሠልጣኞች በቆይታቸው በብቃት ማዕቀፍ ሞዴል፣ የብቃት ማዕቀፍ አስተዳደር ጥቅሞች ፣ የብቃት ማዕቀፍ ማፒንግ፤ የዕድገት መሰላል ዕቅድ እና ልማት እንዲሁም በሌሎች ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች የፅንሰ ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አግኝተዋል፡፡
በተቋሙ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ እንዳሉት በእያንዳንዱ የስራ መደብ የተለያዩ እርከን ያላቸው የብቃት ማዕቀፍ ደረጃዎች ተዘጋጅተዋል፡፡
የብቃት ማዕቀፍ ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ካላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ-ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ልምድ መወሰዱን ዶ/ር ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ላይ የተገኙ ግብአቶችን በማካተት በቀጣይ አንድ ተጨማሪ ውይይት ከተካሔደ በኋላ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ነው ዶ/ር ወንድወሰን ያስታወቁት፡፡
ህዳር 09 ቀን 2013 ዓ/ም