Ethiopian Coffee and Tea Authority
5.96K subscribers
5.79K photos
30 videos
67 files
370 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለሴት ሰራተኞቹ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና እየሰጠ ነው
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ፣ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሴት ሰራተኞች በቡና ዘርፍ ዙሪያ መሰረታዊ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው በቡና ምርት አዘገጃጀት፣ አጠባበቅ፣ አቆላል፣ አፈላል፣ የቅምሻ ጥበብ እና በኤክስፖርት ሂደቶች ላይ ያተኮረ ነው። የዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ ስልጠናውን ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ ይህ መርሃ ግብር ሰራተኞቹ ስለ ዘርፉ ያላቸውን ግንዛቤ የሚያሳድግና ወደፊት በሙያው በስፋት ለመሰማራት ለሚፈልጉ የላቀ መነሳሳትን የሚፈጥር ነው።
ይህ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆየው ስልጠና ሴት ሰራተኞች በኢንዱስትሪው ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎና ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በየአመቱ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የሴቶችን ሙያዊ አቅም ለመገንባትና በቡና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላቸውን ድርሻ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
ECTA Provides Professional Training for its Female Employees!!
In honor of International Women's Day (March 8), the Ethiopian Coffee and Tea Authority (ECTA) is conducting a comprehensive training program for female staff drawn from various departments. The training covers essential aspects of the coffee value chain, including production preparation, preservation, roasting, brewing, cupping, and export procedures. During the opening ceremony, Mr. Sefisa Ababu, Head of the Director General's Office, noted that the training is designed to broaden employees' industry knowledge and inspire those interested in pursuing specialized careers within the sector.
The session, which will continue for the next two days, aims to empower female employees and enhance their competitiveness within the coffee industry. By organizing such annual programs, the Authority reaffirms its commitment to professional capacity building and increasing the meaningful participation of women throughout the coffee value chain.
በቅርቡ በኮሎምቢያ የተካሄደ አዲስ ጥናት እንደጠቆመው፤ የታሸገ ኮንቴይነር እና መጠነኛ የካርቦን ዳይኦክሳይድ (CO2) ጋዝ አጠቃቀም ተራ የሆኑ “ናቹራል” ቡናዎችን ወደ ከፍተኛ የልዩ (Specialty) ቡና ሊያሸጋግራቸው ይችላል።
ጥናቱ ክፍት በሆነ አየር እና በካርቦን ዳይኦክሳይድ የታገዘ (Closed Fermentation) ዘዴዎችን በማነፃፀር በኮሎምቢያ የቴክኖሎጂ ተቋም (SENA) እና በቫሌ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የተከናወነ ነው። ተመራማሪዎቹ ከአንድ ማሳ የተለቀሙ የቡና ፍሬዎችን ከመድረቃቸው በፊት አምስት አይነት አፕሮች በመጠቀም Ferment በማድረግ፤ ቡናው ደርቆና ተቆልቶ በዓለም አቀፉ የልዩ ቡና ማህበር (SCA) ከ100 ነጥብ መለኪያ ተመዝኗል።
በዚህም ለ24 ሰዓታት በካርቦን ዳይኦክሳይድ በታፈነ ስፍራ የቆየው ቡና 86.90 አማካኝ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ሲወጣ፤ ምንም አይነት ሂደት ያልተደረገበት ቡና ደግሞ 82.15 ነጥብ ብቻ አግኝቷል።
በታህሳስ 2025 በታዋቂው Scientific World Journal ላይ የታተመው ይህ ጥናት፤ በልምድና በጥቃቅን ሙከራዎች ላይ ብቻ ተመስርቶ ለሚሰራው የልዩ ቡና ገበያ፣ በሳይንሳዊ መንገድ የተረጋገጠ እና በሰፊው ሊተገበር የሚችል አዲስ አቅጣጫ እንደሚያመላክት ተገልጿል።
ተመራማሪዎቹ እንዲህ ብለዋል፦
“ምንም እንኳ በቡና Fermentation ሂደት ላይ በርካታ ምርምሮች ቢደረጉም፣ አብዛኞቹ በላቦራቶሪ ቁጥጥር ስር ወይም በታጠበ ቡና (Wet processing) ላይ ያተኮሩ በመሆናቸው፤ በፀሐይ በሚደርቅ (Natural) ቡና ላይ ያላቸው ተፈጻሚነት ውስን ነበር። በተለይም በካርቦን ዳይኦክሳይድ የታገዘ የFermentation ዘዴ በተፈጥሯዊ የቡና አዘገጃጀትና በኬሚካላዊ ይዘት ላይ ያለውን ተፅዕኖ በተጨባጭ የምርት ቦታዎች ላይ የሚያሳይ ሳይንሳዊ መረጃ እጥረት ነበረው።”
ይህ አዲስ ግኝት ለቡና አምራቾች ጥራትን ለማሻሻል ቀላልና ውጤታማ መንገድ ይጠቁማል ይለናል አዲሱ ጥናት።
CO2 Fermentation Boosts Natural-Process Coffee Scores in Colombian Trial
Daily Coffee News March 17, 2026
https://dailycoffeenews.com/.../co2-fermentation.../...
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች: እንኳን ለ1447ኛው የዒድ-አልፈጥር በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም በዓል!!
አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር