በዋና ሥራ አስፈፃሚው የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎበኘ
................./////...............
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎብኝቷል።
የግድቡ ግንባታ አሁን የደረሰበትን ደረጃ፣ ቀሪ ግንባታውን ለማፋጠንና ለሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተሰሩ ያሉት ወሳኝ ስራዎችን በተመለከተ በግድቡ ግንባታ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢ/ ር ኤፍሬም ገ/ኪዳን ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
የዋናውን ግድብ ፣ የኮርቻ ቅርፅ ግድቡን የኃይልማመንጫ ቤቱንና ውሃው በግድቡ ላይ የሚፈስበትን ስፍራ ቡድኑ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።
የስራ አመራር ቡድኑ ጉብኝት ዋና ዓላማ በመጀመሪያ ዙር የውሃ መሊት የተመዘገበውን ስኬት በስፍራው በመገኘት ለመመልከትና የፕሮጀክት አስተዳደሩን ለማገዝ ነው።
ይህን መሰል ጉብኝት መዘጋጀቱ የሥራ አመራሩ ፕሮጀክቶችን በቅርበት በመመልከት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ለመስጠት እንደሚያግዘው ታምኖበታል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን በጋራ ሲጎበኝ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው።
የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ በአሁኑ ወቅት 76 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል።
በተያያዘ ዜና የስራ አመራር ቡድኑ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት የተካተተውንና በኮይሻ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትንም ጎብኝቷል።
ጥቅምት 15 ቀን 2013 ዓ/ም
................./////...............
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎብኝቷል።
የግድቡ ግንባታ አሁን የደረሰበትን ደረጃ፣ ቀሪ ግንባታውን ለማፋጠንና ለሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተሰሩ ያሉት ወሳኝ ስራዎችን በተመለከተ በግድቡ ግንባታ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢ/ ር ኤፍሬም ገ/ኪዳን ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
የዋናውን ግድብ ፣ የኮርቻ ቅርፅ ግድቡን የኃይልማመንጫ ቤቱንና ውሃው በግድቡ ላይ የሚፈስበትን ስፍራ ቡድኑ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።
የስራ አመራር ቡድኑ ጉብኝት ዋና ዓላማ በመጀመሪያ ዙር የውሃ መሊት የተመዘገበውን ስኬት በስፍራው በመገኘት ለመመልከትና የፕሮጀክት አስተዳደሩን ለማገዝ ነው።
ይህን መሰል ጉብኝት መዘጋጀቱ የሥራ አመራሩ ፕሮጀክቶችን በቅርበት በመመልከት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ለመስጠት እንደሚያግዘው ታምኖበታል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን በጋራ ሲጎበኝ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው።
የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ በአሁኑ ወቅት 76 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል።
በተያያዘ ዜና የስራ አመራር ቡድኑ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት የተካተተውንና በኮይሻ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትንም ጎብኝቷል።
ጥቅምት 15 ቀን 2013 ዓ/ም
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
………….///……….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ሴቶችን ተሳትፎና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የተቋሙ የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዲኤ ገለፁ፡፡
በተቋሙ በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች፣ በኦፕሬሽንና በሁሉም የስራ መስኮች ከጥናት ጀምሮ እስከ ትግበራ ድረስ ባለው ሰንሰለት ሴቶችን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በስፋት መከናወን እንዳለባቸው በስርዓተ ፆታና ስርፀት ላይ ትኩረት ባደረገው የአምስት ቀናት ስልጠና መዝጊያ ላይ ገልፀዋል፡፡
ወ/ሮ ሌንሴ እንዳሉት ከህብረተሠቡ 50 በመቶ የሚሆኑትን ሴቶች ያገለለ ልማት ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡
በመሆኑም ውጤታማ ስራ ለማከናወን ከተፈለገ ሴቶችን በየደረጃው ተሳታፊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለአምስት ቀናት በቆየው ስልጠና የስርዓተ ፆታ ምንነትና የተዛቡ አመለካከቶች፣ የስርዓተ ፆታ ትንተና፣ የስርዓተ ፆታ ዓለማቀፋዊና ሀገራዊ ነባራዊ እንዲሁም የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቲጂካዊ ሥራዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጧል፡፡
ስልጠናው የተሰጠው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ 25 ባለሙያዎች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ካሉት አጠቃላይ ሠራተኞች ብዛት 15 በመቶዎች ሴቶች መሆናቸውን የተቋሙ የሰው ሀብት መረጃ ያመላክታል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም
………….///……….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ሴቶችን ተሳትፎና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የተቋሙ የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዲኤ ገለፁ፡፡
በተቋሙ በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች፣ በኦፕሬሽንና በሁሉም የስራ መስኮች ከጥናት ጀምሮ እስከ ትግበራ ድረስ ባለው ሰንሰለት ሴቶችን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በስፋት መከናወን እንዳለባቸው በስርዓተ ፆታና ስርፀት ላይ ትኩረት ባደረገው የአምስት ቀናት ስልጠና መዝጊያ ላይ ገልፀዋል፡፡
ወ/ሮ ሌንሴ እንዳሉት ከህብረተሠቡ 50 በመቶ የሚሆኑትን ሴቶች ያገለለ ልማት ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡
በመሆኑም ውጤታማ ስራ ለማከናወን ከተፈለገ ሴቶችን በየደረጃው ተሳታፊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለአምስት ቀናት በቆየው ስልጠና የስርዓተ ፆታ ምንነትና የተዛቡ አመለካከቶች፣ የስርዓተ ፆታ ትንተና፣ የስርዓተ ፆታ ዓለማቀፋዊና ሀገራዊ ነባራዊ እንዲሁም የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቲጂካዊ ሥራዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጧል፡፡
ስልጠናው የተሰጠው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ 25 ባለሙያዎች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ካሉት አጠቃላይ ሠራተኞች ብዛት 15 በመቶዎች ሴቶች መሆናቸውን የተቋሙ የሰው ሀብት መረጃ ያመላክታል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም
ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
………………….////………………..
የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ የሙከራና ፍተሻ ሥራ ለመስራት መታቀዱን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡
የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጁ አቶ ኢዮሲያስ ኃይለማርያም እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቤት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የመኖሪያ እና የቢሮ ግንባታዎች በመከናወን ላይ ነው፡፡
የግንባታ ስራው ህዳር 2011 ፕሮጀክቱ ለአፍዴራ እና አካባቢው ነዋሪዎች ብሎም ለጨው ማምረቻና የአዮዲን ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ አልሞ የተገነባ ነው፡፡
በአፍዴራ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ የኃይል ትራንስፎርመር እንደሚገጠምለት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በረሃማ በሆነ አካባቢ የሚገኝ ቢሆንም ተቋራጩ ጥልቅ ቁፋሮ በማካሔድ ለግንባታ እና ለመጠጥ የሚያገለግል ውሃ ማቅረቡንና ይህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ለጣቢያው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆነውና 195 ኪ.ሜ የሚረዝመው የሠመራ-አፍዴራ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም.
………………….////………………..
የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ የሙከራና ፍተሻ ሥራ ለመስራት መታቀዱን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡
የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጁ አቶ ኢዮሲያስ ኃይለማርያም እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቤት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የመኖሪያ እና የቢሮ ግንባታዎች በመከናወን ላይ ነው፡፡
የግንባታ ስራው ህዳር 2011 ፕሮጀክቱ ለአፍዴራ እና አካባቢው ነዋሪዎች ብሎም ለጨው ማምረቻና የአዮዲን ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ አልሞ የተገነባ ነው፡፡
በአፍዴራ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ የኃይል ትራንስፎርመር እንደሚገጠምለት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በረሃማ በሆነ አካባቢ የሚገኝ ቢሆንም ተቋራጩ ጥልቅ ቁፋሮ በማካሔድ ለግንባታ እና ለመጠጥ የሚያገለግል ውሃ ማቅረቡንና ይህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ለጣቢያው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆነውና 195 ኪ.ሜ የሚረዝመው የሠመራ-አፍዴራ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም.
የአዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ
…………./////………..
በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ በጎርፍ ተጥለቅልቆ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ከነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሞ ነበር፡፡
በወቅቱ ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ ተውጠው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።
ለሁለት ወራት አካባቢ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው ጣቢያ አንድ ዩኒት ወደስራ ማስገባት በመቻሉ ጣቢያው በከፊል ስራ የጀመረ ሲሆን ቀሪውን አንድ ዩኒት ስራ ለማስጀመር በሂደት ላይ ይገኛል።
ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ/ም
…………./////………..
በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ በጎርፍ ተጥለቅልቆ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ከነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሞ ነበር፡፡
በወቅቱ ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ ተውጠው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።
ለሁለት ወራት አካባቢ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው ጣቢያ አንድ ዩኒት ወደስራ ማስገባት በመቻሉ ጣቢያው በከፊል ስራ የጀመረ ሲሆን ቀሪውን አንድ ዩኒት ስራ ለማስጀመር በሂደት ላይ ይገኛል።
ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ/ም
የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈረመ
…………….////……………….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የተሰኘ የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም ተፈራርመዋል፡፡
ሥምምነቱ በዋናነት የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን ከተቋሙ የሥራ ባህሪ አንፃር የመተግበር እና የማዘመን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ሥምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓትን ከሰባት ዓመት በላይ የተገበረውና ውጤታማ አፈፃፀም ያስመዘገበበት በመሆኑ ተቋሙ በቀላሉ ወደ ትግበራ እንዲገባ እና የተሻለ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ ይረዳዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም በበኩላቸው ሁለቱ ተቋማት በርካታ ሥራዎችን በትብብር በመስራት መልካም ግንኙነት መመስረታቸውን ተናግረዋል፡፡
ስምምነት የተፈረመበትን የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስራ በተያዘለት በጀትና ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም.
