የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣንን ጎበኙ!!
መጋቢት 02/2018
የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉጌታ አለማየሁ እና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝታቸው ወቅት የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በመሥሪያ ቤቱ እየተከናወኑ ያሉ አበይት ተግባራትን ለባንኩ አመራሮች አስረድተዋል።
በተለይም በዘመናዊ መልክ የተገነባውን የባለሥልጣኑን አዲስ ሕንፃ፣ የቡና ማሰልጠኛ ማዕከልንና የኦንላይን የግብይት ቁጥጥር ሥርዓትን ለጉብኝቱ ቡድን በዝርዝር አስጎብኝተዋል። ይህ ጉብኝት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የሥራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ለውጦችን ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
Higher level officials of Bunna International Bank Visits Ethiopian Coffee and Tea Authority!!
Mr. Mulugeta Alemayehu, President of Bunna International Bank, accompanied by the bank’s senior executive team, conducted an official working visit to the Ethiopian Coffee and Tea Authority. During the visit, the Director General of the Authority, H.E Dr. Adugna Debella, provided a comprehensive briefing on the institution's key strategic initiatives and ongoing projects.
The delegation visited several milestone developments, including the Authority's state-of-the-art headquarters, the modern Coffee Training Center, and the newly implemented online market regulatory system. This visit highlights the growing synergy between the financial sector and the coffee industry, showcasing the technological advancements driving Ethiopia's coffee value chain forward. Reported By Sahlemariam G/medhin
መጋቢት 02/2018
የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉጌታ አለማየሁ እና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝታቸው ወቅት የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በመሥሪያ ቤቱ እየተከናወኑ ያሉ አበይት ተግባራትን ለባንኩ አመራሮች አስረድተዋል።
በተለይም በዘመናዊ መልክ የተገነባውን የባለሥልጣኑን አዲስ ሕንፃ፣ የቡና ማሰልጠኛ ማዕከልንና የኦንላይን የግብይት ቁጥጥር ሥርዓትን ለጉብኝቱ ቡድን በዝርዝር አስጎብኝተዋል። ይህ ጉብኝት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የሥራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ለውጦችን ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
Higher level officials of Bunna International Bank Visits Ethiopian Coffee and Tea Authority!!
Mr. Mulugeta Alemayehu, President of Bunna International Bank, accompanied by the bank’s senior executive team, conducted an official working visit to the Ethiopian Coffee and Tea Authority. During the visit, the Director General of the Authority, H.E Dr. Adugna Debella, provided a comprehensive briefing on the institution's key strategic initiatives and ongoing projects.
