የገቢዎች ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት ህንጻ ዕድሳትና ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ
--------------
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እየተገነባ የሚገኘው የገቢዎች ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት የህንጻ ዕድሳት እና ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ፡፡
በኮንትራት ስምምነቱ መሰረት የባለ ስድስት ወለል ህንጻ የዕድሳት ሥራ፣ የባለ ሁለት ወለል ካፍቴሪያ ግንባታ፣ የግቢ ማስዋብ ሥራ፣ የአስፋልት ንጣፍ እና የአጥር ሥራዎችን የሚያጠቃልለው ፕሮጀክት በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አክሊሉ ታደሰ ገልጸዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ዘመናዊ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥርዓቶችን በመጠቀም ግንባታውን በተቀላጠፈ መንገድ ለመምራት ከፍተኛ ጥረት ማደረጉን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በቅርቡ ርክክብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡
--------------
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እየተገነባ የሚገኘው የገቢዎች ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት የህንጻ ዕድሳት እና ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ፡፡
በኮንትራት ስምምነቱ መሰረት የባለ ስድስት ወለል ህንጻ የዕድሳት ሥራ፣ የባለ ሁለት ወለል ካፍቴሪያ ግንባታ፣ የግቢ ማስዋብ ሥራ፣ የአስፋልት ንጣፍ እና የአጥር ሥራዎችን የሚያጠቃልለው ፕሮጀክት በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አክሊሉ ታደሰ ገልጸዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ዘመናዊ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥርዓቶችን በመጠቀም ግንባታውን በተቀላጠፈ መንገድ ለመምራት ከፍተኛ ጥረት ማደረጉን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በቅርቡ ርክክብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