…………….////……………….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የተሰኘ የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም ተፈራርመዋል፡፡
ሥምምነቱ በዋናነት የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን ከተቋሙ የሥራ ባህሪ አንፃር የመተግበር እና የማዘመን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ሥምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓትን ከሰባት ዓመት በላይ የተገበረውና ውጤታማ አፈፃፀም ያስመዘገበበት በመሆኑ ተቋሙ በቀላሉ ወደ ትግበራ እንዲገባ እና የተሻለ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ ይረዳዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም በበኩላቸው ሁለቱ ተቋማት በርካታ ሥራዎችን በትብብር በመስራት መልካም ግንኙነት መመስረታቸውን ተናግረዋል፡፡
ስምምነት የተፈረመበትን የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) መሰረተ ልማት ዝርጋታና አቅም ግንባታ ስራ በተያዘለት በጀትና ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም.
ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) ተግባራዊ ለማድረግ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋል ተባለ
.....///.…...
ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን በተቋሙ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሞደርናይዜሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ኃላፊ አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደገለፁት ተቋሙ ያሉትን ሀብቶች በአንድ የመረጃ ቋት ውስጥ መዝግቦ ለማስተዳደር የኢ.አር.ፒ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ በየደረጃው ያሉ የሥራ ክፍሎች በባለቤትነት ስሜት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የአሰራር ሥርዓቱን ለመተግበር ከሀብት ምዝገባ ጋር የተያያዙ የመረጃ ክፍተቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የጠቆሙት ኃላፊው ችግሩን ለመቅረፍም ሁሉም የሥራ ክፍሎች በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
እንደ አቶ ገነቱ ገለፃ ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት ሁለንተናዊ የሆነ ተቋማዊ ለውጥ ከማምጣት ባሻገር መረጃዎችን በአግባቡ በመመዝገብ የሀብት ብክነትን ያስቀራል፡፡
ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት የፋይናንስና ቁጥጥር፣ የሰው ሀብትና ፔሮል፣ የመረጃ ማዕከል፣ የንብረት አስተዳደርና የዕቃ ግምጃ ቤት እንዲሁም መሰል አስተዳደራዊ ሞጁሎች ያሉት ዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሳፕ ከተባለው የጀርመን ሶፍትዌር አምራች ኩባንያ የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓት ሶፍትዌር ፈቃድ ለመግዛት በሂደት ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 18 ቀን 2013 ዓ.ም.
.....///.…...
ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓትን በተቋሙ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሞደርናይዜሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ኃላፊ አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደገለፁት ተቋሙ ያሉትን ሀብቶች በአንድ የመረጃ ቋት ውስጥ መዝግቦ ለማስተዳደር የኢ.አር.ፒ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ በየደረጃው ያሉ የሥራ ክፍሎች በባለቤትነት ስሜት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የአሰራር ሥርዓቱን ለመተግበር ከሀብት ምዝገባ ጋር የተያያዙ የመረጃ ክፍተቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የጠቆሙት ኃላፊው ችግሩን ለመቅረፍም ሁሉም የሥራ ክፍሎች በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
እንደ አቶ ገነቱ ገለፃ ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት ሁለንተናዊ የሆነ ተቋማዊ ለውጥ ከማምጣት ባሻገር መረጃዎችን በአግባቡ በመመዝገብ የሀብት ብክነትን ያስቀራል፡፡
ኢ.አር.ፒ የአሰራር ሥርዓት የፋይናንስና ቁጥጥር፣ የሰው ሀብትና ፔሮል፣ የመረጃ ማዕከል፣ የንብረት አስተዳደርና የዕቃ ግምጃ ቤት እንዲሁም መሰል አስተዳደራዊ ሞጁሎች ያሉት ዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሳፕ ከተባለው የጀርመን ሶፍትዌር አምራች ኩባንያ የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ (ኢ.አር.ፒ) የአሰራር ሥርዓት ሶፍትዌር ፈቃድ ለመግዛት በሂደት ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
ጥቅምት 18 ቀን 2013 ዓ.ም.
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለነቢዩ መሀመድ ልደት(መውሊድ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሠላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል፡፡
በዓሉ የሠላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል፡፡