The delegation visited several milestone developments, including the Authority's state-of-the-art headquarters, the modern Coffee Training Center, and the newly implemented online market regulatory system. This visit highlights the growing synergy between the financial sector and the coffee industry, showcasing the technological advancements driving Ethiopia's coffee value chain forward. Reported By Sahlemariam G/medhin
☕ የቡና ገበያ ሲናወጥ፡ ዘላቂ አጋርነት የውድድር ብልጫ አለው!!
በሳህለማርያም ገ/መድህን
ባለፈው አንድ ዓመት የዓለም አቀፉ የቡና ኢንዱስትሪ ላለፉት አሥርተ ዓመታት አይቶት የማያውቀውን ከፍተኛ የዋጋ መዋዠቅ አስተናግዷል። የዋጋ ጣራ መንካት፣ የአሜሪካ የንግድ ታሪፎች እና የአውሮፓ ህብረት አዲሱ የደን ጥበቃ ደንብ (EUDR) ብዙ የቡና ድርጅቶች ስለ አቅርቦት ዋስትና፣ ስለ ዋጋ ስልቶች እና ስለ ረጅም ጊዜ ዕቅዳቸው ደጋግመው እንዲያስቡ፣ እንዲያጤኑ አስገድዷቸዋል።
⚠️ 2025፡ የኢንዱስትሪው የፈተና ዓመት
ያለፈው ዓመት የገበያ ሁኔታ፣ የዋጋ መከላከያ ዘዴዎች (hedging tools) ለሌላቸው አነስተኛ ቆዪ ኢንዱስትሪዎች እጅግ ፈታኝና ውጣ ውረድ የበዛበት ነበር። ለዚህ አለመረጋጋት ደግሞ ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ነበሩ፦
የጦዘ እና ሪከርድ የሰበረ የቡና ዋጋ ንረት፣
በሚያዝያ 2025 በብራዚል ቡና ላይ የተጣለው የ50% የአሜሪካ ታሪፍ፣
የዓለም አቀፍ ንግድን ያወከ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ እንዲሁም
ከዋና ዋና አምራች አገራት የሚመጣው አቅርቦት መቀነስ።
ምንም እንኳን ቡናው ከታሪፍ ነፃ ቢደረግም፣ የተፈጠረው ድንጋጤ ግን የንግድ ምንጭ አሰባሰብ ስልቶችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀየሩ አድርጓል።
🤝 የጥብቅ ግንኙነት አስፈላጊነት/ Strategic and strong partnership
በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ወቅት በቆዪዎች፣ በአልሚዎች፣ ላኪዎች እና በአምራች ገበሬዎች መካከል ያለው የረጅም ጊዜ አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። በመተማመን፣ በግልጽነት እና በመረጃ ልውውጥ ላይ የተገነባ ግንኙነት፤ ገበያው በሚዋዥቅበት ወቅት እንኳ ድርጅቶች በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንዲቆሙ፣ አቅርቦት እንዲያገኙ፣ ጥራትን እንዲጠብቁ እና ስጋቶችን እንዲቀንሱ ይረዳቸዋል። የአቅርቦት ሰንሰለቱ ሲወጣጠርና ዋጋ ሲንር፣ እነዚህ የቆዩ ጥብቅ ግንኙነቶች የንግድ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲቀጥል ያደርጋሉ። በተለይ ጥራት፣ ጥራት፣ ጥራት።
📉 በ2026 የሚታዩ አዳዲስ ዕድሎች
ወደ 2026 ስንገባ ገበያው እንደ ዓለም አቀፉ የቡና ድርጅት (ICO) ጥር 2026 ሪፖርት፦
የቡና ገበያ ዋጋ (C market) ከነሐሴ 2025 ወዲህ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል፣
በብራዚል የታየው የተሻለ የአየር ሁኔታ የዓለም አቅርቦት ገበያውን ሰፊ የአቅርቦት መጠን እንዲኖረው አድርጎታል። ነገር ግን ደግሞ ይህን ለውጥ ለበጎ ነው ብሎ መቀበል የብልሆች ምርጫ ነው። በንግድ አለም ብዙ ጊዜ ማትረፍ እንዳለ ሁሉ አንዳንዴ ደግሞ ትንሽ ትርፍ አልያም ደግሞ በዋና መሸጥ፣ እልፍ ካለም በጥቂት ኪሳራ መሸጥ ይጠበቃል። ይህ ተፈጥሯዊ፤ ያለ፣ የነበረ ወደ ፊትም የሚኖር የንግድ ዑደት ነው።
ይህ ለውጥ ድርጅቶች ወጪያቸውን እንዲያመጣጥኑ፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ የብልህ አካሄድ እንዲኖራቸው እና የረጅም ጊዜ የቡና ምንጭ ስልቶችን እንዲያቅዱ አዲስ በር ከፍቷል። ቀደም ብለው በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ጠንካራ አጋርነት የፈጠሩ ኩባንያዎች፣ ገበያው ወደ መረጋጋት ሲመለስ ራሳቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማላመድና ጥራቱን የጠበቀ አቅርቦት ለማረጋገጥ ዝግጁ ያደርጋቸዋል ።
📈 ከኢንዱስትሪው ምን እንማር?
