EEP Communication
15.6K subscribers
10.9K photos
33 videos
32 files
2.03K links
EEP Communication
Download Telegram
ከ1 ሺህ 3 መቶ ኪ.ሜ በላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና 14 የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡
…………………..//////…………………
በ2013 በጀት ዓመት የ1 ሺህ 304 ነጥብ 2 ኪ.ሜ የማስተላለፊያ መስመርና 14 የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ኃላፊ ወ/ሮ ጽዮን ብርሃኑ እንዳስታወቁት በአሁኑ ሰዓት በመላው ሀገሪቱ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 14 የማስተላለፊያ መስመር እና 34 የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በግንባታ ላይ ከሚገኙት የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶች መካከል 433 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ባለ 500 ኪ.ቮ፣ 1045 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ባለ 400 ኪ.ቮ፣ 949 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪ.ቮ እና 191 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ባለ 132 ኪ.ቮ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
የሚገነቡት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ደግሞ አንድ ባለ 500 ኪ.ቮ፣ አምስት ባለ 400 ኪ.ቮ፣15 ባለ 230 ኪ.ቮ እና 13ቱ ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ 132 ኪ.ቮ ናቸው፡፡
በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል አራቱ በራስ ኃይል በመከናወን ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ወ/ሮ ጽዮን ገልጸዋል፡፡
በግንባታ ላይ ካሉት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች መካከልም የ14 ማከፋፈያ ጣቢያ እና የ1 ሺህ 304 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባትን በ2013 በጀት ዓመት በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል አራቱ በራስ ኃይል በመከናወን ላይ የሚገኙ ናቸው ተብሏል፡፡
ከአዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተጨማሪ በአንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ አቅም የማሳደግ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝም ነው ወ/ሮ ጽዮን የተናገሩት፡፡

እንደ ወ/ሮ ጽዮን ገለፃ የፕሮጀክቶችን ግንባታ በተያዘላቸው መርሃ ግብር ለማከናወን የወሰን ማስከበር ችግር፣ የፀጥታ ሁኔታ፣ የግብኣት አቅርቦት ችግር፣ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የእንቅስቃሴ ገደብ መደረጉ፤ የሙከራና ፍተሻ ስራ በወቅቱ አለመከናወኑ ተግዳሮቶች ነበሩ፡፡

በአሁኑ ሰዓት በግንባታ ላይ የሚገኙት የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ለ2 ሺህ 661 ያህል ዜጎች የስራ እድል መፍጠር ችለዋል፡፡

በተያዘው የበጀት ዓመት በአማራ፣ በደቡብ እና ኦሮሚያ ክልሎች አምስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጀመርና የአራት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ስራ እንደሚሰራ ኃላፊዋ ተናግረዋል፡፡
በ2013 በጀት ዓመቱ የታቀዱ ስራዎችን በመርሃ ግብራቸው ለማከናወን የካሳ ክፍያ ጥያቄ፣ የፀጥታ ሁኔታ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ኮሮና ቫይረስ እና ከታክስ ጋር በተገናኘ ከዕቃ ማጓጓዝ ላይ የተጫነው የታክስ አዋጅ እንደ ስጋት የተለዩ ችግሮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በመምሪያው ከሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በተቋሙ የራስ ኃይል ቢሮ በርካታ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡

በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ከ18 ሺህ 8መቶ ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመርና ከ2 መቶ በላይ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸው ለ‹‹ገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት›› ለገሱ
……………………//////………………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸው ለ‹‹ገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት›› ሰጡ፡፡

የተቋሙ ስራ አመራር አባላትና የተጠሪ መምሪያ ኃላፊዎች ከሠራተኞች ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ለመስጠት ወስነዋል፡፡

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ሰራተኞቹና አመራሮቹ በ‹‹ገበታ-ለሀገር›› ፕሮጀክት ለሚከናወኑት ልማቶች የወር ደመወዛቸውን በፍቃደኝነት ለመስጠት በመወሰናቸው አመስግነዋል፡፡

በ‹‹ገበታ-ለሀገር›› ከሚከናወኑት ሶስት ፕሮጀክት መካከል አንዱ በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ አካባቢ የሚከናወን ነው፡፡

ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋርጧል
................///////..................
ትናንት ማምሻውን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ዛሬ ከእኩለ ቀን ጀምሮ በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል፡፡
የወደቀውን የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በሌላ ለመተካት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡
የወደቀውን ምሰሶ ሙሉ በሙሉ ለማቆም ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት አካባቢው ነገ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡
በኢንደስትሪ መንደሩና ከዚህ ጋር በተገናኘ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ያላችሁ ነዋሪዎች ችግሩን ለመፍታት የጀመርነውን ጥረት በመገንዘብ በትዕግስት እንድትጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪውን ያቀርባል፡፡
አሁን ችግር በደረሰበት አካባቢ ሰኔ ወር አጋማሽ ላይ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው
................///////..................
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ምክንያት ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው።
የአካባቢው መስመር ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት እስከ ማምሻው ድረስ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.
የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል የተጀመረው ርብርብ በከባድ ዝናብ ውስጥም ቀጥሏል
................///////..................
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና በአካባቢው የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል እየተደረገ ያለውን ርብርብ በአካባቢው እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብና መብረቅ እያስተጓጎለው ቢሆንም ርብርቡ ቀጥሏል።

አካባቢው ኃይል ያገኝ የነበረበትን የቀድሞ መስመር ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት እስከ ማምሻው ድረስ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ይሁንና እየጣለ ያለው ዝናብ እና የመብረቅ ብልጭታ በመስመሩ ውስጥ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ንዝረት በመፍጠር የጥገና ባለሙያዎች ስራቸውን በተገቢው እንዳያጠናቅቁ እንቅፋት እየሆነ ነው፡፡

መስመሩን ለማገናኘት አሁንም ጥረት የቀጠለ መሆኑን በመገንዘብ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.
የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል አግኝቷል
................///////..................
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ምክንያት የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ሲደረግ የነበረው ርብርብ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በምሰሶው መውደቅ ምክንያት በአካባቢው ላለፉት ሁለት ቀናት ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል።
በእነዚህ ቀናት ከነበረው ከባድ ዝናብና የመብረቅ ብልጭታ ከሚፈጥረው ከባድ ንዝረት ጋር በመታገል መስመሩን ላገናኙ የጥገና ባለሙያዎቻችን ላቀ ያለ ምስጋናችንን እያቀረብን የአካባቢው ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችም በትዕግስት ስለጠበቃችሁን ከልብ እናመሰግናለን።
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም.
አዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለጊዜው አገልግሎቱን አቋረጠ
…………./////………..
በአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ በማጋጠሙ ከቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ጣቢያው ለጊዜው አገልግሎት ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ II እና III ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዲሳሳ ገልሜሳ አስታውቀዋል፡፡
ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡
ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ በመዋጣቸው የጉዳቱን መጠን ለማወቅ እንዳልተቻለ አቶ ዲሳሳ ተናግረዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 26 ቀን 2012 ዓ.ም.
ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት እጥረት የጣቢያው ስጋት እየሆኑ ነው ተባለ
--------------/////////----------------
የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት ስራውን እያስተጓጎለበት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ፍቃዱ ደምሴ እንደገለፁት ወደ ጣቢያው የውሃ መቀበያ እየተገመሰ የሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ለኃይል ማመንጫው የኦፕሬሽን ሥራ ከፍተኛ ስጋት እየሆነ ነው፡፡
ተንሳፋፊ ሳሩ ከሐምሌ 9-11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን እስከማስቆም ደርሶ እንደነበረ የገለፁት ኃላፊው ባለፈው ዓመትም በተንሳፋፊ ሳሩ ምክንያት ከ10 ቀን በላይ ጣቢያው መቆሙን አስታውሰዋል፡፡
ጣቢያውን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ኤክስካቬተር በመከራየትና ዋና በሚችሉ የጣቢያው ሠራተኞችን በመጠቀም የኃይል ማመንጫውን ውሃ መቀበያ የዘጋውን ተንሳፋፊው ሣር ለጊዜውም ቢሆን በማስወገድ ሥራ ማስጀመር መቻሉን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡
ጣቢያውን ከተንሳፋፊ ሳር ለመጠበቅ የሚያግዝ መከላከያ (Taff Boom) ያለው ቢሆንም በዘንድሮ ዓመት ከሃይቁ ዳር እየተገመሰ የሚመጣው የሳር ደሴት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ ቀደም ሲል የተገጠመው መከላለያ ሊመልሰው አልቻለም፡፡
በመሆኑም በየጊዜው ወደ ኃይል ማመንጫው ለሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ዘላቂ መፍትሄ ካልተሰጠው በቀር ጣቢያውን እስከ መዘጋት ሊያደርሰው እንደሚችል አብራርተዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 27 ቀን 2012 ዓ.ም.
የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዓለምአቀፍ ትኩረት ስቧል
……………/////………..
የኤሌክትሪክ ዘርፍ ተሸላሚው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለሁሉም ለማዳረስ እገዛ እያደረገ መሆኑን ፓወር የተሰኘው በኃይል ላይ በማተኮር የሚዘጋጀው ዓለምአቀፍ መጽሔት ዘግቧል፡፡
ከህዝቦቿ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኤሌክትሪክ የማያገኙባት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተሻሻለች መምጣቷን መጽሔቱ በዝርዝር አትቷል፡፡
መፅሔቱ ይፋ እንዳደረገው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት መንግስት እ.ኤ.አ እስከ 2025 በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት የሚደረገውን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እገዛ ማድረግ ጀምሯል፡፡
በ3 ተርባይኖች 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ተመርቆ ስራ የጀመረው በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ነበር፡፡
ይህን ሊንክ በመጫን ዝርዝር ዘገባውን ማግኘት ይችላሉ፡፡
https://www.powermag.com/award-winning-hydropower-project-helps-electrify-ethiopia/