ተለዋዋጭ ገበያዎች የሚያስተምሩን ትልቁ ቁምነገር፦ ቡና ማለት ዋጋ ብቻ ሳይሆን ግንኙነት፣ ግልጽነትና የረጅም ጊዜ መተማመን መሆኑን ነው። በጠንካራ አጋርነት ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን ያፈሰሱ ድርጅቶች፣ የቡና ገበያውን የወደፊት ጉዞ በስኬት ለመወጣት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።
መንግስት የዜጎቹ በተለይም ደግሞ የቡናው ተዋናይ ዘለቄታዊ ኑሮ ያስጨንቀዋል፣ ያሳስበዋል። ለዚህም ነው እስከዛሬ አርሶ አደሩ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር፣ ዘርፉም ወደላቀ ደረጃ እንዲደርስ ሌት ተቀን የሚደክመው። ይህ ጥረት ዛሬም፣ ነገም ከነገወዲያም ተጠናክሮ ይቀጥላል። የምርት ዘመኑ መግቢያ ላይ የአለምን የገበያ አዝማሚያ በመመልከት ክቡር የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ እና የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳ/ር ዶ/ር አዱኛ መላ ባለድርሻ አካላትን ሰብስበው የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈው ነበር። በዚህም የገባቸው አብዝተው ተጠቀሙ። አሁንም ብልጥ ከሰራው ስህተት ፈጥኖ ይማራልና የዋጋው ሁኔታ ከዚህም በላይ የከፋ ሁኔታ ላይ ሳይደርስ ቡናን ወደማዕከላዊ ገበያ አቅርቦ ከኪሳራም ሆነ ከተጠያቂነት መዳን ይቻላል። አንድ በዚሁ ዘርፍ የተሰማሩ ወዳጄ ያካፈሉኝን መልዕክት ጠቁሜ ፅሁፌን ላብቃ።
"ባለፈው አመት በዘመኔ አይቼው የማላውቅ ትርፍ አተረፍኩ። ዘንድሮም ያ ይደገማል የሚል ተስፋ ቢኖረኝም የቡና ገበያ የጨዋታ ህግ ተለዋዋጭ መሆኑን ስለማውቅ የበለጠ ከኪሳራ ለመዳን ስል እጄ ላይ የሚገኘውን ምርት አውጥቼ መሸጥ ችያለሁ። በዚህ ፈታኝ ወቅት መንግስት እያቀበለን ላለው መረጃ እና የውይይት መድረኮች የላቀ ክብር እና አድናቆት አለኝ''
በሳህለማርያም ገ/መድህን
ባለፈው አንድ ዓመት የዓለም አቀፉ የቡና ኢንዱስትሪ ላለፉት አሥርተ ዓመታት አይቶት የማያውቀውን ከፍተኛ የዋጋ መዋዠቅ አስተናግዷል። የዋጋ ጣራ መንካት፣ የአሜሪካ የንግድ ታሪፎች እና የአውሮፓ ህብረት አዲሱ የደን ጥበቃ ደንብ (EUDR) ብዙ የቡና ድርጅቶች ስለ አቅርቦት ዋስትና፣ ስለ ዋጋ ስልቶች እና ስለ ረጅም ጊዜ ዕቅዳቸው ደጋግመው እንዲያስቡ፣ እንዲያጤኑ አስገድዷቸዋል።
⚠️ 2025፡ የኢንዱስትሪው የፈተና ዓመት
ያለፈው ዓመት የገበያ ሁኔታ፣ የዋጋ መከላከያ ዘዴዎች (hedging tools) ለሌላቸው አነስተኛ ቆዪ ኢንዱስትሪዎች እጅግ ፈታኝና ውጣ ውረድ የበዛበት ነበር። ለዚህ አለመረጋጋት ደግሞ ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ነበሩ፦
የጦዘ እና ሪከርድ የሰበረ የቡና ዋጋ ንረት፣
በሚያዝያ 2025 በብራዚል ቡና ላይ የተጣለው የ50% የአሜሪካ ታሪፍ፣
የዓለም አቀፍ ንግድን ያወከ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ እንዲሁም
ከዋና ዋና አምራች አገራት የሚመጣው አቅርቦት መቀነስ።
ምንም እንኳን ቡናው ከታሪፍ ነፃ ቢደረግም፣ የተፈጠረው ድንጋጤ ግን የንግድ ምንጭ አሰባሰብ ስልቶችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀየሩ አድርጓል።
🤝 የጥብቅ ግንኙነት አስፈላጊነት/ Strategic and strong partnership
በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ወቅት በቆዪዎች፣ በአልሚዎች፣ ላኪዎች እና በአምራች ገበሬዎች መካከል ያለው የረጅም ጊዜ አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። በመተማመን፣ በግልጽነት እና በመረጃ ልውውጥ ላይ የተገነባ ግንኙነት፤ ገበያው በሚዋዥቅበት ወቅት እንኳ ድርጅቶች በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንዲቆሙ፣ አቅርቦት እንዲያገኙ፣ ጥራትን እንዲጠብቁ እና ስጋቶችን እንዲቀንሱ ይረዳቸዋል። የአቅርቦት ሰንሰለቱ ሲወጣጠርና ዋጋ ሲንር፣ እነዚህ የቆዩ ጥብቅ ግንኙነቶች የንግድ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲቀጥል ያደርጋሉ። በተለይ ጥራት፣ ጥራት፣ ጥራት።
📉 በ2026 የሚታዩ አዳዲስ ዕድሎች
ወደ 2026 ስንገባ ገበያው እንደ ዓለም አቀፉ የቡና ድርጅት (ICO) ጥር 2026 ሪፖርት፦
የቡና ገበያ ዋጋ (C market) ከነሐሴ 2025 ወዲህ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል፣
በብራዚል የታየው የተሻለ የአየር ሁኔታ የዓለም አቅርቦት ገበያውን ሰፊ የአቅርቦት መጠን እንዲኖረው አድርጎታል። ነገር ግን ደግሞ ይህን ለውጥ ለበጎ ነው ብሎ መቀበል የብልሆች ምርጫ ነው። በንግድ አለም ብዙ ጊዜ ማትረፍ እንዳለ ሁሉ አንዳንዴ ደግሞ ትንሽ ትርፍ አልያም ደግሞ በዋና መሸጥ፣ እልፍ ካለም በጥቂት ኪሳራ መሸጥ ይጠበቃል። ይህ ተፈጥሯዊ፤ ያለ፣ የነበረ ወደ ፊትም የሚኖር የንግድ ዑደት ነው።
ይህ ለውጥ ድርጅቶች ወጪያቸውን እንዲያመጣጥኑ፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ የብልህ አካሄድ እንዲኖራቸው እና የረጅም ጊዜ የቡና ምንጭ ስልቶችን እንዲያቅዱ አዲስ በር ከፍቷል። ቀደም ብለው በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ጠንካራ አጋርነት የፈጠሩ ኩባንያዎች፣ ገበያው ወደ መረጋጋት ሲመለስ ራሳቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማላመድና ጥራቱን የጠበቀ አቅርቦት ለማረጋገጥ ዝግጁ ያደርጋቸዋል ።
📈 ከኢንዱስትሪው ምን እንማር?
ተለዋዋጭ ገበያዎች የሚያስተምሩን ትልቁ ቁምነገር፦ ቡና ማለት ዋጋ ብቻ ሳይሆን ግንኙነት፣ ግልጽነትና የረጅም ጊዜ መተማመን መሆኑን ነው። በጠንካራ አጋርነት ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን ያፈሰሱ ድርጅቶች፣ የቡና ገበያውን የወደፊት ጉዞ በስኬት ለመወጣት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።
መንግስት የዜጎቹ በተለይም ደግሞ የቡናው ተዋናይ ዘለቄታዊ ኑሮ ያስጨንቀዋል፣ ያሳስበዋል። ለዚህም ነው እስከዛሬ አርሶ አደሩ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር፣ ዘርፉም ወደላቀ ደረጃ እንዲደርስ ሌት ተቀን የሚደክመው። ይህ ጥረት ዛሬም፣ ነገም ከነገወዲያም ተጠናክሮ ይቀጥላል። የምርት ዘመኑ መግቢያ ላይ የአለምን የገበያ አዝማሚያ በመመልከት ክቡር የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ እና የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳ/ር ዶ/ር አዱኛ መላ ባለድርሻ አካላትን ሰብስበው የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈው ነበር። በዚህም የገባቸው አብዝተው ተጠቀሙ። አሁንም ብልጥ ከሰራው ስህተት ፈጥኖ ይማራልና የዋጋው ሁኔታ ከዚህም በላይ የከፋ ሁኔታ ላይ ሳይደርስ ቡናን ወደማዕከላዊ ገበያ አቅርቦ ከኪሳራም ሆነ ከተጠያቂነት መዳን ይቻላል። አንድ በዚሁ ዘርፍ የተሰማሩ ወዳጄ ያካፈሉኝን መልዕክት ጠቁሜ ፅሁፌን ላብቃ።
"ባለፈው አመት በዘመኔ አይቼው የማላውቅ ትርፍ አተረፍኩ። ዘንድሮም ያ ይደገማል የሚል ተስፋ ቢኖረኝም የቡና ገበያ የጨዋታ ህግ ተለዋዋጭ መሆኑን ስለማውቅ የበለጠ ከኪሳራ ለመዳን ስል እጄ ላይ የሚገኘውን ምርት አውጥቼ መሸጥ ችያለሁ። በዚህ ፈታኝ ወቅት መንግስት እያቀበለን ላለው መረጃ እና የውይይት መድረኮች የላቀ ክብር እና አድናቆት አለኝ''
የስትራቴጂ ሰነድ ርክክብ ተካሄደ
መጋቢት 04/2018
ኢቡሻባ
በጂ አይ ዜድ ፈንድ አድራጊትና በኬር ኢትዮጵያ አዘጋጅነት ለፍጻሜ የበቃውን የሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለመከላከል የሚያስችል ስትራቴጂ ሰነድ 500 ኮፒ ሁለቱ አካላት በጋራ በመሆን ለኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስጣን አስረክበዋል፡፡
በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ እንዳሉት ከአውሮፓ ኅብረት ደንብ ጋር በተያያዘ ብዙ ጉዳዮችን የተከናወኑ እንደሆነ ገልጸው ከሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ጋር በተያያዘ የተኬደው ርቀት ውሱን ሆኖ የቆየ ቢሆንም ከዚህ ስትራቴጂ ሰነድ ጋር በተያያዘ በተደረገው ጥረት ግን ብዙ ስራዎች እንደተከናወኑና ይህ ወሳኝ ሰነድም ግንዛቤን ከማስጨበጥ ባሻገር ብዝበዛውን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም በስራው የተሳተፉትን ጂ አይ ዜድን፣ ኬር ኢትዮጵያን፣ የተቋሙ ስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞችን አመስግነዋል፤ በቀጣይም ይህን ሰነድ ለተፈጻሚነቱ የሚመለከተው አካል መረባረብ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
ከዚሁ ርዕሰ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ባለስልጣን መስሪያቤቱ ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት፣ ከዓለማቀፍ የስራ ድርጅት እና ኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከአውሮፓው ደንብ ጋር ተያይዞ ከዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ሕጎች አንጻር ስለ ሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለቡናው ሴክተር አልሚዎች፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች እና ላኪዎች በአዲስ አበባ፣ ሐዋሳ እና ጅማ ስለጠናዎችን አንደሰጠ ይታወሳል፡፡
አሸናፊ ጌታሁን ዘግቦታል
መጋቢት 04/2018
ኢቡሻባ
በጂ አይ ዜድ ፈንድ አድራጊትና በኬር ኢትዮጵያ አዘጋጅነት ለፍጻሜ የበቃውን የሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለመከላከል የሚያስችል ስትራቴጂ ሰነድ 500 ኮፒ ሁለቱ አካላት በጋራ በመሆን ለኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስጣን አስረክበዋል፡፡
በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ እንዳሉት ከአውሮፓ ኅብረት ደንብ ጋር በተያያዘ ብዙ ጉዳዮችን የተከናወኑ እንደሆነ ገልጸው ከሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ጋር በተያያዘ የተኬደው ርቀት ውሱን ሆኖ የቆየ ቢሆንም ከዚህ ስትራቴጂ ሰነድ ጋር በተያያዘ በተደረገው ጥረት ግን ብዙ ስራዎች እንደተከናወኑና ይህ ወሳኝ ሰነድም ግንዛቤን ከማስጨበጥ ባሻገር ብዝበዛውን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም በስራው የተሳተፉትን ጂ አይ ዜድን፣ ኬር ኢትዮጵያን፣ የተቋሙ ስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞችን አመስግነዋል፤ በቀጣይም ይህን ሰነድ ለተፈጻሚነቱ የሚመለከተው አካል መረባረብ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
ከዚሁ ርዕሰ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ባለስልጣን መስሪያቤቱ ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት፣ ከዓለማቀፍ የስራ ድርጅት እና ኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከአውሮፓው ደንብ ጋር ተያይዞ ከዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ሕጎች አንጻር ስለ ሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለቡናው ሴክተር አልሚዎች፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች እና ላኪዎች በአዲስ አበባ፣ ሐዋሳ እና ጅማ ስለጠናዎችን አንደሰጠ ይታወሳል፡፡
አሸናፊ ጌታሁን ዘግቦታል
ብዙ የቡና አፍቃሪዎች ወደ "ኦርጋኒክ" ቡና እየተሳቡ ነው!!! ይህ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ኦርጋኒክ ቡና ለምታመርተው አገራችን ትልቅ በረከትን ይዞ የሚመጣ ነው...☕
ለጠቅላላ እውቀት ይረዳዎታል
በሳህለማርያም ገ/መድህን
ኦርጋኒክ ቡና ዛሬ ላይ ተራ ምርጫ ሳይሆን የጤና እና የጥራት መገለጫ እየሆነ መጥቷል። ብዙዎች ለጤናቸው፣ ለአካባቢ ጥበቃ እና ለታማኝ ምንጭ ቅድሚያ በመስጠታቸው የኦርጋኒክ ቡና ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።
🌱 ኦርጋኒክ ቡና ማለት ምን ማለት ነው?
ኦርጋኒክ ቡና ማለት ምንም ዓይነት ሰው ሠራሽ ፀረ-ተባይ፣ ማዳበሪያ ወይም የኬሚካል ንጥረ ነገሮች ሳይነኩት በጥላ ዛፍ (shade-grown) እና በተፈጥሮ ማዳበሪያ ብቻ የሚመረት ቡና ነው። ገበሬዎች የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ ኮምፖስት እና የተፈጥሮ ዘዴዎችን ይጠቀማሉ።
ይህ የአመራረት ዘዴ፦
የአካባቢን ብዝሃ ሕይወት ይጠብቃል።
ገበሬዎች ለኬሚካል እንዳይጋለጡ ያደርጋል።
ንጹህ እና ጥራት ያለው ቡና ለተጠቃሚው እንዲቀርብ ያደርጋል።
📈 የገበያው ፈጣን እድገት
በዓለም ዙሪያ የኦርጋኒክ ቡና ፍላጎት በከፍተኛ ፍጥነት እየናረ ነው፦
እ.ኤ.አ. በ2024 የዓለም ኦርጋኒክ ቡና ገበያ ዋጋ 10 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
እስከ 2033 ድረስ በየዓመቱ የ7.7% እድገት ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል።
በ2030 የገበያ ዋጋው ከ13 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚበልጥ ይገመታል።
ከፍተኛው ፍላጎት የሚመጣው ከአውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ሲሆን፣ ደንበኞች ለዘላቂ ልማት እና ለሥነ-ምግባራዊ ንግድ (ethical sourcing) ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ።
☕ ደንበኞች ለምን ኦርጋኒክ ቡናን ይመርጣሉ?
1. ለጤና ተመራጭ መሆኑ ኦርጋኒክ ቡና ከኬሚካል ነፃ በመሆኑ በሰውነት ውስጥ የሚከማቸውን መርዛማ ንጥረ ነገር ይቀንሳል፤ እንዲሁም ከፍተኛ የሰውነት መከላከያ (Antioxidants) ይዘት አለው።
2. የአካባቢ ጥበቃ ተፈጥሮአዊ የእርሻ ዘዴው የአፈርን ጥራት ያሻሽላል፣ የውሃ አካላትን ከኬሚካል ብክለት ይከላከላል እንዲሁም የዱር እንስሳትን መኖሪያ ይጠብቃል።
3. ማህበራዊ ኃላፊነት አብዛኛው ኦርጋኒክ ቡና በ"ፍትሃዊ ንግድ" (Fair Trade) መርህ የሚመረት በመሆኑ፣ ገበሬዎች ተገቢውን ክፍያ እንዲያገኙ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥራ አካባቢ እንዲኖራቸው ይረዳል።
🔍 የኦርጋኒክ ቡና ዕውቅና (Certification) እንዴት ይሰጣል?
የኦርጋኒክ ምስክር ወረቀት ማግኘት ቀላል ሂደት አይደለም። አንድ ማሳ ይህን ዕውቅና ለማግኘት ምናልባትም ከ3 እስከ 5 ዓመታት ጊዜ ያስፈልገዋል።
ሂደቱ የሚከተሉትን ያካትታል፦
✔️ የእርሻ ሂደቱን የሚያሳይ ዝርዝር ሰነድ ማቅረብ።
✔️ በእርሻው እና በፋብሪካው ላይ የሚደረግ በአካል የተገኘ ፍተሻ።
✔️ መስፈርቱን ማሟላቱን ለማረጋገጥ የሚደረግ ዓመታዊ ኦዲት።
ዋነኛ የኦርጋኒክ ማረጋገጫ ምልክቶች፦
USDA Organic (አሜሪካ)
EU Organic (አውሮፓ)
JAS Organic (ጃፓን)
እነዚህ ምልክቶች ቡናው ተፈጥሮን እና አምራቹን ማህበረሰብ ባከበረ መልኩ መመረቱን ማረጋገጫ ናቸው።
ለጠቅላላ እውቀት ይረዳዎታል
በሳህለማርያም ገ/መድህን
ኦርጋኒክ ቡና ዛሬ ላይ ተራ ምርጫ ሳይሆን የጤና እና የጥራት መገለጫ እየሆነ መጥቷል። ብዙዎች ለጤናቸው፣ ለአካባቢ ጥበቃ እና ለታማኝ ምንጭ ቅድሚያ በመስጠታቸው የኦርጋኒክ ቡና ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።
🌱 ኦርጋኒክ ቡና ማለት ምን ማለት ነው?
ኦርጋኒክ ቡና ማለት ምንም ዓይነት ሰው ሠራሽ ፀረ-ተባይ፣ ማዳበሪያ ወይም የኬሚካል ንጥረ ነገሮች ሳይነኩት በጥላ ዛፍ (shade-grown) እና በተፈጥሮ ማዳበሪያ ብቻ የሚመረት ቡና ነው። ገበሬዎች የአፈርን ለምነት ለመጠበቅ ኮምፖስት እና የተፈጥሮ ዘዴዎችን ይጠቀማሉ።
ይህ የአመራረት ዘዴ፦
የአካባቢን ብዝሃ ሕይወት ይጠብቃል።
ገበሬዎች ለኬሚካል እንዳይጋለጡ ያደርጋል።
ንጹህ እና ጥራት ያለው ቡና ለተጠቃሚው እንዲቀርብ ያደርጋል።
📈 የገበያው ፈጣን እድገት
በዓለም ዙሪያ የኦርጋኒክ ቡና ፍላጎት በከፍተኛ ፍጥነት እየናረ ነው፦
እ.ኤ.አ. በ2024 የዓለም ኦርጋኒክ ቡና ገበያ ዋጋ 10 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
እስከ 2033 ድረስ በየዓመቱ የ7.7% እድገት ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል።
በ2030 የገበያ ዋጋው ከ13 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚበልጥ ይገመታል።
ከፍተኛው ፍላጎት የሚመጣው ከአውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ሲሆን፣ ደንበኞች ለዘላቂ ልማት እና ለሥነ-ምግባራዊ ንግድ (ethical sourcing) ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ።
☕ ደንበኞች ለምን ኦርጋኒክ ቡናን ይመርጣሉ?
1. ለጤና ተመራጭ መሆኑ ኦርጋኒክ ቡና ከኬሚካል ነፃ በመሆኑ በሰውነት ውስጥ የሚከማቸውን መርዛማ ንጥረ ነገር ይቀንሳል፤ እንዲሁም ከፍተኛ የሰውነት መከላከያ (Antioxidants) ይዘት አለው።
2. የአካባቢ ጥበቃ ተፈጥሮአዊ የእርሻ ዘዴው የአፈርን ጥራት ያሻሽላል፣ የውሃ አካላትን ከኬሚካል ብክለት ይከላከላል እንዲሁም የዱር እንስሳትን መኖሪያ ይጠብቃል።
3. ማህበራዊ ኃላፊነት አብዛኛው ኦርጋኒክ ቡና በ"ፍትሃዊ ንግድ" (Fair Trade) መርህ የሚመረት በመሆኑ፣ ገበሬዎች ተገቢውን ክፍያ እንዲያገኙ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥራ አካባቢ እንዲኖራቸው ይረዳል።
🔍 የኦርጋኒክ ቡና ዕውቅና (Certification) እንዴት ይሰጣል?
የኦርጋኒክ ምስክር ወረቀት ማግኘት ቀላል ሂደት አይደለም። አንድ ማሳ ይህን ዕውቅና ለማግኘት ምናልባትም ከ3 እስከ 5 ዓመታት ጊዜ ያስፈልገዋል።
ሂደቱ የሚከተሉትን ያካትታል፦
✔️ የእርሻ ሂደቱን የሚያሳይ ዝርዝር ሰነድ ማቅረብ።
✔️ በእርሻው እና በፋብሪካው ላይ የሚደረግ በአካል የተገኘ ፍተሻ።
✔️ መስፈርቱን ማሟላቱን ለማረጋገጥ የሚደረግ ዓመታዊ ኦዲት።
ዋነኛ የኦርጋኒክ ማረጋገጫ ምልክቶች፦
USDA Organic (አሜሪካ)
EU Organic (አውሮፓ)
JAS Organic (ጃፓን)
እነዚህ ምልክቶች ቡናው ተፈጥሮን እና አምራቹን ማህበረሰብ ባከበረ መልኩ መመረቱን ማረጋገጫ ናቸው።
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን በመኸሩ ከ52ሺህ 900 ቶን በላይ የቡና ምርት ተገኝቷል
ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2018
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን በመኸሩ ከ52ሺህ 900 ቶን በላይ የቡና ምርት መገኘቱን የዞኑ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ ከተመረተው ቡና ከ42ሺህ 624 ቶን በላይ የታጠበና ቅሽር የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝም መምሪያው ገልጿል።
በመምሪያው የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማትና ግብይት ቡድን መሪ ሲሳይ በላይነህ፤ በክልሉ ማጃንግ ዞን በዘንድሮው መኸር 52ሺህ 962 ቶን የቡና ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።።
በዞኑ በሚገኙ የጎደሬና መንገሺ ወረዳዎች በአርሶ አደሩና በባለሃብቶች ከለማው 68ሺህ 637 ሄክታር የቡና ተክል የተገኘ ምርት መሆኑንም ተናግረዋል።
በዞኑ በዘንድሮው የምርት ዘመን የተገኘው የቡና ምርት ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ17ሺህ 186 ቶን ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
ለተገኘው ውጤትም በዞኑ የተስተካከል የዝናብ ስርጭትና የአየር ፀባይ በመኖሩና የተጠናከረ የቡና ተክልና እንክብካቤ ስራዎች መከናወናቸው እንዲሁም አርሶ አደሩ ከቡና ልማት የሚያገኘው ጥቅም እያደገ በመምጣቱ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢዜአ
ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2018
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን በመኸሩ ከ52ሺህ 900 ቶን በላይ የቡና ምርት መገኘቱን የዞኑ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ ከተመረተው ቡና ከ42ሺህ 624 ቶን በላይ የታጠበና ቅሽር የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝም መምሪያው ገልጿል።
በመምሪያው የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማትና ግብይት ቡድን መሪ ሲሳይ በላይነህ፤ በክልሉ ማጃንግ ዞን በዘንድሮው መኸር 52ሺህ 962 ቶን የቡና ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።።
በዞኑ በሚገኙ የጎደሬና መንገሺ ወረዳዎች በአርሶ አደሩና በባለሃብቶች ከለማው 68ሺህ 637 ሄክታር የቡና ተክል የተገኘ ምርት መሆኑንም ተናግረዋል።
በዞኑ በዘንድሮው የምርት ዘመን የተገኘው የቡና ምርት ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ17ሺህ 186 ቶን ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
ለተገኘው ውጤትም በዞኑ የተስተካከል የዝናብ ስርጭትና የአየር ፀባይ በመኖሩና የተጠናከረ የቡና ተክልና እንክብካቤ ስራዎች መከናወናቸው እንዲሁም አርሶ አደሩ ከቡና ልማት የሚያገኘው ጥቅም እያደገ በመምጣቱ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢዜአ
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለሴት ሰራተኞቹ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና እየሰጠ ነው
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ፣ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሴት ሰራተኞች በቡና ዘርፍ ዙሪያ መሰረታዊ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው በቡና ምርት አዘገጃጀት፣ አጠባበቅ፣ አቆላል፣ አፈላል፣ የቅምሻ ጥበብ እና በኤክስፖርት ሂደቶች ላይ ያተኮረ ነው። የዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ ስልጠናውን ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ ይህ መርሃ ግብር ሰራተኞቹ ስለ ዘርፉ ያላቸውን ግንዛቤ የሚያሳድግና ወደፊት በሙያው በስፋት ለመሰማራት ለሚፈልጉ የላቀ መነሳሳትን የሚፈጥር ነው።
ይህ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆየው ስልጠና ሴት ሰራተኞች በኢንዱስትሪው ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎና ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በየአመቱ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የሴቶችን ሙያዊ አቅም ለመገንባትና በቡና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላቸውን ድርሻ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ፣ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሴት ሰራተኞች በቡና ዘርፍ ዙሪያ መሰረታዊ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው በቡና ምርት አዘገጃጀት፣ አጠባበቅ፣ አቆላል፣ አፈላል፣ የቅምሻ ጥበብ እና በኤክስፖርት ሂደቶች ላይ ያተኮረ ነው። የዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ ስልጠናውን ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ ይህ መርሃ ግብር ሰራተኞቹ ስለ ዘርፉ ያላቸውን ግንዛቤ የሚያሳድግና ወደፊት በሙያው በስፋት ለመሰማራት ለሚፈልጉ የላቀ መነሳሳትን የሚፈጥር ነው።
ይህ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆየው ስልጠና ሴት ሰራተኞች በኢንዱስትሪው ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎና ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በየአመቱ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የሴቶችን ሙያዊ አቅም ለመገንባትና በቡና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላቸውን ድርሻ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።